#ድሬድዋ
የኮንቴይነር ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠጥ ላይ የሚገኘው የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ በድሬዳዋ ተጨማሪ የጭነት አገልግሎት የሚሰጥበት ጣቢያ መከፈቱን አሳውቋል።
ጣቢያው ፤ ደንበኞች ያላቸውን ጭነት በፈለጉት ቦታና ሰዓት ለማድረስ የሚስችል ተጨማሪ አማራጭ በመሆን ያገለግላል ብሏል።
የኢትዮ - ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ ፤ የባቡር ኮንቴይነሮች የጭነት አገልግሎት በኢትዮጵያ እና በጅቡቲ ዋና ዋና ከተሞች መካከል በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን በድሬዳዋ የተጀመረው የጭነት አገልግሎት አሁን ካሉት ዋና ዋና የእቃ ማጓጓዣ ጣቢያዎች ማለትም፦
- እንዶዴ፣
- ሞጆ፣
- አዳማ
- ናጋድ ጣቢያ በተጨማሪ የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ተገልጿል።
የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ " በድሬዳዋ ባቡር ጣቢያ የተጀመረው የጭነት አገልግሎት የጅምላ ጭነት ማጓጓዝ ለሚፈልጉ ደንበኞች በተመጣጣኝ ዋጋ ወደሚፈልጉት የሀገሪቱ ክፍል ለማጓጓዝ የሚያስችል ነው " ያለ ሲሆን ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብሏል።
#EDR
@tikvahethiopia
የኮንቴይነር ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠጥ ላይ የሚገኘው የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ በድሬዳዋ ተጨማሪ የጭነት አገልግሎት የሚሰጥበት ጣቢያ መከፈቱን አሳውቋል።
ጣቢያው ፤ ደንበኞች ያላቸውን ጭነት በፈለጉት ቦታና ሰዓት ለማድረስ የሚስችል ተጨማሪ አማራጭ በመሆን ያገለግላል ብሏል።
የኢትዮ - ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ ፤ የባቡር ኮንቴይነሮች የጭነት አገልግሎት በኢትዮጵያ እና በጅቡቲ ዋና ዋና ከተሞች መካከል በመስራት ላይ የሚገኝ ሲሆን በድሬዳዋ የተጀመረው የጭነት አገልግሎት አሁን ካሉት ዋና ዋና የእቃ ማጓጓዣ ጣቢያዎች ማለትም፦
- እንዶዴ፣
- ሞጆ፣
- አዳማ
- ናጋድ ጣቢያ በተጨማሪ የጭነት ትራንስፖርት አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያስችል ተገልጿል።
የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አ.ማ " በድሬዳዋ ባቡር ጣቢያ የተጀመረው የጭነት አገልግሎት የጅምላ ጭነት ማጓጓዝ ለሚፈልጉ ደንበኞች በተመጣጣኝ ዋጋ ወደሚፈልጉት የሀገሪቱ ክፍል ለማጓጓዝ የሚያስችል ነው " ያለ ሲሆን ዋጋ በማረጋጋት ረገድ ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብሏል።
#EDR
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ ጉምሩክ ኮሚሽን በኮምፒውተር " ሲስተም ዩኒት " ውስጥ ተደብቀው የገቡ ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች እና ሌሎች የኤሌክትሮኒከስ እቃዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ገለፀ።
ኮሚሽኑ ፤ በሞጆ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ህጋዊ እቃዎችን ሽፋን በማድረግ በኮምፒውተር " ሲስተም ዩኒት " ውስጥ ተደብቀው የገቡ ፦
👉 100 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ፣
👉 ሀርዲስኮች
👉 ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ገልጿል።
ኮሚሽኑ ይፋ ባደረገው መረጃ ፦
- የኤክትሮኒክስ እቃዎቹ (ላፕቶፕ፣ ሀርድዲስክ፣...) የዴስክ ቶፕ ኮምፒውተሮችን ሲስተም ዩኒት ውስጡን ባዶ በማድረግ የገቡ ናቸው።
- በተገኘ የፍተሻ ውጤት ሰነድ ላይ ያልተገለፀው ዕቃ የቀረጥና ታክስ መጠን ከ3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።
- የተፈፀመዉ #የንግድ_ማጭበርበር ተግባር በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፤ ምርመራም እየተጣራበት ነው።
- በተያዘው እቃ ላይም የውርስ ውሳኔ ተሰጥቷል።
መረጃው ከጉምሩክ ኮሚሽን የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
ኮሚሽኑ ፤ በሞጆ ጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ህጋዊ እቃዎችን ሽፋን በማድረግ በኮምፒውተር " ሲስተም ዩኒት " ውስጥ ተደብቀው የገቡ ፦
👉 100 ላፕቶፕ ኮምፒውተሮች ፣
👉 ሀርዲስኮች
👉 ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ ገልጿል።
ኮሚሽኑ ይፋ ባደረገው መረጃ ፦
- የኤክትሮኒክስ እቃዎቹ (ላፕቶፕ፣ ሀርድዲስክ፣...) የዴስክ ቶፕ ኮምፒውተሮችን ሲስተም ዩኒት ውስጡን ባዶ በማድረግ የገቡ ናቸው።
- በተገኘ የፍተሻ ውጤት ሰነድ ላይ ያልተገለፀው ዕቃ የቀረጥና ታክስ መጠን ከ3 ነጥብ 2 ሚሊዮን ብር በላይ ነው።
- የተፈፀመዉ #የንግድ_ማጭበርበር ተግባር በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለው አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል፤ ምርመራም እየተጣራበት ነው።
- በተያዘው እቃ ላይም የውርስ ውሳኔ ተሰጥቷል።
መረጃው ከጉምሩክ ኮሚሽን የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለታት ዓመት በላይ ተቋርጦ የነበረውን የሽረ የመንገደኞች በረራ ዛሬ ዳግም ጀምሯል።
Photo Credit : ENA
@tikvahethiopia
Photo Credit : ENA
@tikvahethiopia
🤔
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፍቃደኛ አለመሆን የሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጣራት እያደረግኩት ባለው ጥረት ላይ እንቅፋት ሆኖብኛል ሲል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ማስታወቁን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አስነብቧል።
የቢሮ ኃላፊ አቶ አሥራት አዳሮ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፦
" በክልሉ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ #ባለሙያዎችንና #ኃላፊዎችን የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን በመያዝ ትምህርታቸውን ባጠናቀቁበት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ በመሄድ ማስረጃዎቹ ሐሰተኛ ናቸው ወይስ አይደሉም የሚለውን ለማጣራት ሙከራ ብናደርግም የግል ትምህርት ተቋማት ፈቃደኞች አይደሉም፡፡
ከ5 እና 6 ወር በኋላ ተመልሳችሁ ኑ የሚል ምላሽ ስለሚሰጡን ወደ ትምህርት ተቋማቱ የምንልካቸው ባለሙያዎች ለእንግልት እየተዳረጉ ነው።
ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የትምህርት ጥራትን ከመጉዳትም ባሻገር የተማረ የሰው ኃይል በተፈለገው ቦታ ላይ እንዳይሠራና ጥራት ያለው አገልግሎት ለኅብረተሰቡ እንዳይሰጥ የሚያደርግ ነው።
በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ተቀጥረው በሥራ ላይ በሚገኙ #አመራርና #ባለሙያዎች ሕዝቡ ትክክለኛ አገልግሎት እንዳያገኝ ሲያደርጉ ነበር ፤ ክልሉ የሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የትምህርት መረጃን አጣርቶ በሚያገኘው ውጤት መሠረት ከሥራ እና ከደመወዝ ከማገድ ባሻገር በሕግ እንዲጠየቁ ይደረጋል።
የማጣራቱን ውጤት ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከ6ቱም ዞኖች የተጠቃለሉ መረጃዎችን በማደራጀት ምን ያህል አመራርና ባለሙያ በሐሰተኛ ትምህርት ማስረጃ ተቀጥሮ ሲሠራ እንደነበር ለሕዝቡ ይፋ ይደረጋል። "
#EPA
@tikvahethiopia
የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፍቃደኛ አለመሆን የሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎችን ለማጣራት እያደረግኩት ባለው ጥረት ላይ እንቅፋት ሆኖብኛል ሲል የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ማስታወቁን የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት አስነብቧል።
የቢሮ ኃላፊ አቶ አሥራት አዳሮ ለኢፕድ በሰጡት ቃል ፦
" በክልሉ ውስጥ ተቀጥረው የሚሠሩ #ባለሙያዎችንና #ኃላፊዎችን የትምህርት ማስረጃዎቻቸውን በመያዝ ትምህርታቸውን ባጠናቀቁበት ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች ድረስ በመሄድ ማስረጃዎቹ ሐሰተኛ ናቸው ወይስ አይደሉም የሚለውን ለማጣራት ሙከራ ብናደርግም የግል ትምህርት ተቋማት ፈቃደኞች አይደሉም፡፡
ከ5 እና 6 ወር በኋላ ተመልሳችሁ ኑ የሚል ምላሽ ስለሚሰጡን ወደ ትምህርት ተቋማቱ የምንልካቸው ባለሙያዎች ለእንግልት እየተዳረጉ ነው።
ሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃ የትምህርት ጥራትን ከመጉዳትም ባሻገር የተማረ የሰው ኃይል በተፈለገው ቦታ ላይ እንዳይሠራና ጥራት ያለው አገልግሎት ለኅብረተሰቡ እንዳይሰጥ የሚያደርግ ነው።
በሐሰተኛ የትምህርት ማስረጃዎች ተቀጥረው በሥራ ላይ በሚገኙ #አመራርና #ባለሙያዎች ሕዝቡ ትክክለኛ አገልግሎት እንዳያገኝ ሲያደርጉ ነበር ፤ ክልሉ የሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች የትምህርት መረጃን አጣርቶ በሚያገኘው ውጤት መሠረት ከሥራ እና ከደመወዝ ከማገድ ባሻገር በሕግ እንዲጠየቁ ይደረጋል።
የማጣራቱን ውጤት ከአንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከ6ቱም ዞኖች የተጠቃለሉ መረጃዎችን በማደራጀት ምን ያህል አመራርና ባለሙያ በሐሰተኛ ትምህርት ማስረጃ ተቀጥሮ ሲሠራ እንደነበር ለሕዝቡ ይፋ ይደረጋል። "
#EPA
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
አዲስ አበባ ፦
#ከመገናኛ ወደ #ቦሌ በሚወስደው መስመር ላይ የሚገኘው የኢምፔሪያል ተሸጋጋሪ ድልድይ የቀኝ ክፍል ከዛሬ ጥዋት ጀምሮ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል።
የአዲስ አበባ መገዶች ባለስልጣን ፤ የተሸጋጋሪ ድልድዩን የግራ ክፍልና ሌሎች የመንገድ ግንባታውን ቀሪ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ አሳውቋል።
Credit : AARA
@tikvahethiopia
አዲስ አበባ ፦
#ከመገናኛ ወደ #ቦሌ በሚወስደው መስመር ላይ የሚገኘው የኢምፔሪያል ተሸጋጋሪ ድልድይ የቀኝ ክፍል ከዛሬ ጥዋት ጀምሮ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል።
የአዲስ አበባ መገዶች ባለስልጣን ፤ የተሸጋጋሪ ድልድዩን የግራ ክፍልና ሌሎች የመንገድ ግንባታውን ቀሪ ሥራዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሠራ እንደሚገኝ አሳውቋል።
Credit : AARA
@tikvahethiopia
#AGOA
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ከዚህ ቀደም ከAGOA ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ በተላለፈው ውሳኔ ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግና ተመልሳ እንድትገባ እንዲያደርግ የአሜሪካ ኢትዮጵያውያን የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ በደብዳቤ ጠይቋል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ የተያያዘ ሲሆን በመግለጫው የተነሱት ሀሳቦች የሚከተሉት ናቸው ፦
- ኢትዮጵያን ከAGOA ዝርዝር ውስጥ ማስወጣት እስካሁን ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የስራ ዕድል እንዳሳጣ፣ በረዥም ጊዜ ተፅዕኖዎች ተጨማሪ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ለኑሯቸው መሰረት የሆነውን የስራ ዕድል ሊያጡ እንደሚችሉ ይጠበቃል ብሏል።
- ማዕቀቡ በግለሰቦች ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን ፤ ብዙሃኑን የኢትዮጵያን ህዝብ የሚጎዳ ነው። አብዛኞቹ ስራ ያጡት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያሉ ሴት ሰራተኞች ናቸው። ይህን ስራ ማጣት ለመላው ቤተሰብ እና ማህበረሰብ ድህነት እና እጦት አስከትሏል።
- የኢትዮጵያ ሕዝብ የተጠየቀውን አድርጓል። መንግሥት ታሪካዊ የሰላም ስምምነት ፈፅሟል ፤ ዕርዳታ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል፣ አስፈላጊ አገልግሎቶች እየተመለሱ ነው፣ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ጥሰትን የሚያጣራ ኮሚሽን ባለፈው ዓመት አዲስ አበባን ጎብኝቷል።
- ኢትዮጵያን ከAGOA ለተጨማሪ አንድ አመት አስወጥቶ ማቆየት ሙሉ በሙሉ ፋይዳ የለውም። የአሜሪካ መንግስት በምትኩ ሀገሪቱ ሰላም ለማስፈን፣ ለመገንባትና ዲሞክራሲያዊትነቷን ለማስጠበቅ እየሰራች ባለችበት ወቅት ድጋፍ ማድረግ አለበት።
ኮሚቴው በመግለጫው ላይ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ውሳኔውን እንደገና እንዲያጤኑት እና በAGOA ውስጥ ኢትዮጵያ እንድትመለስ ጠይቋል።
ኢትዮጵያ ከAGOA ዝርዝር ከወጣች 1 ዓመት ተቆጥሯል።
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ባይደን አስተዳደር ኢትዮጵያ አሁን ያለችበትን ሁኔታ ታሳቢ በማድረግ ከዚህ ቀደም ከAGOA ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ በተላለፈው ውሳኔ ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግና ተመልሳ እንድትገባ እንዲያደርግ የአሜሪካ ኢትዮጵያውያን የሕዝብ ግንኙነት ኮሚቴ በደብዳቤ ጠይቋል።
ሙሉ መግለጫው ከላይ የተያያዘ ሲሆን በመግለጫው የተነሱት ሀሳቦች የሚከተሉት ናቸው ፦
- ኢትዮጵያን ከAGOA ዝርዝር ውስጥ ማስወጣት እስካሁን ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን የስራ ዕድል እንዳሳጣ፣ በረዥም ጊዜ ተፅዕኖዎች ተጨማሪ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ለኑሯቸው መሰረት የሆነውን የስራ ዕድል ሊያጡ እንደሚችሉ ይጠበቃል ብሏል።
- ማዕቀቡ በግለሰቦች ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን ፤ ብዙሃኑን የኢትዮጵያን ህዝብ የሚጎዳ ነው። አብዛኞቹ ስራ ያጡት ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው በጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪ ውስጥ ያሉ ሴት ሰራተኞች ናቸው። ይህን ስራ ማጣት ለመላው ቤተሰብ እና ማህበረሰብ ድህነት እና እጦት አስከትሏል።
- የኢትዮጵያ ሕዝብ የተጠየቀውን አድርጓል። መንግሥት ታሪካዊ የሰላም ስምምነት ፈፅሟል ፤ ዕርዳታ በከፍተኛ ደረጃ ጨምሯል፣ አስፈላጊ አገልግሎቶች እየተመለሱ ነው፣ የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ መብት ጥሰትን የሚያጣራ ኮሚሽን ባለፈው ዓመት አዲስ አበባን ጎብኝቷል።
- ኢትዮጵያን ከAGOA ለተጨማሪ አንድ አመት አስወጥቶ ማቆየት ሙሉ በሙሉ ፋይዳ የለውም። የአሜሪካ መንግስት በምትኩ ሀገሪቱ ሰላም ለማስፈን፣ ለመገንባትና ዲሞክራሲያዊትነቷን ለማስጠበቅ እየሰራች ባለችበት ወቅት ድጋፍ ማድረግ አለበት።
ኮሚቴው በመግለጫው ላይ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ውሳኔውን እንደገና እንዲያጤኑት እና በAGOA ውስጥ ኢትዮጵያ እንድትመለስ ጠይቋል።
ኢትዮጵያ ከAGOA ዝርዝር ከወጣች 1 ዓመት ተቆጥሯል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Lion #Wegagen አንበሳ ኢንተርናሽናል ባንክ በሽረ እንደስላሴና አካባቢው የሚገኙት ቅርንጫፎቹ የባንክ አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን በዛሬው ዕለት አሳውቋል። በሌላ በኩል ፤ ወጋገን ባንክ በግጭት ምክንያት አገልግሎት ተቋርጦባቸው በቆዩት በአላማጣና በራያ ጥሙጋ ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገልጿል። ባንኩ ሰቲት ሁመራ፣ አዲ ረመፅ ፣ ዳንሻ እና ተከዜ ቅርንጫፎች ቀደም ብለው አገልግሎት…
ወጋገን ባንክ ትላንት በመቐለ በ28 ቅርንጫፎች ስራ ጀምሯል።
ባንኩ መስጠት የጀመረው አገልግሎት ከባንክ ሂሳብ ገንዘብ ማውጣት እና ማስገባት ከክልሉ ውጭ የተላከ ገንዘብ መቀበል ናቸው።
የባንኩ የመቐለ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሃፍቶም ገ/እግዚአብሔር ለቪኦኤ የሰጡት ቃል ፦
" ከፌዴራል ሲስተም ጋር በማያያዝ ማንኛውም ተቀማጭ የነበረውን ደንበኛ ገንዘብ መውሰድ ይችላል በቀን እስከ 1,500 ብር ይሄንን ስንል ከአዲስ አበባ ከሌላም ቦታ በተለይ ከትግራይ ክልል ውጭ ያለው ማንኛውም ገቢ ያደረገ ወደ ሂሳብ እሱን እያየን መክፈል እንችላለን። ከዚህ በተጨማሪ የውጭ ሀዋላም ጀምረናል።
መቐለ የጀመርነው በ28 ቅርንጫፎቻችን ነው፤ ብሩ በጣም ትንሽ ነው፤ ሰጠን ብለንም አናስብም ዞሮ ዞሮ ግን ያሉንን ደንበኞችና ድርጅቶች እነሱን በማስተባበር የተወሰነ ገቢ ስላደረጉልን ይሄንን ገቢ በዓልም ከፊታችን ስላለ ህዝባችን የነበረውን ችግር በመጠኑ በጣም በትንሹ እንኳን ለበዓል ለዶሮም ይሁን፣ ለስጋ ይጠቅማል ከሚለው እሳቤ ስለሆነ ነው ይበቃል የሚል እምነት ግን የለንም።
ከፌዴራል ብር እየጠየቅን ስለሆነ ሲመጣ ህዝባችንን እንክሳለን።
...አሁን ከሂሳብ ወደ ሂሳብ እሱን እያስተካከልን ነው በዚህ ሁለት ቀን እጀምራለን። በቀጣይ የATM እና ሞባይል ባንኪንግና ኢንተርኔት ባንኪንግ እሱን እየጨረስን ነው ከዚህ በፊት ጉዳት የደረሰባቸውን ኤቲኤሞች የእየተካን ነው፤ በቅርብ ጊዜ ሙሉ በሙሉ የATM አገልግሎት እንጀምራለን።"
ወጋገን ባንክ ከመቐለ በተጨማሪ ከዛሬ ጀምሮ ኦዲተሮቹን፣ እቃዎቹን እስከ ዓዲግራት ባለው አካባቢ፤ በሌላው መስመር እስከ መኸኒና ዓብይ ዓዲ ያሉት ቅርንጫፎቹ እንደሚያደርስ ገልጿል። በሁለትና ሶስት ቀን ውስጥ የቀሩት ቅርንጫፎች ስራ እንደሚጀምሩ አሳውቋል።
#ቪኦኤ
@tikvahethiopia
ባንኩ መስጠት የጀመረው አገልግሎት ከባንክ ሂሳብ ገንዘብ ማውጣት እና ማስገባት ከክልሉ ውጭ የተላከ ገንዘብ መቀበል ናቸው።
የባንኩ የመቐለ ዲስትሪክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሃፍቶም ገ/እግዚአብሔር ለቪኦኤ የሰጡት ቃል ፦
" ከፌዴራል ሲስተም ጋር በማያያዝ ማንኛውም ተቀማጭ የነበረውን ደንበኛ ገንዘብ መውሰድ ይችላል በቀን እስከ 1,500 ብር ይሄንን ስንል ከአዲስ አበባ ከሌላም ቦታ በተለይ ከትግራይ ክልል ውጭ ያለው ማንኛውም ገቢ ያደረገ ወደ ሂሳብ እሱን እያየን መክፈል እንችላለን። ከዚህ በተጨማሪ የውጭ ሀዋላም ጀምረናል።
መቐለ የጀመርነው በ28 ቅርንጫፎቻችን ነው፤ ብሩ በጣም ትንሽ ነው፤ ሰጠን ብለንም አናስብም ዞሮ ዞሮ ግን ያሉንን ደንበኞችና ድርጅቶች እነሱን በማስተባበር የተወሰነ ገቢ ስላደረጉልን ይሄንን ገቢ በዓልም ከፊታችን ስላለ ህዝባችን የነበረውን ችግር በመጠኑ በጣም በትንሹ እንኳን ለበዓል ለዶሮም ይሁን፣ ለስጋ ይጠቅማል ከሚለው እሳቤ ስለሆነ ነው ይበቃል የሚል እምነት ግን የለንም።
ከፌዴራል ብር እየጠየቅን ስለሆነ ሲመጣ ህዝባችንን እንክሳለን።
...አሁን ከሂሳብ ወደ ሂሳብ እሱን እያስተካከልን ነው በዚህ ሁለት ቀን እጀምራለን። በቀጣይ የATM እና ሞባይል ባንኪንግና ኢንተርኔት ባንኪንግ እሱን እየጨረስን ነው ከዚህ በፊት ጉዳት የደረሰባቸውን ኤቲኤሞች የእየተካን ነው፤ በቅርብ ጊዜ ሙሉ በሙሉ የATM አገልግሎት እንጀምራለን።"
ወጋገን ባንክ ከመቐለ በተጨማሪ ከዛሬ ጀምሮ ኦዲተሮቹን፣ እቃዎቹን እስከ ዓዲግራት ባለው አካባቢ፤ በሌላው መስመር እስከ መኸኒና ዓብይ ዓዲ ያሉት ቅርንጫፎቹ እንደሚያደርስ ገልጿል። በሁለትና ሶስት ቀን ውስጥ የቀሩት ቅርንጫፎች ስራ እንደሚጀምሩ አሳውቋል።
#ቪኦኤ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DigitalLottery አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ህዳር 23 /2015 ዓ/ም በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል። 1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 005187503482 ሆኖ ወጥቷል። 👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 005187503482 👉 800 ሺህ ብር - 005304384029 👉 350 ሺህ ብር - 005255580874 👉 200 ሺህ ብር - 005230182809…
#DigitalLottery
አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ታህሳስ 25 /2015 በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል።
1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 006304740687 ሆኖ ወጥቷል።
👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 006304740687
👉 800 ሺህ ብር - 006299531220
👉 350 ሺህ ብር - 006144680758
👉 200 ሺህ ብር - 006297990128
👉 160 ሺህ ብር - 006266851201
👉 120 ሺህ ብር - 006282798312
(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል)
@tikvahethiopia
አድማስ ዲጂታል ሎተሪ ዛሬ ታህሳስ 25 /2015 በብሄራዊ ሎተሪ የዕጣ ማውጫ አዳራሽ በህዝብ ፊት ወጥቷል።
1.5 ሚሊዮን ብር ባለዕድለኛ የሚያደርገው የዕጣ ቁጥር 006304740687 ሆኖ ወጥቷል።
👉 1.5 ሚሊዮን ብር - 006304740687
👉 800 ሺህ ብር - 006299531220
👉 350 ሺህ ብር - 006144680758
👉 200 ሺህ ብር - 006297990128
👉 160 ሺህ ብር - 006266851201
👉 120 ሺህ ብር - 006282798312
(ተጨማሪ የዕጣ ቁጥሮች ከላይ ተያይዘዋል)
@tikvahethiopia