TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ደሴ ! ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም ፦ - የምግብ ቤቶች ፣ የምሽት መጠጥ ቤቶች/ግሮሰሪዎች/ ከምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ተከልክሏል። - ማንኛውም ምርት ላይ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል። - በመፈናቀል…
#Update

የደሴ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ የከተማዋን ሰላም ሊያስጠብቁ እንደሚገባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ገልጿል።

ነዋሪዎች በሚነዙ ሀሰተኛ ወሬዎች፣ መረጃዎችና አሉባልታ አትደናገሩ ብሏል።

ማንኛውም የተለየና አጠራጣሪ ነገር ሲመለከቱ ነዋሪዎች ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ተጠይቋል።

ከተለያዩ አከባቢዎች ለመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ነገር ግን በዚህም መሃል ሰርገው ሊገቡ የሚችሉ የጥፋት ኃይሎች ካሉ በመከታተል ለሚመለከተው የጸጥታ ኃይል መጠቆም እንደሚገባ አስተዳደሩ ገልጿል።

የባንክና መሰረታዊ አገልግሎቶች ክፍት ሆነው እየተሰጡ መቀጠል እንዳለባቸው አፅንኦት የተሰጠ ሲሆን አገልግሎት በሚያቋርጡና ዋጋ አላግባብ በሚጨምሩ ነጋዴዎች ላይ ጥብቅ እርምጃ እንደሚወሰድ ማስጠንቀቂያ ተላልፏል።

በከተማው የታወጀውን አሰገዳጅ ህግ ሁሉም ሊያከብረው የሚገባ ሲሆን ጥሰት የሚታይ ከሆነ አስተዳደሩ ትእግስት እንደማያደርግና እርምጃ እንደሚወስድ አጥብቆ አስጠንቅቋል።

በሌላ በኩል ፤ የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በየመዝናኛ ቤቶችና ህዝብ በሚሰበሰብበት ቦታዎች ላይ አሉባልታ ወሬ በማናፈስ ህብረተሰቡ እንዳይረጋጋ በማድረግ ኗሪው በፍርሃት ከተማውን ለቆ እንዲወጣ ተልዕኮ ይዘው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች እንዳሉ ገልጿል።

ህብረተሰቡ ይህንን በማወቅ በአሉባልታ ሳይደናገር የራሱን ጥንቃቄ እንዲያደርግ መልዕክት አስተላልፏል።

የከተማው ጸጥታ ማዋቅር የከተማውን ሰላም ለማስጠበቅ እየሰራ መሆኑንም የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡ ተደራጅቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርቧል።

ወልድያን በተመለከተም ዛሬም #ሰላማዊ ሁኔታ የቀጠለ ሲሆን ነዋሪዎች ከአሉባልታ በመራቅ አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁና ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ ቀርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ነዳጅ

የመስከረም ወር የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ያለምንም ለውጥ ይቀጥላል።

የንግድ እና ቀጣናዊ ትሥሥር ሚኒስቴር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ብሏል።

ከነሐሴ 26 ቀን 2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ተግባራዊ የሚደረገው የነዳጅ ምርቶች ዋጋ የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ በነሐሴ ወር 2014 ዓ.ም እየተሸጠበት ባለው ዋጋ ያለምንም ለውጥ ይቀጥላል።

ከሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ያለው የታለመት የነዳጅ ድጎማ አሠራር በተመሳሳይ በመስከረም ወር 2015 ዓ.ም እንደሚቀጥል ሚኒስቴሩ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
#OromiaRegion

" ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://oromia.ministry.et/#/home ላይ መመልከት ይችላሉ " - ኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ

የኦሮሚያ ትምህርት ቢሮ በክልሉ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከዛሬ ጀምሮ በኢንተርኔት ላይ ማየት ይችላሉ ብሏል።

ተማሪዎች ውጤታቸውን በኢንተርኔት የሚያዩበት አድራሻ ‘https://oromia.ministry.et/#/home መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።

የክልሉ ትምህርት ቢሮ በሰጠው መረጃ ፦

👉 451 ሺሕ 21 ተማሪዎች ለፈተና ተመዝግበው 98 ነጥብ 3 በመቶ ፈተናውን ወስደዋል።

👉 የ9ኛ ክፍል የማለፊያ ውጤት ለወንዶች 50 በመቶ እና ለሴቶች 47 በመቶ ነው።

👉 በአርብቶ አደር አካባቢ የ9ኛ ክፍል ማለፊያ ውጤት ለወንዶች 47 % ለሴቶች 44 % ሲሆን ለልዩ ፍላጎት ተማሪዎች ደግሞ ለወንዶች 44% እና ለሴቶች 41% ነው።

Credit : WMCC

@tikvahethiopia
#SafaricomEthiopia #Harari

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ-ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በሐረሪ ክልል መጀመሩን አሳውቋል።

ይህ የደንበኞች የሙከራ ምዕራፍ ኩባንያው በአገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን ለመስጠት ከሚዘጋጅበት ጊዜ አስቀድሞ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች የኔትወርክ እና የአገልግሎት ጥራቱን በተጠናከረ ሁኔታ የሚፈትሽበት ወቅት መሆኑን ተገልጿል።

በሐረሪ ክልል የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በ2G፣ 3G እና 4G ኔትወርኮች የሚካሔድ ሲሆን ደንበኞች በዐ7 በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መስመር የስልክ ቁጥሮቻቸውን መርጠው ሲም ካርድ መግዛት ይችላሉ ተብሏል።

ደንበኞች የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሲም ካርዶችን የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ኔትወርኩን ለአንድ ወር ያህል እንዲሞክሩት የሚረዳ የደንበኝነት ማስጀመሪያ የዳታ፣ የድምጽ እና የጽሁፍ መልዕክቶች ጥቅል እንደሚያገኙ ተገልጿል።

የደንበኝነት ማስጀመሪያ ጥቅሉ በሚያልቅበት ጊዜ ደንበኞች የአየር ሰዓት ከሽያጭ ማዕከላት ወይም መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች በመግዛት መሙላት እና አገልግሎቱን መጠቀም መቀጠል ይችላሉ።

በሐረሪ ክልል አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ አሳውቆናል።

#SafaricomEthiopia #ሐረር_ክልል #Harari

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#SafaricomEthiopia #Harari ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ-ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በሐረሪ ክልል መጀመሩን አሳውቋል። ይህ የደንበኞች የሙከራ ምዕራፍ ኩባንያው በአገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን ለመስጠት ከሚዘጋጅበት ጊዜ አስቀድሞ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች የኔትወርክ እና የአገልግሎት ጥራቱን በተጠናከረ ሁኔታ የሚፈትሽበት ወቅት መሆኑን ተገልጿል። በሐረሪ ክልል የደንበኞች…
#Harari #SafaricomEthiopia

በሐረሪ ክልል ፤ የ " ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ " መለያ በተለጠፈባቸው ሁሉም መደብሮች እና ሱቆች ሲም ካርድ እና የአየር ሰዓት መግዛት ይቻላል ተብሏል።

በተጨማሪ በአራተኛ እና በሥላሴ አካባቢ ባሉት ሁለት የሽያጭ ማዕከሎቹ የሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ የስልክ ቀፎዎች ግዢ እና ልዩ ልዩ የደንበኞች ድጋፍ ማግኘት እንደሚቻል ተገልጿል።

ደንበኞች ለማንኛውም የደንበኞች ድጋፍ አገልግሎት በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ጥሪ ማዕከል በተለያዩ ቋንቋዎች ፦
- በአማርኛ፣
- በአፋን ኦሮሞ ፣
- በሱማሊኛ፣
- በትግርኛ እና እንግሊዝኛ አገልግሎት የማግኘት አማራጭ ያላቸው ሲሆን የደንበኞች አገልግሎት ሠራተኞችን በ 👉 700 ላይ በመደወል ማናገር ይቻላል።

#SafaricomEthiopia #ሐረሪ #Harari

@tikvahethiopia
ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

1. ዛሬ ህወሓት የኤርትራና የኢትዮጵያ መንግስት በጋራ ሆነው በ4 አቅጣጫ ጥቃት ከፍተዋል ሲል ከሷል። ጥቃቱ ከፍቅያ ገብረ እስከ አደመይቲ፣ ከሰላሞ - ሽራሮ፣ ከጎቦ ፅንዓት ወደ እርዲ ማቲዎስና አዲ አሰር እና አዲ ጎሹ በከባድ መሳሪያ ጥቃት እየተፈጸመባቸው ነው ብሏል። እስካሁን ከኢትዮጵያ መንግስት ሆነ ከኤርትራ በኩል ለዚህ ክስ ቀጥተኛ ምላሽ አልተሰጠም።

2. የኢፌዴሪ መንግስት መግለጫ፦

• ሕወሐት ወረራውን እያስፋፋ መጮኹን ቀጥሏል ብሏል። ህወሓት ተደጋጋሚ የሰላም ጥሪዎችን ገፍቶ በየአቅጣጫው በለኮሰውና ዛሬም እያስፋፋ ባለው እሳት ንጹሐን እየተገደሉ፣ ሕዝብ እየተፈናቀለ፣ ንብረትም እየወደመ ነው ብሏል። ሕወሓት ከሀገር አጥፊነት ተግባሩ የማስቆም ግዴታ ደግሞ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕዝብ ላይ መውደቁን ገልጿል።

• በሕወሓት ቡድን እየደረሱ የሚገኙ ጥፋቶችን ለማስቆም ለሰላማዊ  አማራጭ እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች ሁሉ እየመከኑ ባቡለበት ሁኔታ ሕወሓትን መጫን ሲገባቸው "ሁለቱም ወገኖች" በሚል የሚወጡ መግለጫዎች ከእውነታው ያፈነገጡ ስለሆነ ተቀባይነት የላቸውም ብሏል።

• ሕወሓት ተደጋጋሚ የሰላም አማራጮችን በመግፋት የከፈተው ጥቃት ሃገርን እንዳይበትን፣ የመከላከያ ኃይል በሁሉም አቅጣጫ የተከፈተበትን ወረራ ከሰላም ወዳዱ ደጀን ሕዝብ ጋር በመሆን በጽኑ ጀግንነት በመከላከል ላይ ይገኛል ብሏል።

3. የኢትዮጵያ ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን መንግስት የሀገሪቱን ሉአላዊነት ለማስከበር በሕወሓት ላይ የትኛውንም አይነት እርምጃ ለመውሰድ እንደሚገደድ ዛሬ ለአምባሳደሮች፣ የሚሲዮን መሪዎችና የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች በሰጡት ማብራሪያ ገልጽዋል። ከሚወሰደው እርምጃ ጎን ለጎን አሁንም #የሰላም በሮች ክፍት መሆናቸውን አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
ወቅታዊ ጉዳዮች ፦

- የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር በኢትዮጵያ አፋር፣አማራ እና ትግራይ ክልሎች የሰብአዊ እርዳታ ሰጪዎች እስር፣ የነዳጅ ዘረፋና ተሸከርካሪ በኃይል የመውሰድ ጨምሮ ተቀባይነት የሌለው ጣልቃ ገብነት እየደረሰባቸው ነው ብለዋል። ዕርዳታ ለተቸገሩት ይደርስ ዘንድ ሁሉም ወገኖች የሰብአዊ ተግባራትን እንዲያከብሩ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል። ፓወር በዚህ መልዕክታቸው የድርጊቶቹ ፈፃሚዎችን በግልፅ አልተናግሩም። ፓወር ከዚህ ቀደም ህወሓት 150 ሺህ ጋሎን ነዳጅ ከመቐለ WFP መጋዘን መዝረፉንና ሰራተኞችን ማንገላታቱን በመግለፅ ነዳጁን እንዲመልስ ጥሪ ማቅረባቸው የሚታወስ ሲሆን በዚህ መልዕክታቸው በአማራ እና አፋር ክልሎች ውስጥ ስለተፈፀሙ ድርጊቶችና ፈፃሚዎች በግልፅ ሳያብራሩ አልፈዋል።

- አሜሪካ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሯ አንቶኒ ብሊንከን በኩል የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ወታደራዊ ኦፕሬሽኖችን በአስቸኳይ እንዲያቆሙና ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም የሚደረገውን ጥረት በእጥፍ እንዲያጠናክሩ ጠይቃለች። ጦርነቱ እንደገና መቀስቀሱ ​ና በዚህ ሳቢያ አደጋ ላይ የሚወድቀው ህይወት ያሳስበናል ብላለች።

- የዩናይትድ ኪንግደም መንግስት የትግራይ ኃይሎች በአስቸኳይ ከአማራ ክልል ግጭት አቁመው ወደ ትግራይ እንዲመለሱ የኤርትራ ኃይሎችም ከትግራይ እንዲወጡ ጠይቋል። ንግግር ቢጀመር ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት እንደሚቻል ገልጿል። የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ መሰረታዊ አገልግሎት እንዲጀምር እንዲያደርግ ህወሓት ከWFP የወሰደውን ነዳጅ ለሰብዓዊ ስራ እንዲውል እንዲያደርግ ጠይቋል። ይህን ግጭት ለማስቆም ብቸኛው መንገድ ግጭት በማቆም ወደፖለቲካ ድርድር ማምራት ነው ብሏል ለዚህም የUK መንግስት የአፍሪካ ህብረትን የማሸማገል ጥረት እንደሚደግፍ አረጋግጧል።

@tikvahethiopia
#ScholarshipProgram

ካስ ኢትዮጵያ/አፍሪካ ሕብረት ቢሮ የነፃ ትምሕርት ዕድል ለኢትዮጵያዊያን የማስተርስ እና የዶክትሬት ዲግሪ ተማሪዎችና ምሩቃን ማዘጋጀቱን ለቲክቫህ ቤተሰቦች በላከው መረጃ ገልጿል።

የማስተርስ ትምህርታችሁን በሀገር ውስጥ የጀመራችሁ እንዲሁም ለመጀመር እቅድ ያላችሁ የዚህ ስኮላርሽፕ ተጠቃሚ መሆን ትችላላችሁ።

በተጨማሪም የማስተርስ ድግሪ ወይም PHD ኖሯችሁ ተጨማሪ ኮርሶችን መማር ለምትፈልጉ በተመሳሳይ እድሉን እንድትጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

የማመልከቻ ቀን ከነሐሴ 26/2014  - መስከረም 20/2015 ዓ/ም ነው።

ዝርዝር መስፈርቶችንና የማመልከቻ መንገዶችን https://www.kas.de/en/web/aethiopien/sur-place-scholarship-program መመልከት ይቻላል።

መልካም ዕድል!

Via @tikvahethmagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የደሴ ነዋሪዎች አካባቢያቸውን በንቃት በመጠበቅ የከተማዋን ሰላም ሊያስጠብቁ እንደሚገባ የደሴ ከተማ አስተዳደር ገልጿል። ነዋሪዎች በሚነዙ ሀሰተኛ ወሬዎች፣ መረጃዎችና አሉባልታ አትደናገሩ ብሏል። ማንኛውም የተለየና አጠራጣሪ ነገር ሲመለከቱ ነዋሪዎች ለጸጥታ ኃይል በማሳወቅ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡም ተጠይቋል። ከተለያዩ አከባቢዎች ለመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ነገር…
#Update

#ደቡብ_ወሎ

በደቡብ ወሎ ከታች ቀበሌ እስከ ዞን ድረስ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ህዝቡን እንዲረጋጋ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ተብሏል።

በዞኑ ባሉ ወረዳዎች ውስጥ የሀገር መከላከያን ልብስ በመልበስ መከላከያ በመምሰል በአቋራጭ መንገዶች ሲጓዙ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል።

በአሉባልታ ከሰሜን ወሎ ዞን የተፈናቀሉ በርካታ ሰዎች ወደ ዞኑ እየገቡ መሆኑን የገለፀው የደቡብ ወሎ ዞን ከሰሜን ወሎ ዞን ጋር በመሆን መመለስ ያለባቸውን ተፈናቃዮች እና ሰሌዳ አልባ ተሽከርካሪዎችን የመመለስ ስራ እየተሰራ ነው ብሏል።

#አምባሰል_ወረዳ

በአምባሳል ወረዳ ሀሰተኛ አሉባልታ ሲነዙ እና ህብረተሰቡን በማወክ ዘረፋ ሊፈፅሙ ተዘጋጅተው የነበሩ 9 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አሳውቋል።

መላው ነዋሪ በሀሰተኛ ወሬና አሉባልታ ሳይደናገጥ በፍፁም መረጋጋት አካባቢውን በንቃት እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቦለታል።

#ሐይቅ

በሐይቅ ከተማ " ከዚህ ቀደም ህወሓት ቀብሮት የነበረ ከባድ እና ቀላል መሳሪያ ተገኘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን የከተማው ፖሊስ አሳውቋል።

የህብረተሰቡን ሰላም ለማወክና አካባቢው እንዳይረጋጋ እንዲሁም ተከታይ ለማብዛት ሲሉ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

" ምንም ባላያችሁበትና ባላረጋገጣችሁበት አዲስ አበባ ቁጭ ብላችሁ በሀሰተኛ መረጃ ህዝብ የምትረብሹ ኃላፊነት የጎደላችሁ የማህበራዊ አንቂ ነን የምትሉ ግለሰቦች፣ ዩትዩበሮች ከድርጊታችሁ ታቀቡ " ያለው የሐይቅ ፖሊስ ይህን የፈፀሙት ላይ በህግ እንዲጠየቁ እየሰራው ነው ብሏል።

ነዋሪዎች በሀሰተኛ መረጃ ይስደናገጡ በተረጋጋ ሁኔታ የአካባቢውን ሰላም በንቃት እንዲጠብቁ ፖሊስ መልዕክት አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ደቡብ_ወሎ በደቡብ ወሎ ከታች ቀበሌ እስከ ዞን ድረስ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በመሆን ህዝቡን እንዲረጋጋ የማድረግ ስራ እየተሰራ ነው ተብሏል። በዞኑ ባሉ ወረዳዎች ውስጥ የሀገር መከላከያን ልብስ በመልበስ መከላከያ በመምሰል በአቋራጭ መንገዶች ሲጓዙ የነበሩ አካላት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገልጿል። በአሉባልታ ከሰሜን ወሎ ዞን የተፈናቀሉ በርካታ ሰዎች ወደ ዞኑ እየገቡ መሆኑን የገለፀው…
#Update

#ሰቆጣ

መላው የሰቆጣ ነዋሪዎች በአሉባልት እና ሀሰተኛ መረጃዎችን ሳይደናገሩ አካባቢያቸውን በንቃት እንዲጠብቁ ጥሪ ቀርቧል።

#ኮምቦልቻ

ዛሬ በኮምቦልቻ ከከተማው የሀይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ፣ በከተማው ከሚታወቁ ታዋቂ ግለሰቦች ጋር ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ውይይት ተደርጎ ነበር።

በዚህም መድረክ ፤ የተለያዩ ሀሰተኛ አሉባልታዎች በመንዛት ህዝቡን ለማሸበር የሚደረጉ ጥረቶች መኖራቸው ተገልጾ መላው ነዋሪ ተረጋግቶ በንቃት አካባቢውን በመጠበቅ ከፀጥታ ኃይሎች ጋር በጋራ ሊሰራ ይገባል ተብሏል።

በሌላ በኩል ፤ በከተማዋ እስከሁን ባለው ከ400 በላይ ባጃጆች እና 80 ሞተሮች በህግ ቁጥጥር ስር ገብተው ማጣራት ተደርጎ ወደየመጡበት እንዲመለሱ መደረጉ ተገልጿል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች ሁሉም ነዋሪ በቀበሌና ቀጠና ብሎክ ተደራጅቶ አካባቢውን መጠበቅ እንዳለበትና በእቃ ዋጋ ላይ ጭማሪ በሚያደርጉ ነጋዴዎች ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር ይደረግ ሲሉ ጠይቀዋል።

#ደሴ

ዛሬ በደሴ ከአምስቱም ክ/ከተሞች ከተውጣጡ ወጣቶች ጋር በወቅታዊ ጉዳይ ውይይት ተደርጎ የነበረ ሲሆን በዚሁ መድረክ ሀሰተኛ ፕሮፖጋንዳዎችን በማሰራጨት ህዝቡ ላይ የስነልቦና ጫና ለማሳደር ጥረት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም የከተማው ወጣት በሙሉ በሀሰተኛ ወሬ እና በሀሰተኛ ፕሮፖጋንዳ ሳይረበሽ ከመላው የከተማው ነዋሪ ጋር በመሆን አካባቢውን እና የከተማውን ሰላም ሊያረጋግጥ ይገባል ተብሏል።

በከተማው የፀጥታ ኮማንድ ፖስት መቋቋሙ ተነግሯል።

#ወልድያ

ወልዲያ ከተማ አዳሯ ሰላም የነበረ ሲሆን የዛሬ ውሎዋም ሰላም ነው። አሁንም ቢሆን መላው ነዋሪ ተረጋግቶ አካባቢውን በመጠብቅ የከተማዋን ሰላም ሊያረጋግጥ ይገባል ተብሏል።

@tikvahethiopia