#ጥንቃቄ | ዩኒቨርሲቲዎች፣ ተማሪዎችና አጠቃላይ ዩኒቨርሲቲ ማህበረስብ አባላት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላለፈ !
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።
ግብረ ኃይሉ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህውሃት ቡድን ፋይናንስ ያደርጋቸዋል ያላቸው ሚዲያዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለማደናቀፍ ተማሪዎች በብሄርና በሀይማኖት በመከፋፈል ግጭት እንዲፈጠር ለማነሳሳት ሌት ተቀን እሰሩ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ብሏል።
እነዚሁ ሚዲያዎች ሰሞኑን «በአማራ ክልል ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ የኦሮሞ እና የሌሎች ብሄር ተማሪዎችን ለማጥቃት የተደራጀ የደህንነት ቡድን ወደ አማራ ክልል ተልኳል» የሚል በዩኒቨርሲቲዎች ግጭት ለማስነሳት መልዕክት አስተላልፈዋል ብሏል።
የዩኒቨርሲቲዎችን ሰላም ለማናጋት እና ተማሪዎች በሰላም እንዳይማሩ የሚያደርጉ አካላትን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ያሳሰበው ግብረኃይሉ ይህን ተላልፈው በሚገኙት ላይ ጥብቅ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወድ አስጠንቅቋል።
ዩኒቨርሲቲዎች፣ ተማሪዎችና ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ሆን ተብሎ ግጭት ለማስነሳት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን በመገንዘብ እራሳቸውን በመጠብቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ አሳስቧል።
(የግብረ ኃይሉ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ መግለጫ ሰጥቷል።
ግብረ ኃይሉ ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀው ህውሃት ቡድን ፋይናንስ ያደርጋቸዋል ያላቸው ሚዲያዎች የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ሰላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት ለማደናቀፍ ተማሪዎች በብሄርና በሀይማኖት በመከፋፈል ግጭት እንዲፈጠር ለማነሳሳት ሌት ተቀን እሰሩ እንደሆነ ደርሼበታለሁ ብሏል።
እነዚሁ ሚዲያዎች ሰሞኑን «በአማራ ክልል ዩኒቨርስቲዎች የሚማሩ የኦሮሞ እና የሌሎች ብሄር ተማሪዎችን ለማጥቃት የተደራጀ የደህንነት ቡድን ወደ አማራ ክልል ተልኳል» የሚል በዩኒቨርሲቲዎች ግጭት ለማስነሳት መልዕክት አስተላልፈዋል ብሏል።
የዩኒቨርሲቲዎችን ሰላም ለማናጋት እና ተማሪዎች በሰላም እንዳይማሩ የሚያደርጉ አካላትን ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ ያሳሰበው ግብረኃይሉ ይህን ተላልፈው በሚገኙት ላይ ጥብቅ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወድ አስጠንቅቋል።
ዩኒቨርሲቲዎች፣ ተማሪዎችና ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ሆን ተብሎ ግጭት ለማስነሳት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን በመገንዘብ እራሳቸውን በመጠብቅ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይሉ አሳስቧል።
(የግብረ ኃይሉ ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በርካቶች በምዕራብ ወለጋ በንፁሃን በተለይ በህፃናት እና ሴቶች ላይ የተፈፀመውን ጭፍጨፋ እያወገዙ ይገኛሉ። በተለይ በአማራ ክልል በሚገኙት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ፍትህ እንዲሰፍን፣ መንግስት ንፁሃንን የመጠበቅ ኃላፊነቱን እንዲወጣ፣ ተጠያቂነት እንዲሰፍን ሰልፍ በማድረግ ጭምር እየጠየቁ ይገኛሉ። ዛሬ በወልዲያ ዩኒቨርሲቲ ፣ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተጠያቂነት እንዲሰፍን፣ በአማራ…
ፎቶ / ቪድዮ ፦ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ለወገናችን ድምፃችንን ለማሰማት ሰልፍ ብናደርግም ፀጥታ ኃይሎች የአስለቃሽ ጭስ በመተኮስ በተኑን ሲሉ የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ጊዎን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህክምናና ጤና ሳይንስ ተማሪዎች እንደሁም አንዳንድ ሰራተኞች ቅሬታቸውን አቀረቡ።
ምዕራብ ወለጋ ላይ የተከሰተውን አጸያፊ ተግባር የሚያወግዙ መልዕክቶችን ይዘን ነበር ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምፃችንን እያሰማን ነበረው ግን በኃይል ተበትነናል ብለዋል።
" አማራ ተኮር ዘር ጭፍጨፋ ይቁም ፤ ያለማቋረጥ ለሚፈሰው ለአማራ ደም ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ የተኛው መንግስት አካል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፤ እኛ የጤና ባለሙያዎች የታመሙትን የሚያድን እንጂ ጤነኞችን የሚገድል ሀይላትን አንቃወማለን የሚሉ መልዕክቶችን አስተገጋብተናል ነገር ግን ድምፃችንን አሰምተን ሳይጨርስ ፀጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመጠቀም በኃይል በትነውናል " ሲሉ አስረድተዋል።
አንዳንድ የወደቁና በመጠኑ የቆሰሉ ቢኖሩም ሌላ ተጨማሪ ጉዳት እንዳልነበር አመልክተዋል።
ፎቶ / ቪድዮ ፦ NAT. (Tikvah Family)
@tikvahethiopia
ምዕራብ ወለጋ ላይ የተከሰተውን አጸያፊ ተግባር የሚያወግዙ መልዕክቶችን ይዘን ነበር ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምፃችንን እያሰማን ነበረው ግን በኃይል ተበትነናል ብለዋል።
" አማራ ተኮር ዘር ጭፍጨፋ ይቁም ፤ ያለማቋረጥ ለሚፈሰው ለአማራ ደም ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ የተኛው መንግስት አካል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል፤ እኛ የጤና ባለሙያዎች የታመሙትን የሚያድን እንጂ ጤነኞችን የሚገድል ሀይላትን አንቃወማለን የሚሉ መልዕክቶችን አስተገጋብተናል ነገር ግን ድምፃችንን አሰምተን ሳይጨርስ ፀጥታ ኃይሎች አስለቃሽ ጭስ በመጠቀም በኃይል በትነውናል " ሲሉ አስረድተዋል።
አንዳንድ የወደቁና በመጠኑ የቆሰሉ ቢኖሩም ሌላ ተጨማሪ ጉዳት እንዳልነበር አመልክተዋል።
ፎቶ / ቪድዮ ፦ NAT. (Tikvah Family)
@tikvahethiopia
ፎቶ ፦ በሐዋሳ ከተማ ወደ ከተማዋ የመግቢያ በርና የፓርክ ልማት ኘሮጀክት በይፋ መጀመሩን የከተማው አስታዳደር አሳውቋል።
ወደ ከተማዋ የመግቢያ በር ፕሮጀክት ዛሬ ተጀምሯል።
ይህ የሐዋሳ መግቢያ ኘሮጀክት በቢሻን ጉራቻ (ጥቁር ውሃ) በኩል የሚገነባ ሲሆን የሐዋሳን እንዲሁም የሲዳማን ባህል ታሪክና ትውፊት የሚያስተዋውቅ እና ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጠርም እንደሆነ ተገልጿል።
ፕሮጀክቱ ከ1,500 በላይ ለሆኑ ወጣቶች የስራ ዕድል ይፈጥራል የተባለ ሲሆን በአንድ ዓመት የሚጠናቀቅ ፤ አንድ መቶ ሚሊየን ብር የሚፈጅ መሆኑም ተጠቁሟል።
ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አሰተዳደር
@tikvahethiopia
ወደ ከተማዋ የመግቢያ በር ፕሮጀክት ዛሬ ተጀምሯል።
ይህ የሐዋሳ መግቢያ ኘሮጀክት በቢሻን ጉራቻ (ጥቁር ውሃ) በኩል የሚገነባ ሲሆን የሐዋሳን እንዲሁም የሲዳማን ባህል ታሪክና ትውፊት የሚያስተዋውቅ እና ለበርካታ ወጣቶች የስራ እድል የሚፈጠርም እንደሆነ ተገልጿል።
ፕሮጀክቱ ከ1,500 በላይ ለሆኑ ወጣቶች የስራ ዕድል ይፈጥራል የተባለ ሲሆን በአንድ ዓመት የሚጠናቀቅ ፤ አንድ መቶ ሚሊየን ብር የሚፈጅ መሆኑም ተጠቁሟል።
ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ አሰተዳደር
@tikvahethiopia
#ቹ
በዓለም በስፋት (በተናጋሪ ብዛት) ከሚነገሩ ቋንቋዎች በአንደኝነት የሚቀመጠውን፣ የተባበሩት መንግስታት የስራ ቋንቋ የሆነውን፣ ቻይንኛ ቋንቋን ይማሩ!!
ቹ * ቻይንኛ እና ቻይንኛ ብቻ የሚማሩበት የከተማችን የቋንቋ ት/ቤት ነው፡፡
*ለተማሪዎች በክረምት ወቅት የሚሰጥ ልዩ ፕሮግራም አዘጋጅተናል።
አድራሻ፡
*ቦሌ፡ ፋንቱ ሱፐር ማርኬት አካባቢ፣ ሳይ ኬክ ቤት ያለበት ህንጻ፣ 1ኛ ፎቅ
*ስታድየም፡ ትንሸዋ ስታድየም ጀርባ፣ ናሽናል ታወር ፣ 3ኛ ፎቅ
*አያት 49 የአየር መንገድ ቤቶች ፊት ለፊት ማይ ፕላዛ ህንጻ፣ 1ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ በ 0947202020 ይደውሉ፡፡
በዓለም በስፋት (በተናጋሪ ብዛት) ከሚነገሩ ቋንቋዎች በአንደኝነት የሚቀመጠውን፣ የተባበሩት መንግስታት የስራ ቋንቋ የሆነውን፣ ቻይንኛ ቋንቋን ይማሩ!!
ቹ * ቻይንኛ እና ቻይንኛ ብቻ የሚማሩበት የከተማችን የቋንቋ ት/ቤት ነው፡፡
*ለተማሪዎች በክረምት ወቅት የሚሰጥ ልዩ ፕሮግራም አዘጋጅተናል።
አድራሻ፡
*ቦሌ፡ ፋንቱ ሱፐር ማርኬት አካባቢ፣ ሳይ ኬክ ቤት ያለበት ህንጻ፣ 1ኛ ፎቅ
*ስታድየም፡ ትንሸዋ ስታድየም ጀርባ፣ ናሽናል ታወር ፣ 3ኛ ፎቅ
*አያት 49 የአየር መንገድ ቤቶች ፊት ለፊት ማይ ፕላዛ ህንጻ፣ 1ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ በ 0947202020 ይደውሉ፡፡
#NewsAlert
የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ።
በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ።
ዶ/ር ጌዲዮን ፓርቲው ሰላማዊ ውይይት ለማድረግ ዉሳኔ አሳልፏል ብለዋል።
ሚኒስትሩ ፤ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተካሄደው ጦርነት መንግሥት ተገዶ የገባበት መሆኑን ገልፀው ፤ መንግሥት ይህንን ለመፍታት እየሠራ ስለመሆኑም አስረድተዋል ።
ፓርቲዉ ተጨማሪ ደም መፋሰስ እንዳይኖር ታሳቢ በማድረግ #ለሰላም_ቅድሚያ_ይሰጣል ነው ያሉት።
ዶክተር ጌዲዮን እንዳሉት ፓርቲዉ ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የሰላም አማራጩ፡-
1. ሕገ መንግሥታዊ እና ሕጋዊነትን የሚያስከብር መሆን አለበት፡፡
2. የሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ መሆን አለበት፡፡
3. በሀገር ዉስጥ መፍታት ካልተቻለ #በአፍሪካ_ሕብረት ጉዳዩ መታየት እንዳለበት በሥራ አስፈጻሚ እና በማእከላዊ ኮሚቴ ዉይይት ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል።
በተጨማሪም ትንኮሳዎች ካሉ ሕግ አስከባሪዉ አካል እርምጃ እንዲወሰድ ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። ሕዝቡም ለዚህ ተሳታፊ እንዲሆንም ጥሪ ማስተላለፋቸውን ከአሚኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ።
በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ።
ዶ/ር ጌዲዮን ፓርቲው ሰላማዊ ውይይት ለማድረግ ዉሳኔ አሳልፏል ብለዋል።
ሚኒስትሩ ፤ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል የተካሄደው ጦርነት መንግሥት ተገዶ የገባበት መሆኑን ገልፀው ፤ መንግሥት ይህንን ለመፍታት እየሠራ ስለመሆኑም አስረድተዋል ።
ፓርቲዉ ተጨማሪ ደም መፋሰስ እንዳይኖር ታሳቢ በማድረግ #ለሰላም_ቅድሚያ_ይሰጣል ነው ያሉት።
ዶክተር ጌዲዮን እንዳሉት ፓርቲዉ ባስቀመጠዉ አቅጣጫ መሰረት የሰላም አማራጩ፡-
1. ሕገ መንግሥታዊ እና ሕጋዊነትን የሚያስከብር መሆን አለበት፡፡
2. የሀገርን ክብር የሚያስጠብቅ መሆን አለበት፡፡
3. በሀገር ዉስጥ መፍታት ካልተቻለ #በአፍሪካ_ሕብረት ጉዳዩ መታየት እንዳለበት በሥራ አስፈጻሚ እና በማእከላዊ ኮሚቴ ዉይይት ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል።
በተጨማሪም ትንኮሳዎች ካሉ ሕግ አስከባሪዉ አካል እርምጃ እንዲወሰድ ዉሳኔ መተላለፉን አንስተዋል። ሕዝቡም ለዚህ ተሳታፊ እንዲሆንም ጥሪ ማስተላለፋቸውን ከአሚኮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopia
#ETHO_SUDAN
ኢትዮጵያ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር አካባቢ በተከሰተ ግጭት በጠፋው የሰው ህይወት ማዘኗን ገለፀች።
ጎረቤት ሃገር ሱዳን በኢትዮጵያ ጦር 7 ወታደሮቿ እና 1 ሲቪል እንደተገደለባት ክስ አሰምታለች። ግድያው በዚህ ወር አጋማሽ የተፈፀመ ነው ብላለች።
በዚህም ለተመድ ፀጥታ ም/ቤትና ለሌሎች አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋም ክስ አቅርባለሁ ብላለች።
በተጨማሪ ቁጣዋን ለመግለፅ በአዲስ አበባ የሚገኙትን መልዕክተኛዋን ወደ ካርቱም ጠርታለች፣ በአገሯ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደርም ጠርታ ማብራሪያ እንዲሰጡ ብላለች።
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በተመለከተ ባወጣው መግለጫ፣ ግጭት የተከሰተው በህወሓት ድጋፍ የኢትዮጵያን ድንበርን አልፈው በገቡ የሱዳን መደበኛ ወታደሮች መሆኑን ገልጿል።
በሱዳን ሠራዊትና በአካባቢው ሚሊሻዎች መካከል በተከሰተው በዚህ ግጭት በጠፋው ህይወት የኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚያዝን ገልጾ ምርመራ እንደሚደረግም አመልክቷል።
ክስተቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የጠበቀ ግንኙነት ለማደናቀፍ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን በማመልከት፣ የሱዳን መንግሥትም ሁኔታውን የበለጠ ከሚያባብስ እርምጃ እንደሚቆጠብ አሳስቧል።
በሌላ በኩል ደግሞ፥ ሱዳኖቹ በአማራ ክልል ምእራብ ጎንደር ዞን አርማጭሆ ወረዳ “ገላል ውሀ” የተባለ አካባቢን በከባድ መሳሪያ ሲደበድቡ ውለዋል።
ጥቃቱ ካለፈው ሰኔ 15 ጀምሮ አልፎ አልፎ የነበረ ሲሆን ታጣቂዎቹ ተመትተው ከአካባቢው ከተባረሩ በኋላ እንደገና ዛሬ ከጠዋቱ ከ2 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የከፋ ጉዳት ባይደርስም ጥቃት መሰንዘራቸውን ነዋሪዎች እንደገለፁ ዶቼቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ሮይተርስ፣ ዴቼቨለ እና ቢቢሲ ናቸው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር አካባቢ በተከሰተ ግጭት በጠፋው የሰው ህይወት ማዘኗን ገለፀች።
ጎረቤት ሃገር ሱዳን በኢትዮጵያ ጦር 7 ወታደሮቿ እና 1 ሲቪል እንደተገደለባት ክስ አሰምታለች። ግድያው በዚህ ወር አጋማሽ የተፈፀመ ነው ብላለች።
በዚህም ለተመድ ፀጥታ ም/ቤትና ለሌሎች አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ተቋም ክስ አቅርባለሁ ብላለች።
በተጨማሪ ቁጣዋን ለመግለፅ በአዲስ አበባ የሚገኙትን መልዕክተኛዋን ወደ ካርቱም ጠርታለች፣ በአገሯ የሚገኙትን የኢትዮጵያ አምባሳደርም ጠርታ ማብራሪያ እንዲሰጡ ብላለች።
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጉዳዩን በተመለከተ ባወጣው መግለጫ፣ ግጭት የተከሰተው በህወሓት ድጋፍ የኢትዮጵያን ድንበርን አልፈው በገቡ የሱዳን መደበኛ ወታደሮች መሆኑን ገልጿል።
በሱዳን ሠራዊትና በአካባቢው ሚሊሻዎች መካከል በተከሰተው በዚህ ግጭት በጠፋው ህይወት የኢትዮጵያ መንግሥት እንደሚያዝን ገልጾ ምርመራ እንደሚደረግም አመልክቷል።
ክስተቱ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የጠበቀ ግንኙነት ለማደናቀፍ ሆን ተብሎ የተቀነባበረ መሆኑን በማመልከት፣ የሱዳን መንግሥትም ሁኔታውን የበለጠ ከሚያባብስ እርምጃ እንደሚቆጠብ አሳስቧል።
በሌላ በኩል ደግሞ፥ ሱዳኖቹ በአማራ ክልል ምእራብ ጎንደር ዞን አርማጭሆ ወረዳ “ገላል ውሀ” የተባለ አካባቢን በከባድ መሳሪያ ሲደበድቡ ውለዋል።
ጥቃቱ ካለፈው ሰኔ 15 ጀምሮ አልፎ አልፎ የነበረ ሲሆን ታጣቂዎቹ ተመትተው ከአካባቢው ከተባረሩ በኋላ እንደገና ዛሬ ከጠዋቱ ከ2 ሰዓት እስከ 7 ሰዓት የከፋ ጉዳት ባይደርስም ጥቃት መሰንዘራቸውን ነዋሪዎች እንደገለፁ ዶቼቨለ ሬድዮ ዘግቧል።
ምንጭ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ሮይተርስ፣ ዴቼቨለ እና ቢቢሲ ናቸው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" ህግ ይከበር ፤ ፍትህ ይሰጠን " ለማስፋፊያ ስራ ተብሎ #ህግን_ባልተከተለ መልኩ ቤታችን ፈረሰብን ያሉ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል። ያሉበት ቦታ ለማስፋፊያ ስራ ይፈለጋል የተባሉ ዜጎች ለማስፋፊያ አንደሚፈለግ ያወቁት ሰኔ 29/2013 ዓ/ም አንደሆነ ከዛ በፊት ስለጉዳዩ ምንም እንደማያቁ / እንዳልተነገራቸው ፤ ጉዳዩን የሚያውቁት ከወረዳው…
#Update
• " ... ከመሬት ጋር በተያያዘ ከሳሽም ተከሳሽም ቤተክርስቲያኗ አይደለችም " - አዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን
• " የድሆችን የምስኪኖችን ቤት አስፈረሰ፤ አፈናቀለ የተባለው ፍፁም ሀሰት ከዚህም አለፈ ሲል የስም ማጥፋት ወንጀል ነው ጉዳዩን ወደ ህግ ወስጄዋለሁ " - አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ
• " ቤቶችን ያፈረሱት የመንግስት ኃይሎች በኃይል ፣ በጉልበት እና ህግን ባልተከተለ መልኩ ነው። አሁንም ቢሆን ህግ ይከበር ነው እያልን ያለነው። የተበደሉት ሁሉ ፍትህ ያግኙ " - ነዋሪዎች
ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ለማስፋፊያ በሚል ቤታቸው ህግን በጣሰ አካሄድ እንደፈረሰባቸው ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያ ብዙ ሲባል ቆይቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ስሟ የተነሳው የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥታለች።
የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን የአምልኮ ቦታ ከመጠየቀ በዘለለ የዜጎችን ቤት እንዲፈርስ እንዳላደረገች ገልፃለች።
ቤተክርስቲያኗ የሰዎችን ቤት የማፍረስ እና አፍራሽ ግብረኃይልን የማዘዝ አንዳችም ስልጣን እንደሌላት ገልፃለች።
በተጨማሪም ፤ ቤተክርስቲያኗ ከመሬት ጋር በተያያዘ ከሳችም ተከሳሽም እንዳልሆነች፣ የወሰደችው ቦታ ሆነ ዶክመት እንደሌለ እና በቤተክርስቲያን እጅ የሚገኘው የካቢኔ ውሳኔ ብቻ መሆኑን አስገንዝባለች።
በዚህም የሰው ቤት እንዲፈርስ የምታዝበት መብትም ሆነ ስልጣን እንደሌላት ግልፅ አድርጋለች።
" መንግስት የወሰንኩላችሁ ቦታ ይሄ ነው ተረከቡና አምልኩ መብቱ ነው፣ ተገቢውን ቤት፣ ካሳ ሰጥቶ በህግ አግባብ ፣ በመመሪያ እና በአሰራር ማድረግ ያለበትን ማድረግ መብቱ ነው ቦታው ለቤተክርስቲያኗ አይገባም ማለትም መብቱ ነው፣ ወደ ሌላ ቦታ ሂዱ ማለት እንዲሁ የመንግስት መብት ነው ቤተክርስቲያኗ አንዳችም ነገር አያገባትም ፤ በመንግስት አሰራር ውስጥም ጣልቃ አልገባችም " ስትል አስገዝባለች።
አካሄዱ ትክክል ሆነ ስህተት ምንም እንደማያገባት ገልፅ አድርጋለች።
ቤተክርስቲያኗ ምንም ስለማይመለከታት በመንግሥት ጉዳይ እና ስራ ውስጥ ገብታ በዝርዝር ማብራራት እንደማይጠበቅባት ገልፃለች።
ያንብቡ ⬇️
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-27
@tikvahethiopia
• " ... ከመሬት ጋር በተያያዘ ከሳሽም ተከሳሽም ቤተክርስቲያኗ አይደለችም " - አዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን
• " የድሆችን የምስኪኖችን ቤት አስፈረሰ፤ አፈናቀለ የተባለው ፍፁም ሀሰት ከዚህም አለፈ ሲል የስም ማጥፋት ወንጀል ነው ጉዳዩን ወደ ህግ ወስጄዋለሁ " - አገልጋይ ዮናታን አክሊሉ
• " ቤቶችን ያፈረሱት የመንግስት ኃይሎች በኃይል ፣ በጉልበት እና ህግን ባልተከተለ መልኩ ነው። አሁንም ቢሆን ህግ ይከበር ነው እያልን ያለነው። የተበደሉት ሁሉ ፍትህ ያግኙ " - ነዋሪዎች
ከቀናት በፊት በአዲስ አበባ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ የሚኖሩ ነዋሪዎች ለማስፋፊያ በሚል ቤታቸው ህግን በጣሰ አካሄድ እንደፈረሰባቸው ቅሬታ ማቅረባቸው ይታወሳል።
ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በማህበራዊ ሚዲያ ብዙ ሲባል ቆይቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ስሟ የተነሳው የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥታለች።
የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን የአምልኮ ቦታ ከመጠየቀ በዘለለ የዜጎችን ቤት እንዲፈርስ እንዳላደረገች ገልፃለች።
ቤተክርስቲያኗ የሰዎችን ቤት የማፍረስ እና አፍራሽ ግብረኃይልን የማዘዝ አንዳችም ስልጣን እንደሌላት ገልፃለች።
በተጨማሪም ፤ ቤተክርስቲያኗ ከመሬት ጋር በተያያዘ ከሳችም ተከሳሽም እንዳልሆነች፣ የወሰደችው ቦታ ሆነ ዶክመት እንደሌለ እና በቤተክርስቲያን እጅ የሚገኘው የካቢኔ ውሳኔ ብቻ መሆኑን አስገንዝባለች።
በዚህም የሰው ቤት እንዲፈርስ የምታዝበት መብትም ሆነ ስልጣን እንደሌላት ግልፅ አድርጋለች።
" መንግስት የወሰንኩላችሁ ቦታ ይሄ ነው ተረከቡና አምልኩ መብቱ ነው፣ ተገቢውን ቤት፣ ካሳ ሰጥቶ በህግ አግባብ ፣ በመመሪያ እና በአሰራር ማድረግ ያለበትን ማድረግ መብቱ ነው ቦታው ለቤተክርስቲያኗ አይገባም ማለትም መብቱ ነው፣ ወደ ሌላ ቦታ ሂዱ ማለት እንዲሁ የመንግስት መብት ነው ቤተክርስቲያኗ አንዳችም ነገር አያገባትም ፤ በመንግስት አሰራር ውስጥም ጣልቃ አልገባችም " ስትል አስገዝባለች።
አካሄዱ ትክክል ሆነ ስህተት ምንም እንደማያገባት ገልፅ አድርጋለች።
ቤተክርስቲያኗ ምንም ስለማይመለከታት በመንግሥት ጉዳይ እና ስራ ውስጥ ገብታ በዝርዝር ማብራራት እንደማይጠበቅባት ገልፃለች።
ያንብቡ ⬇️
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-27
@tikvahethiopia
Telegraph
Tikvah-Ethiopia
#Update የአዲስ ኪዳን ካህናት ቤተክርስቲያን የአምልኮ ቦታ ከመጠየቀ በዘለለ የዜጎችን ቤት እንዳላፈረሰች ገለፀች። ቤተክርስቲያኗ የሰዎችን ቤት የማፍረስ እና አፍራሽ ግብረኃይልን የማዘዝ አንዳችም ስልጣን እንደሌላት ገልፃለች። በተጨማሪ ቤተክርስቲያኗ ከመሬት ጋር በተያያዘ ከሳሽም ተከሳሽም አይደለችም፣ የወሰደችው ቦታ ሆነ ዶክመት እንደሌለ እና በቤተክርስቲያን እጅ የሚገኘው የካቢኔ ውሳኔ ብቻ መሆኑን…
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የሰሜን ኢትዮጵያውን ጦርነት #በሰላማዊ_መንገድ ለመፍታት ሰላማዊ ድርድሮች እንዲጀመሩ ገዢው ብልፅግና ፓርቲ አቅጣጫ አስቀመጠ። በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ላይ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የሚያስችል ዉይይት በብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እና በማእከላዊ ኮሚቴዉ መካሄዱን የፍትሕ ሚኒስትርና የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ አስታወቁ። ዶ/ር…
#Peace
የተደራዳሪ ቡድኑ !
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል።
የቡድኑ አባላት ፦
1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ
2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል
3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል
4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️ አባል
5ኛ. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ➡️ አባል
6ኛ. ሌ/ል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ ➡️ አባል
7ኛ. ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ➡️ አባል መሆናቸውን የኢፕድ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የተደራዳሪ ቡድኑ !
የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት #በሰላም_ድርድር እንዲፈታ ገዢው የብልፅግና ፓርቲ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት በፌዴራል መንግሥት በኩል የሰላም ተደራዳሪ ቡድን መሰየሙ ተረጋግጧል።
የቡድኑ አባላት ፦
1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን ➡️ ሰብሳቢ
2ኛ. ዶ/ር ጌድዮን ጢሞቲዎስ ➡️ አባል
3ኛ. አቶ ተመስገን ጥሩነህ ➡️ አባል
4ኛ. አምባሳደር ሀሰን አብዱልቃድር ➡️ አባል
5ኛ. አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ➡️ አባል
6ኛ. ሌ/ል ጀኔራል ብርሀኑ በቀለ ➡️ አባል
7ኛ. ዶ/ር ጌታቸው ጀምበር ➡️ አባል መሆናቸውን የኢፕድ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
" አሶሳ ሰላም ናት "
የቤንሺንጉል ጉሙዝ ክልል ፤ መዲና የሆነችው አሶሳ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሳይደናገጥ ለክልሉ ሰላም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
ክልሉ አሶሳ ላይ የፀጥታ ችግር እንደተፈጠረ ተደርጎ መሰረተቢስ እና ሀሰተኛ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጨ ነው ብሏል።
ነገር ግን ከተማይቱ ውስጥ አንዳችም የፀጥታ ችግር እንዳልተፈጠረና ፤ እንደ ወትሮ ሁሉ የከተማው ነዋሪ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
ነዋሪዎችም ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሚሰራጩ ሀሰተኛ እና መሰረተቢስ መረጃዎች ሳይደናገጥ ለክልሉ ሰላም መረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
የቤንሺንጉል ጉሙዝ ክልል ፤ መዲና የሆነችው አሶሳ ሰላም መሆኗን እና ህብረተሰቡ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በመሰራጩ ሀሰተኛ መረጃዎች ሳይደናገጥ ለክልሉ ሰላም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ ቀርቧል።
ክልሉ አሶሳ ላይ የፀጥታ ችግር እንደተፈጠረ ተደርጎ መሰረተቢስ እና ሀሰተኛ መረጃ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ እየተሰራጨ ነው ብሏል።
ነገር ግን ከተማይቱ ውስጥ አንዳችም የፀጥታ ችግር እንዳልተፈጠረና ፤ እንደ ወትሮ ሁሉ የከተማው ነዋሪ ሰላማዊ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ገልጿል።
ነዋሪዎችም ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በሚሰራጩ ሀሰተኛ እና መሰረተቢስ መረጃዎች ሳይደናገጥ ለክልሉ ሰላም መረጋገጥ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጠይቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ጎረቤት ሱዳኖች የጦርነት ጉሰማ ላይ ናቸው !
የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር መጎብኛታቸው ተነግሯል።
ቡርሀን ትንሹ ፋሻጋ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙት አል ዑስራ እና ዋድ ኮሊ አካባቢዎች የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር ነው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ/ም የጎበኙት፡፡
ጉብኝቱ ሱዳን ፤ "ምርኮኛ ወታደሮቼ በኢትዮጵያ ጦር ተገደሉብኝ " ማለቷን ተከትሎ የተካሄደ ነው፡፡ " የአጸፋ ምላሽንማ ሳንሰጥ አንቀርም " ስትልም ዝታ ነበር።
ጄነራል አልቡርሃን ፤ በጉብኝታቸው ጦሩ የሃገሩን ዳር ድንበር ለመጠበቅ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ ስለመሆናቸው ገልጸዋል፡፡
ለሃገራቸው ሲሉ መስዋዕትነትን የሚከፍሉ የጦሩ አባላት ደም "በከንቱ ፈስሶ" አይቀርም ሲሉም ዝተዋል። ሁኔታው ተጨባጭ መልስ እንደሚያገኝ ቃል በመግባት ከሰሞኑ በአል ዑስራ ያጋጠመው ፈጽሞ አይደገምም ብለዋል፡፡
በሱዳን መሬቶች ላይ ሚደረግ ምንም ዐይነት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ሲሉም ትዕዛዝን አስተላልፈዋል፡፡
አል ፋሽቃ፤ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የባለቤትነት ጥያቄ የሚያነሱበት ሰፊና ለም መሬት ሲሆን ኢትዮጵያ ጦርነት ላይ መሆኗን ተከትሎ ወደ አካባቢው ዘልቆ የገባው የሱዳን ጦር መሬቱን ይዞ ለቅቄ አልወጣም ብሏል።
ከዚህ አልፋ ሀገሪቱ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ጥረት እያደረገች መሆኑን #አል_አይን_ኒውስ ዘግቧል።
ከሰሞኑን ፤ ሱዳን ሞቱብኝ ያለቻቸው ወታደሮች ፤ የኢትዮጵያን ድንበርን አልፈው የገቡና (ጠብ አጫሪዎች እራሳቸው ናቸው) ከአካባቢው ሚሊሻ ጋር ግጭት የፈጠሩ የሱዳን መደበኛ ወታደሮች ሲሆኑ ኢትዮጵያም በጠፋው የሰው ህይወት ማዘኗን መግለጿ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር መጎብኛታቸው ተነግሯል።
ቡርሀን ትንሹ ፋሻጋ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙት አል ዑስራ እና ዋድ ኮሊ አካባቢዎች የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር ነው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ/ም የጎበኙት፡፡
ጉብኝቱ ሱዳን ፤ "ምርኮኛ ወታደሮቼ በኢትዮጵያ ጦር ተገደሉብኝ " ማለቷን ተከትሎ የተካሄደ ነው፡፡ " የአጸፋ ምላሽንማ ሳንሰጥ አንቀርም " ስትልም ዝታ ነበር።
ጄነራል አልቡርሃን ፤ በጉብኝታቸው ጦሩ የሃገሩን ዳር ድንበር ለመጠበቅ የሚያደርገውን ጥረት ለመደገፍ ቁርጠኛ ስለመሆናቸው ገልጸዋል፡፡
ለሃገራቸው ሲሉ መስዋዕትነትን የሚከፍሉ የጦሩ አባላት ደም "በከንቱ ፈስሶ" አይቀርም ሲሉም ዝተዋል። ሁኔታው ተጨባጭ መልስ እንደሚያገኝ ቃል በመግባት ከሰሞኑ በአል ዑስራ ያጋጠመው ፈጽሞ አይደገምም ብለዋል፡፡
በሱዳን መሬቶች ላይ ሚደረግ ምንም ዐይነት እንቅስቃሴ እንዳይኖር ሲሉም ትዕዛዝን አስተላልፈዋል፡፡
አል ፋሽቃ፤ ኢትዮጵያ እና ሱዳን የባለቤትነት ጥያቄ የሚያነሱበት ሰፊና ለም መሬት ሲሆን ኢትዮጵያ ጦርነት ላይ መሆኗን ተከትሎ ወደ አካባቢው ዘልቆ የገባው የሱዳን ጦር መሬቱን ይዞ ለቅቄ አልወጣም ብሏል።
ከዚህ አልፋ ሀገሪቱ መሰረተ ልማቶችን ለመገንባት ጥረት እያደረገች መሆኑን #አል_አይን_ኒውስ ዘግቧል።
ከሰሞኑን ፤ ሱዳን ሞቱብኝ ያለቻቸው ወታደሮች ፤ የኢትዮጵያን ድንበርን አልፈው የገቡና (ጠብ አጫሪዎች እራሳቸው ናቸው) ከአካባቢው ሚሊሻ ጋር ግጭት የፈጠሩ የሱዳን መደበኛ ወታደሮች ሲሆኑ ኢትዮጵያም በጠፋው የሰው ህይወት ማዘኗን መግለጿ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ከእስር ተፈቷል። ዛሬ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ 2ኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ማዘዙ ይታወሳል። ይኸው የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተከብሮ ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ከእስር መፈታቱን ጠበቃው ታደለ ገብረመድህን አረጋግጠዋል፡፡ @tikvahethiopia
" ዛሬ ጥዋት ሲቪል በለበሱ ሰዎች ነው ከመኖሪያ ቤቱ የተወሰደው " ጠበቃ ታደለ ገ/መድህን
ከጥቂት ቀን በፊት በዋስ ከእስር የተለቀቀው ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ዛሬ በድጋሚ መታሰሩን ለማወቅ ተችሏል።
ጠበቃ ታደለ ገ/መድህን ፥ ዛሬ ጥዋት ከመኖሪያ ቤቱ ሲቪል የለበሱ የፀጥታ አካላት እንደወሰዱትና ወዴት እንደወሰዱት እንደማያውቁ ገልፀዋል፤ ያለበትን ቦታ ለማወቅም እያፈላለጉ መሆኑን አክለዋል።
በሌላ መረጃ ፦ ጋዜጠኛ በቃሉ አለምረው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ወስኗል።
@tikvahethiopia
ከጥቂት ቀን በፊት በዋስ ከእስር የተለቀቀው ጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ዛሬ በድጋሚ መታሰሩን ለማወቅ ተችሏል።
ጠበቃ ታደለ ገ/መድህን ፥ ዛሬ ጥዋት ከመኖሪያ ቤቱ ሲቪል የለበሱ የፀጥታ አካላት እንደወሰዱትና ወዴት እንደወሰዱት እንደማያውቁ ገልፀዋል፤ ያለበትን ቦታ ለማወቅም እያፈላለጉ መሆኑን አክለዋል።
በሌላ መረጃ ፦ ጋዜጠኛ በቃሉ አለምረው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈታ ፍርድ ቤት ወስኗል።
@tikvahethiopia