TIKVAH-ETHIOPIA
#ደቡብ_ኢትዮጵያ_ክልል " በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንዲደራጅ " የፌዴሬሽን ምክር ቤት ፦ - የወላይታ፣ - የጋሞ፣ - የጎፋ፣ - የደቡብ ኦሞ፣ - የጌዴኦ፣ - የኮንሶ ዞኖች እንዲሁም - የደራሼ፣ - የአማሮ፣ - የቡርጂ፣ - የአሌ፣ - የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በጋራ " የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " ለመመስረት ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጿል። ም/ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት…
#NEBE
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ ለቦርዱ ያቀረበው የሕዝበ ውሣኔ ማደራጀት ጥያቄ ላይ ውሣኔ አሳለፈ !
ነሐሴ 12/2014 የፌዴሬሽን ም/ ቤት ፤ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከ6 ዞኖችን እና 5 ልዩ ወረዳዎችን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በ3 ወር ህዝበ ውሳኔ በማድረጃት ውጤቱን ለምክር/ቤቱ እንዲያሳውቅ ብሎ ነበር።
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለምክር ቤቱ ምላሹን ሰጥቷል። ምላሹ የህግ አግባብን ተከትሎ የተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።
ለህዝበ ወሳኔ የሚወስደውን ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ የመወሰን ፣ የመርሀ ግብር ሰሌዳ የማዘጋጀት የማፅደቅ እንደ አስፈላጊነቱ የማሻሻል እና የማስፈፀም ስርልጣን የተቋሙ ብቻ መሆኑን ምርጫ ቦርድ አስገንዝቧል።
ከቦርዱ ምላሽ ፦
" ... ቦርዱ ለዚህ ጉዳይ አፈፃፀም የሎጂስቲክስ ዝግጅት ለማድረግ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላ እና ምደባ ለመተግበር፣ የምርጫ ፀጥታ ጉዳይን ለመገምገም፣ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ ጣቢያዎች ለማደራጀት፣ ለታዛቢ ሲቪል ማህበራት ፈቃድ ለመስጠት እና በጉዳዩ ላይ የሚያገባቸውን ባለድርሻ አካላት ለማወያየት የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ ለምክር ቤቱ እንደሚገልፅ ከአክብሮት ጋር እናሳውቃለን። "
(ቦርዱ ያሳለፈው ውሳኔ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ ለቦርዱ ያቀረበው የሕዝበ ውሣኔ ማደራጀት ጥያቄ ላይ ውሣኔ አሳለፈ !
ነሐሴ 12/2014 የፌዴሬሽን ም/ ቤት ፤ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከ6 ዞኖችን እና 5 ልዩ ወረዳዎችን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በ3 ወር ህዝበ ውሳኔ በማድረጃት ውጤቱን ለምክር/ቤቱ እንዲያሳውቅ ብሎ ነበር።
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለምክር ቤቱ ምላሹን ሰጥቷል። ምላሹ የህግ አግባብን ተከትሎ የተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።
ለህዝበ ወሳኔ የሚወስደውን ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ የመወሰን ፣ የመርሀ ግብር ሰሌዳ የማዘጋጀት የማፅደቅ እንደ አስፈላጊነቱ የማሻሻል እና የማስፈፀም ስርልጣን የተቋሙ ብቻ መሆኑን ምርጫ ቦርድ አስገንዝቧል።
ከቦርዱ ምላሽ ፦
" ... ቦርዱ ለዚህ ጉዳይ አፈፃፀም የሎጂስቲክስ ዝግጅት ለማድረግ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላ እና ምደባ ለመተግበር፣ የምርጫ ፀጥታ ጉዳይን ለመገምገም፣ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ ጣቢያዎች ለማደራጀት፣ ለታዛቢ ሲቪል ማህበራት ፈቃድ ለመስጠት እና በጉዳዩ ላይ የሚያገባቸውን ባለድርሻ አካላት ለማወያየት የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ ለምክር ቤቱ እንደሚገልፅ ከአክብሮት ጋር እናሳውቃለን። "
(ቦርዱ ያሳለፈው ውሳኔ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትን #በህግ_ተጠያቂ ለማድረግ እየተሰራ ነው " - ዶ/ር እሸቱ ከበደ
የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ስራ ሙሉ በሙሉ በመጠናቅ ላይ መሆኑን የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የፈተና ዝግጅቱም የተማሪዎችን ልፋት ሊለካ በሚችል ከደህንነት ስጋት ነፃ እንዲሆን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ለፈተና አሰጣጡ ውጤታማነት ከመፈተኛ ቦታ መረጣ ጀምሮ የፈተና ኮዶችን ብዛት ከፍ የማድረግ ስራ የተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የራሳቸው ጥረት ውጤት ለማግኘት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ያሳሰቡ ሲሆን ለዚህም የህግ ተጠያቂነት እንዲኖር እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ተማሪዎችና ወላጆችም መረጃዎችን ከተቋሙ እና ከታማኝ የመረጃ ምንጮች ብቻ እንዲከታተሉም ጠይቀዋል።
የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ስራ ሙሉ በሙሉ በመጠናቅ ላይ መሆኑን የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡
የፈተና ዝግጅቱም የተማሪዎችን ልፋት ሊለካ በሚችል ከደህንነት ስጋት ነፃ እንዲሆን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
ለፈተና አሰጣጡ ውጤታማነት ከመፈተኛ ቦታ መረጣ ጀምሮ የፈተና ኮዶችን ብዛት ከፍ የማድረግ ስራ የተሰራ መሆኑም ተገልጿል።
ይህንን ተከትሎ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የራሳቸው ጥረት ውጤት ለማግኘት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ያሳሰቡ ሲሆን ለዚህም የህግ ተጠያቂነት እንዲኖር እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡
ተማሪዎችና ወላጆችም መረጃዎችን ከተቋሙ እና ከታማኝ የመረጃ ምንጮች ብቻ እንዲከታተሉም ጠይቀዋል።
የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#GoE የጠቅላይ ሚኒስትር ፕሬስ ሴክሬተሪያት ቢልለኔ ስዩም ዛሬ በሰጡት መግለጫ የተለያዩ ጉዳዮችን አስንተዋል። ከካነሷቸው ጉዳዮች አንዱ በሰላም አመራጭ ኮሚቴ በኩል ስለ ተዘጋጀው የሰላም ረቂቅ ሰነድ ነው። በዚህም የሰላም ረቂቅ ሰነዱ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ለተከሰተው ግጭት ሰላማዊ መፍትሄ ለመስጠት፤ በመጪዎቹ ሳምንታት የተኩስ አቁም እንዲደረስ፣ የሰላም ውይይት እንዲሁም ሌሎች በእንጥልጥል የቀሩ…
#ETHIOPIA
ለዜጎች ሰላም እና ከጦርነት ጭንቀት እረፍት ይሰጣል ተብሎ የነበረው የተስፋ ጭላጭል " ሙሉ በሙሉ " ይከስም ይሆን ?
የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት ዛሬ ፤ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ " ህወሓት " በምስራቅ ግንባር በቢሶበር ፣ ዞብል ፣ እና ተኩለሽ በኩል ከለሊት 11 ሰዓት አንስቶ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።
በዚህ እርምጃውም ተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሷል ብሏል።
ዜጎችን ከ "ህወሓት" ጥቃት ለመጠበቅም አጠቃላይ የፀጥታ ኃይል በተጠንቀቅ መቆሙን አስገንዝቧል።
የለሊቱ ጥቃት ፤ ከሰሞኑን ከነበረው ትንኮሳ የቀጠለ መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ መንግስት ፤ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊትና አጠቃላይ የፀጥታ መዋቅሩ የተሰነዘረውን ጥቃት በድል እየመከቱት ይገኛሉ ብሏል።
ከኢትዮጵያ መንግስት መግለጫ ቀደም ብሎ ህወሓት የፌዴራል መንግስት ከለሊት 11:00 ጀምሮ በጩቤ በር ፣ ጃኖራ ፣ ጉባጋላ እና በያሎው አቅጣጫ ወደ አላማጣ ፣ ባላና ብሶበር መጠነሰፊ ጥቃት ከፍቷል ሲል ክስ አሰምቷል።
ባለፉት ቀናት ፤ በደቡብ ግንባር በየግንባሩ የነበሩትን እና ከሌላ አካባቢ የተሰባሰቡ የአማራ ልዩ ኃይል ክ/ጦሮች ፣ የወሎ ፋኖና ሚሊሻ ወደፊት የማስጠጋት እንቅስቃሴ ነበር በኃላም የፌዴራል መከላከያ ኃይል ተጨምሮ ዛሬ ጥቃት ተከፍቷል የሚል ክስ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት ግን ይህ የህወሓት ክስ " ጅራፍ ራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል " እንደሚባለው ቀድሞ የተካነበት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ነው ብሎታል።
ትንኮሳው በራሱ በ " ህወሓት " መፈፀሙን የገለፀው መንግስት ትንኮሳውን ከፈፀሙ በኃላ " እራሳቸው እየጮሁ " ነው ብሏል።
የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፤ የህወሓት ቡድን የትግራይ የወጣቶችን ለማስጨረስ እያደረገ ያለውን የጦርነት ጉሰማ እንዲያቆም ጠንካራ ግፊት ማድረግ አለበትም ሲል ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ መንግስት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መፍትሄ የሚያገኘው በሰላም ነው ያለ ሲሆን ዛሬም ነገም የሰላም አማራጭ የመጀመሪያ መፍትሄ እንደሆነ በፅኑ እንደሚያምን ገልጿል።
ነገር ግን ህወሓት በትንኮሳው ከቀጠለ ሀገር የማዳን ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ሞራላዊ ግዴታ ስላለበት ህወሓት ወደደም ጠላም ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመጣ ለማድረግ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
በሰሜን ኢትዮጵያ፤ አሁን አሁን ጠንከር ብለው እየታዩ ያሉት ምልክቶች ከዚህ ቀደም እንደነበረው የለየት ደም አፋሳሽ ግጭት እንዳይወልድ ብዙዎችን አስግቷል። የተጀመረው የሰላም ሂደትም እንዳይደናቀፍ ተፈርቷል።
ከወራት በፊት ለሰብዓዊ ድጋፍ ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ መተላለፉ አይዘነጋም ፤ ይህን ተከትሎ የሰላም ጭላንጭሎች መታየት ችለው ፤ ዜጎችም ከጦርነት እና ግጭት ስጋት ይላቀቃሉ የሚል ተስፋን ሰጥቶ ነበር።
በኃላም ችግሩን በሰላም ድርድር ለመፍታት መወሰኑን ተከትሎ በርካቶች " እፎይ ሰላም ሊገኝ ነው " የሚለው ተስፋቸው እጅግ ተጠናክሮ፤ በዚህም ተደስተው ነበር ነገር ግን ይህ ከሆነ ወራት ሳይቆጠር ዳግም የጦርነት ድባብ አንዣቧል።
ዜጎች የከዚህ ቀደሙ ጉዳት እና ህመማቸው ሳይባባስ ፣ ምንም የማያውቁ ንፁሃን ህፃናት ፤ ሴቶች አረጋዊያን ሳይፈናቀሉ ፣ ምንም የሰው ህይወት ሳይጠፋ ፣ የሀገር ሀብት ከከዚህ ቀደሙ በበለጠ ሳይጎዳ ፤ አሁን እየታዩ ያሉት ምልክቶች ቆመው በፍጥነት ሰላም ወርዶ ፤ ችግሮች ተፈተው #አዲሱን_አመት በደስታ እንቀበለው ይሆን ? ተስፋ እናደርጋለን ! ለሰላም መቼም ጊዜው አይረፍድም።
@tikvahethiopia
ለዜጎች ሰላም እና ከጦርነት ጭንቀት እረፍት ይሰጣል ተብሎ የነበረው የተስፋ ጭላጭል " ሙሉ በሙሉ " ይከስም ይሆን ?
የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት ዛሬ ፤ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ " ህወሓት " በምስራቅ ግንባር በቢሶበር ፣ ዞብል ፣ እና ተኩለሽ በኩል ከለሊት 11 ሰዓት አንስቶ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል።
በዚህ እርምጃውም ተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሷል ብሏል።
ዜጎችን ከ "ህወሓት" ጥቃት ለመጠበቅም አጠቃላይ የፀጥታ ኃይል በተጠንቀቅ መቆሙን አስገንዝቧል።
የለሊቱ ጥቃት ፤ ከሰሞኑን ከነበረው ትንኮሳ የቀጠለ መሆኑን የገለፀው የኢትዮጵያ መንግስት ፤ የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊትና አጠቃላይ የፀጥታ መዋቅሩ የተሰነዘረውን ጥቃት በድል እየመከቱት ይገኛሉ ብሏል።
ከኢትዮጵያ መንግስት መግለጫ ቀደም ብሎ ህወሓት የፌዴራል መንግስት ከለሊት 11:00 ጀምሮ በጩቤ በር ፣ ጃኖራ ፣ ጉባጋላ እና በያሎው አቅጣጫ ወደ አላማጣ ፣ ባላና ብሶበር መጠነሰፊ ጥቃት ከፍቷል ሲል ክስ አሰምቷል።
ባለፉት ቀናት ፤ በደቡብ ግንባር በየግንባሩ የነበሩትን እና ከሌላ አካባቢ የተሰባሰቡ የአማራ ልዩ ኃይል ክ/ጦሮች ፣ የወሎ ፋኖና ሚሊሻ ወደፊት የማስጠጋት እንቅስቃሴ ነበር በኃላም የፌዴራል መከላከያ ኃይል ተጨምሮ ዛሬ ጥቃት ተከፍቷል የሚል ክስ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት ግን ይህ የህወሓት ክስ " ጅራፍ ራሱ ገርፎ እራሱ ይጮሃል " እንደሚባለው ቀድሞ የተካነበት የሀሰት ፕሮፖጋንዳ ነው ብሎታል።
ትንኮሳው በራሱ በ " ህወሓት " መፈፀሙን የገለፀው መንግስት ትንኮሳውን ከፈፀሙ በኃላ " እራሳቸው እየጮሁ " ነው ብሏል።
የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ፤ የህወሓት ቡድን የትግራይ የወጣቶችን ለማስጨረስ እያደረገ ያለውን የጦርነት ጉሰማ እንዲያቆም ጠንካራ ግፊት ማድረግ አለበትም ሲል ጥሪ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ መንግስት የሁሉም ኢትዮጵያውያን መፍትሄ የሚያገኘው በሰላም ነው ያለ ሲሆን ዛሬም ነገም የሰላም አማራጭ የመጀመሪያ መፍትሄ እንደሆነ በፅኑ እንደሚያምን ገልጿል።
ነገር ግን ህወሓት በትንኮሳው ከቀጠለ ሀገር የማዳን ህጋዊ፣ ታሪካዊ እና ሞራላዊ ግዴታ ስላለበት ህወሓት ወደደም ጠላም ወደ ሰላማዊ አማራጭ እንዲመጣ ለማድረግ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።
በሰሜን ኢትዮጵያ፤ አሁን አሁን ጠንከር ብለው እየታዩ ያሉት ምልክቶች ከዚህ ቀደም እንደነበረው የለየት ደም አፋሳሽ ግጭት እንዳይወልድ ብዙዎችን አስግቷል። የተጀመረው የሰላም ሂደትም እንዳይደናቀፍ ተፈርቷል።
ከወራት በፊት ለሰብዓዊ ድጋፍ ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ መተላለፉ አይዘነጋም ፤ ይህን ተከትሎ የሰላም ጭላንጭሎች መታየት ችለው ፤ ዜጎችም ከጦርነት እና ግጭት ስጋት ይላቀቃሉ የሚል ተስፋን ሰጥቶ ነበር።
በኃላም ችግሩን በሰላም ድርድር ለመፍታት መወሰኑን ተከትሎ በርካቶች " እፎይ ሰላም ሊገኝ ነው " የሚለው ተስፋቸው እጅግ ተጠናክሮ፤ በዚህም ተደስተው ነበር ነገር ግን ይህ ከሆነ ወራት ሳይቆጠር ዳግም የጦርነት ድባብ አንዣቧል።
ዜጎች የከዚህ ቀደሙ ጉዳት እና ህመማቸው ሳይባባስ ፣ ምንም የማያውቁ ንፁሃን ህፃናት ፤ ሴቶች አረጋዊያን ሳይፈናቀሉ ፣ ምንም የሰው ህይወት ሳይጠፋ ፣ የሀገር ሀብት ከከዚህ ቀደሙ በበለጠ ሳይጎዳ ፤ አሁን እየታዩ ያሉት ምልክቶች ቆመው በፍጥነት ሰላም ወርዶ ፤ ችግሮች ተፈተው #አዲሱን_አመት በደስታ እንቀበለው ይሆን ? ተስፋ እናደርጋለን ! ለሰላም መቼም ጊዜው አይረፍድም።
@tikvahethiopia
የመንገድ ችግር ...
በኦሮሚያ ክልል፣ ኢሉ አባቦር ዞን ፤ " ኖኖ ሰልኤ ወረዳ " የሚኖሩ ነዋሪዎች የጨዋቃ ቢርብርሳ ገንጂ መንገድ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ ለተለያዩ ችግሮች እየተጋለጡ መሆኑን ለኦቢኤን በሰጡት ቃል ገለፀዋል።
የዚህ መንገድ ችግር በቅርቡ በኦሮሚያ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊዎች የተጎበኘ ሲሆን የመንገዱን ደረጃ ለማሻሻልና እስከዚያው ግን ጠንካራ ጥገና ለማድረግ ቃል ገብቶ እንደነበር ተነግሯል።
የኖኖ ሰልኤ አስተዳዳሪ አቶ ታምሩ ነጋሽ ለኦቢኤን በሰጡት ቃል፤ ስለመንገዱ ችግር ወረዳው ደጋግሞ ከዞኑ እስከ ኦሮሚያ ቢያሳውቅም እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ አልተገኘም ብለዋል።
የኢሉ አባቦር አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ በአውራጃው እየጣለ ከሚገኘው ከባድ ዝናብ ጋር የመንገዱ ደረጃ አይመጣጠንም ብለዋል ፤ ይሄን ችግር ለመፍታት መንገዱን የመጠገን ስራ ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል፣ ኢሉ አባቦር ዞን ፤ " ኖኖ ሰልኤ ወረዳ " የሚኖሩ ነዋሪዎች የጨዋቃ ቢርብርሳ ገንጂ መንገድ የትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጦ ለተለያዩ ችግሮች እየተጋለጡ መሆኑን ለኦቢኤን በሰጡት ቃል ገለፀዋል።
የዚህ መንገድ ችግር በቅርቡ በኦሮሚያ መንገድና ሎጂስቲክስ ቢሮ ኃላፊዎች የተጎበኘ ሲሆን የመንገዱን ደረጃ ለማሻሻልና እስከዚያው ግን ጠንካራ ጥገና ለማድረግ ቃል ገብቶ እንደነበር ተነግሯል።
የኖኖ ሰልኤ አስተዳዳሪ አቶ ታምሩ ነጋሽ ለኦቢኤን በሰጡት ቃል፤ ስለመንገዱ ችግር ወረዳው ደጋግሞ ከዞኑ እስከ ኦሮሚያ ቢያሳውቅም እስካሁን ምንም አይነት ምላሽ አልተገኘም ብለዋል።
የኢሉ አባቦር አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ በአውራጃው እየጣለ ከሚገኘው ከባድ ዝናብ ጋር የመንገዱ ደረጃ አይመጣጠንም ብለዋል ፤ ይሄን ችግር ለመፍታት መንገዱን የመጠገን ስራ ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
#አስቸኳይ
በአሁን ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጨማሪ አሃዶችን የመፍጠር ቴክኖሎጂዎች (Blockchain technologies) ላይ የተመሰረቱ የክሪፕቶ ምርቶችና አገልግሎቶች ሁኔታ በመስፋፋት እና ጥቅም ላይ በመዋል ላይ ይገኛሉ፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ የክሪፕቶግራፊ ውጤት/ምርትንና አገልግሎትን በተመለከተ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 808/06 አንቀጽ 6 (9) በተሰጠው ስልጣን መሰረት " የክሪፕቶ ምርትና ዝውውርን የመቆጣጠር እና አስፈላጊውን መስፈርት ማውጣትና የአጠቃቀም ስርዓት መዘርጋት " ሃላፊነት ተሰጥቶታል።
በዚህም ዘርፉን በአግባቡ ለመግራት ይቻል ዘንድ ፦የክሪፕቶ ምርት፤ አገልግሎት፣ ዝውውርና ማይኒንግን በተመለከተ ስራዎችን የሚያከናውኑ እና መምዝገብ ለሚፈልጉ ወይም ለመመዝገብ ጠይቀው ሂደት ላይ ያሉ በአስተዳድሩ ድረ-ገጽ በተቀመጠው ቅጽ መስረት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እንዲመዘገቡ አስተዳደሩ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይህንን ተግባራዊ በማያደርጉ እና በዚህ ስራ ያለምዝገባ ተሰማርተው በሚገኙ አካላት ላይ አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።
ለተጨማሪ መረጃ የአስተዳደሩን ድረ-ገጽ www.insa.gov.et/Crypto ወይም https://crypto.insa.gov.et መጎብኘት ይቻላል ተብሏል።
@tikvahethiopia
በአሁን ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተጨማሪ አሃዶችን የመፍጠር ቴክኖሎጂዎች (Blockchain technologies) ላይ የተመሰረቱ የክሪፕቶ ምርቶችና አገልግሎቶች ሁኔታ በመስፋፋት እና ጥቅም ላይ በመዋል ላይ ይገኛሉ፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ የክሪፕቶግራፊ ውጤት/ምርትንና አገልግሎትን በተመለከተ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር እንደገና ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 808/06 አንቀጽ 6 (9) በተሰጠው ስልጣን መሰረት " የክሪፕቶ ምርትና ዝውውርን የመቆጣጠር እና አስፈላጊውን መስፈርት ማውጣትና የአጠቃቀም ስርዓት መዘርጋት " ሃላፊነት ተሰጥቶታል።
በዚህም ዘርፉን በአግባቡ ለመግራት ይቻል ዘንድ ፦የክሪፕቶ ምርት፤ አገልግሎት፣ ዝውውርና ማይኒንግን በተመለከተ ስራዎችን የሚያከናውኑ እና መምዝገብ ለሚፈልጉ ወይም ለመመዝገብ ጠይቀው ሂደት ላይ ያሉ በአስተዳድሩ ድረ-ገጽ በተቀመጠው ቅጽ መስረት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ እንዲመዘገቡ አስተዳደሩ ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
ይህንን ተግባራዊ በማያደርጉ እና በዚህ ስራ ያለምዝገባ ተሰማርተው በሚገኙ አካላት ላይ አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ አስጠንቅቋል።
ለተጨማሪ መረጃ የአስተዳደሩን ድረ-ገጽ www.insa.gov.et/Crypto ወይም https://crypto.insa.gov.et መጎብኘት ይቻላል ተብሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ለዜጎች ሰላም እና ከጦርነት ጭንቀት እረፍት ይሰጣል ተብሎ የነበረው የተስፋ ጭላጭል " ሙሉ በሙሉ " ይከስም ይሆን ? የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት ዛሬ ፤ ረቡዕ ባወጣው መግለጫ " ህወሓት " በምስራቅ ግንባር በቢሶበር ፣ ዞብል ፣ እና ተኩለሽ በኩል ከለሊት 11 ሰዓት አንስቶ ጥቃት መፈፀሙን ገልጿል። በዚህ እርምጃውም ተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሷል ብሏል። ዜጎችን ከ "ህወሓት"…
#ተመድ #አፍሪካ_ህብረት
አንቶኒዮ ጉተሬዝ ግጭት እንዲቆም ተማፀኑ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ፤ በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን በመስማታቸው ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን ገልፀዋል።
ይህን የገለፁት ፤ ዛሬ ከሚካሄድ የፀጥታው ም/ ቤት ስብሰባ አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ነው።
በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ በጣም ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን የገለፁት ጉተሬዥ በአስቸኳይ ግጭት እንዲቆም ተማፅነዋል።
" ኢትዮጵያውያን ትግራዋዮች፣ አማራዎች፣ ኦሮሞዎች ፣ አፋሮች ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
" አጠንክሬ የምጠይቀው በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግና የመንግስትና የህወሓት የሰላም ድርድር እንዲቀጥል ነው " ብለዋል።
ጉተሬዥ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ሙሉ ዋስትና እንዲሰጠው ፤ በተጨማሪ የህዝብ አግልግሎቶች ተመልሰው እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ፤ የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ በኢትዮጵያ እንደገና ወታደራዊ ግጭት መፈጠሩን የሚገልፁ ሪፖርቶች መስማታቸው እጅግ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል፤ ሁኔታውን እየተከታተሉ መሆኑንም አመልክተዋል።
ሊቀመንበሩ በአስቸኳይ ግጭት እንዲቆም ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት ንግግሩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት #የሀገሪቱን_ጥቅም_ባስጠበቀ መልኩ የጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሂደትን ለመደገፍ ከሁሉም ወገን ጋር አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ ነው ሲሉ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ሁሉም ወገኖች ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ ከሆኑት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ጋር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
@tikvahethiopia
አንቶኒዮ ጉተሬዝ ግጭት እንዲቆም ተማፀኑ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ፤ በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን በመስማታቸው ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን ገልፀዋል።
ይህን የገለፁት ፤ ዛሬ ከሚካሄድ የፀጥታው ም/ ቤት ስብሰባ አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ነው።
በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ በጣም ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን የገለፁት ጉተሬዥ በአስቸኳይ ግጭት እንዲቆም ተማፅነዋል።
" ኢትዮጵያውያን ትግራዋዮች፣ አማራዎች፣ ኦሮሞዎች ፣ አፋሮች ብዙ መከራ ደርሶባቸዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
" አጠንክሬ የምጠይቀው በአስቸኳይ የተኩስ አቁም እንዲደረግና የመንግስትና የህወሓት የሰላም ድርድር እንዲቀጥል ነው " ብለዋል።
ጉተሬዥ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ሙሉ ዋስትና እንዲሰጠው ፤ በተጨማሪ የህዝብ አግልግሎቶች ተመልሰው እንዲቋቋሙ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ፤ የአፍሪካ ህብረት (AU) ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋኪ በኢትዮጵያ እንደገና ወታደራዊ ግጭት መፈጠሩን የሚገልፁ ሪፖርቶች መስማታቸው እጅግ እንዳሳሰባቸው ገልፀዋል፤ ሁኔታውን እየተከታተሉ መሆኑንም አመልክተዋል።
ሊቀመንበሩ በአስቸኳይ ግጭት እንዲቆም ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን ሰላማዊ መፍትሄ ለማምጣት ንግግሩ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።
የአፍሪካ ህብረት #የሀገሪቱን_ጥቅም_ባስጠበቀ መልኩ የጋራ ስምምነት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ሂደትን ለመደገፍ ከሁሉም ወገን ጋር አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ ነው ሲሉ አረጋግጠዋል።
ለዚህም ሁሉም ወገኖች ከአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ከፍተኛ ተወካይ ከሆኑት የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዚደንት ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ ጋር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተመድ #አፍሪካ_ህብረት አንቶኒዮ ጉተሬዝ ግጭት እንዲቆም ተማፀኑ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ፤ በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን በመስማታቸው ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ፤ ዛሬ ከሚካሄድ የፀጥታው ም/ ቤት ስብሰባ አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ነው። በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ በጣም ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን የገለፁት…
#Update
ተመድ በመቐለ ነዳጅ መዘረፉን ገለፀ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በሰጡት መግለጫ ዛሬ ነሀሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም ጥዋት በትግራይ ክልል መዲና ፤ መቐለ ከተማ የሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን መዘረፉን ገልፀዋል።
ዱጃሪች ፤ " ዛሬ ጥዋት የትግራይ ኃይሎች መቐለ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በኃይል በመግባት 12 ቦቴ የነዳጅ ታንከር 570,000 ሊትር ነዳጅ ውስደዋል " ሲሉ አሳውቀዋል።
በቦታው ላይ የነበረው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ቡድን ዘረፋውን ለመከላከል ጥረት ቢያደርግም እንዳልተሳካለት ተናግረዋል።
የተዘረፈው ነዳጅ ለሰብዓዊ ድጋፍ ፣ ምግብ፣ ማዳበሪያና ሌሎች አስቸኳይ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የሚውል ነበር ያሉት ዱጃሪች " ነዳጁ በመዘረፉ በመላው ሰሜን ኢትዮጵያ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመድረስ የሚሰራው የሰብዓዊው ድጋፍ ስራ ላይ ተፅኖ ይኖረዋል " ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሰብዓዊ ስራ ሊውል የነበረው ነዳጅ ላይ የተፈፀመውን ዝርፊያ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
ተመድ በመቐለ ነዳጅ መዘረፉን ገለፀ።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱጃሪች በሰጡት መግለጫ ዛሬ ነሀሴ 18 ቀን 2014 ዓ/ም ጥዋት በትግራይ ክልል መዲና ፤ መቐለ ከተማ የሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) መጋዘን መዘረፉን ገልፀዋል።
ዱጃሪች ፤ " ዛሬ ጥዋት የትግራይ ኃይሎች መቐለ በሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በኃይል በመግባት 12 ቦቴ የነዳጅ ታንከር 570,000 ሊትር ነዳጅ ውስደዋል " ሲሉ አሳውቀዋል።
በቦታው ላይ የነበረው የዓለም ምግብ ፕሮግራም ቡድን ዘረፋውን ለመከላከል ጥረት ቢያደርግም እንዳልተሳካለት ተናግረዋል።
የተዘረፈው ነዳጅ ለሰብዓዊ ድጋፍ ፣ ምግብ፣ ማዳበሪያና ሌሎች አስቸኳይ ቁሳቁሶችን ለማጓጓዝ የሚውል ነበር ያሉት ዱጃሪች " ነዳጁ በመዘረፉ በመላው ሰሜን ኢትዮጵያ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸውን ሰዎች ለመድረስ የሚሰራው የሰብዓዊው ድጋፍ ስራ ላይ ተፅኖ ይኖረዋል " ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ለሰብዓዊ ስራ ሊውል የነበረው ነዳጅ ላይ የተፈፀመውን ዝርፊያ አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somalia
" ... የሶማሊያ ህዝብ ማብቂያ በሌለው የሀዘን መግለጫ እና ሀዘን መሰላቸቱን አውቃለሁ " - ሀሰን ሼክ ሞሐመድ
የጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ " አልሸባብ " ን ለማጥፋት ሁሉን አቀፍ ጦርነት ለመክፈት ቃል ገቡ።
ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ባወጡት መግለጫ የሶማሊያ ህዝብ የሰላም ጠላት በሆኑት ጨካኞች ላይ ለሚካሄድ አጠቃላይ ጦርነት ይዘጋጅ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
" የሶማሊያ ህዝብ ማብቂያ በሌለው የሀዘን መግለጫና ሀዘን መሰላቸቱን አውቃለሁ " ያሉት ፕሬዝዳንቱ አሸባሪው ቡድን በሚፈጽመው በእያንዳንዱ ግድያ እጅግ የተከበሩ ሰዎች እየሞቱ ነው ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ ወዲህ ከባድ ነው የተባለው የአልሸባብ ጥቃት ባለፈው አርብ ሞቃዲሾ በሚገኘው በ " ሃያት ሆቴል " ውስጥ ተፈፅሟል። በዚሁ ጥቃትም 21 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 117 ቆስለዋል።
የሶማሊያ ጠ/ሚ ፣ የሀገር ውስጥ ጉዳይ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተገኙበትን የብሔራዊ የፀጥታ ኮሚቴ ስብሰባ ያካሄዱት ፕሬዝዳንት ሞሐመድ " ህዝባችንን የሚያጠፉት አሸባሪዎች የሚቆጣጠሯቸው አካባቢዎች ነጻ እስኪወጡ ድረስ ቡድኑን ለማዳከም ቆርጠን ተነስተናል " ብለዋል።
ይህንንም ፤ መንግሥታት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው የእቅዱ ዝግጅትና አተገባበሩ እየተካሄደ መሆኑን ማስታወቃቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
" ... የሶማሊያ ህዝብ ማብቂያ በሌለው የሀዘን መግለጫ እና ሀዘን መሰላቸቱን አውቃለሁ " - ሀሰን ሼክ ሞሐመድ
የጎረቤት ሀገር ሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐመድ " አልሸባብ " ን ለማጥፋት ሁሉን አቀፍ ጦርነት ለመክፈት ቃል ገቡ።
ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ ባወጡት መግለጫ የሶማሊያ ህዝብ የሰላም ጠላት በሆኑት ጨካኞች ላይ ለሚካሄድ አጠቃላይ ጦርነት ይዘጋጅ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።
" የሶማሊያ ህዝብ ማብቂያ በሌለው የሀዘን መግለጫና ሀዘን መሰላቸቱን አውቃለሁ " ያሉት ፕሬዝዳንቱ አሸባሪው ቡድን በሚፈጽመው በእያንዳንዱ ግድያ እጅግ የተከበሩ ሰዎች እየሞቱ ነው ብለዋል።
ፕሬዝዳንቱ ስልጣን ከያዙ ወዲህ ከባድ ነው የተባለው የአልሸባብ ጥቃት ባለፈው አርብ ሞቃዲሾ በሚገኘው በ " ሃያት ሆቴል " ውስጥ ተፈፅሟል። በዚሁ ጥቃትም 21 ሰዎች ሲገደሉ ሌሎች 117 ቆስለዋል።
የሶማሊያ ጠ/ሚ ፣ የሀገር ውስጥ ጉዳይ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች የተገኙበትን የብሔራዊ የፀጥታ ኮሚቴ ስብሰባ ያካሄዱት ፕሬዝዳንት ሞሐመድ " ህዝባችንን የሚያጠፉት አሸባሪዎች የሚቆጣጠሯቸው አካባቢዎች ነጻ እስኪወጡ ድረስ ቡድኑን ለማዳከም ቆርጠን ተነስተናል " ብለዋል።
ይህንንም ፤ መንግሥታት ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ መሆኑን ገልፀው የእቅዱ ዝግጅትና አተገባበሩ እየተካሄደ መሆኑን ማስታወቃቸውን ዶቼ ቨለ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ተመድ #አፍሪካ_ህብረት አንቶኒዮ ጉተሬዝ ግጭት እንዲቆም ተማፀኑ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዥ ፤ በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት መቀስቀሱን በመስማታቸው ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ፤ ዛሬ ከሚካሄድ የፀጥታው ም/ ቤት ስብሰባ አስቀድሞ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ላይ ነው። በኢትዮጵያ ዳግም ግጭት በመቀስቀሱ በጣም ማዘናቸውንና መደንገጣቸውን የገለፁት…
#USA
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ዳግም የተቀሰቀሰው ግጭት አሜሪካን ስጋት እንዳጫረባት ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እና በመጨረሻም ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ብሊንከን ፤ ላለፉት 5 ወራት የነበረው የተኩስ አቁም የበርካቶችን ሕይወት መታደጉንና እርዳታ እንዲደርስ ማስቻሉንም ገልፀዋል።
በቅርብ ጊዜ የተቀሰቀው ጦርነት፣ ትንኮሳ የተሞላባቸው ትርክቶችና እና ዘላቂ የተኩስ አቁም እጦት እየታየ የነበረውን መሻሻል አደጋ ውስጥ መክተቱን ጠቁመዋል።
በተጨማሪ ለጋራ ደኅንነት እና ለመላው ኢትዮጵያውያን ብልጽግናና እድገት ለማምጣት ሁሉንም ያሳተፈ የፖለቲካ ሂደት እንዲፈጠር የሚደረገውን ጥረት እንደሚያዘገየው ገልፀዋል።
እንደገና ወደ ጦርነት መግባት የኢትዮጵያን ሰላምና ደኅንነት ለማደፍረስ በሚጥሩት ላይ ሚና እንደሚጫወት፣ የሰዎችን መጠነ ሰፊ ስቃይ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣና ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ያስከትላል ብለዋል።
ብሊንከን የኢትዮጵያ መንግሥት ተደራዳሪ ቡድን ማቋቋሙንና ለሰላም ውይይት ያለውን ፍላጎት መግለጹን መገንዘባቸውን ጠቁመዋል።
በዚህ ወቅት ሁሉም ወገኖች የሰብአዊ እርዳታ ምግብ እና የነዳጅ አቅርቦትን እንዲያስቀጥሉ፣ ከወታደራዊ ኃይል እንዲታቀቡና መሠረታዊ አገልግሎቶች ወደነበሩበት እንዲመለሱ ጠይቀዋል።
" አሜሪካ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ እና ለአገሪቷ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ቁርጠኛ አቋም አላት። አገሪቷ ያጋጠሟትን ሁለንተናዊ ተግዳሮቶች ታሪካዊ ድርቅን ማሸነፍና ክልላዊ ደኅንነትን ማስፈንን ጨምሮ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ ነን " ብለዋል።
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ዳግም የተቀሰቀሰው ግጭት አሜሪካን ስጋት እንዳጫረባት ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ዘላቂ የሆነ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ እና በመጨረሻም ግጭቱን በዘላቂነት ለማስቆም ጥረታቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርበዋል።
ብሊንከን ፤ ላለፉት 5 ወራት የነበረው የተኩስ አቁም የበርካቶችን ሕይወት መታደጉንና እርዳታ እንዲደርስ ማስቻሉንም ገልፀዋል።
በቅርብ ጊዜ የተቀሰቀው ጦርነት፣ ትንኮሳ የተሞላባቸው ትርክቶችና እና ዘላቂ የተኩስ አቁም እጦት እየታየ የነበረውን መሻሻል አደጋ ውስጥ መክተቱን ጠቁመዋል።
በተጨማሪ ለጋራ ደኅንነት እና ለመላው ኢትዮጵያውያን ብልጽግናና እድገት ለማምጣት ሁሉንም ያሳተፈ የፖለቲካ ሂደት እንዲፈጠር የሚደረገውን ጥረት እንደሚያዘገየው ገልፀዋል።
እንደገና ወደ ጦርነት መግባት የኢትዮጵያን ሰላምና ደኅንነት ለማደፍረስ በሚጥሩት ላይ ሚና እንደሚጫወት፣ የሰዎችን መጠነ ሰፊ ስቃይ፣ የሰብአዊ መብት ረገጣና ተጨማሪ ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ያስከትላል ብለዋል።
ብሊንከን የኢትዮጵያ መንግሥት ተደራዳሪ ቡድን ማቋቋሙንና ለሰላም ውይይት ያለውን ፍላጎት መግለጹን መገንዘባቸውን ጠቁመዋል።
በዚህ ወቅት ሁሉም ወገኖች የሰብአዊ እርዳታ ምግብ እና የነዳጅ አቅርቦትን እንዲያስቀጥሉ፣ ከወታደራዊ ኃይል እንዲታቀቡና መሠረታዊ አገልግሎቶች ወደነበሩበት እንዲመለሱ ጠይቀዋል።
" አሜሪካ ለኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ እና ለአገሪቷ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ቁርጠኛ አቋም አላት። አገሪቷ ያጋጠሟትን ሁለንተናዊ ተግዳሮቶች ታሪካዊ ድርቅን ማሸነፍና ክልላዊ ደኅንነትን ማስፈንን ጨምሮ ከሁሉም ኢትዮጵያውያን ጋር በጋራ ለመስራት ዝግጁ ነን " ብለዋል።
@tikvahethiopia