TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
214 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ማሳሰቢያ📣

" ከሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው " - የደብረ ማርቆስ ፖሊስ መምሪያ

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ማንኛውም ግለሠብ ከፀጥታ ሀይሎች ውጭ ያሉ ግለሠቦች ያለበቂ ምክንያት በከተማ ውስጥ መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን የከተማው ፖሊስ አሳስቧል።

መሣሪያን በመዝናኛ ቦታዎች ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ያለበቂ ምክንያት ይዞ መንቀሳቀስ የፀጥታ ሀይሉን የሚያዘናጋ እና እኩይ ተግባር ያላቸውን ግለሰቦች ለይቶ ለመቆጣጠር የማያስችል ነው ተብሏል።

ከዚህ ባለፈ የጸጥታ ሀይሉ የህግ ማስከበር ስራውን ለመስራት እንቅፋት እንደሆነበትና የተዝረከረከ የጦር መሣሪያ አያያዝ ለከተማው ህዝብ ደህንነት ስጋት እየሆነ በመምጣቱ በህግ ማስከበር ስራ ላይ ከተሠማራ የጸጥታ ሀይል ውጪ ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ በየትኛውም በከተማው ክልል ውስጥ በማንኛውም ሰአት መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እና ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይ ፦
- በአልጋ ድርጅቶች እና ሆቴሎች ፣
- በወለል ቤቶች ፣
- በዶርም ፣
- በመኖሪያ ቤት በእንግድነት የሚመጡ ግለሠቦች መሣሪያ ይዘው የመጡበትን ጉዳይ ቅድሚያ ለፖሊስ እውቅና ሳይፈጥሩ እና ፈቃድ ሳያገኙ አገልግሎት ማግኘት የለባቸውም ተብሏል።

የአልጋ ድርጅቶች ፣ ወለል አከራዮች እና የዶርም አከራዮች የተከራዮችን ማንነት እስከ ታጠቁት መሣሪያ ሙሉ አድራሻውን በመመዝገብ በየጊዜው ለፖሊስ ማሳወቅ ይገባቸዋል ተብሏል።

ማህበረሰቡ ከፀጥታ ኃይል ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ የሚንቀሳቀስ አካላትን በሚመለከትበት ግዜ ፦
0587711232 (3ኛ ፖሊስ ጣቢያ)
0587711669 (1ኛ ፖሊስ ጣቢያ)
0581785658 (2ኛ ፖሊስ ጣቢያ) በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

( ከንጋቱ 11:30 ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ድረስ)

የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር በ #መሰቀል_አደባባይ ባዘጋጀው ስፖርታዊ ዝግጅት እና መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ በሚያደርገው የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ምክንያት ነገ እሁድ ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓ.ም ከንጋቱ 11 ከ30 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰዱ መንገዶች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የሚዘጉት መንገዶች ፦

🛣 ከወሎ ሰፈር መገንጠያ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ደንበል ሲቲ ሴንተር ኦሎምፒያ አደባባይ አካባቢ

🛣 ከመገናኛ ፣ በሃያ ሁለት ወደ መስቀል አደባባይ እንዲሁም ከቦሌ መድሃኒያለም፣ በአትላስ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል ቤተ-ክርስቲያን በሰዓት 50 እና 80 ኪ.ሜ በተፈቀደባቸው በሁለቱም አቅጣጫ

🛣 ከጌጃ ሰፈር ፣ ጤና ጥበቃ፣ ብሄራዊ ቲያአትር የሚወስደው የቀድሞ ደሳለኝ ሆቴል

🛣 ከንግድ ማተሚያ ቤት በኦርማ ጋራዥ በፍል ውሃ ወደ መስቀል አደባባይ ኦርማ ጋራዥ መስቀለኛው ላይ
ከ4 ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ኮንሰን ወይም ወደ ሸራተን ሆቴል የሚወስደው መንገድ ላይ፡፡

🛣 ከሳር ቤት አካባቢ ለሚመጡ አሸከርካሪዎች አፍሪካ ህብረት ትራፊክ መብራት

🛣 ከፒያሳ አካባቢ በቸርቸር ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ፖስታ ቤት ትራፊክ መብራት ላይ

🛣 ከካዛንቺስ በፍል ውሃ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ እና በተመሳሳይ ካዛንቺስ የትራፊክ መብራት በባምቢስ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ካዛንቺስ የትራፊክ መብራት ላይ

🛣 ከጎፋ በቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ ወደ ለገሐር አዲሱ መንገድ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ቂርቆስ ቤ/ክ መስቀለኛው ላይ

🛣 ከቄራ ወደ ሜክሲኮ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ጠማማ ፎቅ አካባቢ

🛣 ከጦር ኃይሎች ፣ በልደታ ፣ ፖሊስ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወሰደው መንገድ ባልቻ ሆስፒታል መስቀለኛ

🛣 ከመርካቶ በበርበሬ በረንዳ ወደ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው አረቄ ፋብሪካ አካባቢ

🛣 ከሳሪስ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሸከርካሪዎች አጎና ሲኒማ አካባቢ

🛣 ከጎተራ በመሿለኪያ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚሄዱ አሽከርካሪዎች የቀድሞ አራተኛ ክፍለ ጦር አካባቢ መንገዱ ይዘጋል።

ህብረተሰቡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት በሚጠቁሙት አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀም እና ለትራፊክ ፖሊስ አባላት ትዕዛዝ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

ውድ ቤተሰቦቻችን ነገ እሁድ የሚያንቀሳቅሳችሁ ጉዳይ ካለ ከላይ በተገለፀው መረጃ መሰረት እንዳትጉላሉ አማራጭ መንገዶችን ተጠቀሙ።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ አማራ ባንክ በዛሬው ዕለት ተመርቆ ሥራውን በይፋ ጀምሯል። የባንኩ የምረቃ እና ስራ ማስጀመሪያ ሰነ ስርዓት ለገሃር በሚገኘው የባንኩ ዋና መስሪያ ቤት ነው የተካሄደው። በምረቃ ስነ ስርዓቱ ላይ ፦ - የብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶክተር ይናገር ደሴ ፣ - የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ - የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ የተለያዩ የመንግስት ባለስልጣናት…
#AmharaBank

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዢ ዶ/ር ይናገር ደሴ ዛሬ በዛሬው የአማራ ባንክ ይፋዊ ምረቃና ስራ ማስጀመሪያ ስነስርዓት ላይ የተናገሩት ፦

" አማራ ባንክ ወደ ገጠሩ ማህበረሰብ በመድረስና ከፍተኛ የአክስዮን ድርሻን በመሸጥ እንዲሁም ከፍተኛ የተከፈለ ካፒታል ይዞ የባንክ ኢንዱስትሪውን በመቀላቀል ቀዳሚው ነው።

በቴክኖሎጂ እና በአገልግሎት አሰጣጥም ተወዳዳሪ በመሆን ቀዳሚ መሆን እንዲችል ራሱን ሊያዘጋጅ ይገባል።

ይህ ከሃገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ከሚታሰቡ የውጭ ባንኮች ጋር ጭምር ለመወዳደር ያስችላል።

ወደ ሀገር እንደሚገቡ ከሚጠበቁት የውጭ ባንኮች ጋር ለመወዳደር ትልቅ ዝግጅት ይጠብቀናል። ለዚህም አማራ ባንክን ጨምሮ ሌሎች የኢትዮጵያ ባንኮች ራሳቸውን ሊያዘጋጁ ይገባል።

አማራ ባንክ ይህን የሚያደርግና የቁጠባ ገንዘብ አቅሙን ለማሳደግ የሚችል ከሆነ በአጭር አመታት ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ ሊደርስ ይችላል።

... 60 ሚሊዮን ገደማ ኢትዮጵያውያን የተንቀሳቃሽ ስልክ (ሞባይል) ተጠቃሚ ናቸው ፤ አማራ ባንክ የተፋጠነ የሞባይል አገልግሎትን በየደረጃው ለመስጠት መስራት አለበት።

የሞባይል አገልግሎት የሚሰጡ የውጭ ተቋማት በቅርብ ጊዜ የአገልግሎት ፈቃድ ሊያገኙ ይችላሉ፤ በአሁኑ ወቅት ቴሌ ብር ብቻ ነው አገልግሎቱን እየሰጠ የሚገኘው በመሆኑም አማራ ባንክ ቅርንጫፎችን ከመክፈት በዘለለ በቴክኖሎጂ ላይ ኢንቨስት ማድረግ ወደ ከፍታ ሊወስደው እንደሚችል አስባለሁ "

#ALAIN

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአፋር ባህላዊ እርቅ (1).pdf
ሙከጀላ በኤደን ገስላሴ.pdf
665.6 KB
#3

#እኔም_የዕርቅ_ሀሳብ_አለኝ

ሙከጀላ ባሕላዊ የዕርቅ ስርዓት በድሬዳዋ ማህበረሠብ

አዘጋጅ፦ ኤደን ገ/ስላሴ

በድሬዳዋ ሙከጀላ የሚባል የቀደመ ባሕል አለ፡፡ ሙከጀላ በማህበረሰቡ መካከል ለሚፈጠረ ማንኛውም ግጭትም ሆነ አለመግባባት በዛፍ ጥላ ሆኖ የሚመከርበት ቀደምት ባህል ነው፡፡

የዕርቁ ሂደት የሚካሔድበትን ቀንና ቦታ የሚመርጡት ማኅበረሰቡ የመረጣቸው፤ ትልቅ ቦታ በሚሰጣቸውና በሚከበሩ ትልልቅ አባቶች
ነው፡፡ የዕርቅ ሥርዓቱም የሚካሄደው በአካባቢው በሚገኘው ሙከጀላ በተባለ የዛፍ ጥላ ስር ነው፡፡

በባህሉ መሠረት ሽማግሌዎች ቀን እና ቦታ በቆረጡበት በሠአቱ ይገኛሉ፡፡ ይህም ሠዓትን የማክበር ልምድ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ የማህበረሰቡ ልምድ እና ባህል ነው፡፡

የተፈፀመው ጥፋት ተመጣጣኝ ነው ተብሎ ከታመነ ይቅር ለፈጣሪ ተባብለው እንዲያልፉት ቢደረግም በዚህ ሂደት ውስጥ ግን ጥፋቱ ከባድ ሆኖ ከተገኘ በመጀመሪያ በዳይ እግር ስር ወድቆ ይቅርታ ይጠይቃል፡፡

ከዚህ በኋላ አላጠፋም ፣ እታረማለው፣ ካሣዬንም እከፍላለው በማለት በአባቶች ፊት መሃላ ይፈፅማል፡፡ ተከሳሽም የሚከፍለው ካሣ መጠን በታዛቢዎች ፊት ለተበዳይ በግዜውና በሠዓቱ አንዲሰጥ ይወሰናል።

ባህላዊ የዕርቅ ሥርዓት ፍትህ እንዲገኝ ትልቅ አስተዋፅኦ የሚያደርገው እውነት ላይ የተመሠረተ በመሆኑ ነው፡፡ ዘርን፣ ሀይማኖትን፣ ፆታን፣ ሀብትን እና ሌሎች ልዩነቶችን ሳያደርግ ሚዛናዊ የሆነ ዳኝነት ስለሚሰጥ የባህላዊ ዕርቅ ሥርዓት ፍትህን ያስገኛል፡፡

ሙከጀላ በፊት ላይ ከፍተኛ ተቀባይነት የነበረው ቢሆንም አሁን ላይ ግን ይህ ስርዓት ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ወደ መረሳት ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ባህል አለ እንኳን ቢባል በጣም በተወሰኑ ቦታዎች ላይ ነው፡፡

📁 ሙሉ ጹሑፉን ከላይ ተያይዟል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ያላየነው ብዙ ጭካኔ ይኖር ይሁን ? በርካቶች በጋምቤላ ተቀርፆ በተሰራጨው ጨካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ቪድዮ የተሰማቸውን ሀዘን በአግባቡ ሳይወጡ ዛሬ ደግሞ አንድ ቀኑ ሆነ አድራሻው የት እንደሆነ የማይታወቅ የጅምላ ርሸና ቪድዮ ተሰራጭቷል። ለጊዜው ድርጊቱ መቼ .. ? የት ? እንዴት ? ተፈፀመ ስለሚለው ማወቅ ቢያዳግትም ከዚህ ቀደም እንዳየናቸው እጅግ በጣም ዘግናኝ እና ህጋዊ ያልሆነ የጭካኔ ተግባር…
#UPDATE #EHRC

በማህበራዊ ሚዲያ የተለቀቀው ቪድዮ

" ... በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ የሚታየው ከሕግ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት (Extra-judicial killings) ኢሰመኮ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. ሪፖርት ላይ የተካተተ ነው።

የኢሰመኮ የምርመራ ሪፖርት ከምስክሮች እና በስፍራው በመገኘት በመስክ ምልከታ ያሰባሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ፣ ድርጊቱ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ ልዩ ቦታው እንቶሊ አካባቢ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት (ቀኑ በትክክል ያልታወቀ) መፈጸሙን፤ እንዲሁም በወቅቱ በነበረው መረጃ መሰረት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሁለት የጭነት መኪኖች ጭነው ያመጡዋቸውን እና ወደ 30 የሚጠጉ የኦነግ ሸኔ አባሎች ናቸው ያሏቸውን ሰዎች በጅምላ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን ይገልጻል። 

ኢሰመኮ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ከተመለከተ በኋላ ባደረገው ተጨማሪ ማጣራትና የቴክኒክ ምርመራ፣ በመስክ ምርመራ በለየው ስፍራና በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ያለውን ስፍራ በቴክኒክ ምርመራ በማነጻጸር፣ እንዲሁም ምስሉ የተቀረጸበትን ቦታ ለማነጻጸርና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የቴክኒክ ምርመራዎችን በማድረግ፤ ከዚህ በላይ የተገለጸው በኢሰመኮ ምርመራ የተዘገበው ከፍርድ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት የሚያመለክት ተጨማሪ ማስረጃ ስለመሆኑ በምክንያታዊ አሳማኝነት አረጋግጧል "

#ኢሰመኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ያላየነው ብዙ ጭካኔ ይኖር ይሁን ? በርካቶች በጋምቤላ ተቀርፆ በተሰራጨው ጨካኔ የተሞላበት አረመኔያዊ ቪድዮ የተሰማቸውን ሀዘን በአግባቡ ሳይወጡ ዛሬ ደግሞ አንድ ቀኑ ሆነ አድራሻው የት እንደሆነ የማይታወቅ የጅምላ ርሸና ቪድዮ ተሰራጭቷል። ለጊዜው ድርጊቱ መቼ .. ? የት ? እንዴት ? ተፈፀመ ስለሚለው ማወቅ ቢያዳግትም ከዚህ ቀደም እንዳየናቸው እጅግ በጣም ዘግናኝ እና ህጋዊ ያልሆነ የጭካኔ ተግባር…
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን በመዘዋወር ላይ የሚገኘውን እና በርካታ ሰዎች ከመኪና እንዲወርዱ በማድረግ በጅምላ ሲገደሉ የሚያሳየውን ተንቀሳቃሽ ምስል ሁኔታ መርምሯል።

በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ የሚታየው ከሕግ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት (Extra-judicial killings) ኢሰመኮ መጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም. “በኢትዮጵያ የአፋር እና የአማራ ክልሎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች እና የዓለም አቀፍ የሰብአዊነት ሕግ ጥሰቶች ላይ የተደረገ ምርመራ ሪፖርት” በሚል ርዕስ ባወጣው ሪፖርት ውስጥ ከተዘረዘሩት ክስተቶች ውስጥ አንዱ መሆኑን ተረድቷል። 

በዚሁ የኢሰመኮ የምርመራ ሪፖርት ከምስክሮች እና በስፍራው በመገኘት በመስክ ምልከታ ያሰባሰበውን መረጃ መሰረት በማድረግ፣ ድርጊቱ በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ደዋ ጨፋ ወረዳ ልዩ ቦታው እንቶሊ አካባቢ በታኅሣሥ ወር 2014 ዓ.ም. የመጀመሪያ ሳምንት (ቀኑ በትክክል ያልታወቀ) መፈጸሙን፤ እንዲሁም በወቅቱ በነበረው መረጃ መሰረት የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በሁለት የጭነት መኪኖች ጭነው ያመጡዋቸውን እና ወደ 30 የሚጠጉ የኦነግ ሸኔ አባሎች ናቸው ያሏቸውን ሰዎች በጅምላ በጥይት ደብድበው መግደላቸውን ይገልጻል። 

ኢሰመኮ ተንቀሳቃሽ ምስሉን ከተመለከተ በኋላ ባደረገው ተጨማሪ ማጣራትና የቴክኒክ ምርመራ፣ በመስክ ምርመራ በለየው ስፍራና በተንቀሳቃሽ ምስሉ ላይ ያለውን ስፍራ በቴክኒክ ምርመራ በማነጻጸር፣ እንዲሁም ምስሉ የተቀረጸበትን ቦታ ለማነጻጸርና ለማረጋገጥ የሚያስችሉ የቴክኒክ ምርመራዎችን በማድረግ፤ ከዚህ በላይ የተገለጸው በኢሰመኮ ምርመራ የተዘገበው ከፍርድ ውጭ የተፈጸመ የግድያ ድርጊት የሚያመለክት ተጨማሪ ማስረጃ ስለመሆኑ በምክንያታዊ አሳማኝነት አረጋግጧል፡፡

ስለሆነም ኢሰመኮ ከዚህ ቀደም ባቀረበው ምክረ ሃሳብ መሰረት የተሟላ የወንጀል ምርመራ ተደርጎ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በድጋሚ ያሳስባል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን
ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ/ም

@tikvahethiopia
#OromiaRegion

ጊምቢ ወረዳ በርካታ ሰዎች ተገደሉ።

በዛሬው ዕለት #በምዕራብ_ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ውስጥ በርካታ ንፁሃን በታጣቂዎች መገደላቸው ተሰምቷል።

መልዕክታቸውን የላኩ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በአካባቢው ይንቀሳቀሳል ያሉት የታጠቀ ቡድን ጥቃት ከፍቶ #በርካታ ሰዎች መገደለቸውን (ትክክለኛ ቁጥሩን ለማወቅ አዳጋች ነው) ታግተው የተወሰዱ መኖራቸውን እንዲሁም ነፍሳቸውን ለማትረፍ ወደ ጫካ የሸሹ ስለመኖራቸውን ገልፀዋል።

ከሟቾች መካከል ህፃናት እና ሴቶች እንደሚበዙ ፤ ቤቶች መንደዳቸውንም ፤ ጥቃቱ ሲፈፀም የነበረው በከባድ መሳሪያ ጭምር እንደነበር አመልክተዋል።

ለሚመለከተው የወረዳው አካል በሰዓቱ ጥቃት መኖሩን ጥቆማ ቢያደርሱም በቶሎ የደረሰ አካል እንዳልነበረ አስረድተዋል።

የዛሬውን እጅግ አሳዛኝ ጥቃት ክልሉም አምኖ አረጋግጧል። ጥቃቱን ጭካኔ የተሞላበትም ነበር ብሏል።

ክልሉ ባወጣው መግለጫ " የሸኔ ቡድን በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ባደረሰው ጥቃት በንጹሃን እና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል " ብሏል።

" ቡድኑ መንግሥት እየወሰደበት ያለውን እርምጃ መቋቋም ሲያቅተው በንጹሃን ላይ ጭካኔ የተሞላበት ጥቃት አድርሷል " ሲል ገልጿል።

በቡድኑ ላይ የፌደራል እና የክልሉ የጸጥታ አካላት የሚወስዱትን እርምጃ አጠናክረው ይቀጥላሉም ብሏል።

ክልሉ ምን ያህል ንፁሃን እንደተገደሉ እንዲሁም ታፍነው ስለተወሰዱ ሰዎች ምንም ያለው ነገር የለም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጋምቤላ ክልል ፡ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ከሕግ አግባብ ውጭ የተፈጸሙ የኃይል እርምጃዎች ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በጋምቤላ ከተማ፣ ጋምቤላ ክልል ከጠዋት እስከ ምሽት የቀጠለ ግጭት እና የፀጥታ እና የደኅንነት ችግርን ተከትሎ ለአንድ ቀን የከተማዋ የመንግሥት አገልግሎቶች፣ የንግድ እንቅስቃሴዎች እና ሌሎችም አገልግሎቶች ተቋርጠው መዋላቸው ይታወሳል። ጥቃቱ በኦሮሞ ነጻነት ግንባር (በተለምዶ ኦነግ…
#Gambella

በጋምቤላ በዚህ ሳምንት ከተፈፀመው ጥቃት ጋር በተያያዘ ንፁሃን ዜጎች ላይ ከማዋከብ አንስቶ እስከ ግድያ የደረሰ ከዚህም በተጨማሪ የዝርፊያ ድርጊት መፈፀሙ መጠቆሙ ይታወሳል።

ክልሉ ካለው ነባራዊ ሁኔታ ጋር በተያያዘ ንፁሃን ሰለባ እንዳይሆኑ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረገ መሆኑን መግለፁ አይዘነጋም።

በከተማው አንድ ወጣት እጁን ወደ ኃላ ታስሮ የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ እና ባለሰቡ አካላት በጥይት ሲደብደብ የሚያሳይ ቪድዮ መሰራጨቱ በርካቶችን አስዝኖም አቆጥቶም ነበር ፤ ይህን ተከትሎ ክልሉ በሰጠው መግለጫ ይህንን ጉዳይ በግልፅ አፍረጥርጦ ባይናገርም ከህግ ውጪ የሆነ ድርጊት የፈፀሙና የስነ- ምግባር ጉድለት ያለባቸው የፀጥታ አካላት እንዳሉ አረጋግጦ ህጋዊ እርምጃ መዉሰድ መጀመሩን አስታውቆ ነበር።

ትላንት ሪፖርተር ጋዜጣ ይዞት በወጣው ዘገባ ደግሞ ክልሉ አንድ ወጣት በጥይት የመደብደቡን ክስተት አረጋግጦ ፤ ከሕግ ውጪ ግድያ በፈጸሙ የፀጥታ ኃይሎች ላይ ዕርምጃ ተወስዷል ብሏል።

የጋምቤላ ክልል ኮሙዩኒኬሸን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡጉት አዲንግ " የኦነግ ሸኔና የጋምቤላ ነፃ አውጪ ቡድን አባላት ለይቶ ሕጋዊ ዕርምጃ የመውሰዱ ጥረት ፈታኝ ነበር " ያሉ ሲሆን " በዚህ የተነሳ ጥንቃቄ ሳያደርጉ ወይም በእልህና በቁጣ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ዕርምጃ የወሰዱ የፀጥታ አስከባሪዎች ነበሩ " ብለዋል።

#አንድ የልዩ ኃይልና #አንድ የመደበኛ ፖሊስን ጨምሮ ሁለት የፀጥታ አስከባሪዎች በሕገወጥ ግድያ ተጠርጥረው ተይዘዋል ሲሉ አሳውቀዋል።

ጥቃት የከፈቱት ታጣቂዎች ሲቭልም የለበሱ ስለነበሩ እንዲሁም አንዳንዶቹ የትጥቅ ልብሳቸው ቀይረው ከህብረተሰቡ ጋር መቀላቀላቸው ሁኔታዎች ፈታኝ አድርጎት እንደነበርም ለጋዜጣው ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OromiaRegion ጊምቢ ወረዳ በርካታ ሰዎች ተገደሉ። በዛሬው ዕለት #በምዕራብ_ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ ውስጥ በርካታ ንፁሃን በታጣቂዎች መገደላቸው ተሰምቷል። መልዕክታቸውን የላኩ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በአካባቢው ይንቀሳቀሳል ያሉት የታጠቀ ቡድን ጥቃት ከፍቶ #በርካታ ሰዎች መገደለቸውን (ትክክለኛ ቁጥሩን ለማወቅ አዳጋች ነው) ታግተው የተወሰዱ መኖራቸውን እንዲሁም ነፍሳቸውን ለማትረፍ…
#EHRC

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥት እና በታጠቁ ኃይሎች በሲቪል ሰዎች ላይ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶችን በቅርበት በመከታተል ላይ ይገኛል። 

ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም. በምዕራብ ወለጋ ዞን ግምቢ ወረዳ ቡሌ ቀበሌ በመንግሥት እና በኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት (በተለምዶ ‘ኦነግ ሸኔ’) ታጣቂዎች መካከል ሲደረግ ከነበረው ውጊያ ጋር በተያያዘ በታጣቂው ቡድን በአካባቢው በሚኖሩ ሲቪል ሰዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት በሰው ሕይወት፣ አካል እና ንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፡፡

አሁንም በአካባቢው ከፍተኛ የፀጥታ ስጋት በመኖሩ ምክንያት ነዋሪዎች በአፋጣኝ ድጋፍ እንዲደርስላቸው በመጠየቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ 

የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ መንግሥት በሲቪል ሰዎች ላይ ተጨማሪ ጥቃት እንዳይፈጸም አስፈላጊ የሆኑ የመከላከል እርምጃዎችን እንዲወስድ፣ በማንኛውም ሁኔታ ሲቪል ሰዎች የጥቃት ዒላማ እንዳይደረጉ ተገቢ የሆነ ጥንቃቄና ጥበቃ እንዲያደርግ፣ እንዲሁም ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንዲያፈላልግ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን
ሰኔ 12 ቀን 2014 ዓ/ም

@tikvahethiopia
ደሴ እና ወልዲያን ጨምሮ በርካታ ከተሞች ኤሌክትሪክ ተቋርጧል።

የ66 ኪቮ ኤሌክትሪክ አስተላለፊ መስመር ተሸካሚ የብረት ታወሮች በመውደቃቸው ፦
- ደሴ፣
- ቢስቲማ፣
- አልብኮ፣
- ኩታበር እና በአካባቢያቸው ባሉ ከተሞች እንዲሁም ከወልድያ ሳብስቴሽን የሚያገኙ በሙሉ ፦
- ወልድያ፣
- ሳንቃ፣
- በቂሎ ማነቂያ፣
- ስርንቃ፣
- መርሳ ፣
- ውጫሌ እና በአካባቢያቸው ባሉ ከተሞች ኤሌክትሪክ መቋረጡን የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።

ጉዳቱ የደረሰው ከኮምቦልቻ ደሴ ባለዉ 2ኛው የ66 ትራንስሚሽን መስመር ላይ 1 ታወር መዉደቅ እና 1 ታወር የመሰበር ጉዳት በመድረሱ እና በተጨማሪም ከደሴ ወልደያ ባለዉ መስመርም ብልሽት በማጋጠሙ መሆኑ ተገልጿል።

የብረት ታወሮቹ እየወደቁ ያሉት ብረቶቹ በሌቦች በመሰረቃችው ምክንያት የሚመጣውን ነፋስ መቋቋም ባለመቻላቸው ነው ተብሏል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተባባሰ የመጣው የኤሌክትሪክ አስተላላፊ መስመር ተሸካሚ ታወር /የብረት ምሰሶ/ ስርቆት በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ከፍተኛ ማነቆ እየፈጠረበት መሆኑና ደንበኞች ጥራት ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል እናዳያገኙ እያደረገ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።

ይህ እኩይ ተግባር ሊቆም የሚችለው በየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደር አካላት በመሰረተ ልማት ጥበቃ ላይ የማህበረሰብ ንቅናቄ በመፍጠር ጥበቃ እንዲደረግላቸው የጋራ ጥረት ማድረግ ሲቻል ብቻ ነው ሲል አስገንዝቧል።

በየደረጃው የሚገኙ የአስተዳደር፣ የፀጥታ እና የፍትህ ተቋማት በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የሚደርሰውን ስርቆትና ውድመት በማስቆም ረገድ የድርሻቸው እንዲወጡ አሳስቧል።

ህብረተሰቡም የስርቆት ተግባር ሲፈፀም ወይም አጠራጣሪ ጉዳዮችን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ቀርቧል።

ምንጭ፦ የአማራ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

@tikvahethiopia