TIKVAH-ETHIOPIA
#USA አሜሪካ በመቐለ የህወሓት ኃይሎች 12 የነዳጅ ቦቴዎች " መውሰዳቸው " እንደሚያሳስባት ገለፀች። ሀገሪቱ በአፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ በኩል ባወጣችው አጭር መግለጫ ፤ " ነዳጁ አስፈላጊ የነፍስ አድን ሰብዓዊ እርዳታ ለማድረስ የሚውል ነው ፤ ለኢትዮጵያውያን የሰብዓዊ ድጋፍ እንዳይደርስ የሚያደርጉ ማንኛውም አይነት ድርጊት እናወግዛለን " ብላለች። @tikvahethiopia
" አሁኑኑ የተሰረቀውን ነዳጅ መልሱ " - WFP
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ድርጅታቸው ለእርዳታ ሥራው የሚያውለውን 570,000 ሊትር ነዳጅ " የትግራይ ባለሥልጣናት ሰርቀዋል " ብለዋል።
" ምግብ ለማድረስ ነዳጅ ከሌለን በሚሊዮኖች ይራባሉ " ያሉት ቢዝሊ ድርጊቱን " የሚያስቆጣ እና አሳፋሪ " ብለውታል።
አሁኑን የተሰረቀው ነዳጅ እንዲመለስ ጠይቀዋል።
@tikvahethiopia
የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ድርጅታቸው ለእርዳታ ሥራው የሚያውለውን 570,000 ሊትር ነዳጅ " የትግራይ ባለሥልጣናት ሰርቀዋል " ብለዋል።
" ምግብ ለማድረስ ነዳጅ ከሌለን በሚሊዮኖች ይራባሉ " ያሉት ቢዝሊ ድርጊቱን " የሚያስቆጣ እና አሳፋሪ " ብለውታል።
አሁኑን የተሰረቀው ነዳጅ እንዲመለስ ጠይቀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GurageZone በደቡብ ክልል ያሉ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ለሁለት ተከፍለው በሁለት አዲስ ክልሎች ለመደራጀት በየም/ቤቶቻቸው ወስነው ውሳኔውን ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ካቀረቡ ቀናት ተቆጥሯል። በጋራ በአዲስ ክልል እንደራጃለን ብለው በምክር ቤት ውሳኔ አሳልፈው ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ጥያቄውን ካቀረቡት መካከል ግን የጉራጌ ዞን እንደሌለበት ይታወቃል። ዞኑ ከአጎራባቾቹ ስልጤ ፣ ከምባታ ጠምባሮ ፣…
#Wolkite : የጉራጌ ዞን ዋና ከተማ በሆነችው ወልቂጤ ከተማ ውስጥ ለ2ኛ ጊዜ የስራ ማቆም እና ከቤት ያለመውጣት አድማ ተመቶ መዋሉን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
የንግድ እንቅስቃሴ እና ትራንስፖርትም ተቋርጦ ነው የዋለው።
ዓድማው ከጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ጋር የተያያዘ ነበር።
ምንም እንኳን በዞኑ ውስጥ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት መሰል የድማ እንቅስቃሴ እንዳይካሄድ ቢያሳውቅም ዛሬ ከተማይቱ በእንቅስቃሴ ውጭ ሆና መዋሏ ተገልጿል።
አሁን ከክልልነት ጥያቄ ጋር ያለው ጥያቄ የቀጠለ ሲሆን በዚህ ሳቢያ ከሰሞኑን ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች እየታሰሩ መሆኑን ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
የደቡብ ክልል ፖሊስ ሰዎች እየታሰሩ መሆኑን አረጋግጦ የሚታሰሩት ህዝብ ከህዝብ ለማጋጨት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አካላት (በዞን ደረጃ በኃላፊነት ደረጃም ጭምር ያሉ) ናቸው ሲል ምላሽ ሰጥቶ ነበር።
@tikvahethiopia
የንግድ እንቅስቃሴ እና ትራንስፖርትም ተቋርጦ ነው የዋለው።
ዓድማው ከጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ጋር የተያያዘ ነበር።
ምንም እንኳን በዞኑ ውስጥ የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት መሰል የድማ እንቅስቃሴ እንዳይካሄድ ቢያሳውቅም ዛሬ ከተማይቱ በእንቅስቃሴ ውጭ ሆና መዋሏ ተገልጿል።
አሁን ከክልልነት ጥያቄ ጋር ያለው ጥያቄ የቀጠለ ሲሆን በዚህ ሳቢያ ከሰሞኑን ሰዎች በፀጥታ ኃይሎች እየታሰሩ መሆኑን ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።
የደቡብ ክልል ፖሊስ ሰዎች እየታሰሩ መሆኑን አረጋግጦ የሚታሰሩት ህዝብ ከህዝብ ለማጋጨት እንቅስቃሴ የሚያደርጉ አካላት (በዞን ደረጃ በኃላፊነት ደረጃም ጭምር ያሉ) ናቸው ሲል ምላሽ ሰጥቶ ነበር።
@tikvahethiopia
#ባህርዳር_ዩኒቨርሲቲ
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ለኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ ነው።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በሃይማኖት አባትነታቸው የተማሩትንና ያስተማሩትን በተግባር ለሚኖሩት፤ ሰውን በሰውነቱ ብቻ ላከበሩት ታላቁ ብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ኢትዮጵያን ብሎም አፍሪካን በስፖርቱ ዓለም በማስጠራት ጀምራ ለኅብረሰተብ ፍቅርና አንድነት መጎልበት ለምትተጋው ኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ የዓመቱን የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።
ዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬቱን የሚያበረክተው ነሐሴ 21 ቀን 2014 በሚያካሂደው የተማሪዎች ምረቃ ላይ ነው።
@tikvahethiopia
የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ለኮሎኔል ደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ ነው።
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ በሃይማኖት አባትነታቸው የተማሩትንና ያስተማሩትን በተግባር ለሚኖሩት፤ ሰውን በሰውነቱ ብቻ ላከበሩት ታላቁ ብጹዕ አቡነ ኤርምያስ እና ኢትዮጵያን ብሎም አፍሪካን በስፖርቱ ዓለም በማስጠራት ጀምራ ለኅብረሰተብ ፍቅርና አንድነት መጎልበት ለምትተጋው ኮሎኔል አትሌት ደራርቱ ቱሉ የዓመቱን የክብር ዶክትሬት ሊሰጥ መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።
ዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬቱን የሚያበረክተው ነሐሴ 21 ቀን 2014 በሚያካሂደው የተማሪዎች ምረቃ ላይ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ዳግም የተቀሰቀሰው ግጭት አሜሪካን ስጋት እንዳጫረባት ገልፀዋል። የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እና በመጨረሻም ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል። ብሊንከን ፤ ላለፉት 5 ወራት የነበረው የተኩስ አቁም የበርካቶችን ሕይወት መታደጉንና…
#Turkiye #UK
ተርኪዬ ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ማርች 24 /2022 በፌዴራል መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል የተኩስ አቁም ከታወጀ በኃላ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን የሚገልፁ ሪፖርቶችን በሀዘን እና ስጋት ውስጥ ሆና እየተከታተለች እንደምትገኝ ገልፃለች።
ሁሉም ወገኖች ግጭት በዘላቂነት እንዲቆም ለማድረግ እና በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ወደ ንግግር እንዲመለሱ ጋብዛለች።
ለዚህ አላማ ደግሞ ሁሉንም አይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን በድጋሚ አረጋግጣለች።
ተርኪዬ በኢትዮጵያ ሰላምን እና መረጋጋትን ለማስፈን ባሚደረገውን ጥረት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፃለች።
በሌላ በኩል ፤ ዩናይትድ ኪንግደም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን የሚገልፁ ሪፖርቶች እንደሚያሳስባት ገልፃለች።
ይህ ሁኔታ ቀድሞም አስከፊ የነበረውን የሰብዓዊ ሁኔታ ይበልጥ ያባብሰዋል ብላለች።
ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ግጭት እንዲያቆሙና የፖለቲካ መፍትሄ እንዲመጣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንዲመጡ አሳስባለች።
@tikvahethiopia
ተርኪዬ ፤ በሰሜን ኢትዮጵያ ማርች 24 /2022 በፌዴራል መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል የተኩስ አቁም ከታወጀ በኃላ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን የሚገልፁ ሪፖርቶችን በሀዘን እና ስጋት ውስጥ ሆና እየተከታተለች እንደምትገኝ ገልፃለች።
ሁሉም ወገኖች ግጭት በዘላቂነት እንዲቆም ለማድረግ እና በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዲሰፍን ወደ ንግግር እንዲመለሱ ጋብዛለች።
ለዚህ አላማ ደግሞ ሁሉንም አይነት ድጋፍ ለመስጠት ዝግጁ መሆኗን በድጋሚ አረጋግጣለች።
ተርኪዬ በኢትዮጵያ ሰላምን እና መረጋጋትን ለማስፈን ባሚደረገውን ጥረት ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፃለች።
በሌላ በኩል ፤ ዩናይትድ ኪንግደም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን የሚገልፁ ሪፖርቶች እንደሚያሳስባት ገልፃለች።
ይህ ሁኔታ ቀድሞም አስከፊ የነበረውን የሰብዓዊ ሁኔታ ይበልጥ ያባብሰዋል ብላለች።
ዩናይትድ ኪንግደም የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ግጭት እንዲያቆሙና የፖለቲካ መፍትሄ እንዲመጣ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ድርድር ጠረጴዛ እንዲመጡ አሳስባለች።
@tikvahethiopia
#ECSOC
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ ቤት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ዳግም የተቀሰቀሰው ትጥቅን ያካተተ ግጭትን እንዲረጋጋ እና የተጀመረው የሰላም ሂደት በአስቸኳይ እንዲቀጥል አበክሮ ጠይቋል።
ም/ቤቱ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል መልሶ ያገረሸው የትጥቅ ግጭት በእጅጉ እንደሚያሳስበው ገልጿጻ።
ከዚህ በፊት የተፈጠረው የትጥቅ ግጭት ተነግሮ የማያልቅ የሰው ልጅ ስቃይ እና ከፍተኛ መሰረተ ልማቶች መውደም ምክንያት መሆኑን ይታወቃል ያለው ም/ቤቱ አሁን ዳግም የተቀሰቀሰው የትጥቅ ግጭት እንዲረጋጋና ግጭቱ እንዳይባባስ አፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ አሳስቧል።
በተጨማሪም ም/ቤቱ አስቸኳይ የሰብዓዊ ተኩስ አቁሙ መከበር ለሰብአዊ ዕርዳታ አቅርቦት ቀጣይነት እና ለሰላም ሂደቱ ስኬታማነት ወሳኝ እንደሆነ ገልጾ አለመግባባቶች በፖለቲካዊ ውይይት መፈታት እንዳለባቸው በጥብቅ እንደሚያምን ገልጿል።
ለዚህም የሰላም ማስፈን ሂደቱ በአስቸኳይ እንዲቀጥልና ሀገሪቱንና ዜጎቿን ከተጨማሪ ጥፋት ለመታደግ የሰላም ሂደቱ በቅን ልቦና እንዲካሄድ ምክር ቤቱ ጠይቋል።
የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግንዛቤ በማስገባት የአፍሪካ ህብረት (AU) የፌደራል መንግስትን እና ህወሃትን የማደራደር ሚናውን በእጥፍ በማሳደግ ሰላማዊ እልባት ላይ እንዲደረስ የበኩሉን እንዲወጣ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
የሰላም ማስፈን ሂደቱን አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ በማንኛውም መንገድ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት እና ዝግጁነትም በድጋሚ አረጋግጧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ም/ ቤት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ዳግም የተቀሰቀሰው ትጥቅን ያካተተ ግጭትን እንዲረጋጋ እና የተጀመረው የሰላም ሂደት በአስቸኳይ እንዲቀጥል አበክሮ ጠይቋል።
ም/ቤቱ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል መልሶ ያገረሸው የትጥቅ ግጭት በእጅጉ እንደሚያሳስበው ገልጿጻ።
ከዚህ በፊት የተፈጠረው የትጥቅ ግጭት ተነግሮ የማያልቅ የሰው ልጅ ስቃይ እና ከፍተኛ መሰረተ ልማቶች መውደም ምክንያት መሆኑን ይታወቃል ያለው ም/ቤቱ አሁን ዳግም የተቀሰቀሰው የትጥቅ ግጭት እንዲረጋጋና ግጭቱ እንዳይባባስ አፈላጊው ሁሉ እንዲደረግ አሳስቧል።
በተጨማሪም ም/ቤቱ አስቸኳይ የሰብዓዊ ተኩስ አቁሙ መከበር ለሰብአዊ ዕርዳታ አቅርቦት ቀጣይነት እና ለሰላም ሂደቱ ስኬታማነት ወሳኝ እንደሆነ ገልጾ አለመግባባቶች በፖለቲካዊ ውይይት መፈታት እንዳለባቸው በጥብቅ እንደሚያምን ገልጿል።
ለዚህም የሰላም ማስፈን ሂደቱ በአስቸኳይ እንዲቀጥልና ሀገሪቱንና ዜጎቿን ከተጨማሪ ጥፋት ለመታደግ የሰላም ሂደቱ በቅን ልቦና እንዲካሄድ ምክር ቤቱ ጠይቋል።
የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግንዛቤ በማስገባት የአፍሪካ ህብረት (AU) የፌደራል መንግስትን እና ህወሃትን የማደራደር ሚናውን በእጥፍ በማሳደግ ሰላማዊ እልባት ላይ እንዲደረስ የበኩሉን እንዲወጣ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።
የሰላም ማስፈን ሂደቱን አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ በማንኛውም መንገድ ለመደገፍ ያለውን ቁርጠኝነት እና ዝግጁነትም በድጋሚ አረጋግጧል።
@tikvahethiopia
#CARD
የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንደ አዲስ ማገርሸቱ ለጥቂት ወራት ታይቶ የነበረውን የሰላም ጭላንጭል ተስፋ እንዳደበዘዘው ገልጿል።
ካርድ ፤ የግጭቱን እና የጦርነት ፕሮፖጋንዳውን ማባባስ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልጾ ሁሉም ወገኖች ጦርነቱንና ግጭቱን ከሚያባብሱ ትርክቶና ድርጊቶች እንዲታቀበ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም የዓለም ዐቀፍ ሰብዓዊነት ህግጋት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
የመብቶችና ዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል (ካርድ) በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንደ አዲስ ማገርሸቱ ለጥቂት ወራት ታይቶ የነበረውን የሰላም ጭላንጭል ተስፋ እንዳደበዘዘው ገልጿል።
ካርድ ፤ የግጭቱን እና የጦርነት ፕሮፖጋንዳውን ማባባስ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልጾ ሁሉም ወገኖች ጦርነቱንና ግጭቱን ከሚያባብሱ ትርክቶና ድርጊቶች እንዲታቀበ ጥሪ አቅርቧል።
በተጨማሪም የዓለም ዐቀፍ ሰብዓዊነት ህግጋት እንዲያከብሩ ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አሁኑኑ የተሰረቀውን ነዳጅ መልሱ " - WFP የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቢዝሊ ድርጅታቸው ለእርዳታ ሥራው የሚያውለውን 570,000 ሊትር ነዳጅ " የትግራይ ባለሥልጣናት ሰርቀዋል " ብለዋል። " ምግብ ለማድረስ ነዳጅ ከሌለን በሚሊዮኖች ይራባሉ " ያሉት ቢዝሊ ድርጊቱን " የሚያስቆጣ እና አሳፋሪ " ብለውታል። አሁኑን የተሰረቀው ነዳጅ እንዲመለስ ጠይቀዋል። @tikvahethiopia
#WFP #UN
" ነዳጁ በቅርቡ በWFP የተገዛ እና ከመሰረቁ ጥቂት ቀናት በፊት መቐለ የደረሰ ነበር " - WFP
የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ከመቐለ ተሰረቀ ባለው ነዳጅ ጉዳይ ላይ በዋና ዳይሬክተሩ ዴቪድ ቢዝሊ በኩል ማብራሪያ ሰጥቷል።
ዋና ዳይሬክተሩ ትላንት ጥዋት የተዘረፈው ነዳጅ ከግማሽ ሚሊዮን ሊትር በላይ (12 ታንከር) መሆኑንና የታጠቁ ቡድኖች ወደ WFP ግቢ ገብተው መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ነዳጁ በቅርቡ በWFP የተገዛ እና ከመሰቀሩ ጥቂት ቀናት በፊት የደረሰ መሆኑን አስረድተዋል።
WFP ያለ ነዳጁ ምግብ፣ ማዳበሪያ፣ መድሃኒት እና ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎችን በመላው ትግራይ ሊያደርስ እንደማይችል ገልጸዋል።
በተጨማሪም ጄነሬተሮችን እና ተሽከርካሪዎች ለማንቀሳቀስ እንደሚቸገር የገለፀው WFP 5.2 ሚሊዮን የሚደርሰውን ረሃብ የተጋረጠበትን ህዝብ ለመድረስ እንቅፋት እንደሚሆንበት አስረድቷል።
የነዳጁ መሰረቅ በግጭት ሳቢያ እየተፈተነ ያለውን በትግራይ ያለውን ማህበረሰብ ወደ ረሃብ አፋፍ ይገፋል ብለዋል።
የትግራይ ባለስልጣናት በአስቸኳይ የነዳጅ ክምችቱን እንዲመልሱ አሳስበዋል።
ህወሓት በበኩሉ " ከወራት በፊት ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ያበደርኩትን ነዳጅ መልሼ ወስድኩ እንጂ ዘረፋ አልፈጸምኩም " ሲል መልሷል።
ዋና ዳይሬክተሩ መሰል አስተያየት ከመስጠታቸው በፊት ዝርዝር ሁኔታውን ማጣራት ነበረባቸው ብሏል።
ከ600 ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ ለWFP አበድርያለሁ ያለው ህወሓት " በነበረን ስምምነት መሠረት ያበደርነውን ነዳጅ ተመላሽ እንዲሆን ነው የጠየቅነው " ሲል ገልጿል።
የወሰድነው ነዳጅ እንደ ሆስፒታል ፣ ክሊኒክ እና ሌሎች የጤና ማዕከላትን ለማንቀሳቀስ ጥቅም ላይ ይውላልም ሲሉ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተርን ክስ አጣጥሏል።
@tikvahethiopia
" ነዳጁ በቅርቡ በWFP የተገዛ እና ከመሰረቁ ጥቂት ቀናት በፊት መቐለ የደረሰ ነበር " - WFP
የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ከመቐለ ተሰረቀ ባለው ነዳጅ ጉዳይ ላይ በዋና ዳይሬክተሩ ዴቪድ ቢዝሊ በኩል ማብራሪያ ሰጥቷል።
ዋና ዳይሬክተሩ ትላንት ጥዋት የተዘረፈው ነዳጅ ከግማሽ ሚሊዮን ሊትር በላይ (12 ታንከር) መሆኑንና የታጠቁ ቡድኖች ወደ WFP ግቢ ገብተው መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
ነዳጁ በቅርቡ በWFP የተገዛ እና ከመሰቀሩ ጥቂት ቀናት በፊት የደረሰ መሆኑን አስረድተዋል።
WFP ያለ ነዳጁ ምግብ፣ ማዳበሪያ፣ መድሃኒት እና ሌሎች አስቸኳይ ድጋፎችን በመላው ትግራይ ሊያደርስ እንደማይችል ገልጸዋል።
በተጨማሪም ጄነሬተሮችን እና ተሽከርካሪዎች ለማንቀሳቀስ እንደሚቸገር የገለፀው WFP 5.2 ሚሊዮን የሚደርሰውን ረሃብ የተጋረጠበትን ህዝብ ለመድረስ እንቅፋት እንደሚሆንበት አስረድቷል።
የነዳጁ መሰረቅ በግጭት ሳቢያ እየተፈተነ ያለውን በትግራይ ያለውን ማህበረሰብ ወደ ረሃብ አፋፍ ይገፋል ብለዋል።
የትግራይ ባለስልጣናት በአስቸኳይ የነዳጅ ክምችቱን እንዲመልሱ አሳስበዋል።
ህወሓት በበኩሉ " ከወራት በፊት ለዓለም ምግብ ፕሮግራም ያበደርኩትን ነዳጅ መልሼ ወስድኩ እንጂ ዘረፋ አልፈጸምኩም " ሲል መልሷል።
ዋና ዳይሬክተሩ መሰል አስተያየት ከመስጠታቸው በፊት ዝርዝር ሁኔታውን ማጣራት ነበረባቸው ብሏል።
ከ600 ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ ለWFP አበድርያለሁ ያለው ህወሓት " በነበረን ስምምነት መሠረት ያበደርነውን ነዳጅ ተመላሽ እንዲሆን ነው የጠየቅነው " ሲል ገልጿል።
የወሰድነው ነዳጅ እንደ ሆስፒታል ፣ ክሊኒክ እና ሌሎች የጤና ማዕከላትን ለማንቀሳቀስ ጥቅም ላይ ይውላልም ሲሉ የዓለም ምግብ ፕሮግራም ዳይሬክተርን ክስ አጣጥሏል።
@tikvahethiopia
#SNNPRS #SouthWestEthiopia
የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑ ዛሬ ተገልጿል።
በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦
👉 ለወንዶች 41፣
👉 ለሴቶች 40 እና
👉 ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።
በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።
ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።
በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።
በዚህም መሰረት ፦
👉 ለወንዶች 39፣
👉 ለሴቶች 38 እና
👉 ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።
የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።
#ENA
@tikvahethiopia
የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የደቡብ ክልል እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑ ዛሬ ተገልጿል።
በሁለቱ ክልሎች ውሳኔ መሰረት የማለፊያ ነጥብ ፦
👉 ለወንዶች 41፣
👉 ለሴቶች 40 እና
👉 ለአይነ ስውራን 39 ሆኖ ተወስኗል።
በዚህ መሰረት ፦ በ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በሁለቱም ክልሎች ለፈተና ከተቀመጡ ከ257 ሺህ በላይ ተማሪዎች 187 ሺህ 500 በላይ ተማሪዎች ወደቀጣይ ክፍል የሚያሳልፋቸውን ውጤት አምጥተዋል።
ለፈተና ከተቀመጠው አጠቃላይ ተማሪ ቁጥር ሲታይ ከ73 በመቶ በላይ ተማሪዎች አልፈዋል።
በተለየ መልኩ ከጸጥታ ጋር በተያያዘ በአሉታዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተማሩና ለፈተና የተቀመጡ የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎችን ውጤት በተለየ መልኩ ታይቷታ።
በዚህም መሰረት ፦
👉 ለወንዶች 39፣
👉 ለሴቶች 38 እና
👉 ለአይነ ስውራን 37 ሆኖ ተወስኗል።
የሁለቱ ክልሎች ተማሪዎች ውጤታቸውን ከነገ ጀምሮ መውሰድ ይችላሉ ተብሏል።
የደራሼ ልዩ ወረዳ ተማሪዎች ግን ውጤታቸው በእጅ የሚሰራ በመሆኑ የ1 ሳምንት ጊዜ ዘግይቶ ይደርሳል እስከዛው በትዕግስት እንዲጠባበቁ መልዕክት ተላልፏል።
#ENA
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#USAID
" ... ኢትዮጵያውያን ሲቪሎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እጅግ የጭካኔ ተግባር ነው። የተዘረፈውን ነዳጅ መልሱ " - ሳማንታ ፓወር
የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት (USAID) አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ፤ ህወሓት (TPLF) የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለስራ የሚጠቀምበትን 150,000 ጋሎን ነዳጅ መዝረፉን በመግለፅ ድርጊቱን አጥበቀው አውግዘዋል።
በተጨማሪም በእርዳታ ሰራተኞች ላይ እንግልት መድረሱን በመጠቆም ፤ ህወሓት (TPLF) በእርዳታ ሰራተኞች ላይ ያደረሰውን እንግልት ድርጅታቸው አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
" ኢትዮጵያውያን ሲቪሎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እጅግ የጭካኔ ተግባር ነው " ያሉት ፓወር ህወሓት (TPLF) የዘረፈውን ነዳጅ እንዲመልስ እና የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችን እንዲያከብር በድርጅታቸው ስም ጥሪ አቅርበዋል።
ከነዳጅ ዝርፊያ ጋር በተያያዘ አሁንም ዓለም አቀፍ ተቋማት ድርጊቱን እያወገዙ ሲሆን ህወሓት (TPLF) በሰጠው ምላሽ " ከወራት በፊት ለዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ያበደርኩትን ነዳጅ መልሼ ወስድኩ እንጂ ዘረፋ አልፈጸምኩም " ብሏል።
ነዳጁን ለድርጅቱ ያበደርኩት ከጥቂት ወራት በፊት በነዳጅ እጥረት ምክንያት የምግብ እርዳታ ማከፋፈል ባለመቻሉ ነው ያለው ህወሓት ድርጅቱ ነዳጅ መበደሩንና እንደሚመልስ ግንዛቤ ነበር ሲል ገልጿል፤ " ስምምነታችን በጽሁፍ ተሰንዶ ተቀምጧል " ሲል እየቀረበበት ላለው ክስ ምላሽ ሰጥቷል።
@tikvahethiopia
" ... ኢትዮጵያውያን ሲቪሎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እጅግ የጭካኔ ተግባር ነው። የተዘረፈውን ነዳጅ መልሱ " - ሳማንታ ፓወር
የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት (USAID) አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ፤ ህወሓት (TPLF) የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለስራ የሚጠቀምበትን 150,000 ጋሎን ነዳጅ መዝረፉን በመግለፅ ድርጊቱን አጥበቀው አውግዘዋል።
በተጨማሪም በእርዳታ ሰራተኞች ላይ እንግልት መድረሱን በመጠቆም ፤ ህወሓት (TPLF) በእርዳታ ሰራተኞች ላይ ያደረሰውን እንግልት ድርጅታቸው አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
" ኢትዮጵያውያን ሲቪሎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እጅግ የጭካኔ ተግባር ነው " ያሉት ፓወር ህወሓት (TPLF) የዘረፈውን ነዳጅ እንዲመልስ እና የሰብዓዊ ድጋፍ ስራዎችን እንዲያከብር በድርጅታቸው ስም ጥሪ አቅርበዋል።
ከነዳጅ ዝርፊያ ጋር በተያያዘ አሁንም ዓለም አቀፍ ተቋማት ድርጊቱን እያወገዙ ሲሆን ህወሓት (TPLF) በሰጠው ምላሽ " ከወራት በፊት ለዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ያበደርኩትን ነዳጅ መልሼ ወስድኩ እንጂ ዘረፋ አልፈጸምኩም " ብሏል።
ነዳጁን ለድርጅቱ ያበደርኩት ከጥቂት ወራት በፊት በነዳጅ እጥረት ምክንያት የምግብ እርዳታ ማከፋፈል ባለመቻሉ ነው ያለው ህወሓት ድርጅቱ ነዳጅ መበደሩንና እንደሚመልስ ግንዛቤ ነበር ሲል ገልጿል፤ " ስምምነታችን በጽሁፍ ተሰንዶ ተቀምጧል " ሲል እየቀረበበት ላለው ክስ ምላሽ ሰጥቷል።
@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
በአፍሪካ ግዙፉና በደህንነቱ አስተማማኝ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽልማት ተበረከተለት።
አየር መንገዱ " Global Travel Magazine " ከመንገደኞች ባሰባሰበው ድምፅ መሰረት " የ2022 ዓ.ም ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ " ሽልማትን ማሸነፍ ችሏል።
@tikvahethiopia
በአፍሪካ ግዙፉና በደህንነቱ አስተማማኝ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሽልማት ተበረከተለት።
አየር መንገዱ " Global Travel Magazine " ከመንገደኞች ባሰባሰበው ድምፅ መሰረት " የ2022 ዓ.ም ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ " ሽልማትን ማሸነፍ ችሏል።
@tikvahethiopia