TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61.5K photos
1.55K videos
215 files
4.26K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ🇪🇹 በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮን በዓለም 2ኛ ደረጃ ይዞ ያጠናቀቀው የአትሌቲክስ ቡድናችን በአዲስ አበባ አቀባበል እየተደረገለት ነው። ቡድኑ ትላንት ካረፈበት ስካይላት ሆቴል በመነሳት በአጅብ እየተጓዘ ደስታው ከህዝቡ ጋር እየገለፀ ህዝቡም ያለውን ፍቅር እና ምስጋና እያሳየ ይገኛል። አሁን ወደ ቤተ መንግስት እየተቃረቡ ይገኛሉ። ይህን መልዕክት የደረሳችሁ የቤተሰባችን አባላት የሀገራችንን…
ፎቶ ፦ ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ የኢትዮጵያ ኩራት !

በዓለም ሻምፒዮና ሀገራችን ኢትዮጵያ ከፍተኛ ድል እንድታመጣ ቡድኑን በመምራት ፣ በማስተባበር፣ አይዟችሁ በማለት፣ በማበርታት፣ አንድነቱን በማስጠበቅ ኮ/ር አትሌት ደራርቱ ቱሉ ከፍተኛውን ሚና ተጫውታለች።

ከሰሞኑን በሚዲያ ላይ ቃሏን የሰጠችው የማራቶን የወርቅ አሸናፊዋ ጎተይቶም ገ/ስላሰ ደራርቱ ቱሉ " የኢትዮጵያውያን እናት " ስትል ነበር የገለፀቻት።

ደራርቱ አትሌቶቻችን ሲያለቅሱ አልቅሳ፣ ሲስቁ ስቃ ፣ ሲደሰቱ ተደስታ በአትሌቲክሱ ዘርፍ ሀገራችን እያስመዘገበች ላለው ከፍተኛ ድል ትልቁን ሚና እየተጫወተች ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች❤️

የኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ ነዋሪ ጀግኖች ልጆቹን የሚገባቸውን ክብር በመስጠት እየተቀበላቸው ነው።

ጀግኖቹ በሚያልፉበት መንገዶች ሁሉ ነዋሪዎች በነቂስ አደባባይ ወጥተው ከከፍተኛ የደስታና የኩራት ስሜት ጋር " እንኳን ደህና መጣችሁንል ፤ ኢትዮጵያን አኩርታችኃል " እያለ ይገኛል።

የሀገር ኩራት የሆኑት ጀግኖች ልጆችም የሚገባቸውን ክብር እያገኙ ነው።

አሁን " ሜክሲኮ " አካባቢ ይገኛሉ ፤ ይህ መልዕክት በስልክ የሚደርሳችሁ ልጆቻችሁን ወጥታችሁ ተቀበሉ ፤ እንኳን ደህና መጣችሁልን በሏቸው።

@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን በአሁን ሰዓት በብሄራዊ ቤተመንግስት አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል።

በአቀባበል ስነስርዓቱ የኢፌዴሪ ፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሩ የተለያዩ ሚኒስትሮች ተገኝተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ችሎት

• ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የዋስትና መብቱ ውድቅ ተደረገ።

• ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ወይኒ ቤት እንዲወርድ አዟል።

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የዋስትና መብቱ ላይ አቃቤ ህግ ይግባኝ አልኩኝ ባለው መሠረት ዛሬ ሐምሌ 21/2014 ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የአቃቤ ህግ አቤቱታ ልክ ነው በማለት የተመስገንን ዋስትና ውድቅ አድሮጎ ተመስገን ክሱን እስር ቤት ሆኖ እንዲከታተል ወስኗል።

አወሳሰኑም በአብላጫ ድምጽ ( ከሦስቱ ዳኞች በሁለቱ ፤ በግራና በቀኝ ) ድጋፍ ፣ እንዲሁም የመሃል ዳኛ በልዩነት የተወሠነ መሆኑን ከወንዱም ከታሪኩ ደሳለኝ የተገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ውጤታችሁን በየት/ቤታችሁ ማየት እና መወሰድ ትችላላችሁ " - ትምህርት ቢሮ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸድን በየትምህርት ቤታቸው ማየት እና መውሰድ ይችላሉ ብሏል። ቢሮው " ይፋ በተደረገው የውጤት መመልከቻ ሊንክ #በኔትዎርክ_መጨናነቅ ምክንያት ውጤታችሁን ያላያችሁ ተማሪዎች በየት/ቤታችሁ ማየት እና መውሰድ ትችላላችሁ " ብሏል። ተማሪዎች ውጤታቸውን እንዲያዩ…
" ከውጤት ጋር ተያይዞ ቅሬታ ያላችሁ ተማሪዎች ቅሬታችሁን ማቅረብ ትችላላችሁ " - አዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ

ከ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ጋር ተያይዞ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች ቅሬታቸውን ማቅረብ እንደሚችሉ የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

ተማሪዎች ቅሬታቸውን ወደ ከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ #በአካል በመሄድ ማቅረብ እንደሚችሉ የቢሮው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አበበ ቸርነት ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።

የተማሪዎቹ ውጤት ወደየትምህርት ቤቶች መላኩን የገለጹት ኃላፊው፤ በተፈጠረው የኔትወርክ መጨናነቅ ምክንያት ውጤታቸውን ማየት ያልቻሉ ተማሪዎች ወደትምህርት ቤታቸው በመሄድ ማየት እና መውሰድ ይችላሉ ብለዋል፡፡

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
#ነፃ_ጥቅል_ከኢትዮ_ቴሌኮም !

ኢትዮ ቴሌኮም በ2014 በጀት አመት 61.3 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘቱን ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

ይህም የእቅዱን 87.6 በመቶ ነው ብሏል።

ይህን በማስመልከት ለሦስት ቀናት የሚቆይ ነጻ ጥቅል ስጦታ ማቅረቡን ገልጿል።

ኢትዮ ቴሌኮም ያስመዘገበውን ስኬት አስመልክቶ ከህብረተሰቡ ጋር ለመጋራት ሲል የዳታ፣ ድምፅ እና የመልዕክት ጥቅል ስጦታዎችን ማቅረቡን ነው ዛሬ ያሳወቀው።

በዚህም፦

👉 1.5 ጌጋባይት ዳታ በቀን 512 ሜባ፤

👉 45 ደቂቃ በቀን 15 ደቂቃ፤

👉 100 መልዕክት በቀን 33 መልዕክቶችን፤

👉 የ10 ደቂቃ አለምአቀፍ ጥሪ በቀን 3 ደቂቃ ለተጠቃሚዎች በነጻ አቅርቧል።

(ማስታወሻ ፦ ዓለም አቀፍ የጥሪ ስጦታው የተበረከተው ያልተገደበ የድምጽ ጥቅል፣ የጹሑፍና የኢንተርኔት ለሚጠቀሙ ነው)

ስጦታው ከዛሬ ሐምሌ 21 ከሌሊቱ 06:00 ሰአት - እስከ ምሽቱ 12 ሰአት ድረስ ለ3 ቀናት ይቆያል።

@tikvahethmagazine
#ደራርቱ_ቱሉ

' አይክፋችሁ እንክሳችኃለን '

ኮማንደር አትሌት ደራርቱ ቱሉ በብሔራዊ ቤተመንግስት የተናግረችው ፦

" ... ቶክዮ እኔ ውጭ ሀገር መኖር ሆነ መጥፋት አስቤው አላውቅም ከመጀመሪያው ጀምሮ የዛሬ ዓመት ግን መጥፋትም አስቤ ነበር፤ በጣምም ከፍቶኝ ነበር።

አንገታችንን ቀና አድርገን እንድንመጣ እነ ሰለሞን ባረጋ እና ሌሎችም ናችሁ ጥሩ ድጋፍ ያደረጋችሁልን።

ዛሬ ደግሞ የኢትዮጵያ ህዝብ በሚወደው 5 ሺ እና 10 ሺህ ውድድር ውጤት አላገኘንም። በእርግጠኝነት የዛሬ ዓመት እና የዛሬ ሁለት እንክሳችኃለን አይክፋችሁ።

እነ ሰለሞንም ሞራላችሁ አይነካ እንወዳችኃለን፤ ወርቆቻችን ናችሁ።

በስፖርቱ ቤተሰብ ፊት ቆሜ ቃል ገባላችኃለሁ የምንወደው እና የምንፈልገው ዘንድሮ ያጣነው ውጤት ይመጣል። ተስፋ አደርጋለሁ እንሰራለን ከሰራን እናመጣዋለን "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ቡድን በአሁን ሰዓት በብሄራዊ ቤተመንግስት አቀባበል እየተደረገላቸው ይገኛል። በአቀባበል ስነስርዓቱ የኢፌዴሪ ፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴን ጨምሩ የተለያዩ ሚኒስትሮች ተገኝተዋል። @tikvahethiopia
#ሽልማት

ወርቅ ያመጡ አትሌቶቻችን !

ለሁሉም 1.5 ሚሊዮን ብር ሽልማት ተበርክቷል።

እንደተሳትፏቸው መጠንና እንዳስመዘገቡት ስኬት ተጨማሪ ሽልማት ተበርክቷል።

🇪🇹 ለተሰንበት ግደይ (1.5 ሚሊዮን ብር + 500 ሺህ ብር ለቡድን ስራ )

🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ (2.5 ሚሊዮን ብር - ሁለት ሜዳሊያ በማምጣቷ)

🇪🇹 ታምራት ቶላ (1.5 ሚሊዮን ብር + 250 ሺህ ብር ሪከርድ በመስበሩ)

🇪🇹 ጎተይቶም ገብረስላሰ (1.5 ሚሊዮን ብር + 250 ሺህ ብር የሻምፒዮናውን ሪከርድ በመስበሯ)

@tikvahethiopia