TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ

እንደ FIAS 777 አይነት ሌሎች ተመሳሳይ ስራ የሚሰሩ ስላሉ ገንዘባችሁን እንዳትበሉ አደራ እንላለን።

በተለይ አሁን ያሉብንን ኢኮኖሚያዊ ችግሮችን ተገን በማድረግ በርካታ ወጣቶችን የሚያጭበረብሩ፤ ትንሽ ሰዎች እየከበሩ ሌሎች ብዙሃኑ ባዷቸውን የሚቀሩበት የማታለል ስራዎች በስፋት እየተስተዋለ ነው።

በትንሽ ብር ብዙ ታተርፋላችሁ፣ ዘመናዊ ስራ ነው፣ ከኢኮኖሚ ችግራችሁ በቶሎ ትላቀቃላችሁ እያሉ ወጣቶች ንብረታቸውን ሽጠው፣ ከሰው ተበድረው ገንዘብ ከከፈሉ በኃላ የውሃ ሽታ እየሆነባቸው ነው።

አንድ የቤተሰባችን አባል ልክ FIAS 777 እንደሚባለው አይነት HDUHDU በሚባል ተመሳሳይ ድርጅት እስከ 70,000 የተበሉ የሚያውቃቸው ብዙ ሰዎች መኖራቸውን ጠቁሞ እነዚህም አካላት ዛሬ ደብዛቸውን ማጥፋታቸውን ገልጿል።

አንድ ሌላ የቤተሰባችን አባል በዚህ HDUHDU በሚባለው እስከ 93000 ብር ድረስ የተበሉ ብዙ ጓደኞች እንዳሉት ገልጾ በርካታ ወጣቶች ብዙ ለማግኘት ሲሉ ያላቸውን ገንዘብ እና ጊዜያቸውን እያጡነውና ይጠንቀቁ ብሏል።

ሌሎች ከላይ ከተገለፁት ባለፈ ስም እየቀያየሩ በርካቶችን ገንዘብ የሚቀበሉ በሂደቱ ትንሽ ሰው አትርፎ ብዙሃኑ ያለውን የሚያጣበትን ስርዓት የዘረጉ ስላሉ ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ዋነኛዋቹ ሰዎች ውጭ ናቸው እየተባለ የሚነገር ሲሆን ገንዘብ የሚሰበሰበው እዚህ ኢትዮጵያ ባሉ ኤጀንቶች ነው።

ሁሌም ወደ ሆነ እንቅስቃሴ ሲገባ ህጋዊ እና ትክክለኝነቱን ማረጋገጥ ማጣራት ያስፈልጋል ፤ አሁን አሁን እየመጡ ያሉ ህገወጥ ድርጊቶች የሰዎችን ገንዘብ በመብላት ባለፈ ወዳጆችን እርስ በእርስ እንዲኮራረፉም እያደረገ ነው ፤ ህጋዊ መንገድ ብቻ እንከተል እንላለን።

(ማስረጃዎቻችሁን ለሚመለከታቸው አካላት ለማድረስ እና ምላሽ ካለ ለማሳወቅ እንጥራለን)

@tikvahethiopia
#እገታ

ከኦሮሚያ ክልል፣ ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ወደ አዲስ አበባ እየመጡ የነበሩ 4 የሕዝብ ማመላለሻና 1 የጭነት ተሸከርካሪዎች መታገታቸው ተሰምቷል።

ተሳፋሪዎቹ ከደራ ወረዳ ጉንዶ መስቀል ከተማ ተነስተው ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላይ ሳሉ መታገታቸው የተገለፀ ሲሆን እገታው የተፈፀመው በሂደቡአቦቴ ወረዳ ወዘሚ በሚባል መንደር ነው።

የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ ውብሸት አበራ 4 የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡሶችና 1 የጭነት መኪና መታገታቸውን አረጋግጠዋል።

የመንግስት የጸጥታ ኃይል ወደስፍራው መሄዱን ያነሱት አቶ ውብሸት እስካሁን 230 ሰዎች ከእገታው መለቀቃቸውን ተናግረዋል።

በአጠቃላይ በተሸከርካሪዎቹ ውስጥ ምን ይህል ሰዎች እንደተሳፈሩ ከጉንዶ መስቀል መረጃ እየሰበሰቡ እንደሆነ ያነሱት ገልፀው፤ የተለቀቁ ቢኖሩም አሁንም የታገቱ እንዳሉ ማወቃቸውን ተናግረዋል።

እገታው የተፈጸመው መንግስት ሸኔ እራሱን ደግሞ የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ በሚጠራው ቡድን እንደሆነም ነው የገለፁት። ተሸከርካሪቹ የታገቱበት አካባቢ በብዛት ቡድኑ የሚንቀሳቀስበት ነው ብለዋል።

አሁን በእገታ ላይ ያሉ ሰዎችን ትክክለኛ ቁጥር ለማወቅ አስቸጋሪ መሆኑን ገልፀዋል።

የደራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የታገቱት ሰዎች ጨለንቆ እንደተወሰዱ ገልጸው በስፍራው መንግስት " ሸኔ " እራሱን ደግሞ " የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት " ብሎ የሚጠራው ቡድን #ማሰልጠኛ እንዳለው ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ክልል አስተዳደርና ጸጥታ ቢሮ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል አበበ ገረሱ ይህንን ጉዳይ እንዳልሰሙና በአካባቢው ”ሽፍታ ይንቀሳቀስ ይሆናል” እንጅ ሌላ ችግር የለም ሲሉ ተናግረዋል።

የደራ ፍቼ አዲስ አበባ መንገድ ለ8 ወራት ያህል ተዘግቶ የነበረ ሲሆን አገልግሎት መስጠት የጀመረው በቅርቡ ነው ተብሏል።

ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ

@tikvahethiopia
#WorldBank #Ethiopia

የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስቴር ከዓለም ባንክ ጋር የ600 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍና የብድር ስምምነት መፈራረሙን አገለፀ።

ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ ፥ ከ600 ሚሊየን ዶላሩ ውስጥ 200 ሚሊየን ዶላሩ በድጋፍ መልክ ሲሆን 400 ሚሊየን ዶላሩ በብድር መልክ መሆኑን ገልጿል።

ስምምነቱ በኢትዮጵያ ያለውን የስርአተ ምግብ ለማሻሻል እና የምግብ እጥረት አደጋን ለመቀነስ የሚውል መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ የገንዘብ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
#ተራኪ

የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ - ሙሉ የመጽሐፍ ትረካ 🎧

17 ልብ አንጠልጣይ እውነተኛ ታሪኮች ከራሱ ከልብ ጠጋኙ ዶክተር ፈቀደ አግዋር በማስታወሻነት ቀርቦላቿል። ሙሉ የመጽሐፉን ትረካ፤ ተራኪ ላይ ያድምጡ!

ተራኪ - መተግበሪያን ከጉግል ፕሌስቶር እና አፕ ስቶር ላይ ያውርዱ!
⬇️Google Play | ጉግል ፕሌስቶር - bit.ly/3CTALq3
⬇️App Store | አፕ ስቶር - https://apple.co/3AVp0i3
Telegram - https://t.iss.one/terakiapp
☎️ አብረውን መስራት ለሚፈለጉ ደራሲያን በ +251920958300 | +251911637874
ፎቶ / ቪድዮ ፦ በኦሮሚያ ክልል ፤ ምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ፤ ቶሌ ቀበሌ ላይ ባለፈው ሰኔ 11 /2014 የተፈፀመውን የንፁሃን ግድያ በማውገዝ ሰልፍ የወጡ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፀጥታ ኃይሎች እንደበተኗቸው ለማወቅ ተችሏል።

ተማሪዎቹ " ሞት ይብቃን፣ አትግደሉን...ያልሞትነው ተራችን ገና ስለሆነ ነው ፣ ዛፉ ከሰው ልጅ ያንሳል እንጂ አይበልጥም ፣ አባይን የምንገድበው ለሰው ፣ ለድሃ እንጂ ለዛፍ ማጠጫ አይደለም እና ሌሎች መስል መልዕክቶችን እያሰሙ ከዩኒቨርሲቲው ተነስተው ወደ 4 ኪሎ ቤተ መንግስት አቅጣጫ እየተጓዙ ነበር።

የፀጥታ ኃይሎች በሰልፈኞች ላይ የማባረር እና የመደብደብ ድርጊት መፈፀማቸውን በተሰራጩ ቪድዮዎች ለማየት ተችላሏል።

ከዩኒቨርሲቲው አልያም ከፌዴራል ፖሊስ የሚገኝ ማብራሪያ ካለ ተከታትለን እናሳውቃለን።

ፎቶ/ ቪድዮ ፦ BTY (Tikvah Family) & ሶሻል ሚዲያ

More : @tikvahuniversity

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA በዚህ ትውልድ ያለነው ወጣቶች ፣ ጎልማሶች ፣ በእድሜም የገፋን ሰዎች ጭምር በሰው ልጆች ሊደረጉ ይችላሉ ተብለው የማይገመቱ እጅግ በርካታ አስደንጋጭ አሰቃቂ ግፎችን በቪድዮ፣ በፎቶ ተመልክተናል። ይህ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ መሰባሰቢያ ከተፈተ ጀምሮ (ያለፉትን 3ና 4 ዓመታት) እጅግ በርካታ አሰቃቂ ክስተቶችን፣ የሰው ልጅ አንገት የሚያስደፉ ድርጊቶችን ታዝበናል፤ በይፋም እርስ በእርስ…
#Update

በህይወት ያለን ሰው ያቃጠሉት ግለሰቦች ምን ተደረጉ ?

• ካቃጠሉት ውስጥ እስካሁን አራት የሚደርሱ አልተያዙም።

• ወንጀሉን ከፈፀሙት ውስጥ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ከድተው ጠፍተዋል፤ 2 የአማራ ልዩ ኃይል አባላት ለህግ እንዲሰጡ ለክልሉ ፖሊስ አመራሮች ተጠይቋል።

• 3 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገ ነው (ሁለት የደቡብ ክልል ልዩ ኃይል አባላት አንድ ሲቪል) ።

የፍትህ ሚኒስቴር በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ማንነትን መሰረት በማድረግ ወንጀል እየፈፀሙ ያሉ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ እየሰራው ነው ብሏል።

በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ አቃቤ ህግ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፍቃዱ ፀጋ ፥ ውሳኔ ባገኙ ጉዳዮችና በምርመራ ላይ ስላሉ ጉዳዮች ለሚዲያ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህ መግለጫቸው በቤኒሻንጉል ጉሙዝ የሰውን ልጅ ከእነ ነፍሱ ሲያቃጥሉ ከነበሩ ግለሰቦች መካከል እስካሁን ድረስ ያልተያዙ መኖራቸውን ለማወቅ ችለናል።

የሰውን ልጅ ሲያቃጥሉ ከነበሩት መካከል የፀጥታ ኃይሎች እንደነበሩ የሚታወስ ነው ፤ ከነዚህ ውስጥ በወንጀሉ የተሳተፉ 3 ሰዎች (2 የደቡብ ልዩ ኃይል አባላት እና 1 ሲቪል) በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑን አቶ ፍቃዱ ገልፀዋል።

አክለውም ፤ ሁለት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ማንነታቸው ቢለይም ወንጀሉን ከፈፀሙ በኃላ ከሰራዊቱ ከድተው በመጥፋታቸው እነሱን በቁጥጥር ስር ለማዋል የፌዴራል ፖሊስ ሙከራ እያደረገ መሆኑን ፤ ሁለት የአማራ ክልል ልዩ ኃይል አባላት በወንጀሉ ላይ ስለመሳተፋቸው በግልፅ በምስል ማስረጃ ተረጋግጦ ማንነታቸው ተለይቶ ለህግ አካላት እንዲሰጡ የክልሉ የፖሊስ አመራሮች ተጠይቀዋል ሲሉ አስረድተዋል።

ተጨማሪ ያንብቡ - https://telegra.ph/ETH-06-24-2

@tikvahethiopia
" ህግ ይከበር ፤ ፍትህ ይሰጠን "

ለማስፋፊያ ስራ ተብሎ #ህግን_ባልተከተለ መልኩ ቤታችን ፈረሰብን ያሉ በአዲስ አበባ ከተማ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ቅሬታ አቅርበዋል።

ያሉበት ቦታ ለማስፋፊያ ስራ ይፈለጋል የተባሉ ዜጎች ለማስፋፊያ አንደሚፈለግ ያወቁት ሰኔ 29/2013 ዓ/ም አንደሆነ ከዛ በፊት ስለጉዳዩ ምንም እንደማያቁ / እንዳልተነገራቸው ፤ ጉዳዩን የሚያውቁት ከወረዳው ጀምሮ እስከ መሬት ማናጅመት ድረስ ያሉ አካላቶች እንደነበሩ አስረድተዋል።

አሁን ላይ ህግን ሳይከተል መኖሪያቸው የፈረሰባቸው ወገኖች ፍትህ እንዲሰጣቸው እየጠየቁ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ክረምት ወቅት ዝናብ እየወረደባቸው ውጭ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ያንብቡ ⬇️
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-06-25
TIKVAH-ETHIOPIA
አዲስ_አበባ_፤_ኮሪያ_ሆስፒታል_አካባቢ_ያሉ_ቤቶች_ማስረጃ.pdf
ቪድዮ ፦ በአዲስ አበባ ፤ ገርጂ ኮርያ ሆስፒታል አካባቢ " ህግን ባልተከተለ መልኩ ፤ ፍርድ ቤት ለእኛ ፈርዶልን ቤታችን ፈረሰብን " ያሉ ወገኖች ፍትህ ይሰጠን በማለት ሲጠይቁ።

የ80 ዓመት እድሜ ያለቸው አዛውንት ፦

" ... ለማን አቤት ይባላል ? ለማን አቤት ልበል ? 60 ዓመት የኖርኩበትን ቦታዬን ፣ ቤቴን መንግስት ፈርዶልኝ ፣ አርብ ተፈርዶልኝ ሰኞ ውሳኔ ልቀበል ቅዳሜ ለሊት መጥተው ቤቴን አፈረሱብኝ፣ ንብረቴን አወደሙብኝ።

ልጆቼም ተበተኑ ፣ ፀሃይ እና ዝናብ እየተፈራረቀብኝ ነው። ለማን አቤት ይባላል ? የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረድልኝ ፣ ዘመዶቼ ምን ልሁን ? እንዴት እንደምሆን እስኪ ፍረዱኝ፤ የምሆነው ነገር ግራ ገብቶኛል፤ ብቻዬን ነኝ "

🔻

ሌላ እናት የአካባቢው ነዋሪ ፦

" ... በደካሞች ላይ ቤት አፍርሶ ለሌላ መስጠት ለባለሃብት መስጠት ማለት ይከብዳል ያማል።

ለሌላ ትንኮላም አልሄድን ዓመት ሙሉ ስንሟገት አርብ ተወሰነልን ተብሎ ደስታችንን ሳንጨርስ የስራ ሰዓት አዘናግተው በእረፍት ሰዓት መጥተው ቁጭ ባልንበት ነው ያፈረሱብን። ዋና ዋና እቃዎችን እንኳን ማውጣት አልቻልንም ነበር።

... እኔ ልጄን ልያዝ እቃ ልጎትት ? እነሱም ደካማ ናቸው። አባታችንም እራሳቸውን መቆጣጠር አይችሉም ። ጎረቤት ባይደርስልን የተሻለ የምንለውን እቃ ማውጣት አንችልም ነበር።

መንግስትን በጣም ነበር የምንደግፈው ለውጥ አየን ብለን ግን አሁን ላይ በሰው የምናየው ስናዝን የነበረው ነገር በራሳችን ላይ ስለተፈፀመ እግዚአብሔር ፍትህ ይስጠን።

ጠቅላይ ሚኒስትራችን ለፍትህ ነው የምቆመው ብሏል ፍትህ ይስጠን ፤ ልጅ ይዘን ነው እየኖርን ያለነው። "

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሙከጀላ በኤደን ገስላሴ.pdf
ኔሞ የሽናሻ_ታምሩ ዳኘው.pdf
305.2 KB
#4

#እኔም_የዕርቅ_ሀሳብ_አለኝ

''ኔሞ'' የሽናሻ ብሔረሰብ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት

አዘጋጅ: ታምሩ ዳኘው

" ኔሞ " ሽናሾች የሚመሩበት፣ የሚተዳደሩበት፣ እና ፍትህ የሚያገኙበት የህይወታቸው አንድ አካል ነው። የሺናሻ ብሄረሰብ በውስጡ ከ16 በላይ ንዑሳን ጎሳዎች ሲኖሩት እነዚህ ጎሳዎች ለኔሞ ስርዓት እንዲያመች ሆነው በሶስት ይከፈላሉ።

እነዚህም ጎሳዎች በብሄረሰቡ ባህል መሰረት “ሦስት ጉልቻ” ተብለው ይጠራሉ። ሦስቱ ጎሳዎች ዶዎ፣ ኢኖሮ፣ እና ኢንዲዎ ይባላሉ። ከእነዚህ ሶስቱ ጉልቻዎች አንዱ እንኳን ቢጎድል የኔሞ ስርዓትአይከወንም።

የቦሮ-ሽናሻ ብሄረሰብ ባህላዊ የፍርድ አሰጣጥ ሂደቶች አራት ደረጃዎች አሉት። እነዚህም፦

#ቡራ፦ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ የሚሰጥበት “ቡራ”በመባል ይታወቃል:: ቡራ አንድ ሽማግሌ ብቻውን ሆኖ የሚፈርድበት የቤተሰብ ባህላዊ ችሎት ነው።

#ኔማ፦ ሁለተኛ ደረጃ ፍርድ የሚሰጥበት የዳኝነት ክፍል”ኔማ” ይሰኛል። በዚህኛው ደረጃ ሦስት ሽማግሌዎች ግራናቀኝ አይተው ፍርድ ወይም ፍትህ ይሰጣሉ ተብሎ ይታመናል።

#ፄራ፦ ሶስተኛው የዳኝነት ክፍል ወይም ችሎት “ፄራ” ይባላል::ይህ ባህላዊ ችሎት የሚመራው በአንድ ባህላዊ ሹም ዳኛ ነው። በዚህ ክፍል ኔማ ችሎት መፍታት ያልቻለው ጉዳይ በጥልቀት ይታያል።

#ፋላ፦ ይህ በሺናሻ የመጨረሻ ወይም ከፍተኛ የዳኝነት አካል ነው፡፡

የሽናሾች ባህላዊ የኔሞ ስርዓት ዘመናዊውን ዳኝነት እጅጉን የማገዝ አቅም አለው። በአመክንዮአዊነቱ (ምክንያታዊነቱ) ዘመናዊ አስተሳሰብንና ፍትህን በሚዛናዊነት አስተናግዶህብረተሰቡ በሰላም ተሳስቦ መኖር እንዲችል አስተዋፅኦውወደር የሌለው በመሆኑ ትልቅ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ባህላዊ እሴት ነው።

📁 ሙሉ ጹሑፉን ከላይ ተያይዟል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" አሁንም 10 ሰዎች ታግተዋል ፤ አጋቾቹ ብር ይፈልጋሉ " - አቶ ውብሸት አበራ

ከኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ደራ ወረዳ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ከታገቱ ዜጎች መካከል እስካሁን 360ዎቹ የክልሉ መንግስት የፀጥታ ኃይሎች በሰሩት ስራ መለቀቃቸውን የደራ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ውብሸት አበራ ለአል ዓይን ኒውስ በሰጡት ቃል ገለፁ።

አጋቾቹ በራሳቸው አንድ ወንድ እና አንድ ሴት መልቀቃቸውን ዋና አስተዳዳሪው ገልፀዋል።

አሁንም 10 ሰዎች መታገታቸውን የገለፁት ዋና አስተዳዳሪው አጋቾቹ ብር እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።

ትናንት በስፍራው ከታገቱት ዜጎች ውስጥ ሁለት የደራ ባለሀብቶች እንዳሉበት ተገልጿል። ዋና አስተዳዳሪው የታጋቾችን ብዛት እና ማንነት በተመለከተ መረጃው የተገኘው አምልጠው እና ተለቀው ከመጡ ሰዎች መካከል እንደሆነ አስረድተዋል።

በሌላ በኩል ፤ በአዲስ አበባ ፍቼ ደራ መስመር የፌዴራል የጸጥታ ኃይል እንዲሰማራ ተጠይቋል።

የደራ ወረዳ አስተዳዳሪ ውብሸት አበራ የደራ ፍቼ አዲስ አበባ መስመር ላለፉት ስምንት ወራት ተዘግቶ መቆየቱን አስታውሰዋል። የመኪና መንገዱ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት ቢጀምርም ትናንት ሰዎች ግን መታገታቸውን ገልጸዋል።

አሁን ላይ የመከላከያ ሰራዊትና የፌዴራል ፖሊስ በአካባቢው እንዲሰማራ ጠይቀዋል።

ዋና አስተዳዳሪው የፌዴራል ሰራዊት እንዲሰማራ በተደጋጋሚ ጊዜ ለሰላም ሚኒስቴር ጥያቄ ማቅረባቸውን እና ምላሽ እንዳላገኙ ገልፀዋል።

#አልዓይን

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት እና ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋማት ማኅበር፣ ከግል ከፍተኛ ተቋማት የሚወጡ ምሩቃን በአንዳንድ የመንግሥትና የግል ቀጣሪዎች ተቀባይነት እንዳላገኙ አስታወቀ፡፡

ማኅበሩ ይህንን ያስታወቀው ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ረቡዕ ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ውይይት ነው፡፡

የማኅበሩ ፕሬዚዳንት ሞላ ፀጋዬ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ አንዳንድ የመንግሥትና የግል ቀጣሪዎች ከግል ከፍተኛ ተቋማት የሚወጡ ተማሪዎችን አይቀጥሩም ብለዋል፡፡

በተለያዩ የትምህርት መርሐ ግብሮች ተመርቀው በሥራ ላይ የሚገኙ ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የወጡ ሠራተኞችም፣ ‹‹የደረጃ ዕድገት አንሰጥም›› እንደተባሉም አስረድተዋል፡፡

ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተመረቁ ተማሪዎችን አንቀጥርም የሚሉ የመንግሥትና የግል ድርጅቶች መኖራቸውን፣ ከእነዚህም መካከል ባንኮችና የተለያዩ መሥሪያ ቤቶችም መሆናቸውን ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡

ከመንግሥት ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዱ መሆኑን፣ ሌሎችም የመንግሥትና የግል ተቋማት፣ ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሩ ምሩቃንን አንቀበልም (አንቀጥርም) መባላቸውን ለቋሚ ኮሚቴው ገልጸዋል፡፡

በተለይ በአንዳንድ የክልል ከተሞች ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በትምህርት መርሐ ግብር መሠረት ተመርቀው በሥራ ላይ የሚገኙ ሠራተኞች፣ የደረጃ ዕድገት እንደማያገኙና የማይቀጥሩ ተቋማት እንዳምሉ ተናግረዋል፡፡

ተመራቂ ተማሪዎችን ከማይቀበሉና ለሠራተኞችም የደረጃ ዕድገት ከሚከለክሉ ክልሎች መካከል አማራና ደቡብ ይገኙበታል ብለዋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-06-26-2

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#ZH

ያገለገሉ እና አዲስ ካሜራ እና የካሜራ እቃዎችን እንገዛለን እንሸጣለን ከታች ባለው ቴሌግራም ሊንክ ያገኙ https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEUTeB3LSYVFukiuQw

ይደውሉልን 0911284905

አድራሻ= ቦሌ ወሎ ሰፈር HMM ህንፃ 2ኛ ፍቅ 205