TIKVAH-ETHIOPIA
" የሰላም ንግግር አሁንም ይቻላል " - አምባሳደር ዘነበ ከበደ በጄኔቫ የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛና ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዘነበ ከበደ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የሰላም ንግግር አሁንም ይቻላል ብለዋል። ነገር ግን ፤ ይህ የሚወሰነው የሰላም ንግግርን ውድቅ አድርጎ ወደ ጦርነት ባመራው ህወሓት /TPLF/ አቋም ነው ሲሉ ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መንግስት ለሰላም ያለውን አቋም በዓለም…
#KOBO
የኢትዮጵያ መከላከያ " ቆቦ " ን ለቆ መውጣቱን መንግስት ገለፀ።
የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ " አሻባሪው ህወሓት የሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም የቆቦ ከተማን ከውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው " ብሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ በከተማ ውስጥ ሠርጎ ገቦችን በማሥረግ የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ ይገኛል ብሏል።
በዚህም ፤ " የሕዝብን ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ የመከላከያ ኃይል የቆቦ ከተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመከላከል የሚስችለውን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ ተገዷል " ሲል አሳውቋል።
የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፥ " አሸባሪው ኃይል የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱን ካላቆመ መከላከያ ሕጋዊ ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ግዴታውን ለመወጣት የሚገደድ ይሆናል " ብሏል።
ምንም እንኳን ከተለያየ አቅጣጫ ሰላም እንዲሰፍን እና መሳሪያ ወርዶ ንግግር እንዲጀመር ጥሪዎች ቢቀርቡም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መጥቷል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መከላከያ " ቆቦ " ን ለቆ መውጣቱን መንግስት ገለፀ።
የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ " አሻባሪው ህወሓት የሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም የቆቦ ከተማን ከውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው " ብሏል።
በሌላ በኩል ደግሞ በከተማ ውስጥ ሠርጎ ገቦችን በማሥረግ የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ ይገኛል ብሏል።
በዚህም ፤ " የሕዝብን ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ የመከላከያ ኃይል የቆቦ ከተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመከላከል የሚስችለውን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ ተገዷል " ሲል አሳውቋል።
የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፥ " አሸባሪው ኃይል የትግራይን ወጣት እየማገደ በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱን ካላቆመ መከላከያ ሕጋዊ ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ግዴታውን ለመወጣት የሚገደድ ይሆናል " ብሏል።
ምንም እንኳን ከተለያየ አቅጣጫ ሰላም እንዲሰፍን እና መሳሪያ ወርዶ ንግግር እንዲጀመር ጥሪዎች ቢቀርቡም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ መጥቷል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እኛ ለጎንደር ከተማ እና ለህዝቡ ክብር አለን " - አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን በዛሬው ዕለት የምርጫ የጠቅላላ ጉባኤውን በአዲስ አበባ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስብሰባ አዳራሽ በማካሄድ ላይ ይገኛል ። ምርጫው ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ለምን ተቀየረ ? " ይሄ አስተዳደራዊ ጉዳይ ነው " ያሉት የወቅቱ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ " ጣልቃ ገብነቶች እና…
#Update
አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት ለመምራት በአብላጫ ድምፅ መመረጣቸው ተገልጿል።
አቶ ኢሳያስ ጅራ ለሁለተኛ የስራ ዘመን ፌዴሬሽኑን ለመምራት በሀላፊነት ተመርጠዋል።
ድምፅ ፦
• አቶ ኢሳያስ ጅራ 👉 94
• አቶ መላኩ ፈንታ 👉 27
• አቶ ቶኪቻ አለማየሁ 👉 17
https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x
More : @tikvahethsport
አቶ ኢሳያስ ጅራ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንን ለቀጣዮቹ አራት ዓመታት ለመምራት በአብላጫ ድምፅ መመረጣቸው ተገልጿል።
አቶ ኢሳያስ ጅራ ለሁለተኛ የስራ ዘመን ፌዴሬሽኑን ለመምራት በሀላፊነት ተመርጠዋል።
ድምፅ ፦
• አቶ ኢሳያስ ጅራ 👉 94
• አቶ መላኩ ፈንታ 👉 27
• አቶ ቶኪቻ አለማየሁ 👉 17
https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x
More : @tikvahethsport
TIKVAH-ETHIOPIA
#KOBO የኢትዮጵያ መከላከያ " ቆቦ " ን ለቆ መውጣቱን መንግስት ገለፀ። የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ " አሻባሪው ህወሓት የሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም የቆቦ ከተማን ከውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው " ብሏል። በሌላ በኩል ደግሞ በከተማ ውስጥ ሠርጎ ገቦችን በማሥረግ የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ…
#ወልድያ
የወልድያ ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላለፈ።
የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።
" የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው " ያለው የወልድያ ከተማ " የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
ከተማ አስተዳደሩ " የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም " ያለ ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።
የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት መሆኑን አመልክቷል።
ምንም እንኳን አሁንም መሳሪያ ወርዶ ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ እየቀረቡ ቢሆንም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። ህወሓት ከዚህ ቀደም ለሰብዓዊነት ሲባል ተኩስ አቁም በታወጀበት ወቅት ከነበረበት ቦታ ወደፊት በመምጣት የአማራ ክልል ቦታዎችን እየያዘ ነው።
በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ መንግስት እንደተገለፀው የኢትዮጵያ መከላከያ ከቆቦ ከተማ ለቆ ወጥቷል፤ በዚህም ቆቦ በህወሓት ስር ይገኛል።
መንግስት ፤ ህወሓት #የህዝብ_ማዕበል ስልት በመጠቀም ጥቃት እያደረሰ መሆኑን በመግለፅ የህዝብ ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ መከላከያው " ቆቦ " ን መልቀቁን በትለንትናው መግለጫ ማስረዳቱ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የወልድያ ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላለፈ።
የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።
" የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው " ያለው የወልድያ ከተማ " የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።
ከተማ አስተዳደሩ " የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም " ያለ ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።
የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት መሆኑን አመልክቷል።
ምንም እንኳን አሁንም መሳሪያ ወርዶ ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ እየቀረቡ ቢሆንም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። ህወሓት ከዚህ ቀደም ለሰብዓዊነት ሲባል ተኩስ አቁም በታወጀበት ወቅት ከነበረበት ቦታ ወደፊት በመምጣት የአማራ ክልል ቦታዎችን እየያዘ ነው።
በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ መንግስት እንደተገለፀው የኢትዮጵያ መከላከያ ከቆቦ ከተማ ለቆ ወጥቷል፤ በዚህም ቆቦ በህወሓት ስር ይገኛል።
መንግስት ፤ ህወሓት #የህዝብ_ማዕበል ስልት በመጠቀም ጥቃት እያደረሰ መሆኑን በመግለፅ የህዝብ ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ መከላከያው " ቆቦ " ን መልቀቁን በትለንትናው መግለጫ ማስረዳቱ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
#UN_ETHIOPIA
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ህወሓት ህፃናትን ለውትድርና እየመለመለና ህፃናትን በህዝብ ማዕበል ስትራቴጂ እየተጠቀመ ነው ሲሉ ገለፁ።
አምባሳደሩ ፥ እንደ ዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እና የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) ዓይነት ተቋማትን ጨምሮ ሌሎችንም ፤ " እውነት ስለ ህፃናት ያሳስበናል የምትሉ ይህን ድርጊት አውግዙ " ብለዋል።
የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ዳግም ካገረሸ ቀናት ተቆጥረዋል። አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች ወታደራዊ ግጭቶች መቀጠላቸውን የሚጠቁሙ መረጃዎች አሉ።
@tikvahethiopia
በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ የሆኑት አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ ህወሓት ህፃናትን ለውትድርና እየመለመለና ህፃናትን በህዝብ ማዕበል ስትራቴጂ እየተጠቀመ ነው ሲሉ ገለፁ።
አምባሳደሩ ፥ እንደ ዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እና የህፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) ዓይነት ተቋማትን ጨምሮ ሌሎችንም ፤ " እውነት ስለ ህፃናት ያሳስበናል የምትሉ ይህን ድርጊት አውግዙ " ብለዋል።
የሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ዳግም ካገረሸ ቀናት ተቆጥረዋል። አሁንም በተለያዩ አካባቢዎች ወታደራዊ ግጭቶች መቀጠላቸውን የሚጠቁሙ መረጃዎች አሉ።
@tikvahethiopia
ፎቶ : እርቀ ሰላም !
በአዊ እና በመተከል ዞን አዋሳኝ ወረዳዎች በሚኖሩ ህዝቦች መካከል የሚፈጠሩ የግጭት መንስኤዎችን በዘላቂነት ለማስወገድ ዛሬ የእርቀ ሰላም ስነ ስርዓት ተካሂዷል።
በሁለቱ ዞኖች አጎራባች በሆኑ ፓዊና ጃዊ ወረዳዎች በሚኖሩ ህዝቦች የሚፈጠረውን ግጭት በዘላቂነት ለማስወገድ ተስፋ የተጣለበት ይኸው እርቀ ሰላም በጃዊ ወረዳ ወርቅ ሀገር ቀበሌ ነው የተካሄደው።
Photo Credit : መተከል ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopia
በአዊ እና በመተከል ዞን አዋሳኝ ወረዳዎች በሚኖሩ ህዝቦች መካከል የሚፈጠሩ የግጭት መንስኤዎችን በዘላቂነት ለማስወገድ ዛሬ የእርቀ ሰላም ስነ ስርዓት ተካሂዷል።
በሁለቱ ዞኖች አጎራባች በሆኑ ፓዊና ጃዊ ወረዳዎች በሚኖሩ ህዝቦች የሚፈጠረውን ግጭት በዘላቂነት ለማስወገድ ተስፋ የተጣለበት ይኸው እርቀ ሰላም በጃዊ ወረዳ ወርቅ ሀገር ቀበሌ ነው የተካሄደው።
Photo Credit : መተከል ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopia
#ATTENTION
ደባርቅ !
የደባርቅ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ከወቅታዊ ፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን አሳውቋል።
የፀጥታ ምክር ቤቱ በከተማው ውስጥ የሚገኘው የተፈናቃይ መጠለያ ነዋሪ ከ12:00 በሗላ ወደ ውስጥም ሆነ ወደ ከተማ መግባት እንደማይችል ከልክሏል።
የባጃጅ ተሽከርካሪችም ከምሽቱ 1:00 በሗላ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ይህን በሚያደርጉ ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ አሳስቧል።
ሌላው፤ የከተማው ባለሆቴሎች እና ባለአልጋ ቤቶች ማንነቱ ያልታወቀ አንጋች በድርጅታቸው ሲጋጥምቻቸው ለህግ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡ ምክር ቤቱ አሳስቧል።
የቤት አከራይዎች ቤታቸውን ሲያከራዩ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና የሚያከራቱትን ግለሰብ ማንነት ለይታተው እንሲያውቁ በመረጃ ፎርም ሞልተው ለፀጥታ ጽ/ቤት እንዲያሳውቁ ብሏል።
ከዚህ በተጨማሪ ምክር ቤቱ መላው የከተማው ማህበረሰብ በአደረጃጀቶች አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላፍሏል።
የተላለፉትን የውሳኔ ሀሳቦች የሚጥስ ማንኛውም አካል ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia
ደባርቅ !
የደባርቅ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ከወቅታዊ ፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን አሳውቋል።
የፀጥታ ምክር ቤቱ በከተማው ውስጥ የሚገኘው የተፈናቃይ መጠለያ ነዋሪ ከ12:00 በሗላ ወደ ውስጥም ሆነ ወደ ከተማ መግባት እንደማይችል ከልክሏል።
የባጃጅ ተሽከርካሪችም ከምሽቱ 1:00 በሗላ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ይህን በሚያደርጉ ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ አሳስቧል።
ሌላው፤ የከተማው ባለሆቴሎች እና ባለአልጋ ቤቶች ማንነቱ ያልታወቀ አንጋች በድርጅታቸው ሲጋጥምቻቸው ለህግ አካላት ጥቆማ እንዲሰጡ ምክር ቤቱ አሳስቧል።
የቤት አከራይዎች ቤታቸውን ሲያከራዩ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና የሚያከራቱትን ግለሰብ ማንነት ለይታተው እንሲያውቁ በመረጃ ፎርም ሞልተው ለፀጥታ ጽ/ቤት እንዲያሳውቁ ብሏል።
ከዚህ በተጨማሪ ምክር ቤቱ መላው የከተማው ማህበረሰብ በአደረጃጀቶች አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት አስተላፍሏል።
የተላለፉትን የውሳኔ ሀሳቦች የሚጥስ ማንኛውም አካል ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ደባርቅ ! የደባርቅ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት ከወቅታዊ ፀጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ የተለያዩ ውሳኔዎች ማሳለፉን አሳውቋል። የፀጥታ ምክር ቤቱ በከተማው ውስጥ የሚገኘው የተፈናቃይ መጠለያ ነዋሪ ከ12:00 በሗላ ወደ ውስጥም ሆነ ወደ ከተማ መግባት እንደማይችል ከልክሏል። የባጃጅ ተሽከርካሪችም ከምሽቱ 1:00 በሗላ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ይህን በሚያደርጉ ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ…
#ATTENTION
ወልድያ !
የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን አካባቢ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ አስቀምጧል።
በዚህም ፦
• ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ #ተከልክሏል።
• ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጠው ተሽከርካሪ ውጭ ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ እንደማይችል ማሳሰቢያ ተላልፏል።
@tikvahethiopia
ወልድያ !
የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን አካባቢ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ አስቀምጧል።
በዚህም ፦
• ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ #ተከልክሏል።
• ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጠው ተሽከርካሪ ውጭ ማንኛውም ተሽከርካሪ ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ መንቀሳቀስ እንደማይችል ማሳሰቢያ ተላልፏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION ወልድያ ! የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን አካባቢ ወቅታዊ የጸጥታ ሁኔታ መነሻ በማድረግ ከነሐሴ 22 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ የሰዓት እላፊ ገደብ አስቀምጧል። በዚህም ፦ • ከተመደበው የጸጥታ ኃይል በስተቀር ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ንጋቱ 12:00 ሰዓት ድረስ ማንኛውም ሰው መንቀሳቀስ #ተከልክሏል። • ለጸጥታ ስራ ስምሪት ከተሰጠው ተሽከርካሪ ውጭ ማንኛውም ተሽከርካሪ…
#ATTENTION
ደሴ !
ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል።
በዚህም ፦
- የምግብ ቤቶች ፣ የምሽት መጠጥ ቤቶች/ግሮሰሪዎች/ ከምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ተከልክሏል።
- ማንኛውም ምርት ላይ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።
- በመፈናቀል ሆነ በሌላ ማንኛውም ምክንያት ወደ ደሴ ከተማ የገቡ ተፈናቃዮች የከተማውን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል የፀጥታ ኃይሎች ለጋራ ደህንነት ለሚተገብሯቸው የፍተሻና የቅድመ-ጥንቃቄ ስራዎች ተባባሪ የመሆን ግዴታ አለባቸው ተብሏል።
- አልጋ ቤት፣ የመኖሪያ ቤት ወይም መደብ ቤት አከራዮች የየትኛውንም ተከራይ ማንነትን የሚገልፅ መረጃ ለፀጥታ ተቋማት የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል።
- ወደ ደሴ በማንኛውም ምክንያት የገቡ እንግዶች ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- ከተፈቀደላቸው የከተማው የፀጥታ ሃይሎች ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ ተከልክሏል።
- ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም የከተማችን ነዋሪ ከምሽቱ 2:00 /ሁለት/ ሰዓት ጀምሮ በተናጠልም ሆነ በጋራ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- በከተማ ደረጃ እውቅና ያላቸው የተሰጣቸው የታክሲ አሽከርካሪዎች እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ብቻ ህዝቡን እንዲያገለግሉ ተወስኗል።
- በሁሉም አካባቢወች የሚገኙ ባጃጆች እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ውሳኔ ተላልፏል።
- የDSTV አገልግሎት መስጫዎች ፣ በጋራ ተሰብሰቦ ጫት የሚቃምባቸው መቃሚያ ቤቶች ፣ የሽሻ ቤቶች ከዛሬ ጀምሮ በይፋም ሆነ በስውር አገልግሎት መስጠት ተከልክሏል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ደሴ !
ከደሴ ከተማ የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የከተማው ሰላም እና ደህንነት ላይ መክሮ ውሳኔ አሳልፏል።
በዚህም ፦
- የምግብ ቤቶች ፣ የምሽት መጠጥ ቤቶች/ግሮሰሪዎች/ ከምሽቱ 1፡ዐዐ ሰዓት ጀምሮ በማንኛውም ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንደማይችሉ ተከልክሏል።
- ማንኛውም ምርት ላይ የዋጋ ጭማሬ የሚያደርጉ አካላት ላይ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል።
- በመፈናቀል ሆነ በሌላ ማንኛውም ምክንያት ወደ ደሴ ከተማ የገቡ ተፈናቃዮች የከተማውን ደህንነት ለማስጠበቅ ሲባል የፀጥታ ኃይሎች ለጋራ ደህንነት ለሚተገብሯቸው የፍተሻና የቅድመ-ጥንቃቄ ስራዎች ተባባሪ የመሆን ግዴታ አለባቸው ተብሏል።
- አልጋ ቤት፣ የመኖሪያ ቤት ወይም መደብ ቤት አከራዮች የየትኛውንም ተከራይ ማንነትን የሚገልፅ መረጃ ለፀጥታ ተቋማት የመስጠት ግዴታ ተጥሎባቸዋል።
- ወደ ደሴ በማንኛውም ምክንያት የገቡ እንግዶች ከምሽቱ 1:00 ሰዓት በኋላ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- ከተፈቀደላቸው የከተማው የፀጥታ ሃይሎች ውጭ ጦር መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈፅሞ ተከልክሏል።
- ከዛሬ ጀምሮ የትኛውም የከተማችን ነዋሪ ከምሽቱ 2:00 /ሁለት/ ሰዓት ጀምሮ በተናጠልም ሆነ በጋራ መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- በከተማ ደረጃ እውቅና ያላቸው የተሰጣቸው የታክሲ አሽከርካሪዎች እስከ ምሽቱ 2:00 ሰዓት ብቻ ህዝቡን እንዲያገለግሉ ተወስኗል።
- በሁሉም አካባቢወች የሚገኙ ባጃጆች እስከ ምሽቱ 1:00 ሰዓት ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ ውሳኔ ተላልፏል።
- የDSTV አገልግሎት መስጫዎች ፣ በጋራ ተሰብሰቦ ጫት የሚቃምባቸው መቃሚያ ቤቶች ፣ የሽሻ ቤቶች ከዛሬ ጀምሮ በይፋም ሆነ በስውር አገልግሎት መስጠት ተከልክሏል።
(ተጨማሪ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቀጠለ ... ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከመሠረተ ልማት ግንባታ በተጨማሪ ሌሎች የሰራቸው ስራዎች ፦ 👉 የተሳካ አገልግሎት ለማቀረብ አንዲሁም የሙያ እና የክህሎት ሽግግርን ለማጠናከር ብቃት ያለው የአመራሮች ሰብስቦ አዋቅሯል። 👉 የሰው ኃብቱን ወደ 500 ያሳደገ ሲሆን ከዚህም ውስጥ 320ዎቹ ኢትዮጵያዊያን ናቸው። በቀጣይም ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍል የተውጣጡ ሠራተኞች እንዲኖሩት ለማድረግ እየሰራ ነው። 👉…
#ሳፋሪኮም
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በድሬዳዋ ከተማ ጀምሯል።
ይህ የደንበኞች የሙከራ ምዕራፍ ኩባንያው በአገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን ለመስጠት ከሚዘጋጅበት ጊዜ አስቀድሞ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች የኔትወርክ እና የአገልግሎት ጥራቱን በተጠናከረ ሁኔታ የሚፈትሽበት ወቅት ነው።
በድሬዳዋ ከተማ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በ2G፣ 3G እና 4G ኔትወርኮች የሚካሔድ ሲሆን ደንበኞች በዐ7 በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መስመር የስልክ ቁጥሮቻቸውን መርጠው ሲም ካርድ መግዛት ይችላሉ፡፡
ደንበኞች የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሲም ካርዶች የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ኔትወርኩን ለአንድ ወር ያህል እንዲሞክሩት የሚረዳ የደንበኝነት ማስጀመሪያ የዳታ፣ የድምጽ እና የጽሁፍ መልዕክቶች ጥቅል ያገኛሉ።
የደንበኝነት ማስጀመሪያ ጥቅሉ በሚያልቅበት ጊዜ ደንበኞች የአየር ሰዓት ከሽያጭ ማዕከላት ወይም መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች በመግዛት መሙላት እና አገልግሎት መጠቀም መቀጠል ይችላሉ፡፡
በከዚራ፣ መስቀለኛ እና ኮርኔል ያሉ 3 የሳፋሪኮም ሽያጭ ማዕከሎች ለሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ ለስልክ ቀፎዎች ግዢ እና ልዩ ልዩ የደንበኞች ድጋፍ ለመስጠት ክፍት እንደሆኑ ተገልጿል።
በድሬዳዋ አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ ይችላሉ፡፡
@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት መጠነ ሰፊ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በድሬዳዋ ከተማ ጀምሯል።
ይህ የደንበኞች የሙከራ ምዕራፍ ኩባንያው በአገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን ለመስጠት ከሚዘጋጅበት ጊዜ አስቀድሞ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች የኔትወርክ እና የአገልግሎት ጥራቱን በተጠናከረ ሁኔታ የሚፈትሽበት ወቅት ነው።
በድሬዳዋ ከተማ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በ2G፣ 3G እና 4G ኔትወርኮች የሚካሔድ ሲሆን ደንበኞች በዐ7 በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መስመር የስልክ ቁጥሮቻቸውን መርጠው ሲም ካርድ መግዛት ይችላሉ፡፡
ደንበኞች የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሲም ካርዶች የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ኔትወርኩን ለአንድ ወር ያህል እንዲሞክሩት የሚረዳ የደንበኝነት ማስጀመሪያ የዳታ፣ የድምጽ እና የጽሁፍ መልዕክቶች ጥቅል ያገኛሉ።
የደንበኝነት ማስጀመሪያ ጥቅሉ በሚያልቅበት ጊዜ ደንበኞች የአየር ሰዓት ከሽያጭ ማዕከላት ወይም መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች በመግዛት መሙላት እና አገልግሎት መጠቀም መቀጠል ይችላሉ፡፡
በከዚራ፣ መስቀለኛ እና ኮርኔል ያሉ 3 የሳፋሪኮም ሽያጭ ማዕከሎች ለሲም ካርድ ሽያጭ ምዝገባ፣ ለስልክ ቀፎዎች ግዢ እና ልዩ ልዩ የደንበኞች ድጋፍ ለመስጠት ክፍት እንደሆኑ ተገልጿል።
በድሬዳዋ አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሁፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም የዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ ይችላሉ፡፡
@tikvahethiopia