TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
* ቡልቡሎ

የሀይቅ ቢስቲማ መንገድ " ቡልቡሎ " ላይ በጎርፍ በመቆረጡ ማህበረሰቡ ለእንግልት እየተዳረገ እንደሚገኝ የወረባቦ ኮሚኒኬሽን ገልጿል።

የአካባቢው የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም በጉዳዩ ዙሪያ መልዕክት የላኩ ሲሆን መንገዱ በጎርፍ በመቋረጡ ከፍተኛ የሆነ እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ አስረድተዋል።

የወረባቦ ኮሚኬሽን ያናገራቸው የፖወርኮን መንድ ስራ ተቋራጭ ድርጅት የሀይቅ ቢስቲማ ጭፍራ መንገድ ግንባታ አስተባባሪ አቶ አለሙ አባይነህ ተከታዩን ብለዋል፦

" ድርጅታችን በአጠቃላይ መንገዱን ከመስከረም በኋላ ሙሉ ጥገና ያደርጋል። አሁንም በመንገዱ ላይ የተሰበሩና ለትራንስፖርት መስተጓጉል የሚፈጥሩ ቦታዎች ላይ ጊዜያዊ ጥገና እያደረግን እንገኛለን።

ነገር ግን ጊዜያዊ መፍትሄ ለመስጠት መንገዶቹ የተቆረጡበት ቦታ የወሰን ማስከበርና የሴሌክት ማቴሪያል እጥረት እያጋጠመ ነው "

የወረባቦ ወረዳ መንገድ ትራንስፖርት ኃላፊ አቶ ሁሴን ሰይድ በበኩላቸው ተከታዩን ብለዋል፦

" የሀይቅ ቢስቲማ መንገድ የአስፓልት መንገድ ለመስራት በፌደራል መንግስት ለተቋራጭ የተሰጠ በመሆኑ ወሎ ገጠር መንገድ ከጥገና አገልጎሎቱ ላይ አስወጥቶታል በዚህም መንገዱን እየጠገነ የሚያስተዳድረው ተቋራጭ ድርጅቱ ፖወርኮን ነው።

ፓወርኮን በአሁኑ ሰአት መንገዱን ሙሉ ጥገና ለማድረግ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ መጠገን ስለማልችል ሙሉ ጥገና ከመስከረም በኋላ ይደረጋል።

ነገር ግን ዛሬ ላይ ቡልቡሎ አውራጎዶና አካባቢ ሙሉ በሙሉ በጎርፍ በመቆረጡ ጊዜያዊ መፍትሄ በመስጠት መኪኖች እንዲተላለፉ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።

ይህ የተቆረጠበት ቦታ ከወደፊት አንፃር ለጥገና በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ በጋቢዎን መታሰር ይኖርበታል። "

ፎቶ፦ ወረባቦ ኮሚኒኬሽን፣ ABD (ቲክቫህ ቤተሰብ)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
4ኛው ዙር ስልጠና ተጀመረ! ስቴም ፓወር (STEM POWER) ከቪዛ (VISA) እና ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ባዘጋጁት የሥራ ፈጠራ ክህሎት እና መሰረታዊ የፋይናንስ ትምህርት ላይ ባለፉት ዙሮች ከ450 በላይ ሰልጣኞችን አስመርቋል። ስልጠናውን ከተከታተሉ መካከል ንግድ ፍቃድ በማውጣት ሥራቸውን የጀመሩ ይገኙበታል። ሌሎቹም የቴክኒካል እና ማማከር ድጋፍ እየተደረገላቸው ይገኛል። አሁን ላይ 4ተኛ…
#UPDATE

ስቴም ፓወር ከቪዛ እንዲሁም ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ሲሰጥ የቆየው የሥራ ፈጠራ ክህሎት እና መሰረታዊ የፋይናንስ ትምህርት 4ኛ ዙር በማጠናቀቅ 240 ሰልጣኞችን አስመርቋል።

ስቴም ፓወር በቀጣይ አምስተኛ ዙር ሰልጣኞችን መዝገባ በማከናወን ሥልጠናውን ለመስጠት ቅድመ ዝግጅት በማጠናቀቅ የፊታችን ሰኞ ነሀሴ 16 ሥልጠናው መሰጠት ይጀምራል። በኦላይን ለመሰልጠን ለተመዘገቡም ስለጠናውን እየተሰጠ ይገኛል።

ከ4ኛው ዙር የተመረጡ ምርጥ 4 ፕሮጀክቶች፦

1. ግብርና እና ምግብ ዘርፍ፦

- ዮፍታሔ ሳሙኤል - Mushroom Agro-processing

- ​​ስጦታው አበራ - Punt Flour from Gipto

2. አገልግሎት ዘርፍ፦

- Wujo Digital Iqub

3. ምህንድስና እና ቴክኖሎጂ:

- መኮንን አስማረ - Agricultural Chemical Spray & Aerial Mapping Drone

በልዩ ዘርፍ፦ ዶ/ር ትዝታ አለሙ - Biruh Hiwot Mental Health Consultancy

#STEMpower #VISA #TIKVAH_ETHIOPIA

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ጥንቃቄ

የዘንድሮው ክረምት ተጠንክሮ በመቀጠሉ በሁሉም አካባቢ ያላችሁ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቻችን ጥንቃቄ ማድረጋችሁን እንዳትዘነጉ።

በተለይ ለጎርፍ ተጋላጭ በሆኑ አካባቢዎች ያላችሁ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደረጉ ለማስታወስ እንወዳለን።

የመኪና አሽከርካሪ የሆችሁ ቤተሰቦቻችንም በየአካባቢው እየጣለ ባለው ከባድ ዝናብ ሳቢያ ጉዞ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ በማድረግ የራሳችሁን እና የሌሎችንም ወገኖች ደህንነት ልታስጠብቁ ይገባል።

ሌላው ልጆች ያላችሁ የቤተሰባችን አባላት ልጆቻሁን ጠብቁ ፤ በተቻለ መጠን ከባድ ዝናብ ሲጥል ቤት ውስጥ እንዲቀመጡ በማድረግ ወቅቱን ማሳለፍ ይገባል። እጅግ አስፈላጊ ቦታ የሚሄዱ ከሆነም እንዲጠነቀቁ ማሳሰብ እንዳትዘነጉ።

#መልዕክት : ክረምት ሲመጣ ኑሯቸውን በጎዳና ላይ ያደረጉ ወገኖቻችን ምን ያህል እንደሚሰቃዩ ይታወቃል ፤ በግለሰብ ደረጃ ዘላቂ መፍትሄ መስጠት ባንችልም አንዳንድ የሚለበሱ ለብርድ የሚሆኑ አልባሳትን በመስጠት እንደሁል ጊዜው በበጎ ስራችን እንቀጥል።

ቪድዮ : AN ከአዲስ አበባ (አዳዋ ድልድይ) ቲክቫህ ቤተሰብ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE " የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች…
#NationalExam

መስከረም 30 ቀን 2015 መሰጠት የሚጀምረው የ2014 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና " ተሰርቆ ወጥቷል " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆነን  የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የአገልግሎተ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከፈተና ስርቆት ጋር በተያያዘ እተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል።

በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የዘንድሮ " ነው ተብሎ የሚሰራጨው ፈተና በ2013/14 (2021) ዓ.ም የተሰጠ እንደሆነ አስረድተዋል። እየተሰራጩ ያሉት ፈተናዎች ዓመቱ ኤዲት ተደርጎ መሆኑንም አመልክተዋል።

" ተፈታኝ ተማሪዎች በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የሚሰራጩ መሰል መረጃዎችን ከማመናቸው በፊት የአሰራጩን ታማኝነት እንዲያጣሩና ትክክለኛነቱን እንዲመረምሩ " መልዕክታቸውን አስተላፈዋል።

የአገር አቀፍ ፈተናን የተመለከቱ ሀሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩ አካላት " ፖለቲካን ከታዳጊዎች ህይዎት ቢለዩ መልካም ነው " ሲሉ ለ " ኢትዮጵያ ቼክ " መረጃ አጣሪ ድረገፅ በሰጡት ቃል አሳስበዋል።

የ2014 ዓ/ም የሀገር አቀፍ ፈተና ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በሁለት ዙር የሚሰጥ ይሆናል።

ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት እንደሰማነው ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ይገኛል ፤ ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው ተብሏል።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam መስከረም 30 ቀን 2015 መሰጠት የሚጀምረው የ2014 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና " ተሰርቆ ወጥቷል " በሚል የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆነን  የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የአገልግሎተ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር እሸቱ ከበደ ከፈተና ስርቆት ጋር በተያያዘ እተሰራጨ ያለው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑን ገልፀዋል። በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " የዘንድሮ "…
#Update

የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 11 ቀን 2015 ድረስ በሁለት ዙር እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

ለዚህም ተማሪዎች እራሳቸውን እንዲያዘጋጁ ጥሪ አቅርቧል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ረዲ ሽፋ #ለኦቢኤን በሰጡት ቃል ፤ በአጠቃላይ በሁለት ዙር በሚሰጠው ፈተና ከ984,000 በላይ ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

ፈተናውን ከሚወስዱት ውስጥ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር 622,739 መሆኑን አመልክተዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ብዛት ያላቸው በመሆኑ በመጀመሪያው ዙር ከመስከረም 30 እስከ ጥቅምት 3 /2015 አስቀድሞ ፈተናው እንደሚሰጣቸው አቶ ረዲ ተናግረዋል።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ቁጥር ደግሞ 361,279 ሲሆን በሁለተኛው ዙር ከጥቅምት 8 እስከ 11/2015 ፈተናውን እንደሚወስዱ አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም የነበሩ የፈተና ችግሮችን ለመፍታት ፈተናው በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እንደሚሰጥ አረጋግጠዋል ፤ ፈታኞቹ ደግሞ የዩኒቨርሲቲ መምህራን መሆናቸውን አሳውቀዋል።

በተጨማሪም ፤ ፈተናው ከዚህ ቀደም ከነበረው ከ4 ኮድ ከፍ ማለቱን ገልፀዋል።

ፈተናው ተዘጋጅቶ እየታተመ ሲሆን ፈተናው እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ ተፈታኞች እራሳቸውን ማዘጋጀት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

@tikvahethiopia
#SNNPRS #GurageZone

" ሰዎች ለምን የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ በሚል እየታሰሩ ናቸው " - ነዋሪዎች

" ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር ውለዋል " - የደቡብ ክልል ፖሊስ

በደቡብ ክልላዊ መንግስት ጉራጌ ዞን ከክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች እየተሰሩ መሆናቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።

እየታሰሩ ከሚገኙት መካከል በዞኑ በኃላፊነት ቦታ ያሉ ጭምር መሆናቸው ተጠቁሟል።

ትላንት ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ቃላቸውን የሰጡ አቶ በላቸው ገብረማርያን የተባሉ በግብርና ስራ የሚተዳደሩ የዞኑ ነዋሪ ካለፈው ቅዳሜ አንስቶ 13 ሰዎች እንደታሰሩ ከነዚህ ውስጥ ልጃቸውም እንደሙገኝበት ገልፀዋል። እሳቸውንም ፖሊስ እያፈላለገ መሆኑን አመልክተዋል።

እስሩ እየተካሄደ ያለው ለምን " የክልልነት ጥያቄ ትደግፋላችሁ " በሚል እንደሆነ አንዳችም ወንጀል እንዳልተፈፀመ ተናግረዋል።

አንድ የወልቂጤ ነዋሪ ደግሞ ወንድማቸው ለወቅታዊ ስበስባ ተብሎ ተጠርቶ መታሰሩን ገልፀዋል።

የደቡብ ክልል ፖሊስ የዞን ስራ ኃላፊዎች ጨምሮ ቁጥራቸው ያልተገለፀ ሰዎች መታሰራቸውን የደቡብ ክልል ፖሊስ አረጋግጧል።

የደቡብ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አለማየሁ ማሞ ለሬድዮ ጣቢያው ተከታዩን ቃል ሰጥተዋል ፦

" ... ማንም ሰው ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ በአግባቡ በስርዓት መጠየቅ መነጋገር፣ መወያየት፣ መወሰን መብቱ ነው ነገር ግን ተቀጥረው ህዝቦችን ለማጋጫት ስራ የሚሰሩ አካላት አሉ በዚህ ምክንያት ነው የተለያዩ የስራ ኃላፊዎች ጭምር በቁጥጥር ስር የዋሉት። ምርመራ እየተጣራባቸው ነው። አሁን በአካባቢው የተለየ የፀጥታ ችግር የለም "

ያንብቡ : https://telegra.ph/VOA-08-24

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ደቡብ_ኢትዮጵያ_ክልል " በ3 ወር ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንዲደራጅ " የፌዴሬሽን ምክር ቤት ፦ - የወላይታ፣ - የጋሞ፣ - የጎፋ፣ - የደቡብ ኦሞ፣ - የጌዴኦ፣ - የኮንሶ ዞኖች እንዲሁም - የደራሼ፣ - የአማሮ፣ - የቡርጂ፣ - የአሌ፣ - የባስኬቶ ልዩ ወረዳ ብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በጋራ " የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል " ለመመስረት ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጿል። ም/ቤቱ ውሳኔ ለመስጠት…
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፌዴሬሽን ም/ቤት አፈ-ጉባዔ ለቦርዱ ያቀረበው የሕዝበ ውሣኔ ማደራጀት ጥያቄ ላይ ውሣኔ አሳለፈ !

ነሐሴ 12/2014 የፌዴሬሽን ም/ ቤት ፤ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከ6 ዞኖችን እና 5 ልዩ ወረዳዎችን የክልልነት ጥያቄ ጋር ተያይዞ በ3 ወር ህዝበ ውሳኔ በማድረጃት ውጤቱን ለምክር/ቤቱ እንዲያሳውቅ ብሎ ነበር።

ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ለምክር ቤቱ ምላሹን ሰጥቷል። ምላሹ የህግ አግባብን ተከትሎ የተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።

ለህዝበ ወሳኔ የሚወስደውን ጊዜ ምን ያህል እንደሆነ የመወሰን ፣ የመርሀ ግብር ሰሌዳ የማዘጋጀት የማፅደቅ እንደ አስፈላጊነቱ የማሻሻል እና የማስፈፀም ስርልጣን የተቋሙ ብቻ መሆኑን ምርጫ ቦርድ አስገንዝቧል።

ከቦርዱ ምላሽ ፦

" ... ቦርዱ ለዚህ ጉዳይ አፈፃፀም የሎጂስቲክስ ዝግጅት ለማድረግ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ምልመላ እና ምደባ ለመተግበር፣ የምርጫ ፀጥታ ጉዳይን ለመገምገም፣ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት፣ የምርጫ ጣቢያዎች ለማደራጀት፣ ለታዛቢ ሲቪል ማህበራት ፈቃድ ለመስጠት እና በጉዳዩ ላይ የሚያገባቸውን ባለድርሻ አካላት ለማወያየት የሚያስፈልገውን ጊዜ ታሳቢ ያደረገ የጊዜ ሰሌዳ አውጥቶ ለምክር ቤቱ እንደሚገልፅ ከአክብሮት ጋር እናሳውቃለን። "

(ቦርዱ ያሳለፈው ውሳኔ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትን #በህግ_ተጠያቂ ለማድረግ እየተሰራ ነው " - ዶ/ር እሸቱ ከበደ

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ስራ ሙሉ በሙሉ በመጠናቅ ላይ መሆኑን የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ተናግረዋል፡፡

የፈተና ዝግጅቱም የተማሪዎችን ልፋት ሊለካ በሚችል ከደህንነት ስጋት ነፃ እንዲሆን በቴክኖሎጂ በመታገዝ በከፍተኛ ጥንቃቄ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ለፈተና አሰጣጡ ውጤታማነት ከመፈተኛ ቦታ መረጣ ጀምሮ የፈተና ኮዶችን ብዛት ከፍ የማድረግ ስራ የተሰራ መሆኑም ተገልጿል።

ይህንን ተከትሎ ተማሪዎች አስፈላጊውን ዝግጅት በማድረግ የራሳቸው ጥረት ውጤት ለማግኘት መስራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

የተሳሳቱ መረጃዎችን በመልቀቅ ተማሪዎች የስነ ልቦና ጫና እንዲደርስባቸው የሚያደርጉ አካላትም ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ዋና ዳይሬክተሩ ያሳሰቡ ሲሆን ለዚህም የህግ ተጠያቂነት እንዲኖር እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ተማሪዎችና ወላጆችም መረጃዎችን ከተቋሙ እና ከታማኝ የመረጃ ምንጮች ብቻ እንዲከታተሉም ጠይቀዋል።

የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።

መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።

@tikvahethiopia