TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሐምሌ19
በየዓመቱ ሐምሌ19 የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ንግሥ በአል በደመቀና በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን የምስራቅ ሐረረርጌ ዞን ፖሊስ ገልጿል።
በበዓለ ንግሱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ከአገር ውስጥና ከወጭ የመጡ ምዕመናን እና ሌሎች አንግዶች ታድመው ነበር።
በዘንድሮ ንግስ በዓል የስርቆት ወንጀል በፈፀመ ተጠርጣሪ ላይ በስፍራው የተቋቋመው ጊዜያዊ ፍርድ ቤት የሁለት አመት እስራት መወሰኑን ፖሊስ ገልጿል።
ዘንድሮ የተፈፀመው ስርቆት ወንጀል ከባለፉት ዓመታት ከተፈፀሙ የወንጀል ድርጊት እጅግ ማነሱን የፖሊስ ሪፖርት አመልክቷል።
በመንገድ ትራፊክ በኩልም ምንም ዓይነት የትራፊክ አደጋ አልደረሰም።
በሌላ በኩል ፤ በሀዋሳ ሐምሌ19 የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
በዓሉ ከወትሮው በተለየ ከፍተኛ የሰው ቁጥር የተገኘበት ነው።
በበዓሉ በርካታ ቁጥር ያላቸው ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የእምነቱ ተከታዮች እንዲሁም ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር የመጡ ጎብኚዎች፣ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች እና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች፣ የክልልና የሐዋሳ ከተማ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው የተከበረው።
እንደ ፖሊስ ሪፖርት በዓሉ ያለአንዳች የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሯል።
ከወንጀል ጋር በተያያዘ አንዲት የበዓሉ ታዳሚ ላይ የሞባይል ስርቆት የፈጸመ ተጠርጣሪ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በጊዜያዊነት በተቋቋመው ችሎት ማስረጃ ቀርቦበት የ2 ዓመት እስራት ቅጣት ተላልፎበታል። የተሰረቀውን ሞባይል ለግለሰቧ ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ ገልጿል።
Photo Credit : የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ ENA
@tikvahethiopia
በየዓመቱ ሐምሌ19 የሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ንግሥ በአል በደመቀና በሰላማዊ ሁኔታ መጠናቀቁን የምስራቅ ሐረረርጌ ዞን ፖሊስ ገልጿል።
በበዓለ ንግሱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ከአገር ውስጥና ከወጭ የመጡ ምዕመናን እና ሌሎች አንግዶች ታድመው ነበር።
በዘንድሮ ንግስ በዓል የስርቆት ወንጀል በፈፀመ ተጠርጣሪ ላይ በስፍራው የተቋቋመው ጊዜያዊ ፍርድ ቤት የሁለት አመት እስራት መወሰኑን ፖሊስ ገልጿል።
ዘንድሮ የተፈፀመው ስርቆት ወንጀል ከባለፉት ዓመታት ከተፈፀሙ የወንጀል ድርጊት እጅግ ማነሱን የፖሊስ ሪፖርት አመልክቷል።
በመንገድ ትራፊክ በኩልም ምንም ዓይነት የትራፊክ አደጋ አልደረሰም።
በሌላ በኩል ፤ በሀዋሳ ሐምሌ19 የሚከበረው የቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።
በዓሉ ከወትሮው በተለየ ከፍተኛ የሰው ቁጥር የተገኘበት ነው።
በበዓሉ በርካታ ቁጥር ያላቸው ከተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የመጡ የእምነቱ ተከታዮች እንዲሁም ከሀገር ውስጥና ከውጭ ሀገር የመጡ ጎብኚዎች፣ ታላላቅ የሀይማኖት አባቶች እና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች፣ የክልልና የሐዋሳ ከተማ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት ነው የተከበረው።
እንደ ፖሊስ ሪፖርት በዓሉ ያለአንዳች የፀጥታ ችግር በሰላም ተከብሯል።
ከወንጀል ጋር በተያያዘ አንዲት የበዓሉ ታዳሚ ላይ የሞባይል ስርቆት የፈጸመ ተጠርጣሪ ግለሰብ እጅ ከፍንጅ ተይዞ በጊዜያዊነት በተቋቋመው ችሎት ማስረጃ ቀርቦበት የ2 ዓመት እስራት ቅጣት ተላልፎበታል። የተሰረቀውን ሞባይል ለግለሰቧ ማስመለስ መቻሉን ፖሊስ ገልጿል።
Photo Credit : የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ ENA
@tikvahethiopia
#MyMusicShop
🎼 Box Guitar, Lead Guitar, Bass guitar.
🎼 Keybord for Bigginers, for Stage & Midi keybord.
🎼 Home/Studio/recording equipments.
🎼 Different kinds of musical instruments & accessories are avial with us!
ለበለጠ መረጃ፦ 0911192909 or 0939854210 ወይም በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/dagmusical
Join በማድረግ ይጎበኙን ! @dagmusical
አድራሻ፦📍መገናኛ ዘፍመሽ ግራንድ ሞል 3ተኛ ፎቅ #325 ላይ እንገኛለን
🎼 Box Guitar, Lead Guitar, Bass guitar.
🎼 Keybord for Bigginers, for Stage & Midi keybord.
🎼 Home/Studio/recording equipments.
🎼 Different kinds of musical instruments & accessories are avial with us!
ለበለጠ መረጃ፦ 0911192909 or 0939854210 ወይም በቴሌግራም ቻናላችን https://t.iss.one/dagmusical
Join በማድረግ ይጎበኙን ! @dagmusical
አድራሻ፦📍መገናኛ ዘፍመሽ ግራንድ ሞል 3ተኛ ፎቅ #325 ላይ እንገኛለን
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
የቅዱስነታቸው የአሜሪካ ጉዞ !
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ አሜሪካ ጉዞ ላይ ናቸው።
ከጥቂት ቀናት በፊት ለህክምና ጉዳይ ከሀገር እንደሚወጡ ገልፀው የነበሩት ቅዱስነታቸው ትላንት ምሽት ነው የአሜሪካ ጉዟቸውን የጀመሩት።
ትላንት ምሽት ከኢትዮጵያ የተነሱት ቅዱስነታቸው ዛሬ ማክሰኞ #ምሽት ቨርጂንያ ዳላስ ኤርፖርት ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ አሜሪካ ጉዞ ላይ ናቸው።
ከጥቂት ቀናት በፊት ለህክምና ጉዳይ ከሀገር እንደሚወጡ ገልፀው የነበሩት ቅዱስነታቸው ትላንት ምሽት ነው የአሜሪካ ጉዟቸውን የጀመሩት።
ትላንት ምሽት ከኢትዮጵያ የተነሱት ቅዱስነታቸው ዛሬ ማክሰኞ #ምሽት ቨርጂንያ ዳላስ ኤርፖርት ይደርሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቅዱስነታቸው የአሜሪካ ጉዞ ! ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ አሜሪካ ጉዞ ላይ ናቸው። ከጥቂት ቀናት በፊት ለህክምና ጉዳይ ከሀገር እንደሚወጡ ገልፀው የነበሩት ቅዱስነታቸው ትላንት ምሽት ነው የአሜሪካ ጉዟቸውን የጀመሩት። ትላንት ምሽት ከኢትዮጵያ የተነሱት ቅዱስነታቸው ዛሬ ማክሰኞ #ምሽት ቨርጂንያ ዳላስ…
" አጠቃላይ ሂደቱ ህግን የተከተለ ነበር "
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ትላንት ምሽት የአሜሪካ ጉዟቸውን ለማድረግ በአዲስ አበባ ኤርፖርት በተገኙበት ወቅት " ከቅዱስነታቸው ጋር ሕገ ወጥ ቅርስ ከሀገር ሊሸሽ ሲል ተያዘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ተገልጿል።
ቅዱስነታቸው ሁለት ጽላቶችን ፣ 3 የብር የእጅ መስቀሎችን (የግል ንብረታቸውንና ስማቸው የተፃፈባቸውን) ፣ 5 አዲስ እትም የግእዝ መጽሐፍ ቅዱስ እና አንድ ሊትር ቅብዓ ሜሮን ይዘው ለመሄድ ለቦሌ ኤርፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተጻፈ ደብዳቤ ጥያቄ ቅርቦ ነበር።
አጠቃላይ ሂደቱም ህግን የተከተለ እንደነበር ተገልጿል።
ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ተፈቅደው በአድራሻ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የተጻፈ ሕጋዊ ደብዳቤ ያለ እና ሂደቱ ትክክለኛ ነው።
ስለሂደቱ ሕጋዊነት ሚገልፁ የሰነድ ማስረጃዎችም አሉ።
ይህ ሆኖ ሳለ በተለያዩ ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች በሰበር ዜና እየተላለፈ የሚገኘው " በአባቶች ሻንጣ ውስጥ ተደብቀው የነበሩ ቅርሶች ተያዙ " የሚሉ መረጃዎች መሰረተ ቢስ መሆናቸው ተገልጿል።
ቅዱስ ፓትርያርኩ ለአገልግሎት ይዘዋቸው የሚጓዙ ንዋያተ ቅድሳት ሲሆኑ ህጋዊ ሰነዶች የተዘጋጁላቸው ናቸው።
Credit : TMC
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ትላንት ምሽት የአሜሪካ ጉዟቸውን ለማድረግ በአዲስ አበባ ኤርፖርት በተገኙበት ወቅት " ከቅዱስነታቸው ጋር ሕገ ወጥ ቅርስ ከሀገር ሊሸሽ ሲል ተያዘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ተገልጿል።
ቅዱስነታቸው ሁለት ጽላቶችን ፣ 3 የብር የእጅ መስቀሎችን (የግል ንብረታቸውንና ስማቸው የተፃፈባቸውን) ፣ 5 አዲስ እትም የግእዝ መጽሐፍ ቅዱስ እና አንድ ሊትር ቅብዓ ሜሮን ይዘው ለመሄድ ለቦሌ ኤርፖርት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በተጻፈ ደብዳቤ ጥያቄ ቅርቦ ነበር።
አጠቃላይ ሂደቱም ህግን የተከተለ እንደነበር ተገልጿል።
ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት እና ከብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤት ተፈቅደው በአድራሻ ለሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የተጻፈ ሕጋዊ ደብዳቤ ያለ እና ሂደቱ ትክክለኛ ነው።
ስለሂደቱ ሕጋዊነት ሚገልፁ የሰነድ ማስረጃዎችም አሉ።
ይህ ሆኖ ሳለ በተለያዩ ማኅበራዊ ድኅረ ገጾች በሰበር ዜና እየተላለፈ የሚገኘው " በአባቶች ሻንጣ ውስጥ ተደብቀው የነበሩ ቅርሶች ተያዙ " የሚሉ መረጃዎች መሰረተ ቢስ መሆናቸው ተገልጿል።
ቅዱስ ፓትርያርኩ ለአገልግሎት ይዘዋቸው የሚጓዙ ንዋያተ ቅድሳት ሲሆኑ ህጋዊ ሰነዶች የተዘጋጁላቸው ናቸው።
Credit : TMC
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" አጠቃላይ ሂደቱ ህግን የተከተለ ነበር " ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ትላንት ምሽት የአሜሪካ ጉዟቸውን ለማድረግ በአዲስ አበባ ኤርፖርት በተገኙበት ወቅት " ከቅዱስነታቸው ጋር ሕገ ወጥ ቅርስ ከሀገር ሊሸሽ ሲል ተያዘ " እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጨው መረጃ ሀሰተኛ መሆኑ ተገልጿል። ቅዱስነታቸው…
#ነገ_መግለጫ_ይሰጣል !
በቅዱስ ፓትርያርኩ ጉዞ ላይ በቦሌ ኤርፖርት በተፈፀመው አሳዛኝ ድርጊት ጋር ተያይዞ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነገው ዕለት ቀን 8:30 መግለጫ እንደሚሰጡ ታውቋል።
ብፁዕነታቸው ስለተፈፀመው ድርጊት መረጃውን እንደሰሙትና እንዳሳዘናቸው በመግለጽ ወጡ የተባሉት ጽላትና ንዋያተ ቅድሳት በሕጋዊ መንገድ መውጣታቸውንና ለዚህም ሕጋዊ ፍቃድ መያዛቸውን ተናግረዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም ይህ ለአዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ ድርብ ለሚፈልጉ አብያተ ክርስቲያናት በሀገረ ስብከታቸው ጥያቄ መሰረት በመንበረ ፓትርያርክ ፍቃድ የሚሰጥ አስቀድሞ የነበረ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አሠራር ነው ብለዋል።
#EOTC_TV
@tikvahethiopia
በቅዱስ ፓትርያርኩ ጉዞ ላይ በቦሌ ኤርፖርት በተፈፀመው አሳዛኝ ድርጊት ጋር ተያይዞ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በነገው ዕለት ቀን 8:30 መግለጫ እንደሚሰጡ ታውቋል።
ብፁዕነታቸው ስለተፈፀመው ድርጊት መረጃውን እንደሰሙትና እንዳሳዘናቸው በመግለጽ ወጡ የተባሉት ጽላትና ንዋያተ ቅድሳት በሕጋዊ መንገድ መውጣታቸውንና ለዚህም ሕጋዊ ፍቃድ መያዛቸውን ተናግረዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም ይህ ለአዳዲስ አብያተ ክርስቲያናትም ሆነ ድርብ ለሚፈልጉ አብያተ ክርስቲያናት በሀገረ ስብከታቸው ጥያቄ መሰረት በመንበረ ፓትርያርክ ፍቃድ የሚሰጥ አስቀድሞ የነበረ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አሠራር ነው ብለዋል።
#EOTC_TV
@tikvahethiopia
#ትውልድእንገንባ
የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በጦርነት ሳቢያ ተቋርጦ የቆየው ዓመታዊው የመማሪያ መፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ በዚህ ዓመት እየተካሄደ ይገኛል።
የዚህኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ ትኩረቱን በአዲስ አበባ ያደረገ ሲሆን ከ5ኛው ዓመት የተቋረጠ ነው። እስካሁን ባለው በርከት ያሉ የቤተሰባችን አባላት መፅሀፍ አስረክበዋል።
በሌላ በኩል ፤ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትን የ5ኛ ዓመት ጉዞን ምክንያት በማድረግ በመላው ቤተሰቡ ስም በመጀመሪያ ዙር ግምቱ 25 ሺህ ብር የሆነ 521 መደበኛ እና 192 አጋዥ መፅሀፍ ማበርከት ተችሏል።
ዓመታዊው የመማሪያ መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ የሚቀጥል ሲሆን እንዳለፉት ዓመታት ስራዎች መፅሀፉ የሚበረከተው ከከተማ ወጣ ባሉ የገጠር ት/ቤቶች ነው።
ቤታችሁ ውስጥ ያሉትን የመማሪያ መፀሀፍ (ከKG - 12ኛ ክፍል) መስጠት የምትፈልጉ የአዲስ አበባ ቤተሰቦቻችን በያላችሁበት አካባቢ እየመጣን መፅሀፉን የምንረከባችሁ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎች @tikvahuniversity ላይ እንዲሁም @tikvahethmagazine / @tikvahethiopiaBOT ላይ ታገኛላችሁ።
@tikvahethiopia
የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በኮቪድ-19 ወረርሽኝ እና በጦርነት ሳቢያ ተቋርጦ የቆየው ዓመታዊው የመማሪያ መፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ በዚህ ዓመት እየተካሄደ ይገኛል።
የዚህኛው ዓመት የመማሪያ መፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ ትኩረቱን በአዲስ አበባ ያደረገ ሲሆን ከ5ኛው ዓመት የተቋረጠ ነው። እስካሁን ባለው በርከት ያሉ የቤተሰባችን አባላት መፅሀፍ አስረክበዋል።
በሌላ በኩል ፤ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትን የ5ኛ ዓመት ጉዞን ምክንያት በማድረግ በመላው ቤተሰቡ ስም በመጀመሪያ ዙር ግምቱ 25 ሺህ ብር የሆነ 521 መደበኛ እና 192 አጋዥ መፅሀፍ ማበርከት ተችሏል።
ዓመታዊው የመማሪያ መፅሀፍት ማሰባሰብ ዘመቻ የሚቀጥል ሲሆን እንዳለፉት ዓመታት ስራዎች መፅሀፉ የሚበረከተው ከከተማ ወጣ ባሉ የገጠር ት/ቤቶች ነው።
ቤታችሁ ውስጥ ያሉትን የመማሪያ መፀሀፍ (ከKG - 12ኛ ክፍል) መስጠት የምትፈልጉ የአዲስ አበባ ቤተሰቦቻችን በያላችሁበት አካባቢ እየመጣን መፅሀፉን የምንረከባችሁ ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎች @tikvahuniversity ላይ እንዲሁም @tikvahethmagazine / @tikvahethiopiaBOT ላይ ታገኛላችሁ።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቅዱስነታቸው የአሜሪካ ጉዞ ! ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ አሜሪካ ጉዞ ላይ ናቸው። ከጥቂት ቀናት በፊት ለህክምና ጉዳይ ከሀገር እንደሚወጡ ገልፀው የነበሩት ቅዱስነታቸው ትላንት ምሽት ነው የአሜሪካ ጉዟቸውን የጀመሩት። ትላንት ምሽት ከኢትዮጵያ የተነሱት ቅዱስነታቸው ዛሬ ማክሰኞ #ምሽት ቨርጂንያ ዳላስ…
#Update
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰሜን አሜሪካ ደርሰዋል ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ሰኔ 10 ቀን 2014 ዓመተ ምሕረት በወሰነው መሠረት ለሕክምና ሐምሌ 18 2014 ዓመተ ምህረት ወደ ሰሜን አሜሪካን የተጓዙት ብፁዕ ወቅዱስነታቸው በትናንትናው ዕለት በሰላም ገብተዋል።
የሕክምና ክትትላቸውንም በተያዘው መርሐ ግብር መሠረት በዛሬው ዕለት የሚጀምሩ ሲሆን ከሕክምናው ጋር ተያያዥ የሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን በተመለከተ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በቀጣይ ይገለፃል ተብሏል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ወደ ሰሜን አሜሪካ ደርሰዋል ።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ሰኔ 10 ቀን 2014 ዓመተ ምሕረት በወሰነው መሠረት ለሕክምና ሐምሌ 18 2014 ዓመተ ምህረት ወደ ሰሜን አሜሪካን የተጓዙት ብፁዕ ወቅዱስነታቸው በትናንትናው ዕለት በሰላም ገብተዋል።
የሕክምና ክትትላቸውንም በተያዘው መርሐ ግብር መሠረት በዛሬው ዕለት የሚጀምሩ ሲሆን ከሕክምናው ጋር ተያያዥ የሆኑ ዝርዝር ጉዳዮችን በተመለከተ አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ በቀጣይ ይገለፃል ተብሏል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
#Ethiopia
በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ የ44 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሬታ ሰዋሰው እና የልማት ባንኩ የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ልማትና የቢዝነስ አቅርቦት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱል ካማራ ናቸው።
የመጀመሪያው የ40 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ ፈተናዎችን በመቋቋም የምግብ ዋስትና ማረጋገጥን አላማ ላደረገ መርሃ ግብር ተፈጻሚነት የሚውል ነው።
የተቀረው 4. 4 ሚሊዮን ዶላር የማክሮኢኮኖሚ አስተዳደር አቅምን የማጠናከር ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ እንደሚውል የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።
#ENA
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ግሩፕ የ44 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ስምምነቶችን ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሬታ ሰዋሰው እና የልማት ባንኩ የምስራቅ አፍሪካ ቀጠናዊ ልማትና የቢዝነስ አቅርቦት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር አብዱል ካማራ ናቸው።
የመጀመሪያው የ40 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት በምስራቅ አፍሪካ ፈተናዎችን በመቋቋም የምግብ ዋስትና ማረጋገጥን አላማ ላደረገ መርሃ ግብር ተፈጻሚነት የሚውል ነው።
የተቀረው 4. 4 ሚሊዮን ዶላር የማክሮኢኮኖሚ አስተዳደር አቅምን የማጠናከር ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ እንደሚውል የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።
#ENA
@tikvahethiopia
ልጆቻችን እየመጡ ነው❤️
በአትሌቲክሱ ዘርፍ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ከፍ ያደረጉት ያስከበሩት የሀገራችን ልጆች ዛሬ ምሽት ኢትዮጵያ ይገባሉ።
የአትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድናችን ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
በስካይ ላይት ሆቴልም ያርፋል።
ነገ ሀሙስ ሐምሌ 21/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ ካረፈበት ስካይላይት ሆቴል ተነስቶ ፦ በእስጢፋኖስ ፣ 4 ኪሎ ፣ ፒያሳ ፣ ቸርችል አድርጎ በለገሀር ወደ መስቀል አደባባይ በመሄድ ደስታቸውን ለህዝቡ ይገልፃሉ።
በመቀጠልም በቤተ መንግስት ከፍተኛ የሀገሪቱ መሪዎች በተገኙበት የእውቅናና የማበረታቻ ፕሮግራም ይደረጋል።
@tikvahethiopia
በአትሌቲክሱ ዘርፍ ኢትዮጵያን በዓለም መድረክ ከፍ ያደረጉት ያስከበሩት የሀገራችን ልጆች ዛሬ ምሽት ኢትዮጵያ ይገባሉ።
የአትሌቲክስ ብሔራዊ ቡድናችን ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 20/2014 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ላይ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቃል።
በስካይ ላይት ሆቴልም ያርፋል።
ነገ ሀሙስ ሐምሌ 21/2014 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ሰዓት ጀምሮ ካረፈበት ስካይላይት ሆቴል ተነስቶ ፦ በእስጢፋኖስ ፣ 4 ኪሎ ፣ ፒያሳ ፣ ቸርችል አድርጎ በለገሀር ወደ መስቀል አደባባይ በመሄድ ደስታቸውን ለህዝቡ ይገልፃሉ።
በመቀጠልም በቤተ መንግስት ከፍተኛ የሀገሪቱ መሪዎች በተገኙበት የእውቅናና የማበረታቻ ፕሮግራም ይደረጋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
እፀገነትን የገደሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ! የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የነበረችውን ወ/ሮ እፀገነት አንተነህን የገደሉ ሦስት #ተጠርጣሪዎች መያዙን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ ወ/ሮ እፀገነት አንተነህ መስከረም 6 ቀን 2012 ዓ.ም በግምት ከጠዋቱ 12 ሰዓት 30 አቃቂ ቃሊት ክፍለ ከተማ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቷ ወደ ስራ ለመሄድ ትራንስፖርት በመጠበቅ ላይ እንዳለች ሦስቱ ተጠርጣሪዎች ወንጀል…
#ተፈርዶባቸዋል
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የነበረችውን ወጣት እፀገነትን አንተነህ የገደሉ 3 ወንጀለኞች የ13 ዓመት ፅኑ እስራት እንደፈረደባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ግለሰቦቹ ከልዩ ከህዝባዊ መብቶቻቸው በተለይ ፦
- በምርጫ ላይ ተካፋይ ከመሆን ፣
- ለህዝብ አገልግሎት ስራ ከመመረጥ ፣
- በሰነድ ወይም የውል ስምምነት ላይ ምስክር ከመሆን ፣
- በቤተ ዘመድ ካለው መብት በተለይም የወላጅነት ስልጣን ከመያዝ ችሎታ ፣
- ከሞግዚትነት እና የንግድ ፈቃድ የሚያስፈልገውን የሙያ ፣
- የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ ስራ ከመስራት መብታቸው ለአምስት ዓመት እንዲሻሩ ፍርድ ቤት እንደወሰነባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
የእፀገነት ጉዳይ ጉዳይ ለማስታወሻ ፦
👉 https://t.iss.one/tikvahethiopia/39362
👉 https://t.iss.one/tikvahethiopia/39871
@tikvahethiopia
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የነበረችውን ወጣት እፀገነትን አንተነህ የገደሉ 3 ወንጀለኞች የ13 ዓመት ፅኑ እስራት እንደፈረደባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ግለሰቦቹ ከልዩ ከህዝባዊ መብቶቻቸው በተለይ ፦
- በምርጫ ላይ ተካፋይ ከመሆን ፣
- ለህዝብ አገልግሎት ስራ ከመመረጥ ፣
- በሰነድ ወይም የውል ስምምነት ላይ ምስክር ከመሆን ፣
- በቤተ ዘመድ ካለው መብት በተለይም የወላጅነት ስልጣን ከመያዝ ችሎታ ፣
- ከሞግዚትነት እና የንግድ ፈቃድ የሚያስፈልገውን የሙያ ፣
- የኢንዱስትሪ ወይም የንግድ ስራ ከመስራት መብታቸው ለአምስት ዓመት እንዲሻሩ ፍርድ ቤት እንደወሰነባቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
የእፀገነት ጉዳይ ጉዳይ ለማስታወሻ ፦
👉 https://t.iss.one/tikvahethiopia/39362
👉 https://t.iss.one/tikvahethiopia/39871
@tikvahethiopia