#Dubai #Ethiopia
የዱባይ ቱሪዝም የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች ኤግዚቢሽን በኢትዮጵያ ተካሄደ።
ዱባይ ቱሪዝም የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች ኤግዚቢሽን ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል ተካሂዷል።
ኤግዚቢሽኑ በኢትዮጵያ ካሉ የዘርፉ ባለድሻዎች ጋር በቅርበት በመስራት ዱባይ በውድ ዋጋ ብቻ ሳይሆን በተመጣጣኝ ክፍያ መጎብኘት የሚቻልባቸውን መንገዶች ማመላከት ዓላማ አድርጎ መካሄዱ ነው የተገለጸው።
በዚህ ዝግጅት ከዱባይ ቱሪዝም ጋር ወደ አዲስ አበባ ከ25 የማያንሱ ድርጅቶች ተወካዮቻቸውን የላኩ ሲሆን በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በማቅረብ በኢትዮጵያ ካሉ የአስጎብኚ ድርጅቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል።
ዛሬ ከተካሄደው የዱባይን የቱሪዝም ገብያ ከማስተዋወቅ ባለፈ በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ ለሚገኙ ለቁጥራቸው 200 ለሚጠጉ በኢትዮጵያ ለሚገኙ አስጎብኚ ድርጅቶች ሥልጠና ተሰጥቷል።
ከሁለት ቀኑ መርሐግብር በተጨማሪ በዛሬው የመዝጊያ መርሐግብርም በዕለቱ ከተገኙ የቢዝነስ አጋሮች እንዲሁም የአስጎብኚ ድርጅቶች ዕጣ በማውጣት የነጻ ጉዞ ዕድሎች እንደሚመቻችላቸው አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ይህና መሰል የትውውቅ መድረክ ከዚህ ቀደም ሳይኖር #ኢትዮጵያ ከሰሀራ በታች ከሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ዱባይ በሚደረግ የንግድና የቱሪዝም ጉዞ ከናይጄሪያ ቀጥላ ሁለተኛ ሀገር ናት።
በቀጣይም በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ሰፊ ሥራዎች ለመስራት ታቅዷል።
ፎቶ : ዛሬ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል የተካሄደው የትውውቅ መድረክ
@tikvahethiopia
የዱባይ ቱሪዝም የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች ኤግዚቢሽን በኢትዮጵያ ተካሄደ።
ዱባይ ቱሪዝም የምስራቅ አፍሪካ ከተሞች ኤግዚቢሽን ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል ተካሂዷል።
ኤግዚቢሽኑ በኢትዮጵያ ካሉ የዘርፉ ባለድሻዎች ጋር በቅርበት በመስራት ዱባይ በውድ ዋጋ ብቻ ሳይሆን በተመጣጣኝ ክፍያ መጎብኘት የሚቻልባቸውን መንገዶች ማመላከት ዓላማ አድርጎ መካሄዱ ነው የተገለጸው።
በዚህ ዝግጅት ከዱባይ ቱሪዝም ጋር ወደ አዲስ አበባ ከ25 የማያንሱ ድርጅቶች ተወካዮቻቸውን የላኩ ሲሆን በዛሬው ዕለት ሥራቸውን በማቅረብ በኢትዮጵያ ካሉ የአስጎብኚ ድርጅቶችና ባለድርሻ አካላት ጋር ትውውቅ አድርገዋል።
ዛሬ ከተካሄደው የዱባይን የቱሪዝም ገብያ ከማስተዋወቅ ባለፈ በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ ለሚገኙ ለቁጥራቸው 200 ለሚጠጉ በኢትዮጵያ ለሚገኙ አስጎብኚ ድርጅቶች ሥልጠና ተሰጥቷል።
ከሁለት ቀኑ መርሐግብር በተጨማሪ በዛሬው የመዝጊያ መርሐግብርም በዕለቱ ከተገኙ የቢዝነስ አጋሮች እንዲሁም የአስጎብኚ ድርጅቶች ዕጣ በማውጣት የነጻ ጉዞ ዕድሎች እንደሚመቻችላቸው አዘጋጆቹ ጠቁመዋል።
ይህና መሰል የትውውቅ መድረክ ከዚህ ቀደም ሳይኖር #ኢትዮጵያ ከሰሀራ በታች ከሚገኙ የአፍሪካ ሀገራት ወደ ዱባይ በሚደረግ የንግድና የቱሪዝም ጉዞ ከናይጄሪያ ቀጥላ ሁለተኛ ሀገር ናት።
በቀጣይም በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ሰፊ ሥራዎች ለመስራት ታቅዷል።
ፎቶ : ዛሬ በሀያት ሪጀንሲ ሆቴል የተካሄደው የትውውቅ መድረክ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ምስጋና ! የኢሰመኮ ምክትል ዋና ኮሚሽነር ራኬብ መሰለ ፦ " የአፋር ክልላዊ መንግሥት በሰመራ እና አጋቲና መጠለያ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ በማድረጉ ኢሰመኮ እውቅና ይሰጠል። በተለይ በዚህ ሥራ ላይ በዋናነት የተሳተፉትን የአፋር የክልል አደጋ መከላከል እና የምግብ ዋስትና ቢሮ፣ የክልሉ የጤና…
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ፦
- ኢሰመኮ ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ላይ ባወጣው መግለጫ በአፋር ክልል ፤ ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች በታኅሣሥ ወር 2014 ተይዘው የቆዩና በሁለቱ ካምፖች የሚገኙ ወደ 9 ሺህ የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ያሉበትን አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በመግለጽ በአፋጣኝና ያለቅድመ ሁኔታ እንደለቀቁ አሳስቦ ነበር።
- በሁለቱ ካምፖች ውስጥ ተይዘው የሚገኙ ሰዎች ችግር በሚፈታበት ሁኔታ ላይ በሐምሌ 6 ቀን 2014 ዓ.ም. በሰመራ ከተማ ከክልሉ መንግሥት ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ምክክር የክልሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀው ነበር። በዚሁ መሰረት በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር የምግብ፣ ሕክምና እና መጠለያ አቅርቦትን ለማሻሻል እንዲሁም የመንቀሳቀስ ነፃነቶቻቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማረጋገጥ ጥረቶች ተደርገዋል፤ እንዲሁም ምዝገባ እና በሁለቱም ካምፖች የሚገኙ ሰዎች ወደየትኛው አካባቢዎች መመለስ እንደሚፈልጉ ለማወቅ የፍላጎት ዳሰሳዎች ተከናውናዋል።
- ኢሰመኮ ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ላይ ባወጣው መግለጫ በእነዚህ ካምፖች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን ወደ መኖሪያ ቀዬአቸው የመመለሱን ሂደት በበጎ የሚመለከተው እና ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል መሆኑን አሳውቆ ነበር።
- በሰመራ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የነበሩ ሰዎች በዋናነት በአፋር ክልል አብአላ አካባቢ ወደሚገኙ የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው የመመለስ ፍላጎት በማሳየታቸው ከነሐሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. በተከናወነ የመመለስ ሥራ ወደ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው እንዲመለሱ ተደርጎ የሰመራ መጠለያ ጣቢያ #እንዲዘጋ ሆኗል።
- በአጋቲና የመጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ወደ 600 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች በተከናወነው የፍላጎት ዳሰሳ ወደ ትግራይ ክልል መሄድ የሚፈልጉ መሆኑን የገለጹ ቢሆንም በአፋር ክልል መንግሥት እና በትግራይ ክልል አስተዳደር መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ባለመኖሩ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል ለማስፈጸም ጥረቶች በመደረግ ላይ ባሉበት ወቅት ጦርነቱ በድጋሚ በመቀስቀሱ ለማስፈጸም አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል።
- ኢሰመኮ የአፋር ክልላዊ መንግሥት በሰመራ እና አጋቲና መጠለያ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ በማድረጉ ምስጋና አቅርቧል።
@tikvahethiopia
- ኢሰመኮ ሰኔ 22 ቀን 2014 ዓ.ም. ላይ ባወጣው መግለጫ በአፋር ክልል ፤ ሰመራ ከተማ በሚገኙ ሰመራ እና አጋቲና ካምፖች በመባል በሚታወቁ ቦታዎች ከትግራይ ክልል አዋሳኝ ከሆኑ 3 የአፋር ክልል ወረዳዎች በታኅሣሥ ወር 2014 ተይዘው የቆዩና በሁለቱ ካምፖች የሚገኙ ወደ 9 ሺህ የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ያሉበትን አሳሳቢ የሰብአዊ መብቶች ሁኔታ በመግለጽ በአፋጣኝና ያለቅድመ ሁኔታ እንደለቀቁ አሳስቦ ነበር።
- በሁለቱ ካምፖች ውስጥ ተይዘው የሚገኙ ሰዎች ችግር በሚፈታበት ሁኔታ ላይ በሐምሌ 6 ቀን 2014 ዓ.ም. በሰመራ ከተማ ከክልሉ መንግሥት ኃላፊዎች ጋር በተደረገ ምክክር የክልሉ የመንግሥት ኃላፊዎች ችግሩን ለመፍታት አስፈላጊውን እርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀው ነበር። በዚሁ መሰረት በክልሉ ከሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር በመተባበር የምግብ፣ ሕክምና እና መጠለያ አቅርቦትን ለማሻሻል እንዲሁም የመንቀሳቀስ ነፃነቶቻቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማረጋገጥ ጥረቶች ተደርገዋል፤ እንዲሁም ምዝገባ እና በሁለቱም ካምፖች የሚገኙ ሰዎች ወደየትኛው አካባቢዎች መመለስ እንደሚፈልጉ ለማወቅ የፍላጎት ዳሰሳዎች ተከናውናዋል።
- ኢሰመኮ ነሐሴ 12 ቀን 2014 ዓ.ም. ላይ ባወጣው መግለጫ በእነዚህ ካምፖች የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን ወደ መኖሪያ ቀዬአቸው የመመለሱን ሂደት በበጎ የሚመለከተው እና ክትትል ማድረጉን የሚቀጥል መሆኑን አሳውቆ ነበር።
- በሰመራ መጠለያ ጣቢያ ውስጥ የነበሩ ሰዎች በዋናነት በአፋር ክልል አብአላ አካባቢ ወደሚገኙ የቀድሞ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው የመመለስ ፍላጎት በማሳየታቸው ከነሐሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም. እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2014 ዓ.ም. በተከናወነ የመመለስ ሥራ ወደ መኖሪያ አካባቢዎቻቸው እንዲመለሱ ተደርጎ የሰመራ መጠለያ ጣቢያ #እንዲዘጋ ሆኗል።
- በአጋቲና የመጠለያ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ ወደ 600 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች በተከናወነው የፍላጎት ዳሰሳ ወደ ትግራይ ክልል መሄድ የሚፈልጉ መሆኑን የገለጹ ቢሆንም በአፋር ክልል መንግሥት እና በትግራይ ክልል አስተዳደር መካከል ቀጥተኛ ግንኙነት ባለመኖሩ በዓለም አቀፍ ድርጅቶች በኩል ለማስፈጸም ጥረቶች በመደረግ ላይ ባሉበት ወቅት ጦርነቱ በድጋሚ በመቀስቀሱ ለማስፈጸም አስቸጋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል።
- ኢሰመኮ የአፋር ክልላዊ መንግሥት በሰመራ እና አጋቲና መጠለያ ጣቢያዎች ተይዘው የነበሩ ሰዎች በኢሰመኮ ምክረ ሃሳቦች መሰረት እንዲለቀቁና በፍላጎታቸው መሰረት ወደመጡባቸው አካባቢዎች እንዲመለሱ በማድረጉ ምስጋና አቅርቧል።
@tikvahethiopia
* ጥንቃቄ
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና መቃረብን ተከትሎ የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ በመሆኑ ተማሪዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል።
" የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተሸጋገረ " እየተባለ በአንዳንድ የማህበራዊ ገፆች ላይ የሚሰራጨው መረጃ ምንጩ የማይታወቅ በትምህርት ሚኒስቴር ሆነ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ያልተገለፀ ነው።
ተማሪዎች ከፈተና ጋር በተያያዘ ማንኛውም አዲስ መረጃ ሲኖር በትምህርት ሚኒስቴር / በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፆች እንዲሁም በህዝብ መገናኛ ብዙሃን የሚገለፅ መሆኑን በማወቅ በሀሰተኛ መረጃ ሳትረበሹ ተረጋግታችሁ ዝግጅታችሁን ልታደርጉ ይገባል።
የተማሪ ወላጆችም ትክክለኛና የተረጋገጡ መረጃዎች በትክክለኛ የመስሪያ ቤቶቹ አድራሻ እንዲሁም በህዝብ መገናኛ ብዙሃን የሚነገሩት መሆናቸውን በማስገንዘብ ልጆቻችሁ እንዳይረበሹ ልታድርጉ ይገባል።
ተፈታኝ ተማሪዎች እንዲረበሹ እና ብዙ የለፉበት ዝግጅታቸው እንዲደናቀፍባቸው የሚያደርጉ ሀሰተኛ የፈጠራ ወሬዎችን የምታሰራጩ አካላት ድርጊታችሁ ፍፁም ተገቢ ያልሆነ ፤ በትውልድ ላይም አሉታዊ ተፅእኖ ያለው መሆኑን በማወቅ ከድርጊታችሁ ልትታቀቡ ይገባል።
ተማሪዎች ምንጩ የማይታወቅ እና የተለያዩ አካላት ተከታይ ለማፍራት እንዲሁም ሆን ብለው ተማሪ እንዲረበሽ ለማድረግ ሲሉ በማህበራዊ ሚዲያ የሚያሰራጩትን መረጃ ወደ ጓደኞቻችሁ ባለመላክ ሀሰተኛ መረጃዎችን ተከላከሉ።
@tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና መቃረብን ተከትሎ የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ በመሆኑ ተማሪዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል።
" የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተሸጋገረ " እየተባለ በአንዳንድ የማህበራዊ ገፆች ላይ የሚሰራጨው መረጃ ምንጩ የማይታወቅ በትምህርት ሚኒስቴር ሆነ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ያልተገለፀ ነው።
ተማሪዎች ከፈተና ጋር በተያያዘ ማንኛውም አዲስ መረጃ ሲኖር በትምህርት ሚኒስቴር / በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፆች እንዲሁም በህዝብ መገናኛ ብዙሃን የሚገለፅ መሆኑን በማወቅ በሀሰተኛ መረጃ ሳትረበሹ ተረጋግታችሁ ዝግጅታችሁን ልታደርጉ ይገባል።
የተማሪ ወላጆችም ትክክለኛና የተረጋገጡ መረጃዎች በትክክለኛ የመስሪያ ቤቶቹ አድራሻ እንዲሁም በህዝብ መገናኛ ብዙሃን የሚነገሩት መሆናቸውን በማስገንዘብ ልጆቻችሁ እንዳይረበሹ ልታድርጉ ይገባል።
ተፈታኝ ተማሪዎች እንዲረበሹ እና ብዙ የለፉበት ዝግጅታቸው እንዲደናቀፍባቸው የሚያደርጉ ሀሰተኛ የፈጠራ ወሬዎችን የምታሰራጩ አካላት ድርጊታችሁ ፍፁም ተገቢ ያልሆነ ፤ በትውልድ ላይም አሉታዊ ተፅእኖ ያለው መሆኑን በማወቅ ከድርጊታችሁ ልትታቀቡ ይገባል።
ተማሪዎች ምንጩ የማይታወቅ እና የተለያዩ አካላት ተከታይ ለማፍራት እንዲሁም ሆን ብለው ተማሪ እንዲረበሽ ለማድረግ ሲሉ በማህበራዊ ሚዲያ የሚያሰራጩትን መረጃ ወደ ጓደኞቻችሁ ባለመላክ ሀሰተኛ መረጃዎችን ተከላከሉ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፕሬዜዳንት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ ስለ #ኢትዮጵያ እና ታላላቅ ሀይቆች ቀጠና ምን አሉ ? ዛሬ ቃለ መሀላ የፈፀሙት የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ባደረጉት ንግግር በኢትዮጵያ ሰላም ለማምጣት በሚደረገው ጥረት የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የሚያከናውኑትን ተግባር እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል። ሩቶ ፤ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በኢትዮጵያ እና በታላላቅ ሐይቆች ቀጠና (ግሬት ሌክስ) ሰላም ለማምጣት…
#KENYA
አሜሪካ ያሰራጨችው ፅሁፍ ?
ከቀናት በፊት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የኬንያ ፕሬዜዳንት ሆነው ቃለመሀላ በፈፀሙ ወቅት ባሰሙት ንግግር የቀድሞ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ #በኢትዮጵያ እና በታላላቅ ሐይቆች ቀጠና (ግሬት ሌክስ) ሰላም ለማምጣት የሚያስመሰግን ተግባር ማከናወናቸውን ገልፀው እሳቸውም የተጀመሩ የሰላም ጥረቶች ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አሳውቀው ነበር።
ሩቶ ፤ የቀድሞው ፕሬዝዳንት የጀመሩትን ሰላም የማምጣት ጥረት ለመቀጠል መስማማታቸውን እና የኬንያ ሕዝብን በመወከል የሰላም ንግግሮችን ለመምራት መስማማታቸውንም በዕለቱ ገልፀው ነበር።
ትላንት የአሜሪካ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባሰራጨው መልዕክት ኡሁሩ ኬንያታ በሰሜን ኢትዮጵያ እና በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ላለው ግጭት የሰላም ልዩ ልዑክ ሆነው መሾማቸውን በደስታ እንደምትቀበለው ገልፃለች።
አሁሩ በሰላም ልዩ ልዑክነት የተሾሙበት ወቅት ለሁለቱም ግጭቶች ወሳኝ በሆነ ጊዜ መሆኑን እና ስራቸውም ወሳኝ እንደሚሆን አሳውቃለች።
አሜሪካ ትላንት ባሰራጨችው መልዕክት ኡሁሩ ኬንያታን ማን እንደሾማቸው በግልፅ አለመፃፏን ተከትሎ በርካቶች ዘንድ ግርታን ፈጥሯል፤ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ምትክ የተሾሙ የመሰላቸውም አልጠፉም።
ግርታው አሜሪካ ያሰራጨችው መልዕክት ሙሉ ባለመሆኑ የተፈጠረ ሲሆን ኡሁሩ ኬንያታ የተሾሙት በሀገራቸው ኬንያ ፤ የኬንያን ህዝብ እና መንግስት ወክለው የተጀመሩ ሰላም ንግግሮችን እንዲቀጥሉ ነው እንጂ በአፍሪካ ህብረት ስር አይደለም።
የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦባሳንጆ አሁንም ስራ ላይ ናቸው፤ ከጥቂት ቀናት በፊት የኃላፊነት ጊዜያቸው እንደተራዘመላቸው መገለፁ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
አሜሪካ ያሰራጨችው ፅሁፍ ?
ከቀናት በፊት ዶ/ር ዊሊያም ሩቶ የኬንያ ፕሬዜዳንት ሆነው ቃለመሀላ በፈፀሙ ወቅት ባሰሙት ንግግር የቀድሞ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ #በኢትዮጵያ እና በታላላቅ ሐይቆች ቀጠና (ግሬት ሌክስ) ሰላም ለማምጣት የሚያስመሰግን ተግባር ማከናወናቸውን ገልፀው እሳቸውም የተጀመሩ የሰላም ጥረቶች ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆናቸውን አሳውቀው ነበር።
ሩቶ ፤ የቀድሞው ፕሬዝዳንት የጀመሩትን ሰላም የማምጣት ጥረት ለመቀጠል መስማማታቸውን እና የኬንያ ሕዝብን በመወከል የሰላም ንግግሮችን ለመምራት መስማማታቸውንም በዕለቱ ገልፀው ነበር።
ትላንት የአሜሪካ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባሰራጨው መልዕክት ኡሁሩ ኬንያታ በሰሜን ኢትዮጵያ እና በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ላለው ግጭት የሰላም ልዩ ልዑክ ሆነው መሾማቸውን በደስታ እንደምትቀበለው ገልፃለች።
አሁሩ በሰላም ልዩ ልዑክነት የተሾሙበት ወቅት ለሁለቱም ግጭቶች ወሳኝ በሆነ ጊዜ መሆኑን እና ስራቸውም ወሳኝ እንደሚሆን አሳውቃለች።
አሜሪካ ትላንት ባሰራጨችው መልዕክት ኡሁሩ ኬንያታን ማን እንደሾማቸው በግልፅ አለመፃፏን ተከትሎ በርካቶች ዘንድ ግርታን ፈጥሯል፤ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዜዳንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ምትክ የተሾሙ የመሰላቸውም አልጠፉም።
ግርታው አሜሪካ ያሰራጨችው መልዕክት ሙሉ ባለመሆኑ የተፈጠረ ሲሆን ኡሁሩ ኬንያታ የተሾሙት በሀገራቸው ኬንያ ፤ የኬንያን ህዝብ እና መንግስት ወክለው የተጀመሩ ሰላም ንግግሮችን እንዲቀጥሉ ነው እንጂ በአፍሪካ ህብረት ስር አይደለም።
የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦባሳንጆ አሁንም ስራ ላይ ናቸው፤ ከጥቂት ቀናት በፊት የኃላፊነት ጊዜያቸው እንደተራዘመላቸው መገለፁ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
ለግል_መገልገያ_እንዲውሉ_ወደ_አገር_የሚገቡ_ወይም_ከአገር_የሚወጡ_ዕቃዎችን_ለመወሰን_የወጣ_መመሪያ_ቁጥር.PDF
4.6 MB
#ጉምሩክ_ኮሚሽን
የግል መገልገያ እቃዎች መመሪያ ተሻሻለ።
የግል መገልገያ እቃዎች ወደሀገር የሚገቡበትን ሁኔታ የሚወስነው በስራ ላይ ያለው መመሪያ ለህገወጥ ንግድ በር የከፈተና የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ተፅዕኖ የፈጠረ በመሆኑ በመመሪያ ቁጥር 923/14 ተተክትቷል ሲል የጉምሩክ ኮሚሽን አሳውቋል።
ቀድሞ በነበረው መመሪያ ከቀረጥና ታክስ ነፃ ሆነው በመንገደኞች እንድገቡ የተፈቀዱ 102 አይነት እቃዎች ወደ 16 አይነት (84%) ዝቅ እንዲሉ ተደርጓል።
ተመላሽ ኢትዮጵያዊ ቢያንስ ለ12 ወራት ሲገለገሉባቸው የነበሩትን የግል መገልገያ እቃዎች ከቀረጥ ታክስ ነፃ ማስገባት ይችላሉ።
የግል መገልገያ እቃ በስጦታ የተላከለት ሰው የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የሌለው ከሆነ ከቀረጥና ታክስ በተጨማሪ 30% የገቢ ግብር ይከፍላል።
በአንድ ዓመት ውስጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ስጦታ መቀበል አይቻልም።
መመሪያው ከነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተፈፃሚ መሆን እንደጀመረ ተገልጿል።
የመመሪያው ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የግል መገልገያ እቃዎች መመሪያ ተሻሻለ።
የግል መገልገያ እቃዎች ወደሀገር የሚገቡበትን ሁኔታ የሚወስነው በስራ ላይ ያለው መመሪያ ለህገወጥ ንግድ በር የከፈተና የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ተፅዕኖ የፈጠረ በመሆኑ በመመሪያ ቁጥር 923/14 ተተክትቷል ሲል የጉምሩክ ኮሚሽን አሳውቋል።
ቀድሞ በነበረው መመሪያ ከቀረጥና ታክስ ነፃ ሆነው በመንገደኞች እንድገቡ የተፈቀዱ 102 አይነት እቃዎች ወደ 16 አይነት (84%) ዝቅ እንዲሉ ተደርጓል።
ተመላሽ ኢትዮጵያዊ ቢያንስ ለ12 ወራት ሲገለገሉባቸው የነበሩትን የግል መገልገያ እቃዎች ከቀረጥ ታክስ ነፃ ማስገባት ይችላሉ።
የግል መገልገያ እቃ በስጦታ የተላከለት ሰው የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የሌለው ከሆነ ከቀረጥና ታክስ በተጨማሪ 30% የገቢ ግብር ይከፍላል።
በአንድ ዓመት ውስጥ ከሁለት ጊዜ በላይ ስጦታ መቀበል አይቻልም።
መመሪያው ከነሐሴ 23 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተፈፃሚ መሆን እንደጀመረ ተገልጿል።
የመመሪያው ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ለግል_መገልገያ_እንዲውሉ_ወደ_አገር_የሚገቡ_ወይም_ከአገር_የሚወጡ_ዕቃዎችን_ለመወሰን_የወጣ_መመሪያ_ቁጥር.PDF
ለግል መገልገያ ከቀረጥ እና ታክስ ነፃ ሆነው የሚገቡ ዕቃዎች የትኞቹ ናቸው ?
- ሲጋራ | መለኪያ ➤ ግራም | የሚፈቀደው መጠን ➤ 200
- ሲጋር | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 20
- ብትን ትንባሆ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 250
- የአልኮል መጠጥ | መለኪያ ➤ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 2
- ለስላሳ ሽቶ | መለኪያ ➤ ሚሊ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 500
- ሽቶ | መለኪያ ➤ ሚሊ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 500
- #ሞባይል | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 2 (#ሁለት)
- #ላፕቶፕ | መለኪያ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን 1 (#አንድ)
- #የፎቶግራፍ_ካሜራ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- #ዊልቸር | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- #የእጅ_ሰዓት | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- የፂም ወይም የፀጉር መላጫ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- የፀጉር ማድረቂያ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- የፀጉር መተኮሻ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- መንገደኛው የሚጠቀምባቸው መድሃኒቶች እና የህክምና በቁጥር መገልገያዎች | መለኪያ ➤በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ ለአንድ ሰው በሚያስፈልግ መመጠን
- በጉዞ ወቅት ጥቅም ላይ የሚውሉ እና ለቤተሰብ የሚያገለግሉ ፣ ልብሦች፣ ጫማዎች፣ እና የፅዳት እቃዎች | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ ለአንድ ቤተሰብ ከሚያስፈልገው ያልበለጠ
የተሻሻለው የግል መገልገያ እቃዎች - የጉምሩክ መመሪያ https://t.iss.one/tikvahethiopia/73728
@tikvahethiopia
- ሲጋራ | መለኪያ ➤ ግራም | የሚፈቀደው መጠን ➤ 200
- ሲጋር | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 20
- ብትን ትንባሆ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 250
- የአልኮል መጠጥ | መለኪያ ➤ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 2
- ለስላሳ ሽቶ | መለኪያ ➤ ሚሊ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 500
- ሽቶ | መለኪያ ➤ ሚሊ ሊትር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 500
- #ሞባይል | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 2 (#ሁለት)
- #ላፕቶፕ | መለኪያ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን 1 (#አንድ)
- #የፎቶግራፍ_ካሜራ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- #ዊልቸር | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- #የእጅ_ሰዓት | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- የፂም ወይም የፀጉር መላጫ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- የፀጉር ማድረቂያ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- የፀጉር መተኮሻ | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ 1
- መንገደኛው የሚጠቀምባቸው መድሃኒቶች እና የህክምና በቁጥር መገልገያዎች | መለኪያ ➤በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ ለአንድ ሰው በሚያስፈልግ መመጠን
- በጉዞ ወቅት ጥቅም ላይ የሚውሉ እና ለቤተሰብ የሚያገለግሉ ፣ ልብሦች፣ ጫማዎች፣ እና የፅዳት እቃዎች | መለኪያ ➤ በቁጥር | የሚፈቀደው መጠን ➤ ለአንድ ቤተሰብ ከሚያስፈልገው ያልበለጠ
የተሻሻለው የግል መገልገያ እቃዎች - የጉምሩክ መመሪያ https://t.iss.one/tikvahethiopia/73728
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የጉራጌ ዞን ምክር ቤት #በክላስተር_ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ውድቅ አድርጓል። የጉራጌ ዞን ምክር ቤት ፤ ዛሬ ሐሙስ ባካሄደው አስቸካይ ጉባኤ ከሌሎች የአስተዳደር መዋቅሮች ጋር በክላስተር ለመደራጀት የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ በአብላጫ ድምጽ ውድቅ አደርጓል። የጉራጌ ዞንን በደቡብ ክልል ስር ከሚገኙ ሌሎች 4 ዞኖች እና አንድ ልዩ ወረዳ ጋር በማዳመር የጋራ ክልል ለመመስረት የቀረበው…
የምክር ቤቱ አጀንዳዎች ምንድናቸው ?
የጉራጌ ዞን ም/ቤት ነገ መስከረም 7 ቀን 2015 ዓ/ም 4ኛ ዙር 8ኛ ዓመት 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ለማካሄድ ለምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርቧል።
በጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎች ፦
- የ2014 ዓም የአስተዳደር ምክር ቤት እቅድ አፈጻጸም
- የዞኑ ፍርድ ቤት የ2014 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማ
- የ2015 የመንግስት የምክርቤቱና የፍርድ ቤት አመታዊ እቅድ እና
- የ2015 የዞኑ አመታዊ በጀት ላይ በመምከር ዉሳኔ ማሳለፍ እንደሆነ የም/ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አርሺያ አህመድ ተናግረዋል።
ከላይ ከተጠቀሱት አጀንዳዎች ውጪ ሌላ የተለየ አጀንዳ አለመኖሩን አፈጉባኤዋ ገልፀዋል።
በጉባኤው ላይ መያዝ የሚገባቸው አጀንዳዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የተያዙ መሆናቸውንና ጉባኤው የሚመራው በህገመንግስቱ መነሻነት ከፌደራልና ከክልል ህገመንግስት መነሻ በማድረግ በጉራጌ ዞን ም/ቤት በተዘጋጀው የአሰራር ስነምግባር መሰረት መሆኑን አስረድተዋል።
የጉራጌ ዞን ም/ቤት የደቡብ ክልላዊ መንግስትን ለ2 በሚከፍለው የክላስተር አደረጃጃት ላይ ተወይይቶ የቀረበውን የክላስተር አደረጃጀት በአብላጫ ድምፅ ውድቅ ካደረገበት የባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር አስቸኳይ ጉባኤ ወዲህ ለስብሰባ ሲቀመጥ የነገው የመጀመሪያ ይሆናል።
@tikvahethiopia
የጉራጌ ዞን ም/ቤት ነገ መስከረም 7 ቀን 2015 ዓ/ም 4ኛ ዙር 8ኛ ዓመት 22ኛ መደበኛ ጉባኤ ለማካሄድ ለምክር ቤት አባላቱ ጥሪ አቅርቧል።
በጉባኤው የተያዙ አጀንዳዎች ፦
- የ2014 ዓም የአስተዳደር ምክር ቤት እቅድ አፈጻጸም
- የዞኑ ፍርድ ቤት የ2014 ዓ.ም ማጠቃለያ ሪፖርት ግምገማ
- የ2015 የመንግስት የምክርቤቱና የፍርድ ቤት አመታዊ እቅድ እና
- የ2015 የዞኑ አመታዊ በጀት ላይ በመምከር ዉሳኔ ማሳለፍ እንደሆነ የም/ቤቱ ዋና አፈ ጉባኤ አርሺያ አህመድ ተናግረዋል።
ከላይ ከተጠቀሱት አጀንዳዎች ውጪ ሌላ የተለየ አጀንዳ አለመኖሩን አፈጉባኤዋ ገልፀዋል።
በጉባኤው ላይ መያዝ የሚገባቸው አጀንዳዎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመነጋገር የተያዙ መሆናቸውንና ጉባኤው የሚመራው በህገመንግስቱ መነሻነት ከፌደራልና ከክልል ህገመንግስት መነሻ በማድረግ በጉራጌ ዞን ም/ቤት በተዘጋጀው የአሰራር ስነምግባር መሰረት መሆኑን አስረድተዋል።
የጉራጌ ዞን ም/ቤት የደቡብ ክልላዊ መንግስትን ለ2 በሚከፍለው የክላስተር አደረጃጃት ላይ ተወይይቶ የቀረበውን የክላስተር አደረጃጀት በአብላጫ ድምፅ ውድቅ ካደረገበት የባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር አስቸኳይ ጉባኤ ወዲህ ለስብሰባ ሲቀመጥ የነገው የመጀመሪያ ይሆናል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA " አሜሪካ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ትቆማለች ፤ የአፍሪካ ህብረትን (AU) ዲፕሎማሲያዊ ጥረትን ትደግፋለች " - አንቶኒ ብሊንከን የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሀገራቸው አሜሪካ #ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንደምትቆም እና በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት #እንደምትደግፍ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ለሊት ባወጡት መግለጫ ነው። ብሊንከን ፤…
#USA #ETHIOPIA
" ለኢትዮጵያ አንድነት ፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቁርጠኛ ነን " - አሜሪካ
አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋ አምባሳደር ማይክ ሀመር ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር #ውጤታማ ውይይት አድርገዋል ስትል አሳወቀች።
ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲው በኩል ነው።
የአምባሳደር ማይክ ሐመር የኢትዮጵያ ጉብኝት ውጤታ ነበር ያለችው አሜሪካ " ለኢትዮጵያ #አንድነት ፣ #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ቁርጠኛ ነን " ስትል አስታውቃለች።
በተጨማሪ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲበለጽጉ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ እንደምትፈልግ ገልፃለች።
@tikvahethiopia
" ለኢትዮጵያ አንድነት ፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቁርጠኛ ነን " - አሜሪካ
አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋ አምባሳደር ማይክ ሀመር ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር #ውጤታማ ውይይት አድርገዋል ስትል አሳወቀች።
ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲው በኩል ነው።
የአምባሳደር ማይክ ሐመር የኢትዮጵያ ጉብኝት ውጤታ ነበር ያለችው አሜሪካ " ለኢትዮጵያ #አንድነት ፣ #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ቁርጠኛ ነን " ስትል አስታውቃለች።
በተጨማሪ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲበለጽጉ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ እንደምትፈልግ ገልፃለች።
@tikvahethiopia
* የታክስ ማሻሻያ
ገንዘብ ሚኒስቴር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኢንቨስትመንትንና አስመጪዎችን የሚያበረታታ እንዲሁም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን አሳወቀ።
ከውጭ የሚገቡ ሆነ ሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎችና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው ሲሆን ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ #ነፃ እንደሚደረጉ ታውቋል፡፡
የታክስ ማሻሻያው አላማ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የተሽከርካሪዎች ቁጥር በፖሊሲ ማዕቀፍ ከአካባቢ ደህንነት ጋር የሚስማማ ለማድረግ፣ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የማያስከትል፣ በአየር ንብረትና በብዝሃ ህይወት ላይ ተጽእኖ የማያሳርፍ እና ታዳሽ የኃይል ምንጮችን በአግባቡ የሚጠቀም የመጓጓዣ ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ሲሆን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ ለማስቻልም ነው፡፡
በታክስ ማሻሻያው መሰረት የኤሌክትሪክ የቤት አውቶሞቢሎችን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡
በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡
ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ ደግሞ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተወስኗል፡፡
@tikvahethiopia
ገንዘብ ሚኒስቴር የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ኢንቨስትመንትንና አስመጪዎችን የሚያበረታታ እንዲሁም ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርግ የታክስ ማሻሻያ ተግባራዊ መደረጉን አሳወቀ።
ከውጭ የሚገቡ ሆነ ሀገር ውስጥ የሚመረቱ የኤሌክትሪክ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች፣ የቤት አውቶሞቢሎችና የእቃ መጫኛ ተሽከርካሪዎች ላይ ዝቅተኛ የጉምሩክ ታሪፍ የሚጣልባቸው ሲሆን ከተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ከኤክሳይዝ ታክስና ከሱር ታክስ #ነፃ እንደሚደረጉ ታውቋል፡፡
የታክስ ማሻሻያው አላማ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ የመጣውን የተሽከርካሪዎች ቁጥር በፖሊሲ ማዕቀፍ ከአካባቢ ደህንነት ጋር የሚስማማ ለማድረግ፣ በህብረተሰቡ ጤና ላይ ጉዳት የማያስከትል፣ በአየር ንብረትና በብዝሃ ህይወት ላይ ተጽእኖ የማያሳርፍ እና ታዳሽ የኃይል ምንጮችን በአግባቡ የሚጠቀም የመጓጓዣ ሥርዓት ተግባራዊ ለማድረግ ሲሆን የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለህብረተሰቡ እንዲቀርቡ ለማስቻልም ነው፡፡
በታክስ ማሻሻያው መሰረት የኤሌክትሪክ የቤት አውቶሞቢሎችን በተመለከተ ሙሉ በሙሉ ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ አውቶሞቢሎች ከጉምሩክ ቀረጥ፣ ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡
በከፊል ተበትነው ወደ ሀገር ውስጥ ገብተው የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ የቤት አውቶ ሞቢሎችን 5 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡
ሙሉ ለሙሉ ተገጣጥመው ያለቀላቸው የኤሌክትሪክ አውቶሞቢሎች ወደ ሀገር ሲገቡ ደግሞ 15 በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ የሚጣልባቸው ሲሆን ከኤክሳይዝ ታክስ፣ ከተጨማሪ እሴት ታክስና ከሱር ታክስ ሙሉ በሙሉ ነጻ እንዲሆኑ ተወስኗል፡፡
@tikvahethiopia