TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዜዳንቱ አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል። ሩቶ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የተገለፀ ሲሆን ሁለቱ መሪዎች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል። ዶ/ር…
#HappeningNow

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱን በአዲስ አበባ " ወዳጅነት አደባባይ " በአሁን ሰዓት እያካሄደ ይገኛል።

በዚሁ ስነስርዓት ላይ ቀደም ብሎ እንደተገለፀው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ተገኝተዋል።

Photo Credit : Safaricom Ethiopia

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#HappeningNow ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱን በአዲስ አበባ " ወዳጅነት አደባባይ " በአሁን ሰዓት እያካሄደ ይገኛል። በዚሁ ስነስርዓት ላይ ቀደም ብሎ እንደተገለፀው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የኬንያው ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ተገኝተዋል። Photo Credit : Safaricom Ethiopia @tikvahethiopia
#BREAKING

ለሳፋሪኮም ሞባይል መኒ ተፈቀደ።

የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ " ሞባይል መኒ " መፈቀዱን አስታውቀዋል።

ይህን ያሳወቁት በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ነው።

ውድ ቤተሰቦቻችን ተጨማሪ መረጃዎችን እንልክላችኃለን።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING ለሳፋሪኮም ሞባይል መኒ ተፈቀደ። የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ " ሞባይል መኒ " መፈቀዱን አስታውቀዋል። ይህን ያሳወቁት በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ነው። ውድ ቤተሰቦቻችን ተጨማሪ መረጃዎችን እንልክላችኃለን። @tikvahethiopia
#MobileMoney

ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ምስጋና አቀረቡ።

የኬንያው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ዊልያም ሩቶ የኢትዮጵያ መንግስት ለሳፋሪኮም የሞባይል ገንዘብ ዝውውር እንዲያደርግ በመፍቀዱ ደስታ እንደተሰማቸው ገልፀዋል።

ፕሬዜዳንት ሩቶ " የኬንያ ህዝብ ወደ ኢትዮጵያ ስመጣ  ይህን እንዳስፈጽም የቤት ስራ ሰጥቶኝ ነበር፤ የኢትዮጵያ መንግስት ይህን አገልግሎት በመፍቀዱ አመሰግናለሁ " ብለዋል።

ሳፋሪኮም በኬንያ በ " ኤም ፔሳ " የገንዘብ አገልግሎት ያገኘውን ስኬት በኢትዮጵያ ለመድገም እንደሚሰራም ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኬንያ ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። ፕሬዜዳንቱ አዲስ አበባ ሲደርሱ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ተቀብለዋቸዋል። ሩቶ በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የሁለትዮሽ ውይይት እንደሚያደርጉ የተገለፀ ሲሆን ሁለቱ መሪዎች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሀገር አቀፍ የቴሌኮም ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ እንደሚገኙም ለማወቅ ተችሏል። ዶ/ር…
#Kenya #Ethiopia

ፕሬዜዳንት ዶክተር ዊሊያም ሩቶ የኢትዮጵያ የስራ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ኬንያ አመሻሹን ተመልሰዋል።

ጉብኝታቸው ምን ይመስል ነበር ? የኬንያ ፕ/ት ፅ/ቤት ምን አለ ?

- ፕሬዝዳንት ሩቶ ጥዋት አዲስ አበባ ሲገቡ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና ከፍተኛ ባለስልጣናት ናቸው ቦሌ ኤርፖርት ተገኝተው የተቀበሏቸው።

- ከዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል።

- ከቀናት በፊት የተመረቀውን የኢትዮጵያ ሳይንስ ሙዚየምን ከዶ/ር ዐቢይ ጋር ሆነው ጎብኝተዋል።

- ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ጋር ሆነው በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የቴሌኮም አገልግሎት ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

እንደ ኬንያ ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት (ስቴት ሀውስ) መረጃ ፦

ኬንያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ረጅም ጊዜ የዘለቀ ግኝኑነት እና ቅርበት በመጠቀም የድንበር ተሻጋሪ ንግድን ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላት የገለፀች ሲሆን ፕሬዜዳንት ሩቶም ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ ጋር በቅርበት እንደሚሰሩ ገልፀዋል።

" የኬንያ - ኢትዮጵያ አጋርነት ለጋራ ተጠቃሚነታችን እና ቀጠናዊ መረጋጋት የማዕዘን ድንጋይ ነው " ሲሉ ሩቶ ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ #የላሙ_ወደብን ለደቡብ ኢትዮጵያ ክፍል እንደ መነሻ ወደብ እንድትጠቀም ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ጠይቀዋል።

ምንጭ፦ የኬንያ ፕ/ት ፅ/ቤት / የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ፅ/ቤት

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር መግለጫቸው ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገው በሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በሚመለከት ነው።

በመግለጫቸው ምን አሉ ?

- 391 የሚደርሱ ሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ተዘግቷል ፤ የግለሠቦቹን ስም ዝርዝር ለፍትሕ ሚኒስቴር በመላክ ክስ የመመስረት ሂደት ይጀመራል።

- በህገ ወጥ መልኩ #በጥቁር_ገበያ ላይ በተሠማሩ አካላት ላይ የተጠናከረ እርምጃ ይወሰዳል።

- በባንክ ቤቶች ውስጥ ያሉ የባንክ #ኃላፊዎችና #ሰራተኞችም በህገወጥ ተግባር ላይ የተሰማሩ አሉ በነዚህ አካላት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃና ሕጋዊ እርምጃ ይወሰዳል።

- ሕገወጥ ድርጊት ለሚጠቁሙ ዜጎች የወሮታ አከፋፈል ስርዓት ተዘጋጅቷል።

ይህ ማለት ፦

• ከተፈቀደው በላይ በቤት ውስጥ የብር ክምችት የሚያደርጉ፣

• የሀሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን የሚሠሩና የሚያሠራጩ አካላት፣

• በህገወጥ መልኩ የሐዋላ አገልግሎት የሚሠጡ ወይም በጥቁር ገበያ ላይ የተሰማሩ አካላትን ለሚጠቁሙ ዜጎች #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸውን በጠበቀ መልኩ #የሚሸልምና #ወረታውን የሚከፈል ይሆናል።

- የዋጋ ግሽበቱን ለመቆጣጠር የፈቀደውን የፍራኮ ቫሉታ ፍቃድ እንደ እድል በመጠቀም በህገወጥ መንገድ ዶላር በመጠቀም ሸቀጦችን የማስገባት ተግባር የተስተዋለ በመሆኑ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶች የባን ማስረጃ ለብሔራዊ ባንክ እንዲያቀርቡ ይደረጋል።

Credit : EPA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶክተር ይናገር ደሴ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተው ነበር መግለጫቸው ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገው በሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች በሚመለከት ነው። በመግለጫቸው ምን አሉ ? - 391 የሚደርሱ ሕገወጥ የሐዋላ ስራ ላይ የተሰማሩ ሰዎች የባንክ ሂሳባቸው ተዘግቷል ፤ የግለሠቦቹን ስም ዝርዝር ለፍትሕ ሚኒስቴር በመላክ ክስ የመመስረት ሂደት ይጀመራል። …
የብሔራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ፦

- ኢትዮጵያዊያን በግለሰብ ደረጃ ከ100 ሺህ ብር በላይ ለድርጅቶች ደግሞ ከ200 ሺህ ብር በላይ ቤት ውስጥ ማስቀመጥ የተከለከለ መሆኑን መገንዘብ ይኖርባቸወል።

- ገንዘብ በባንክ መቀመጥ አለበት ፤ የግብይት ስርዓትም በባንክ ማካሄድ ይቻላል።

- መመሪያው ከሚፈቅደው የገንዘብ መጠን በላይ አስቀምጦ የተገኘን አካል #የጠቆመ ግለሰብ 15 በመቶ የወረታ ክፍያ ይከፈለዋል።

- በውጭ አገራት ገንዘብ ግብይት መፈጸምም ሆነ በህገወጥ መንገድ ይዞ መገኘት አይቻልም።

- ወርቅን በህገወጥ መልኩ ቤት ውስጥ ማከማቸት የማይቻል ሲሆን በህገወጥ መልኩ ወርቅን ያከማቸ ግለሰብ ለጠቆመ ግለሰብ ባንኩ በወቅቱ ባለው ግብይት የ15 በመቶ ወረታ ይከፈለዋል።

- በህገወጥ የሃዋላ የውጭ አገራት የተሰማሩ አካላትን ለጠቆመም እስከ 25 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል።

- በህገወጥ ገንዘብ ህትመት የተሰማሩ አካላትን ያጋለጠም ከ20 ሺህ እስከ 200 ሺህ ብር ወረታ ይከፈለዋል።

- ጠቋሚዎች ወረታውና ሽልማቱ የሚበረከትላቸው #ደህንነታቸው እና #ሚስጥራዊነታቸው በተጠበቀ መልኩ ነው።

Credit : ENA

@tikvahethiopia