TIKVAH-ETHIOPIA
#SeriLanka • ፕሬዜዳንት ጎታብያ ራጃፓክሳ ሀገር ለቀው ወደ ማልዴቪስ ሄደዋል። • " ፕሬዜዳንቱ ስልጣን መልቀቃቸውን በይፋዊ ደብዳቤ ካላሳወቁ / ወጥተው ካልተናገሩ ከቤታቸው አንወጣም " - ተቃዋሚዎች ዓለምን እያነጋገረ ያለው የሲሪላንካ ጉዳይ አሁንም የቀጠለ ሲሆን ፕሬዜዳንት ጎታብያ ራጃፓክሳ ሀገር ለቀው መሄዳቸው ተሰምቷል። ፕሬዜዳንቱ ከሚስት እና 2 የግል ጠባቂዎቻቸው ጋር በሀገሪቱ የአየር…
#Update
ከሀገራቸው የተሰደዱት የስሪላንካ ፕሬዝዳንት ጎታብያ ራጃፓክሳ ከስልጣን መልቀቃቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለሀገሪቱ አፈ ጉባኤ ልከዋል።
@tikvahethiopia
ከሀገራቸው የተሰደዱት የስሪላንካ ፕሬዝዳንት ጎታብያ ራጃፓክሳ ከስልጣን መልቀቃቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ለሀገሪቱ አፈ ጉባኤ ልከዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert አቶ ምትኩ ካሳ በቁጥጥር ስር ዋሉ። የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር የነበሩት አቶ ምትኩ ካሳ በቁጥጥር ስር ዋሉ። ኮሚሽነሩ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ነው ዛሬ በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር የዋሉት። በፌደራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የሙስና ወንጀሎች ምርመራ መምሪያ ሃላፊ ረዳት ኮሚሽነር ታደሰ አያሌው እንደገለጹት፥ ኮሚሽነሩ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኤልሻዳይ…
የአቶ ምትኩ ካሳ ጉዳይ !
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ ትላንት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉ ይታወቃል።
አቶ ምትኩ ከኤልሻዳይ የበጎ አድራጎት ማህበር ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል በሚል ነው የታሰሩት።
ፖሊስ የእሳቸውን ጉዳይ መከታተል ከጀመረ የቆየ ሲሆን (ከሁለት ዓመት በፊት) እስከዛሬ እንዴት ሳይታሰሩ ሊቆዩ ቻሉ ? የሚለውን በተመለከተ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያበሰጡት ቃል ተከታዩን ብለዋል ፦
" ፖሊስ በ2012 ዓ/ም አካባቢ ነው ጉዳዩን ያጣራው ፤ እስከዛ ግን የመንግስት ውሳኔ ስለሚያስፈልገው ፖሊስ አጣርቶ ጨርሶ እሳቸው ሳይያዙ የቆዩት በዚህ ምክንያት ተጓቶ ነው አሁን ላይ የደረሰው አሁን ውሳኔ ስለተሠጠ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል "
ዛሬ አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤት የቀረቡት ከልጃቸው ጋር ነው ፦ https://telegra.ph/Trial-07-14-2
በሌላ በኩል፤ ከአቶ ምትኩ ጋር ተመሳጥረው ተፈናቃዮች በሌሉበት ተፈናቃዮች አሉ በማለት በተደጋጋሚ የእርዳት እህል እና አልባሳት በመረከብ ለሽያጭ አውለዋል የተባሉ የኤልሻዳይ ኃላፊዎች በፖሊስ እየተፈለጉ ነው ተብሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር ምትኩ ካሳ ትላንት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ማድረጉ ይታወቃል።
አቶ ምትኩ ከኤልሻዳይ የበጎ አድራጎት ማህበር ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈፅመዋል በሚል ነው የታሰሩት።
ፖሊስ የእሳቸውን ጉዳይ መከታተል ከጀመረ የቆየ ሲሆን (ከሁለት ዓመት በፊት) እስከዛሬ እንዴት ሳይታሰሩ ሊቆዩ ቻሉ ? የሚለውን በተመለከተ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጄይላን አብዲ ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያበሰጡት ቃል ተከታዩን ብለዋል ፦
" ፖሊስ በ2012 ዓ/ም አካባቢ ነው ጉዳዩን ያጣራው ፤ እስከዛ ግን የመንግስት ውሳኔ ስለሚያስፈልገው ፖሊስ አጣርቶ ጨርሶ እሳቸው ሳይያዙ የቆዩት በዚህ ምክንያት ተጓቶ ነው አሁን ላይ የደረሰው አሁን ውሳኔ ስለተሠጠ በቁጥጥር ስር ሊውሉ ችለዋል "
ዛሬ አቶ ምትኩ ካሳ ፍርድ ቤት የቀረቡ ሲሆን ፍርድ ቤት የቀረቡት ከልጃቸው ጋር ነው ፦ https://telegra.ph/Trial-07-14-2
በሌላ በኩል፤ ከአቶ ምትኩ ጋር ተመሳጥረው ተፈናቃዮች በሌሉበት ተፈናቃዮች አሉ በማለት በተደጋጋሚ የእርዳት እህል እና አልባሳት በመረከብ ለሽያጭ አውለዋል የተባሉ የኤልሻዳይ ኃላፊዎች በፖሊስ እየተፈለጉ ነው ተብሏል።
@tikvahethiopia
ጋምቤላ - ሰዓት እላፊ !
በጋምቤላ ከተማ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሕገወጥ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የሰዓት እላፊ ተጥሎ እንደነበር ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ለማህበረሰቡ ደህንነት ታስቦ የተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ክፍተት መታየቱን ተገልጿል።
በዙህም በከተማው የሰዎች እና የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴን በመለየት ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ንጋቱ 11፡30 ድረስ የተጣለው ገደብ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።
ከአንቡላንስና ከፀጥታ ሀይል ተሽከርካሪ በስተቀር ማንኛውም ተሽከርካሪና ሰዎች መንቀሳቀስ የሚችሉት ከንጋቱ 11፡30 እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት መሆኑ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
በአሁኑ ወቅት በጋምቤላ ከተማ ሰላማዊ ሁኔታ መኖሩ የተገለፀ ሲሆን በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች የተጠናከረ ጥበቃ እያደረጉ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ በየአካባቢው ተደራጅቶ መረጃ በመስጠት እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
በጋምቤላ ከተማ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ሕገወጥ እንቅስቃሴን ለመቆጣጠር የሰዓት እላፊ ገደብ መጣሉን የክልሉ መንግስት አስታውቋል።
ከዚህ ቀደም በጋምቤላ ከተማ ተከስቶ በነበረው የፀጥታ መደፍረስ ምክንያት የሰዓት እላፊ ተጥሎ እንደነበር ይታወሳል።
ይሁን እንጂ ለማህበረሰቡ ደህንነት ታስቦ የተጣለው የሰዓት እላፊ ገደብ ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ክፍተት መታየቱን ተገልጿል።
በዙህም በከተማው የሰዎች እና የተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴን በመለየት ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ ንጋቱ 11፡30 ድረስ የተጣለው ገደብ ተግባራዊ ሊደረግ ይገባል ተብሏል።
ከአንቡላንስና ከፀጥታ ሀይል ተሽከርካሪ በስተቀር ማንኛውም ተሽከርካሪና ሰዎች መንቀሳቀስ የሚችሉት ከንጋቱ 11፡30 እስከ ምሽቱ 2 ሰዓት መሆኑ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
በአሁኑ ወቅት በጋምቤላ ከተማ ሰላማዊ ሁኔታ መኖሩ የተገለፀ ሲሆን በየደረጃው የሚገኙ የጸጥታ ሃይሎች የተጠናከረ ጥበቃ እያደረጉ ነው ተብሏል።
ህብረተሰቡ በየአካባቢው ተደራጅቶ መረጃ በመስጠት እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
መረጃው የጋምቤላ ክልል ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ አልዓዛር ተረፈ ታሰረ።
የ " አል አይን ኒውስ " የኢትዮጵያ ዘጋቢ መታሰሩን ለማወቅ ችለናል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መገናኛ ብዙሃን ለሆነው " አል አይን ኒውስ " በዘጋቢነት የሚሰራው ጋዜጠኛ አልዓዛር ተረፈ ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 7 ከሰዓት ሲቪል በለበሱ ጸጥታ ኃይሎች መያዙን ባለቤቱ እና ባልደረባው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት ገልፀዋል።
ጋዜጠኛው በጸጥታ አካላት ከተያዘ በኋላ በአዲስ አበባ ላምበረት አካባቢ ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዱን አመልክተዋል።
አልዓዛርን በታሰረበት ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ የጎበኘው ባልደረባው ዳዊት በጋሻው፤ ጋዜጠኛው የተያዘው ላምበረት መናኸሪያ አካባቢ ከሚገኝ ካፌ እንደሆነ ገልጿል።
የሲቪል ልብስ የለበሱ ሁለት ግለሰቦች ጋዜጠኛውን መታወቂያ እንዲያሳያቸው እንደጠየቁት እና " እንፈልግሃለን " ብለው እንደወሰዱት የዓይን እማኞች ነግረውኛል ብሏል።
ሁለቱ ግለሰቦች አልዓዛርን በያዙበት ወቅት " ለችግኝ ተከላ ጥሩ አመለካከት የለህም፤ ‘ቤተ መንግስት ገብተን፤ በደም የበቀለውን ችግኝ እንነቅላለን’ ብለሃል " በሚል ሲወነጅሉት መሰማታቸውን ጋዜጠኛ ዳዊት ተናግሯል።
" አል ዓይን ኒውስ " የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መገናኛ ብዙሃን ሲሆን በአማርኛ አገልግሎት ክፍሉ በኩል በተለይ የውጭ ሀገር መረጃዎችን እንዲሁም የሀገር ውስጥ መረጃዎችን በማቅረብ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
የ " አል አይን ኒውስ " የኢትዮጵያ ዘጋቢ መታሰሩን ለማወቅ ችለናል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መገናኛ ብዙሃን ለሆነው " አል አይን ኒውስ " በዘጋቢነት የሚሰራው ጋዜጠኛ አልዓዛር ተረፈ ዛሬ ሐሙስ ሐምሌ 7 ከሰዓት ሲቪል በለበሱ ጸጥታ ኃይሎች መያዙን ባለቤቱ እና ባልደረባው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት ገልፀዋል።
ጋዜጠኛው በጸጥታ አካላት ከተያዘ በኋላ በአዲስ አበባ ላምበረት አካባቢ ወደሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ መወሰዱን አመልክተዋል።
አልዓዛርን በታሰረበት ፖሊስ ጣቢያ በመሄድ የጎበኘው ባልደረባው ዳዊት በጋሻው፤ ጋዜጠኛው የተያዘው ላምበረት መናኸሪያ አካባቢ ከሚገኝ ካፌ እንደሆነ ገልጿል።
የሲቪል ልብስ የለበሱ ሁለት ግለሰቦች ጋዜጠኛውን መታወቂያ እንዲያሳያቸው እንደጠየቁት እና " እንፈልግሃለን " ብለው እንደወሰዱት የዓይን እማኞች ነግረውኛል ብሏል።
ሁለቱ ግለሰቦች አልዓዛርን በያዙበት ወቅት " ለችግኝ ተከላ ጥሩ አመለካከት የለህም፤ ‘ቤተ መንግስት ገብተን፤ በደም የበቀለውን ችግኝ እንነቅላለን’ ብለሃል " በሚል ሲወነጅሉት መሰማታቸውን ጋዜጠኛ ዳዊት ተናግሯል።
" አል ዓይን ኒውስ " የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች መገናኛ ብዙሃን ሲሆን በአማርኛ አገልግሎት ክፍሉ በኩል በተለይ የውጭ ሀገር መረጃዎችን እንዲሁም የሀገር ውስጥ መረጃዎችን በማቅረብ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በህይወት ያለን ሰው ያቃጠሉት ግለሰቦች ምን ተደረጉ ? • ካቃጠሉት ውስጥ እስካሁን አራት የሚደርሱ አልተያዙም። • ወንጀሉን ከፈፀሙት ውስጥ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከድተው ጠፍተዋል፤ 2 የአማራ ልዩ ኃይል አባላት ለህግ እንዲሰጡ ለክልሉ ፖሊስ አመራሮች ተጠይቋል። • 3 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ ነው (ሁለት የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል አባላት አንድ ሲቪል)…
የፍትህ ሚኒስቴር የምርመራ ሪፖርት ምን ይላል ?
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር በመተባበር በሚያዚያ ወር ላይ በጎንደር ፣ በወራቤና በጂንካ አካባቢ በተከሰተ ግጭት ተፈፅመዋል ያላቸውን ወንጀሎች የምርመራ ግኝት ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ በሚያዚያ 2014 በጎንደር እና በወራቤ ሀይማኖትን መሰረት አድርጎ እንዲሁም በጂንካና አካባቢው ማንነትን መሰረት አድርጎ ተከስቷል ባለድ ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎችን የምርመራ ግኝት በዚህ ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Ministry-of-Justice-07-15
@tikvahethiopia
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር በመተባበር በሚያዚያ ወር ላይ በጎንደር ፣ በወራቤና በጂንካ አካባቢ በተከሰተ ግጭት ተፈፅመዋል ያላቸውን ወንጀሎች የምርመራ ግኝት ይፋ አድርጓል።
ሚኒስቴሩ በሚያዚያ 2014 በጎንደር እና በወራቤ ሀይማኖትን መሰረት አድርጎ እንዲሁም በጂንካና አካባቢው ማንነትን መሰረት አድርጎ ተከስቷል ባለድ ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎችን የምርመራ ግኝት በዚህ ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Ministry-of-Justice-07-15
@tikvahethiopia
#Ethiopia 🇪🇹
ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትካፈልበት ተጠባቂው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ ለሊት ይጀምራል።
ዛሬ ለሊት አትሌቶቻችን ውድድራቸውን ያካሂዳሉ።
በዚህም መሰረት :-
- ሌሊት 9:15 :- የወንዶች 3,000 ሜትር መሰናክል ማጣርያ
🇪🇹 ለሜቻ ግርማ
🇪🇹 ጌትነት ዋሌ
🇪🇹 ኃይለማሪያም አማረ
- ሌሊት 10:10 :- የሴቶች 1,500 ሜትር ማጣርያ
🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ
🇪🇹 ፍሬወይኒ ኃይሉ
🇪🇹 ሒሩት መሸሻ
የ " ኦሪጎን የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር " በDSTV ልዩ ቻናል እና ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ መዝናኛ ቻናሎች በቀጥታ መከታተል ይችላሉ ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ #ስፖርት https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x
@tikvahethsport
ሀገራችን ኢትዮጵያ የምትካፈልበት ተጠባቂው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር ዛሬ ለሊት ይጀምራል።
ዛሬ ለሊት አትሌቶቻችን ውድድራቸውን ያካሂዳሉ።
በዚህም መሰረት :-
- ሌሊት 9:15 :- የወንዶች 3,000 ሜትር መሰናክል ማጣርያ
🇪🇹 ለሜቻ ግርማ
🇪🇹 ጌትነት ዋሌ
🇪🇹 ኃይለማሪያም አማረ
- ሌሊት 10:10 :- የሴቶች 1,500 ሜትር ማጣርያ
🇪🇹 ጉዳፍ ፀጋይ
🇪🇹 ፍሬወይኒ ኃይሉ
🇪🇹 ሒሩት መሸሻ
የ " ኦሪጎን የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ውድድር " በDSTV ልዩ ቻናል እና ብሄራዊው ቴሌቪዥን ጣቢያ መዝናኛ ቻናሎች በቀጥታ መከታተል ይችላሉ ።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ #ስፖርት https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x
@tikvahethsport
#Kenya
የጎረቤት ኬንያ መንግስት ምንም እንኳን በዓለም አቀፉ ገበያ የነዳጅ ዋጋ ቢጨምርም በሀገሪቱ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል አዲስ የነዳጅ ድጎማ አድርጓል።
ይህ ውሳኔ ኬንያውያን በሌሎች መሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ካጋጠማቸው የዋጋ ጭማሪ በተጨማሪ ከሌላ የዋጋ ንረት ጋር ትግል ውስጥ እንዳይገቡ ነው ተብሏል።
መንግሥት ከወረሃዊ የዋጋ ማሻሻያ በፊት በነዳጅ ላይ ያደርግ የነበረው ድጎማ ሊያነሳ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቶ ነበር።
ይሁን እንጂ የአገሪቱ መንግሥት የውሳኔ ለውጥ በማድረግ አሁን ያለውን የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ለተጨማሪ 30 ቀናት ባለበት እንዲቀጥል የ141 ሚሊዮን ዶላር ድጎማ አድርጓል።
በሰኔ ወር ባለስጣናት አሁን እየተደረገ ያለው የነዳጅ ድጎማ ''ዘላቂነት የሌለው ነው" ብለው ነበር።
ባለፈው ዓመት ኬንያ በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መከሰቱን ተከትሎ ለነዳጅ ድጎማ ከ860 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ አድርጋለች።
ኬንያ በቀጠናው ካሉ አገራት ነዳጅ በውድ የምታቀርብ አገር ነች። ድጎማው ባይኖር ኖሮ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ አንድ ሊትር ቤንዚን 1.80 ዶላር (93 ብር ከ90 ሳንቲም) ይደርስ ነበር። አሁን ላይ ዋጋው 1.34 ዶላር (69 ብር 90 ሳንቲም) ነው።
ከኬንያ ቀጥሎ በአካባቢው በከፍተኛ ዋጋ ነዳጅ የሚገዛባቸው አገራት ሱዳንና ኡጋንዳ ናቸው።
ነዳጅ የምታመርተው ሱዳን ለ1 ሊትር 1.50 ዶላር (78 ብር ከ25 ሳንቲም) ስታስከፍል፣ በቅርቡ የነዳጅ ዘይት ያገኘችው ኡጋንዳ 1 ሊትር በ1.6 ዶላር (83 ብር 47 ሳንቲም) ታቀርባለች።
በአፍሪካ ነዳጅ በከፍተኛ ዋጋ ከሚሸጡባቸው አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ ተጠቃሽ ናት ፤ 1 ሊትር ነዳጅ የሚሸጠው በ1.48 ዶላር (77 ብር ከ21 ሳንቲም) መሆኑን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
የጎረቤት ኬንያ መንግስት ምንም እንኳን በዓለም አቀፉ ገበያ የነዳጅ ዋጋ ቢጨምርም በሀገሪቱ ያለውን የነዳጅ ዋጋ ባለበት እንዲቀጥል አዲስ የነዳጅ ድጎማ አድርጓል።
ይህ ውሳኔ ኬንያውያን በሌሎች መሠረታዊ የፍጆታ እቃዎች ላይ ካጋጠማቸው የዋጋ ጭማሪ በተጨማሪ ከሌላ የዋጋ ንረት ጋር ትግል ውስጥ እንዳይገቡ ነው ተብሏል።
መንግሥት ከወረሃዊ የዋጋ ማሻሻያ በፊት በነዳጅ ላይ ያደርግ የነበረው ድጎማ ሊያነሳ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቶ ነበር።
ይሁን እንጂ የአገሪቱ መንግሥት የውሳኔ ለውጥ በማድረግ አሁን ያለውን የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ ለተጨማሪ 30 ቀናት ባለበት እንዲቀጥል የ141 ሚሊዮን ዶላር ድጎማ አድርጓል።
በሰኔ ወር ባለስጣናት አሁን እየተደረገ ያለው የነዳጅ ድጎማ ''ዘላቂነት የሌለው ነው" ብለው ነበር።
ባለፈው ዓመት ኬንያ በዓለም ገበያ የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ መከሰቱን ተከትሎ ለነዳጅ ድጎማ ከ860 ሚሊየን ዶላር በላይ ወጪ አድርጋለች።
ኬንያ በቀጠናው ካሉ አገራት ነዳጅ በውድ የምታቀርብ አገር ነች። ድጎማው ባይኖር ኖሮ በኬንያ ዋና ከተማ ናይሮቢ አንድ ሊትር ቤንዚን 1.80 ዶላር (93 ብር ከ90 ሳንቲም) ይደርስ ነበር። አሁን ላይ ዋጋው 1.34 ዶላር (69 ብር 90 ሳንቲም) ነው።
ከኬንያ ቀጥሎ በአካባቢው በከፍተኛ ዋጋ ነዳጅ የሚገዛባቸው አገራት ሱዳንና ኡጋንዳ ናቸው።
ነዳጅ የምታመርተው ሱዳን ለ1 ሊትር 1.50 ዶላር (78 ብር ከ25 ሳንቲም) ስታስከፍል፣ በቅርቡ የነዳጅ ዘይት ያገኘችው ኡጋንዳ 1 ሊትር በ1.6 ዶላር (83 ብር 47 ሳንቲም) ታቀርባለች።
በአፍሪካ ነዳጅ በከፍተኛ ዋጋ ከሚሸጡባቸው አገራት መካከል ደቡብ አፍሪካ ተጠቃሽ ናት ፤ 1 ሊትር ነዳጅ የሚሸጠው በ1.48 ዶላር (77 ብር ከ21 ሳንቲም) መሆኑን ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ከ14ኛ ዙር የ20/80 እና ከ40/60 3ኛ ዙር እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ ከሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮና የቤቶች ቢሮ የተለያየ እርምጃ የተወሰደባቸው አመራሮችና ባለሙያዎችን ስም ዝርዝር ይፋ ተደረገ። በዚህም መሰረት፦ 1ኛ. ዶ/ር ሙሉቀን ሃፍቱ ቢሮ ሃላፊ ከሃላፊነታቸው የተነሱ በቁጥጥር ስር የዋሉ፡- 1ኛ. አብርሀም ሰርሞሎ የዘርፉ ምክትል ቢሮ ሃላፊ 2 ኛ . መብራቱ ወልደኪዳን፦…
" ያለመከሰስ መብታቸው ይነሳ "
የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ጥያቄ ቀረበ።
ጥያቄው መቅረቡ የተገለፀው በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው በ3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ጉባኤ ላይ ነው።
የፍትህ ሚኒስቴር #ከጋራ_መኖሪያ_ቤቶች እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባልና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ጥያቄ አቅርቧል፡፡
በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልቃድር ፤ የፍትህ ሚኒስቴር የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ እንዲነሳ ጥያቄ ማቅረቡን ተናግረዋል፡፡
የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት ይነሳልን ጥያቄው ከጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና የተሰጣቸውን ስልጣንና ሃላፊነት በአግባቡ ባለመጠቀም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለው እንዲጣራ ለማድረግ የቀረበ መሆኑንም አስረድተዋል።
(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር)
@tikvahethiopia
የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ጥያቄ ቀረበ።
ጥያቄው መቅረቡ የተገለፀው በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው በ3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ጉባኤ ላይ ነው።
የፍትህ ሚኒስቴር #ከጋራ_መኖሪያ_ቤቶች እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባልና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ጥያቄ አቅርቧል፡፡
በጉባኤው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የምክር ቤት አፈ ጉባኤ ቡዜና አልቃድር ፤ የፍትህ ሚኒስቴር የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ እንዲነሳ ጥያቄ ማቅረቡን ተናግረዋል፡፡
የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት ይነሳልን ጥያቄው ከጋራ መኖሪያ ቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና የተሰጣቸውን ስልጣንና ሃላፊነት በአግባቡ ባለመጠቀም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ውለው እንዲጣራ ለማድረግ የቀረበ መሆኑንም አስረድተዋል።
(የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ያለመከሰስ መብታቸው ይነሳ " የዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት እንዲነሳ ጥያቄ ቀረበ። ጥያቄው መቅረቡ የተገለፀው በአሁን ሰዓት እየተካሄደ በሚገኘው በ3ኛው የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 1ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 3ኛ እና የበጀት ዓመቱ ማጠቃለያ ጉባኤ ላይ ነው። የፍትህ ሚኒስቴር #ከጋራ_መኖሪያ_ቤቶች እጣ ማውጣት ጋር በተያያዘ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባልና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና…
#NewsAlert
የዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ /ያለመከሰስ መብት ተነሳ።
የደገፉ የምክር ቤት አባላት ፦ 93
ድምፀ ተአቅቦ ፦ 6
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል እና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ እንዲነሳ የተደረገው በፍትህ ሚኒስቴር በቀረበ ጥያቄ ነው።
የህግ ከለላው የተነሳው ከቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና የተሰጣቸውን ስልጣንና ሃላፊነት በአግባቡ ባለመጠቀም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለው እንዲጣራ ለማድረግ ነው።
@tikvahethiopia
የዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ /ያለመከሰስ መብት ተነሳ።
የደገፉ የምክር ቤት አባላት ፦ 93
ድምፀ ተአቅቦ ፦ 6
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል እና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ እንዲነሳ የተደረገው በፍትህ ሚኒስቴር በቀረበ ጥያቄ ነው።
የህግ ከለላው የተነሳው ከቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና የተሰጣቸውን ስልጣንና ሃላፊነት በአግባቡ ባለመጠቀም በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለው እንዲጣራ ለማድረግ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ /ያለመከሰስ መብት ተነሳ። የደገፉ የምክር ቤት አባላት ፦ 93 ድምፀ ተአቅቦ ፦ 6 የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት አባል እና የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የሆኑት ዶክተር ሙሉቀን ሀፍቱ የህግ ከለላ እንዲነሳ የተደረገው በፍትህ ሚኒስቴር በቀረበ ጥያቄ ነው። የህግ ከለላው የተነሳው ከቤቶች እጣ አወጣጥ ጋር በተያያዘ እና የተሰጣቸውን…
#የጋራ_መኖሪያ_ቤቶች #ፍትህሚኒስቴር
ፍትህ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በፃፈው ደብዳቤ ላይ (ከዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት መነሳት ጋር የተያያዘ) ፦
" ... ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ምሩፅ ለከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ቀርበው በሰጡት መግላጫ እንዲሁም በእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱ ላይ ለህዝብ በይፋ በሰጡት ማብራሪያ ቢሮው በአዋጅ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ቴክኖሎጂውን አልምቶ የጨረሰ በመሆኑ ቴክኖሎጂው ከሰው ንክኪ ነፃ በመሆኑና በኢንሳ በኩል ተፈትሾ ማረጋገጫ ያገኘ እንዲሁም ለዕጣው አወጣጥ ከባንክ የተላከው ዳታ በአግባቡ የተጫነ መሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተው ነበር።
መስተዳደሩም የኃላፊውን ማረጋገጫ በመቀበል እና በማመን ዕጣው ሐምሌ 1 በህዝብ ፊት እንዲወጣ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ከተሰጠው ማረጋገጫ በተቃራኒ ከፍተኛ ከፍተኛ የሆነ የዳታ ማጭበርበር ተግባር የተፈፀመ መሆኑ አመላካች መረጃ በማግኘት ኦዲት እንዲደረግ አቅጣጫ ተሰጥቶ እንዲፈተሽ ተደርጓል።
በዚህ መሰረት ከኢንሳ ፣ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና ከኢኖቬሽን ሚኒስቴር በተዋቀረው የባለሞያ ቡድን በተደረገው ማጣራት ፦
1ኛ. ሲስተሙ አዲስ እና የገባው ዳታ በማንም ያልታየ ለመሆኑ ለከተማው አመራር ጭምር በኃላፊው ማረጋገጫ የተሰጠ ቢሆንም ዕጣው ከመውጣቱ በፊት ወደ ኮምፒዩተሩ የገባውን ዳታ ለአምስት ጊዜ የተመለከቱ መሆኑ፤
2ኛ. ለዕጣ ብቁ ናቸው ተብሎ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተላከው 79 ሺህ ተመዝጋቢዎች በላይ ለዕጣው ብቁ ያልሆኑ 73 ሺህ ሰዎችን በድብቅ ወደ ኮምፒዩተሩ በመጫን የተጠቃሚዎችን ቁጥር ወደ 172 ሺህ እንዲያድግ ያደረጉ መሆኑ፤
3ኛ. ኃላፊው ከቤቶች ልማት የተላከውን የተወዳዳሪዎችን መረጃ ለሚያስገባ ባለሞያ ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ እንዲሰራ ማድረግ ሲገባቸው በቀጥታ ለአልሚው በመስጠት የዳታ ማጭበርበሩ እንዲፈፀም ያስደረጉ መሆኑ፤
4ኛ. ሲስተሙ የማልማት ተግባሩ አለም አቀፍ ስታንዳርዱን ያልጠበቀና የሚና መደበላለቅ የታየበት በተለይም ሶስቱን አካላት አልሚውን፣ የተጠቃሚውን እና አረጋጋጩን አካላት የሚና ክፍፍል የሌለበት እና ሁሉም በአንድ ሰው ማለትም በአልሚው ብቻ የተሰራ በመሆኑ አሁን ለተከሰተው ማጭበርበር በር እንዲከፍት ያደረገ መሆኑ፤
5ኛ. ዳታው የተጫነበት ኮምፒዩተር አዲስ እና የዳታ አጠቃቀሙን ከእጅ ንክኪ ነፃ እንዲሆን የሚፈልግ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኮምፒዩተሩ ለስራው የማይፈለግ ባዕድ ሶፍትዌር ጭምር የተጫነበት ከመሆኑ በላይ የዕጣ አወጣጥ ሂደቱን በኦንላይን ጭምር እንዲከታተሉ የሚያስችል የነበረ መሆኑ ፤
6ኛ. ስለደህንነቱ ምንም አይነት ፍተሻ ባልተደረገበት ቴክኖሎጂ በኢንሳ ተፈትሾ ችግር እንደሌለበት ማረጋገጫ የተሰጠበት ነው በሚል የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ የከተማ አስታዳደር አመራሩን በማሳሳት ዕጣ እንዲወጣ ያስደረጉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።
በአጠቃላይ ዕጣውን ለማውጣት ጥቅም ላይ የዋለው ቴክኖሎጂ ወይም ሲስተም የአሰራር ስርዓቱን ያልተከተለ፣ አግባብ ባለው ተቋም ያልታየና ምንም አይነት የደህንነት ማረጋገጫ ያልተሰጠበት፣ ለማጭበርበር የሚረዳ ባዕድ ሶፍትዌር የተጫነበት ፣ ለዕጣው ብቁ ናቸው ተብሎ ከሚመለከተው አካል ተረጋግጦ ከተላከው ዳታ ውጭ ሌላ ዳታ ማስገባት መረጃ መጨመር፣ ማጥፋት እንዲሁም ማስተካከል የሚያስችል እድል ለአልሚው በድብቅ የሚሰጥ ስለመሆኑ ማረጋገጥ ተችሏል።
ድርጊቱ በቢሮው ኃላፊ እና በስሩ የተሳተፉት ሌሎች ግለሰቦች የተፈፀመ መሆኑ ተረጋግጦ አብዛኛዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የወንጀል ምርመራ እየተደረገ ይገኛል። "
@tikvahethiopia
ፍትህ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በፃፈው ደብዳቤ ላይ (ከዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት መነሳት ጋር የተያያዘ) ፦
" ... ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ምሩፅ ለከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ቀርበው በሰጡት መግላጫ እንዲሁም በእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱ ላይ ለህዝብ በይፋ በሰጡት ማብራሪያ ቢሮው በአዋጅ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ቴክኖሎጂውን አልምቶ የጨረሰ በመሆኑ ቴክኖሎጂው ከሰው ንክኪ ነፃ በመሆኑና በኢንሳ በኩል ተፈትሾ ማረጋገጫ ያገኘ እንዲሁም ለዕጣው አወጣጥ ከባንክ የተላከው ዳታ በአግባቡ የተጫነ መሆኑ ማረጋገጫ ሰጥተው ነበር።
መስተዳደሩም የኃላፊውን ማረጋገጫ በመቀበል እና በማመን ዕጣው ሐምሌ 1 በህዝብ ፊት እንዲወጣ አድርጎ የነበረ ቢሆንም ከተሰጠው ማረጋገጫ በተቃራኒ ከፍተኛ ከፍተኛ የሆነ የዳታ ማጭበርበር ተግባር የተፈፀመ መሆኑ አመላካች መረጃ በማግኘት ኦዲት እንዲደረግ አቅጣጫ ተሰጥቶ እንዲፈተሽ ተደርጓል።
በዚህ መሰረት ከኢንሳ ፣ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት እና ከኢኖቬሽን ሚኒስቴር በተዋቀረው የባለሞያ ቡድን በተደረገው ማጣራት ፦
1ኛ. ሲስተሙ አዲስ እና የገባው ዳታ በማንም ያልታየ ለመሆኑ ለከተማው አመራር ጭምር በኃላፊው ማረጋገጫ የተሰጠ ቢሆንም ዕጣው ከመውጣቱ በፊት ወደ ኮምፒዩተሩ የገባውን ዳታ ለአምስት ጊዜ የተመለከቱ መሆኑ፤
2ኛ. ለዕጣ ብቁ ናቸው ተብሎ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከተላከው 79 ሺህ ተመዝጋቢዎች በላይ ለዕጣው ብቁ ያልሆኑ 73 ሺህ ሰዎችን በድብቅ ወደ ኮምፒዩተሩ በመጫን የተጠቃሚዎችን ቁጥር ወደ 172 ሺህ እንዲያድግ ያደረጉ መሆኑ፤
3ኛ. ኃላፊው ከቤቶች ልማት የተላከውን የተወዳዳሪዎችን መረጃ ለሚያስገባ ባለሞያ ሚስጢራዊነቱን ጠብቆ እንዲሰራ ማድረግ ሲገባቸው በቀጥታ ለአልሚው በመስጠት የዳታ ማጭበርበሩ እንዲፈፀም ያስደረጉ መሆኑ፤
4ኛ. ሲስተሙ የማልማት ተግባሩ አለም አቀፍ ስታንዳርዱን ያልጠበቀና የሚና መደበላለቅ የታየበት በተለይም ሶስቱን አካላት አልሚውን፣ የተጠቃሚውን እና አረጋጋጩን አካላት የሚና ክፍፍል የሌለበት እና ሁሉም በአንድ ሰው ማለትም በአልሚው ብቻ የተሰራ በመሆኑ አሁን ለተከሰተው ማጭበርበር በር እንዲከፍት ያደረገ መሆኑ፤
5ኛ. ዳታው የተጫነበት ኮምፒዩተር አዲስ እና የዳታ አጠቃቀሙን ከእጅ ንክኪ ነፃ እንዲሆን የሚፈልግ የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ኮምፒዩተሩ ለስራው የማይፈለግ ባዕድ ሶፍትዌር ጭምር የተጫነበት ከመሆኑ በላይ የዕጣ አወጣጥ ሂደቱን በኦንላይን ጭምር እንዲከታተሉ የሚያስችል የነበረ መሆኑ ፤
6ኛ. ስለደህንነቱ ምንም አይነት ፍተሻ ባልተደረገበት ቴክኖሎጂ በኢንሳ ተፈትሾ ችግር እንደሌለበት ማረጋገጫ የተሰጠበት ነው በሚል የተሳሳተ መረጃ በማቅረብ የከተማ አስታዳደር አመራሩን በማሳሳት ዕጣ እንዲወጣ ያስደረጉ መሆናቸውን ማረጋገጥ ተችሏል።
በአጠቃላይ ዕጣውን ለማውጣት ጥቅም ላይ የዋለው ቴክኖሎጂ ወይም ሲስተም የአሰራር ስርዓቱን ያልተከተለ፣ አግባብ ባለው ተቋም ያልታየና ምንም አይነት የደህንነት ማረጋገጫ ያልተሰጠበት፣ ለማጭበርበር የሚረዳ ባዕድ ሶፍትዌር የተጫነበት ፣ ለዕጣው ብቁ ናቸው ተብሎ ከሚመለከተው አካል ተረጋግጦ ከተላከው ዳታ ውጭ ሌላ ዳታ ማስገባት መረጃ መጨመር፣ ማጥፋት እንዲሁም ማስተካከል የሚያስችል እድል ለአልሚው በድብቅ የሚሰጥ ስለመሆኑ ማረጋገጥ ተችሏል።
ድርጊቱ በቢሮው ኃላፊ እና በስሩ የተሳተፉት ሌሎች ግለሰቦች የተፈፀመ መሆኑ ተረጋግጦ አብዛኛዎቹ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን የወንጀል ምርመራ እየተደረገ ይገኛል። "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#የጋራ_መኖሪያ_ቤቶች #ፍትህሚኒስቴር ፍትህ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ምክር ቤት በፃፈው ደብዳቤ ላይ (ከዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ያለመከሰስ መብት መነሳት ጋር የተያያዘ) ፦ " ... ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ምሩፅ ለከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ቀርበው በሰጡት መግላጫ እንዲሁም በእጣ አወጣጥ ስነስርዓቱ ላይ ለህዝብ በይፋ በሰጡት ማብራሪያ ቢሮው በአዋጅ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ቴክኖሎጂውን አልምቶ የጨረሰ በመሆኑ…
#Update
ዶ/ር መሉቀን ሀፍቱ በፀጥታ ኃይሎች ተያዙ።
የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የነበሩትና ያለመከሰስ መብታቸው በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የተነሳው ሙሉቀን ሀፍቱ (ዶ/ር) ከአዲስ አበባ ምክር ቤት ስብሰባ እንደወጡ ሲቪል በለበሱ ሰዎች ተይዘዋል።
ዶ/ር ሙሉቀን ከቅርብ ደቂቃዎች በፊት ከአዲስ አበባ ምክር ቤት ስብሰባ በመውጣት ላይ ሳሉ በመንግሥት የጸጥታ ኃይል ተይዘው መወሰዳቸውን " አዲስ ማለዳ ጋዜጣ " ከስፍራው ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ዶ/ር መሉቀን ሀፍቱ በፀጥታ ኃይሎች ተያዙ።
የአዲስ አበባ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ የነበሩትና ያለመከሰስ መብታቸው በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የተነሳው ሙሉቀን ሀፍቱ (ዶ/ር) ከአዲስ አበባ ምክር ቤት ስብሰባ እንደወጡ ሲቪል በለበሱ ሰዎች ተይዘዋል።
ዶ/ር ሙሉቀን ከቅርብ ደቂቃዎች በፊት ከአዲስ አበባ ምክር ቤት ስብሰባ በመውጣት ላይ ሳሉ በመንግሥት የጸጥታ ኃይል ተይዘው መወሰዳቸውን " አዲስ ማለዳ ጋዜጣ " ከስፍራው ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
በም/ቤቱ እራሳቸውን የተከላከሉት ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ !
" እኔ መጀመሪያ ማንሳት የምፈልገው ፤ መጀመሪያ ከግል ስብእናዬ መነሳት ፈልጋለሁ እኔ እስከማስበው ድረስ ምስኪኑ ህዝብ ቆጥቦ ቤት እንዲያገኝ ነው ፍላጎቴ ፤ ይሄ ከነበረኝ ስብእና እንፃር ሙስና የሚለው የሚገልፀኝ አይደለም።
ነገር ግን ድርጊቱ ተደርጎ ከሆነ እኔም አዝኛለሁ፤ ይሄም ጥልቅ የሆነ ምርመራ ተደርጎ ነገ ሁላችንም የምናየው ይሆናል።
ወደ ዋናው ሀሳቤ ስሄድ የአመራር ሚና ምድነው እኔ የቢሮ ኃላፊነ ነኝ፣ በተለይ የቢሮ ኃላፊ ስሆን አጠቃላይ strategic የሆነ direction ነው የምሰጠው።
እነዚህ የ routine የሆኑ ስራዎች ላይ ስራዎችን አልሰጥም። ነገር ግን በዚህ ሂደት ማየት የሚገባኝን የአመራር ክፍተቶችን እወስዳለሁ። እሱን የምክደው አይደለም።
እኔ በ Presentation ላይ በኢንሳ ተረጋገጠ አላልኩም። የቪድዮ ቅጂ ስላለ እሱን ማየት ይቻላል። ነገር ግን እንዴት ነበር የሚለውን ለዚህ ምክር ቤት ለታሪክ መቅረት ስላለበት ማቅረብ ይገባኛል።
መጀመሪያ ለዕጣው ዝግጁ ስናደርገው ከ9 ወር በፊት ነው ይሄ ስራ ያተጀመረው ይሄ ስራ ከተጀመረ በኃላ መጀመሪያ የተደረገው ለኢኖቬሽን ... እ "
የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ወ/ሮ ሱፌና አልከድር ፦
" የተከበሩ ዶ/ር ሙልቀን ... በሂደቱ ላይ ሳይሆን "
ዶ/ር ሙሉቀን ፦
" አይደለም ሀሳቤን ... "
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" በቀረበው ላይ ብቻ አስተያየት ይስጡ "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" ገብቶኛል ክብርት አፈጉባኤ ... "
የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ፦
" እሱን ፍርድ ቤት የማያጣራው ጉዳይ ይሆናል "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" አይደለም፤ ይሄ ም/ቤትም... ለመደመጥም እንትን ልሁን ምክንያቱም ይሄ ምክር ቤትም ማወቅ የሚገባውን አካሄዱን ማወቅ ስለሚገባው ስላለበት ነው መናገር ያለብኝ ።
ስለዚህ በሂደቱ አስተያየት መስጠት ያለብኝ በዚህ መልክ ነው።
ሎተሪው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት 2 ደብዳቤ በህዳር 17 /2014 በአብርሃም ተፈርሞ ለኢኖቬሽን ሚኒስቴር እና ለኢንሳ የሞያዊ ድጋፍ ኣስፈላጊድን እንድታደርጉ ብለን ፅፈናል።
የኢኖቬሽን ሚኒስቴር በታህሳስ 26/2014 በደብዳቤ ምክረ ሀሳብ ሰጥቶናል። ከዛ በምክረ ሀሳቡ መሰረት የሚስተካከለውን አስተካክለናል። ኢንሳን በተመለከተ ግን ምንም አይነት ነጥብ አልሰጠንም personally እንደውም ዶ/ር ሹመቴን አግኝቼ ለማውራት እባክህን...ክብርት ያስሚንም ስላለች ክብርት ያስሚንም ደውላለት እንደውም ፍቃደኛ ያልሆነበት ሁኔታ ነበር የነበረው። ዕጣው ከመውጣቱ በፊት የነበረው ሂደት ይሄው ነው።
ሰኔ 21 ቀን 2014 በአቶ ሽመልስ የተፃፈ ደብዳቤ ተወካይ ይመደብልን በተባለው ሰዓት ..."
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" በጣም ያሳጥሩልን "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" አሳጥራለሁ ግን ካልተሰማሁ at least ይሄ ምክር ቤት ይስማኝ ካዛ በኃላ ችግር የለውም ሌላውን ነገር ..."
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" ማለት ይሄ የተከበረው ምክር ቤት ይሄንን ከማጣራት ስልጣን የለውም፤ የማጣራት ስልጣን ያለው ፍትህ ሚኒስቴር ነው "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት እኔ ከግል ስብእናዬ ከከፈልኩት የፖለቲካ ዋጋ ካለኝ ነገር ይሄ ምክር ቤት understand አድርጎ ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት ነው። ይሄን መናገር የፈለኩት።
ከይቅርታ ጋር ክብርት አፈጉባኤ ባያቋርጡኝ ብቀጥል። አጭር አጭር አድርጌ ልግለፅ።
ስለዚህ ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ በተፃፈው ደብዳቤ የዘርፉ ምክትል ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ አብርሃም ደርሷቸዋል። "
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" አሁንም ላስቆሞት ነው። አልፈቅድም። ሁሉንም ዝርዝር እንዳያቀርቡልን አልፈቅድም "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" አጭር ነው ፤ ሀሳቤን ወይም ደቂቃ ይስጡኝና... "
የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦
" ሀሳቡን አጭር አድርገው፣ የሚቃወሙትን ነገር ላይ ብቻ "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍታ፦
" ክብርት አፈ ጉባኤ የምቃወመው ይሄን ሀሳቤን ገለፅኩኝ በኃላ ነው "
የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦
" ለማስቆም እየተገደድኩ ነው "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ፦
" እሺ በምን ልናገር ታዲያ ? "
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" በጣም በማሳጠር "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" እሺ፣ ችግር የለውም ! በጣም አሳጥራለሁ። የምክር ቤት አባላትን በጣም ይቅርታ ጠይቃለሁ። ማወቅ ስላለባችሁ ነው።
ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ የተፃፈው ደብዳቤ እኔ ሰኔ 21 ምናልባት በጊዜው አልነበርኩም በባለቤቴ ወሊድ ምክንያት በዚህ ሰዓት ዳታ ሲቀበሉ፣ እንዲህ ያለውን ደብዳቤ ሲፃፃፉም በጊዜው አልነበርኩም።
የኔ ምክትል የነበረው ግን ይሄንን ዳብዳቤ ተቀብሎ ባለሞያ ወክልሉልን ባለን መሰረት ለሶፍትዌር ዳይሬክተር ባለሞያ እንዲወክል ፅፏል።
ከዛም በድጋሚ አቶ ሽመልስ ሰኔ 21 የቤት መረጃ ለቢሯቹ የላክን መሆኑን ይላል። እዚህ ጋር አቶ ሽመልስ አጠቃላይ የቤት ምዝገባ ያተደረጉበትን፣ ዕጣ የሚወጣባቸውን አቶ ሽመልስ ልኳል።
እኔ በዛ ሰዓት ስላልነበርኩ ምክትሌ አቶ አብርሃም አሁንም ይሄንን ለሶፍትዌር ዳይሬክተሮች መርቶ ወደባለሞያው የገባበት ሁኔታ አለ።
ለምን ይሄን አነሳሁኝ ለሚለው ሁለት ነገር ነው።
አንደኛው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት ክብርት ያስሚንም እንደውም እኔ አልነበርኩም ክብርት ያስሚን የእኔ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች ይዛ ቢሯችን መጥታ እዛ ስላልነበርኩኝ ያለውን ነገር ውይይት አድርጋ ሲስተሙ እንዴት ነበር ተብሎ display ተደርጎ ነበር እሱ በማየት ደረጃ እሳቸውም ስላሉ ይገልፁታል።
ሌላው ከ4 በላይ ሙከራ ተደርጓል የተባለው ምናልባት ክብርት ከንቲባ ባሉበት ሙከራ አድርገናል። ከዛም በኃላ ይሄ ኮምፒዩተር እኛ አዲስ ብለን ነው የሰጠነው። እንግዲህ ይሄ too በጣም technical እኔ የተማርኩት በሰላምና ደህንነት more of social science ነው። እኔ strategically በሆነ way ነው እንጂ መሥጠት ያለብኝ ምን አይነት algorithm ተጠቅሟል፣ behind የሰራውን ምን አይነት ሶፍትዌር ይጫን የሚልውን ነገር እኔ አላውቀውም።
ነገር ግን ይሄ ኮምፒዩተር አዲስ ነው። ከግዢ የሰጠነው ነው። ሰጠን ባለሞያው ይጠቀምበት ይሄን ያድርግበት እኔ እንደ አመራርነቴ ወርጄ የማየት role አለኝ ብዬ አላስብም።
ዕጣው ከመውጣቱ ለፊት ማታ ታሸገ፣ ከታሸገ በኃላ ታዛቢ ባለበት ታሸገ፣ ምንም ዳታ እንደሌለው ታይቶ ታሸገ። እኔ ኮምፒዩተሩ ጋርም ቀርቤ አላውቅም። ከዛ በነገታው መጡ ክብርት ያስሚን ባለችበት ሌላም ታዛቢ ባለበት በሩ ተከፍቶ ተገባ ካዛ ኮምፒዩተሩ ታየ ከዛም ክብርት ከንቲባ ባለችበት ያሬድ የሚባል ባለሞያ በቴክኖሎጂ የታወቀ ነው እሱ ይየው ተብሎ መጣ ያሬድ የሚባለው ሰውዬ ክሊክ አድርጎ ያለውን ነገር ጠቅላላ አየ መሄድ ይችላል ብሎ እዛው confirmation ሰጠን ምክንያቱም ክብርት ያስሚንም ስላሉ በዚህ መሰረት ወደ እጣው መጣ።
ወደ ዕጣው ሢመጣ presentation ተዘጋጀ፣ ከዛም ለቢሮው ይመጥናል አንተ ብታቀርበው ተብዬ እንዳቀርብ ተደረገ፤ ከዛ ውጭ Presentation ላይ ያቀረብኩት ደግሞ አንዱ ነገር ጠቅላላ የተሰጠኝን ሀሳብ ነው።
ለምሳሌ ከታች ባለሞያ አለ ከባለሞያው በላይ ዳይሬክተር አለ፣ ከዳይሬክተር በኃላ..."
ዶ/ር ሙሉቀን ይህንን እየተናገሩ እያሉ በቀጥታ በአዲስ ቴሌቪዥን ለህዝብ ሲሰራጭ የነበረው ንግግር ተቋርጧል። በኃላም ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቷል።
@tikvahethiopia
" እኔ መጀመሪያ ማንሳት የምፈልገው ፤ መጀመሪያ ከግል ስብእናዬ መነሳት ፈልጋለሁ እኔ እስከማስበው ድረስ ምስኪኑ ህዝብ ቆጥቦ ቤት እንዲያገኝ ነው ፍላጎቴ ፤ ይሄ ከነበረኝ ስብእና እንፃር ሙስና የሚለው የሚገልፀኝ አይደለም።
ነገር ግን ድርጊቱ ተደርጎ ከሆነ እኔም አዝኛለሁ፤ ይሄም ጥልቅ የሆነ ምርመራ ተደርጎ ነገ ሁላችንም የምናየው ይሆናል።
ወደ ዋናው ሀሳቤ ስሄድ የአመራር ሚና ምድነው እኔ የቢሮ ኃላፊነ ነኝ፣ በተለይ የቢሮ ኃላፊ ስሆን አጠቃላይ strategic የሆነ direction ነው የምሰጠው።
እነዚህ የ routine የሆኑ ስራዎች ላይ ስራዎችን አልሰጥም። ነገር ግን በዚህ ሂደት ማየት የሚገባኝን የአመራር ክፍተቶችን እወስዳለሁ። እሱን የምክደው አይደለም።
እኔ በ Presentation ላይ በኢንሳ ተረጋገጠ አላልኩም። የቪድዮ ቅጂ ስላለ እሱን ማየት ይቻላል። ነገር ግን እንዴት ነበር የሚለውን ለዚህ ምክር ቤት ለታሪክ መቅረት ስላለበት ማቅረብ ይገባኛል።
መጀመሪያ ለዕጣው ዝግጁ ስናደርገው ከ9 ወር በፊት ነው ይሄ ስራ ያተጀመረው ይሄ ስራ ከተጀመረ በኃላ መጀመሪያ የተደረገው ለኢኖቬሽን ... እ "
የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ወ/ሮ ሱፌና አልከድር ፦
" የተከበሩ ዶ/ር ሙልቀን ... በሂደቱ ላይ ሳይሆን "
ዶ/ር ሙሉቀን ፦
" አይደለም ሀሳቤን ... "
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" በቀረበው ላይ ብቻ አስተያየት ይስጡ "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" ገብቶኛል ክብርት አፈጉባኤ ... "
የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ ፦
" እሱን ፍርድ ቤት የማያጣራው ጉዳይ ይሆናል "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" አይደለም፤ ይሄ ም/ቤትም... ለመደመጥም እንትን ልሁን ምክንያቱም ይሄ ምክር ቤትም ማወቅ የሚገባውን አካሄዱን ማወቅ ስለሚገባው ስላለበት ነው መናገር ያለብኝ ።
ስለዚህ በሂደቱ አስተያየት መስጠት ያለብኝ በዚህ መልክ ነው።
ሎተሪው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት 2 ደብዳቤ በህዳር 17 /2014 በአብርሃም ተፈርሞ ለኢኖቬሽን ሚኒስቴር እና ለኢንሳ የሞያዊ ድጋፍ ኣስፈላጊድን እንድታደርጉ ብለን ፅፈናል።
የኢኖቬሽን ሚኒስቴር በታህሳስ 26/2014 በደብዳቤ ምክረ ሀሳብ ሰጥቶናል። ከዛ በምክረ ሀሳቡ መሰረት የሚስተካከለውን አስተካክለናል። ኢንሳን በተመለከተ ግን ምንም አይነት ነጥብ አልሰጠንም personally እንደውም ዶ/ር ሹመቴን አግኝቼ ለማውራት እባክህን...ክብርት ያስሚንም ስላለች ክብርት ያስሚንም ደውላለት እንደውም ፍቃደኛ ያልሆነበት ሁኔታ ነበር የነበረው። ዕጣው ከመውጣቱ በፊት የነበረው ሂደት ይሄው ነው።
ሰኔ 21 ቀን 2014 በአቶ ሽመልስ የተፃፈ ደብዳቤ ተወካይ ይመደብልን በተባለው ሰዓት ..."
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" በጣም ያሳጥሩልን "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" አሳጥራለሁ ግን ካልተሰማሁ at least ይሄ ምክር ቤት ይስማኝ ካዛ በኃላ ችግር የለውም ሌላውን ነገር ..."
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" ማለት ይሄ የተከበረው ምክር ቤት ይሄንን ከማጣራት ስልጣን የለውም፤ የማጣራት ስልጣን ያለው ፍትህ ሚኒስቴር ነው "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት እኔ ከግል ስብእናዬ ከከፈልኩት የፖለቲካ ዋጋ ካለኝ ነገር ይሄ ምክር ቤት understand አድርጎ ለታሪክ መቀመጥ ስላለበት ነው። ይሄን መናገር የፈለኩት።
ከይቅርታ ጋር ክብርት አፈጉባኤ ባያቋርጡኝ ብቀጥል። አጭር አጭር አድርጌ ልግለፅ።
ስለዚህ ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ በተፃፈው ደብዳቤ የዘርፉ ምክትል ኃላፊ ለሆኑት ለአቶ አብርሃም ደርሷቸዋል። "
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" አሁንም ላስቆሞት ነው። አልፈቅድም። ሁሉንም ዝርዝር እንዳያቀርቡልን አልፈቅድም "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" አጭር ነው ፤ ሀሳቤን ወይም ደቂቃ ይስጡኝና... "
የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦
" ሀሳቡን አጭር አድርገው፣ የሚቃወሙትን ነገር ላይ ብቻ "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍታ፦
" ክብርት አፈ ጉባኤ የምቃወመው ይሄን ሀሳቤን ገለፅኩኝ በኃላ ነው "
የም/ቤቱ አፈ ጉባኤ፦
" ለማስቆም እየተገደድኩ ነው "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ፦
" እሺ በምን ልናገር ታዲያ ? "
የም/ቤቱ አፈጉባኤ፦
" በጣም በማሳጠር "
ዶ/ር ሙሉቀን ሀፍቱ ፦
" እሺ፣ ችግር የለውም ! በጣም አሳጥራለሁ። የምክር ቤት አባላትን በጣም ይቅርታ ጠይቃለሁ። ማወቅ ስላለባችሁ ነው።
ሰኔ 21 ቀን በአቶ ሽመልስ የተፃፈው ደብዳቤ እኔ ሰኔ 21 ምናልባት በጊዜው አልነበርኩም በባለቤቴ ወሊድ ምክንያት በዚህ ሰዓት ዳታ ሲቀበሉ፣ እንዲህ ያለውን ደብዳቤ ሲፃፃፉም በጊዜው አልነበርኩም።
የኔ ምክትል የነበረው ግን ይሄንን ዳብዳቤ ተቀብሎ ባለሞያ ወክልሉልን ባለን መሰረት ለሶፍትዌር ዳይሬክተር ባለሞያ እንዲወክል ፅፏል።
ከዛም በድጋሚ አቶ ሽመልስ ሰኔ 21 የቤት መረጃ ለቢሯቹ የላክን መሆኑን ይላል። እዚህ ጋር አቶ ሽመልስ አጠቃላይ የቤት ምዝገባ ያተደረጉበትን፣ ዕጣ የሚወጣባቸውን አቶ ሽመልስ ልኳል።
እኔ በዛ ሰዓት ስላልነበርኩ ምክትሌ አቶ አብርሃም አሁንም ይሄንን ለሶፍትዌር ዳይሬክተሮች መርቶ ወደባለሞያው የገባበት ሁኔታ አለ።
ለምን ይሄን አነሳሁኝ ለሚለው ሁለት ነገር ነው።
አንደኛው ዕጣ ከመውጣቱ በፊት ክብርት ያስሚንም እንደውም እኔ አልነበርኩም ክብርት ያስሚን የእኔ ምክትል ቢሮ ኃላፊዎች ይዛ ቢሯችን መጥታ እዛ ስላልነበርኩኝ ያለውን ነገር ውይይት አድርጋ ሲስተሙ እንዴት ነበር ተብሎ display ተደርጎ ነበር እሱ በማየት ደረጃ እሳቸውም ስላሉ ይገልፁታል።
ሌላው ከ4 በላይ ሙከራ ተደርጓል የተባለው ምናልባት ክብርት ከንቲባ ባሉበት ሙከራ አድርገናል። ከዛም በኃላ ይሄ ኮምፒዩተር እኛ አዲስ ብለን ነው የሰጠነው። እንግዲህ ይሄ too በጣም technical እኔ የተማርኩት በሰላምና ደህንነት more of social science ነው። እኔ strategically በሆነ way ነው እንጂ መሥጠት ያለብኝ ምን አይነት algorithm ተጠቅሟል፣ behind የሰራውን ምን አይነት ሶፍትዌር ይጫን የሚልውን ነገር እኔ አላውቀውም።
ነገር ግን ይሄ ኮምፒዩተር አዲስ ነው። ከግዢ የሰጠነው ነው። ሰጠን ባለሞያው ይጠቀምበት ይሄን ያድርግበት እኔ እንደ አመራርነቴ ወርጄ የማየት role አለኝ ብዬ አላስብም።
ዕጣው ከመውጣቱ ለፊት ማታ ታሸገ፣ ከታሸገ በኃላ ታዛቢ ባለበት ታሸገ፣ ምንም ዳታ እንደሌለው ታይቶ ታሸገ። እኔ ኮምፒዩተሩ ጋርም ቀርቤ አላውቅም። ከዛ በነገታው መጡ ክብርት ያስሚን ባለችበት ሌላም ታዛቢ ባለበት በሩ ተከፍቶ ተገባ ካዛ ኮምፒዩተሩ ታየ ከዛም ክብርት ከንቲባ ባለችበት ያሬድ የሚባል ባለሞያ በቴክኖሎጂ የታወቀ ነው እሱ ይየው ተብሎ መጣ ያሬድ የሚባለው ሰውዬ ክሊክ አድርጎ ያለውን ነገር ጠቅላላ አየ መሄድ ይችላል ብሎ እዛው confirmation ሰጠን ምክንያቱም ክብርት ያስሚንም ስላሉ በዚህ መሰረት ወደ እጣው መጣ።
ወደ ዕጣው ሢመጣ presentation ተዘጋጀ፣ ከዛም ለቢሮው ይመጥናል አንተ ብታቀርበው ተብዬ እንዳቀርብ ተደረገ፤ ከዛ ውጭ Presentation ላይ ያቀረብኩት ደግሞ አንዱ ነገር ጠቅላላ የተሰጠኝን ሀሳብ ነው።
ለምሳሌ ከታች ባለሞያ አለ ከባለሞያው በላይ ዳይሬክተር አለ፣ ከዳይሬክተር በኃላ..."
ዶ/ር ሙሉቀን ይህንን እየተናገሩ እያሉ በቀጥታ በአዲስ ቴሌቪዥን ለህዝብ ሲሰራጭ የነበረው ንግግር ተቋርጧል። በኃላም ያለመከሰስ መብታቸው ተነስቷል።
@tikvahethiopia