TIKVAH-ETHIOPIA
#DiamondLeague 🇪🇹 በሴቶች የ5 ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀቁ። በኦስሎ ከተማ ዳይመንድ ሊግ ውድድር እየተካሄደ ሲሆን ከጥቂት ደቂቃ በፊት በተጠናቀቀው የ5 ሺህ ሜትር የሴቶች ሩጫ ውድድር ፦ 1ኛ. ዳዊት ስዩም (የግል ሰዓቷን በማሻሻል 14:25.84) 2ኛ. ጉዳፍ ፀጋይ 3ኛ. ለተሰንበት ግደይ ተከታትለው በመግባት ማሸነፍ ችለዋል። ሌሎች በውድድሩ ላይ የተካፈሉት…
#Update 🇪🇹
በወንዶች 5 ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀቁ።
1ኛ ጥላሁን ሃይሌ ፣ 2ኛ ሳሙኤል ተፈራ፣ 3ኛ ጌትነት ዋሌ በተከታታይ በመግባት አሸንፈዋል።
ሌሎች ውድድሩን የተካፈሉ አትሌቶች ሚልኬሳ መንገሻ 5ኛ፣ አሊ አብዱለመና 10ኛ ሆነው አጠናቀዋል።
ቲክቫህ ስፖርት https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x
@tikvahethiopia
በወንዶች 5 ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀቁ።
1ኛ ጥላሁን ሃይሌ ፣ 2ኛ ሳሙኤል ተፈራ፣ 3ኛ ጌትነት ዋሌ በተከታታይ በመግባት አሸንፈዋል።
ሌሎች ውድድሩን የተካፈሉ አትሌቶች ሚልኬሳ መንገሻ 5ኛ፣ አሊ አብዱለመና 10ኛ ሆነው አጠናቀዋል።
ቲክቫህ ስፖርት https://t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ አንዳንድ የፀጥታ ኃይሎች ፍፁም ህግን ባልተከተለ እንዲሁም ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ሰዎችን ሲደበድቡ ፣ በጥይት ተኩሰው ሲገድሉ፣ በህይወት ያለን ሰው በእሳት ሲያቃጥሉ ተመልክተናል።
የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ከወራት በፊት በአዲስ አበባ (አንዲት እናት በፖሊስ ስትደበደብ) ፣ በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንዲሁም በትግራይ ክልል የተፈፀሙና ተቀረፃው የተሰራጩ እጅግ አሳዛኝ እና ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ዋነኞቹ ናቸው።
አሁን ዳግሞ በአዲስ አበባ ከተማ እና በጋምቤላ እንደተፈፀሙ የተገለፀላቸው በፍፁም ህግን ያልተከተሉ ድርጊቶች በቪድዮ ተሰራጭተዋል።
በአዲስ አበባ አንድ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም የለበሰ ተማሪ በፖሊስ አባላት ተከቦ ሲደበደብ ይታያል ፤ አንዱን ተማሪ የሚደበድቡት የነበሩት ቁጥራቸው ከሁለት በላይ የሆኑ የፖሊስ አባላት ተሰብስበው ነው።
ህግ እያለ በአግባቡ መጠየቅ እየተቻለ ይህንን ማድረግ ለምን አስፈለግ ? የፀጥታ ኃይላት ህግን ማስከበር እና የማያውቁትን ማስተማር ሲገባቸው በዚህ አይነት ድርጊት መሳተፋቸው ምን ይባላል ?
ሌላው ከጋምቤላ የወጣ ቪድዮ አንድ ወጣት እጁን ወደኃላ ተስሮ በጥይት ሲደበደብ ይታያል። ወጣቱን በጥይት ሲደበድቡ የነበሩት የፀጥታ ኃይል ልብስ የለበሱ እንዲሁም የፀጥታ ኃይል ልብስ ያለበሱ ሰዎች ተሰብስበው ነው።
በእርግጥ ከተማዋ ከቀናት በፊት ያስተናገደችው ክስተት የሚታወቅ ቢሆንም ይህን መሰል እጅግ ኢሰብዓዊ ፣ የጭካኔ ድርጊት መፈፀም ለምን አስፈለገ ? ሰው ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ እንኳን በህግ መጠየቅ አይቻልም ? ግልፅ ምላሽ ያስፈልጋል።
ውድ ቤተሰቦቻችን ጉዳዩን በተለመከተ ኢሰመኮ ክትትል እያደረገ እንደሆነ ጠይቀን የምንልክላችሁ ይሆናል።
@tikvahethiopia
ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ አንዳንድ የፀጥታ ኃይሎች ፍፁም ህግን ባልተከተለ እንዲሁም ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ሰዎችን ሲደበድቡ ፣ በጥይት ተኩሰው ሲገድሉ፣ በህይወት ያለን ሰው በእሳት ሲያቃጥሉ ተመልክተናል።
የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ከወራት በፊት በአዲስ አበባ (አንዲት እናት በፖሊስ ስትደበደብ) ፣ በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንዲሁም በትግራይ ክልል የተፈፀሙና ተቀረፃው የተሰራጩ እጅግ አሳዛኝ እና ኢሰብዓዊ ድርጊቶች ዋነኞቹ ናቸው።
አሁን ዳግሞ በአዲስ አበባ ከተማ እና በጋምቤላ እንደተፈፀሙ የተገለፀላቸው በፍፁም ህግን ያልተከተሉ ድርጊቶች በቪድዮ ተሰራጭተዋል።
በአዲስ አበባ አንድ የትምህርት ቤት ዩኒፎርም የለበሰ ተማሪ በፖሊስ አባላት ተከቦ ሲደበደብ ይታያል ፤ አንዱን ተማሪ የሚደበድቡት የነበሩት ቁጥራቸው ከሁለት በላይ የሆኑ የፖሊስ አባላት ተሰብስበው ነው።
ህግ እያለ በአግባቡ መጠየቅ እየተቻለ ይህንን ማድረግ ለምን አስፈለግ ? የፀጥታ ኃይላት ህግን ማስከበር እና የማያውቁትን ማስተማር ሲገባቸው በዚህ አይነት ድርጊት መሳተፋቸው ምን ይባላል ?
ሌላው ከጋምቤላ የወጣ ቪድዮ አንድ ወጣት እጁን ወደኃላ ተስሮ በጥይት ሲደበደብ ይታያል። ወጣቱን በጥይት ሲደበድቡ የነበሩት የፀጥታ ኃይል ልብስ የለበሱ እንዲሁም የፀጥታ ኃይል ልብስ ያለበሱ ሰዎች ተሰብስበው ነው።
በእርግጥ ከተማዋ ከቀናት በፊት ያስተናገደችው ክስተት የሚታወቅ ቢሆንም ይህን መሰል እጅግ ኢሰብዓዊ ፣ የጭካኔ ድርጊት መፈፀም ለምን አስፈለገ ? ሰው ጥፋተኛ ሆኖ ቢገኝ እንኳን በህግ መጠየቅ አይቻልም ? ግልፅ ምላሽ ያስፈልጋል።
ውድ ቤተሰቦቻችን ጉዳዩን በተለመከተ ኢሰመኮ ክትትል እያደረገ እንደሆነ ጠይቀን የምንልክላችሁ ይሆናል።
@tikvahethiopia
#UNHCR
" ባለፈው ዓመት ብቻ በዓለም ላይ 89.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በጦርነት፣ ጥቃት እና የሰብዓዊ መብት ረገጣ ምክንያት ከሀገራቸው ተገፍተው ወጥተዋል ፤ ይህም ብዛት ከዚህ በፊት ያልታየ ነው " - የተመድ የስደተኞች ጉዳይ የዛሬ ሪፖርት
@tikvahethiopia
" ባለፈው ዓመት ብቻ በዓለም ላይ 89.3 ሚሊዮን የሚሆኑ ሰዎች በጦርነት፣ ጥቃት እና የሰብዓዊ መብት ረገጣ ምክንያት ከሀገራቸው ተገፍተው ወጥተዋል ፤ ይህም ብዛት ከዚህ በፊት ያልታየ ነው " - የተመድ የስደተኞች ጉዳይ የዛሬ ሪፖርት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ አንዳንድ የፀጥታ ኃይሎች ፍፁም ህግን ባልተከተለ እንዲሁም ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ሰዎችን ሲደበድቡ ፣ በጥይት ተኩሰው ሲገድሉ፣ በህይወት ያለን ሰው በእሳት ሲያቃጥሉ ተመልክተናል። የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ከወራት በፊት በአዲስ አበባ (አንዲት እናት በፖሊስ ስትደበደብ) ፣ በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንዲሁም በትግራይ ክልል የተፈፀሙና ተቀረፃው…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update
የአዲስ አበባ ፖሊስ ተማሪ ላይ የድብደባ ወንጀል የፈፀሙ የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።
ፖሊስ ድርጊቱ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር ሆቴል በሚባል አካባቢ ሰኔ 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ መፈፀሙን ገልጿል።
ተማሪው በክፍል ውስጥ ርንቺት ተኩሶ ከት/ቤት ውስጥ አምልጦ መሄዱን ከዛም በኃላ አራት የፖሊስ አባላት ተከታትለው በመያዝ የድብደባ ወንጀል እንደፈፀሙበት አስረድቷል።
ህገ- ወጥ ድርጊቱ እንደተፈፀመ ፖሊስ በደረሰው መረጃ እና ባደረገው ማጣራት ድል በር 2ኛ ደረጃ በሚባል ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ነው በሚል ፕሮግራም ላይ በክፍል ውስጥ በተደረገ ዝግጅት ተማሪው ርችት እንደተኮስ እና በትምህርት ቤት ውስጥ ርችት መተኮሱ ሌሎች ተማሪዎችን እንደረበሻቸው ፖሊስ መረጃ እንደደረሰው ገልጿል።
በእለቱ ድርጊቱን ፈፅሟል የተባለው ተማሪ ከት/ቤቱ ቅጥር ግቢ እንደወጣ የተነገራቸው 4 የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት ክትትል በማድረግ ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር የሚባል ሆቴል አካባቢ ተማሪውን ይዘውት ተገቢ ያልሆነ ድብደባ ፈፅመውበታል ብሏል።
ፖሊስ መረጃው ካደርሰው በኋላ ተጠርጣሪ የፖሊስ አባላቱን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ገልጿል።
በማነኛውም ሁኔታ ውስጥ የህግ አስከባሪነት መነሻው ህግን ማክበር መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ የዜጎችን ህጋዊ መብት በሚፃረሩ የፖሊስ አባላት ላይ የሚወሰደውን ዕርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልና በማንኛውም ሁኔታ ህገወጥ ተግባራት ሲፈፀሙ ህ/ሰቡ በያገባኛል ስሜት የሚሰጠውን መረጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ፖሊስ ተማሪ ላይ የድብደባ ወንጀል የፈፀሙ የፖሊስ አባላትን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን ዛሬ አሳውቋል።
ፖሊስ ድርጊቱ በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 7 ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር ሆቴል በሚባል አካባቢ ሰኔ 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ መፈፀሙን ገልጿል።
ተማሪው በክፍል ውስጥ ርንቺት ተኩሶ ከት/ቤት ውስጥ አምልጦ መሄዱን ከዛም በኃላ አራት የፖሊስ አባላት ተከታትለው በመያዝ የድብደባ ወንጀል እንደፈፀሙበት አስረድቷል።
ህገ- ወጥ ድርጊቱ እንደተፈፀመ ፖሊስ በደረሰው መረጃ እና ባደረገው ማጣራት ድል በር 2ኛ ደረጃ በሚባል ት/ቤት የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ነው በሚል ፕሮግራም ላይ በክፍል ውስጥ በተደረገ ዝግጅት ተማሪው ርችት እንደተኮስ እና በትምህርት ቤት ውስጥ ርችት መተኮሱ ሌሎች ተማሪዎችን እንደረበሻቸው ፖሊስ መረጃ እንደደረሰው ገልጿል።
በእለቱ ድርጊቱን ፈፅሟል የተባለው ተማሪ ከት/ቤቱ ቅጥር ግቢ እንደወጣ የተነገራቸው 4 የጉለሌ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ አባላት ክትትል በማድረግ ሰሜን ማዘጋጃ ጋበር የሚባል ሆቴል አካባቢ ተማሪውን ይዘውት ተገቢ ያልሆነ ድብደባ ፈፅመውበታል ብሏል።
ፖሊስ መረጃው ካደርሰው በኋላ ተጠርጣሪ የፖሊስ አባላቱን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ እንደሚገኝ ገልጿል።
በማነኛውም ሁኔታ ውስጥ የህግ አስከባሪነት መነሻው ህግን ማክበር መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ የዜጎችን ህጋዊ መብት በሚፃረሩ የፖሊስ አባላት ላይ የሚወሰደውን ዕርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥልና በማንኛውም ሁኔታ ህገወጥ ተግባራት ሲፈፀሙ ህ/ሰቡ በያገባኛል ስሜት የሚሰጠውን መረጃ አጠናክሮ እንዲቀጥል ፖሊስ ጥሪ አስተላልፏል፡፡
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Alert🚨 በራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ የተነሳውን እሳት መቆጣጠር አልተቻለም። በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 016 ቀበሌ በተለምዶ ራስ ጠቆሮ እየተባለ በሚጠራ ጥብቅ ደን ላይ ሰኔ 6/2014 ሌሊት ጀምሮ የተከሰተው የእሳት አደጋን እስካሁን ድረስ መቆጣጠር አልተቻለም። በጥብቅ ደኑ ውስጥ ወይራ፣ ጥድ፣ ኮሶ፣ ዝግባና ሌሎች የደን ሐብቶች እንዲሁም የተለያዩ እንሰሳትና አዕዋፋት እንደሚገኙ ተጠቁሟል።…
#Update
" እሳቱ 4 ሄክታር መሬት ላይ የሚገኝ ደን ላይ ጉዳት አድርሷል "
በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 016 ቀበሌ ራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ 4 ሄክታር መሬት ላይ የሚገኝ ደን ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿጻ።
ሰኔ 6/2014 ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ በራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ ሰኔ 9/2014 ዓም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተነግሯል።
የእሳት አደጋው ወደሌላ አካባቢ እንዳይዛመትና እሳቱን ለማጥፋት የአካቢቢው ማህበረሰብ፣ መምህራንና የፀጥታ ኃይሎች እርብርብ ማድረጋቸውን ተገልጿል።
በደረሰው የእሳት አደጋም ወይራ ፣ጥድ፣ ኮሶ፣ ዝግባና ሌሎች ሐገር በቀን ደኖች ላይ ጉዳት ደርሷል።
የራስ ጠቆሮ ደን ስፋት 8 ሄክታር ስፋት ሲሆን አራት ሄክታሩ መሬት ላይ የሚገኘው ጥብቅ ደን ላይ ጉዳት መድረሱ ተረጋግጧል።
በአምባሰል ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ከራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ቃጠሎ ጋር ተያይዞ አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ነው ብሏል። የአደጋው መንስኤ የእርሻ ማሳን ለማስፋፋት በተለኮሰ እሳት መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
መረጃው የአምባሰል ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
" እሳቱ 4 ሄክታር መሬት ላይ የሚገኝ ደን ላይ ጉዳት አድርሷል "
በደቡብ ወሎ ዞን አምባሰል ወረዳ 016 ቀበሌ ራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ በደረሰው የእሳት አደጋ 4 ሄክታር መሬት ላይ የሚገኝ ደን ላይ ጉዳት ማድረሱ ተገልጿጻ።
ሰኔ 6/2014 ዓ.ም ሌሊት ጀምሮ በራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ላይ የደረሰው የእሳት አደጋ ሰኔ 9/2014 ዓም ከቀኑ 5 ሰዓት ላይ በቁጥጥር ስር መዋሉን ተነግሯል።
የእሳት አደጋው ወደሌላ አካባቢ እንዳይዛመትና እሳቱን ለማጥፋት የአካቢቢው ማህበረሰብ፣ መምህራንና የፀጥታ ኃይሎች እርብርብ ማድረጋቸውን ተገልጿል።
በደረሰው የእሳት አደጋም ወይራ ፣ጥድ፣ ኮሶ፣ ዝግባና ሌሎች ሐገር በቀን ደኖች ላይ ጉዳት ደርሷል።
የራስ ጠቆሮ ደን ስፋት 8 ሄክታር ስፋት ሲሆን አራት ሄክታሩ መሬት ላይ የሚገኘው ጥብቅ ደን ላይ ጉዳት መድረሱ ተረጋግጧል።
በአምባሰል ወረዳ ፖሊስ ጽህፈት ቤት ከራስ ጠቆሮ ጥብቅ ደን ቃጠሎ ጋር ተያይዞ አንድ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ነው ብሏል። የአደጋው መንስኤ የእርሻ ማሳን ለማስፋፋት በተለኮሰ እሳት መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።
መረጃው የአምባሰል ወረዳ ኮሚኒኬሽን ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ችሎት በትላንትናው እለት 06/10/2014 ዓ.ም በደረሰው መጥሪያ መሰረት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአራዳ ምድብ ቻሎት ዛሬ ጠዋት 3:00 ሰዓት ላይ የቀረበው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አቃቤ ህግ ቀርቦ ተጨማሪ 15 የክስ መመሥረቻ ቀን ጠይቆ ተፈቅዶለታል ስለሆነም ለሰኔ 22/2014ዓ.ም ጠዋት 3 ሰዓት ተቀጥሯል። በተመሳሳይ ጋዜጠኛ መዓዛ እንዲሁም ጋዜጠኛ ሰለሞን ላይ የተጠየቀው…
#Update
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ለዛሬ 10/2014 ዓ.ም በሰጠው ቀጠሮ ላይ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬን በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ትዕዛዙን ተከትሎ ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ከእስር መፈታቱ ተረጋግጧል።
@tikvahethiopia
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ለዛሬ 10/2014 ዓ.ም በሰጠው ቀጠሮ ላይ ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬን በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ትዕዛዙን ተከትሎ ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ከእስር መፈታቱ ተረጋግጧል።
@tikvahethiopia
#Update
የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የጤና ሚኒስቴር ከግንቦት 01 - 04/2014 ዓ.ም የተሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ከሰኔ 10/2014 ዓ.ም ጀምሮ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራቸውን (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ አሳውቋቃ።
በውጤት ላይ ቅሬታ ያላቸው ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936/ 0118275337 በመደወል ወይም በኢሜይል [email protected] ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄያቸድን ማቅረብ እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የጤና ሚኒስቴር ከግንቦት 01 - 04/2014 ዓ.ም የተሰጠውን የብቃት ምዘና ፈተና የወሰዱ ተመዛኞች ከሰኔ 10/2014 ዓ.ም ጀምሮ hple.moh.gov.et ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራቸውን (Registration No) በማስገባት የፈተና ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ አሳውቋቃ።
በውጤት ላይ ቅሬታ ያላቸው ተመዛኞች ውጤት ከተገለጸበት ዕለት አንስቶ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0118275936/ 0118275337 በመደወል ወይም በኢሜይል [email protected] ላይ ሙሉ ስም፣ ዲፓርትመንት፣ የመለያ ቁጥር እና የተማራችሁበትን የትምህርት ተቋም ስም በመሙላት ጥያቄያቸድን ማቅረብ እንደሚችሉ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA ከዚህ ቀደም በተለያዩ አካባቢዎች ላይ አንዳንድ የፀጥታ ኃይሎች ፍፁም ህግን ባልተከተለ እንዲሁም ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ሰዎችን ሲደበድቡ ፣ በጥይት ተኩሰው ሲገድሉ፣ በህይወት ያለን ሰው በእሳት ሲያቃጥሉ ተመልክተናል። የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ከወራት በፊት በአዲስ አበባ (አንዲት እናት በፖሊስ ስትደበደብ) ፣ በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል እንዲሁም በትግራይ ክልል የተፈፀሙና ተቀረፃው…
#Update
2 ጉዳዮች ከጋምቤላ፦
ዛሬ የጋምቤላ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አጉቱ አዲንያግ በወቅታዊ ጉዳይ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ክልሉ ንፁሃን ላይ የሚደርስን ጉዳት ለመቆጣጠር ከፀጥታ ኃይሎች በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። ኃላፊው በከተማይቱ ብሄርን መሰረት አድርጎ ጥቃት አልተፈፀመም ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚነገረው ወሬ ሁሉ ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል።
ነገር ግን ከከተማው ህዝብ ጋር ተመሳሳይለው ተጨማሪ ጥቃት ሊከፍቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የታጣቂዎቹ ጦር ላይ እርምጃ ተወስዷል ሲሉ ገልፀዋል።
ሌላው ኃላፊው ከሰሞኑ ግጭት ጋር በተያያዘ የስነ- ምግባር ጉድለት ያለባቸው የፀጥታ አካላት እንዳሉ መንግስት ባደረገው ማጣራት ማረጋገጡን ገልፀው ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ህጋዊ እርምጃ መዉሰድ መጀመሩን አስታውቀዋል።
እርምጃው ምን እንደሆነ እንዲሁም የፈፀሙትን ድርጊት ግልፅ አድርገው አላብራሩም።
በቀጣይም ያልተገባ ተግባር የፈፀሙና የሚፈፅሙ የፀጥታ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለዉ ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ማስታወሻ፦ ከቀናት በፊት በጋምቤላ በተፈጠረው ክስተት የታጣቂዎችን እንቅስቃሴ መግታት ከተቻለ በኃላ ንፁሃንን ከአማፅያን (ታጣቂዎች) ጋር አደባልቆ የማየት እና በአንዳንድ ሰፈሮችም ንፁሃንን የማንገላታት ከዚህም አልፎ የማጥቃት ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን የሞቱ ሰዎችም ስለመኖራቸው እንደሰሙን ይህ ህጋዊ ያልሆነ ድርጊት በአፋጣኝ እንዲቆም የጋምቤላ ቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጥቆማ መስጠታቸው የሚዘነጋ አይደለም።
ሌላው፥ አንድ ወጣት እጁን ወደኃላ ታስሮ የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ እና ባለበሱ ሰዎች በጥይት ሲደበደብ የሚያሳይ ቪድዮ መሰራጨቱን ተከትሎ ማብራሪያ እንዲሰጥ እየተጠየቀ ነበር፤ በዚህ ላይ ግልፅ ማብራሪያ አልተሰጠም።
@tikvahethiopia
2 ጉዳዮች ከጋምቤላ፦
ዛሬ የጋምቤላ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አጉቱ አዲንያግ በወቅታዊ ጉዳይ ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።
በዚህም ክልሉ ንፁሃን ላይ የሚደርስን ጉዳት ለመቆጣጠር ከፀጥታ ኃይሎች በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል። ኃላፊው በከተማይቱ ብሄርን መሰረት አድርጎ ጥቃት አልተፈፀመም ማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚነገረው ወሬ ሁሉ ከእውነት የራቀ ነው ብለዋል።
ነገር ግን ከከተማው ህዝብ ጋር ተመሳሳይለው ተጨማሪ ጥቃት ሊከፍቱ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የታጣቂዎቹ ጦር ላይ እርምጃ ተወስዷል ሲሉ ገልፀዋል።
ሌላው ኃላፊው ከሰሞኑ ግጭት ጋር በተያያዘ የስነ- ምግባር ጉድለት ያለባቸው የፀጥታ አካላት እንዳሉ መንግስት ባደረገው ማጣራት ማረጋገጡን ገልፀው ተገቢውን ማጣራት በማድረግ ህጋዊ እርምጃ መዉሰድ መጀመሩን አስታውቀዋል።
እርምጃው ምን እንደሆነ እንዲሁም የፈፀሙትን ድርጊት ግልፅ አድርገው አላብራሩም።
በቀጣይም ያልተገባ ተግባር የፈፀሙና የሚፈፅሙ የፀጥታ አካላት ላይ እየተወሰደ ያለዉ ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ማስታወሻ፦ ከቀናት በፊት በጋምቤላ በተፈጠረው ክስተት የታጣቂዎችን እንቅስቃሴ መግታት ከተቻለ በኃላ ንፁሃንን ከአማፅያን (ታጣቂዎች) ጋር አደባልቆ የማየት እና በአንዳንድ ሰፈሮችም ንፁሃንን የማንገላታት ከዚህም አልፎ የማጥቃት ድርጊት እየተፈፀመ መሆኑን የሞቱ ሰዎችም ስለመኖራቸው እንደሰሙን ይህ ህጋዊ ያልሆነ ድርጊት በአፋጣኝ እንዲቆም የጋምቤላ ቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጥቆማ መስጠታቸው የሚዘነጋ አይደለም።
ሌላው፥ አንድ ወጣት እጁን ወደኃላ ታስሮ የፀጥታ ኃይል ልብስ በለበሱ እና ባለበሱ ሰዎች በጥይት ሲደበደብ የሚያሳይ ቪድዮ መሰራጨቱን ተከትሎ ማብራሪያ እንዲሰጥ እየተጠየቀ ነበር፤ በዚህ ላይ ግልፅ ማብራሪያ አልተሰጠም።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UK አሜሪካ #በጥብቅ የምትፈልገው የ " ዊኪሊክስ " መስራች ጁሊያን አሳንጅ ለአሜሪካ ተላፎ እንዲሰጥ የብሪታኒያ ፍርድ ቤት ዛሬ ወስኗል። አሳንጅ ለአሜሪካ ፍርድ ቤት ተላልፎ እንዲሰጥ ፍርድ ቤቱ ያሳለፈው ውሳኔ ተፈጻሚ የሚሆነው የብሪታኒያ የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር ሲያጸድቀው ነው ተብሏል። አሳንጅ የአሜሪካን ወታደራዊ መረጃዎች አውጥቷል ፤ አትሟል ፤ ወታደራዊ ሚስጥሮችን የያዙ ሰነዶች ለውጭ ኃይሎች…
#UK #USA
አሜሪካ በጥብቅ የምትፈልገው ጁሊያን አሳንጅ ተላልፎ ሊሰጥ ይችላል ተብሏን።
የዊክሊክስ መስራች ጁሊያን አሳንጄ ለአሜሪካ ተላልፎ የመሰጠቱ ጉዳይ በUK የሃገር ውስጥ ሚኒስትር ፕሪቲ ፓቴል ተቀባይነት እንዳገኘ ቢቢሲ ዘግቧል።
ጁሊያን አሳንጄ ውሳኔውን ይግባኝ ለማለት 14 ቀናት እንዳለውም የዩናይትድ ኪንግደም ሃገር ውስጥ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
ፍርድ ቤቶች ጁሊያን አሳንጄን አሳልፎ የመስጠት ጉዳይ " ከሰብዓዊ መብቱ ጋር የማይጣጣም " መሆኑን ቢገነዘቡም በአሜሪካ ውስጥ " በተገቢው ሁኔታ እንደሚስተናገድ " ማረጋገጣቸውን ገልጿል።
ጁሊያን አሳንጄ በአውሮፓውያኑ 2010 እና 2011 አሹልኮ ባወጣቸው ሰነዶች ምክንያት በአሜሪካ ባለስልጣናት ይፈለጋል።
በዊክሊክስ የታተሙት እነዚህ ሾልከው የወጡት ሰነዶች ከኢራቅና አፍጋኒስታን ጦርነት ጋር የተያያዙ ናቸው።
የአውስትራሊያ ዜግነት ያለው ጁሊያን አሳንጅ በለንደን ቤልማርሽ እስር ቤት የሚገኝ ሲሆን ተላልፎ ላለመሰጠትም ከፍተኛ ትግል እያደረገ ነው።
@tikvahethiopia
አሜሪካ በጥብቅ የምትፈልገው ጁሊያን አሳንጅ ተላልፎ ሊሰጥ ይችላል ተብሏን።
የዊክሊክስ መስራች ጁሊያን አሳንጄ ለአሜሪካ ተላልፎ የመሰጠቱ ጉዳይ በUK የሃገር ውስጥ ሚኒስትር ፕሪቲ ፓቴል ተቀባይነት እንዳገኘ ቢቢሲ ዘግቧል።
ጁሊያን አሳንጄ ውሳኔውን ይግባኝ ለማለት 14 ቀናት እንዳለውም የዩናይትድ ኪንግደም ሃገር ውስጥ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
ፍርድ ቤቶች ጁሊያን አሳንጄን አሳልፎ የመስጠት ጉዳይ " ከሰብዓዊ መብቱ ጋር የማይጣጣም " መሆኑን ቢገነዘቡም በአሜሪካ ውስጥ " በተገቢው ሁኔታ እንደሚስተናገድ " ማረጋገጣቸውን ገልጿል።
ጁሊያን አሳንጄ በአውሮፓውያኑ 2010 እና 2011 አሹልኮ ባወጣቸው ሰነዶች ምክንያት በአሜሪካ ባለስልጣናት ይፈለጋል።
በዊክሊክስ የታተሙት እነዚህ ሾልከው የወጡት ሰነዶች ከኢራቅና አፍጋኒስታን ጦርነት ጋር የተያያዙ ናቸው።
የአውስትራሊያ ዜግነት ያለው ጁሊያን አሳንጅ በለንደን ቤልማርሽ እስር ቤት የሚገኝ ሲሆን ተላልፎ ላለመሰጠትም ከፍተኛ ትግል እያደረገ ነው።
@tikvahethiopia
#ጥቆማ
ነፃ የጡት ካንሰር ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት ነገ በአዲስ አበባ ግዮን ግሮቭ ጋርደን ዋክ ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ከጥዋት 3:30 ጀምሮ ነው የሚካሄደው።
ውድ ፤ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆናችሁ እንስቶች የነገ ፕሮግራማችሁን አመቻችታችሁ አንድአፍታ ወደ ዝግጅቱ ቦታ ጎራ ብላችሁ የጡት ካንሰር ምርመራ በነፃ እንድታደርጉና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቱን እንድትታደሙ መልዕክት እናስተላልፋለን።
ወንዶችም መልዕክቱን ለእናቶቻችሁ፣ ለእህቶቻችሁ ፣ ለጓደኞቻችሁ እንዲሁም ለትዳር አጋሮቻችሁ በማድረስ አሳውቋቸው።
@tikvahethiopia
ነፃ የጡት ካንሰር ምርመራ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት ነገ በአዲስ አበባ ግዮን ግሮቭ ጋርደን ዋክ ይካሄዳል።
ዝግጅቱ ከጥዋት 3:30 ጀምሮ ነው የሚካሄደው።
ውድ ፤ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሆናችሁ እንስቶች የነገ ፕሮግራማችሁን አመቻችታችሁ አንድአፍታ ወደ ዝግጅቱ ቦታ ጎራ ብላችሁ የጡት ካንሰር ምርመራ በነፃ እንድታደርጉና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቱን እንድትታደሙ መልዕክት እናስተላልፋለን።
ወንዶችም መልዕክቱን ለእናቶቻችሁ፣ ለእህቶቻችሁ ፣ ለጓደኞቻችሁ እንዲሁም ለትዳር አጋሮቻችሁ በማድረስ አሳውቋቸው።
@tikvahethiopia
#AmharaBank
የአማራ ባንክ ነገ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።
ባንኩ ነገ በይፋ ስራ የሚጀምርበትን የምረቃት ስነስርአት ከጥዋት 3:00 ጀምሮ ለገሃር በሚገኘው ዋናው መስሪያ ቤት ያካሂዳል።
ነገ ቅዳሜ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም የሚያካሂደውን የምርቃ ስነስርዓት በማስመልከት በልዩ ሁኔታ ለአዲስ አበባ እና ዙሪያው #አንበሳ አውቶቡስ ተጠቃሚዎች በሙሉ የሙሉ ቀን (ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3፡ዐዐ ሠዓት) የጉዞ ክፍያን ሸፍኗል።
የአዲስ አበባ እና የዙሪያዋ የአንበሳ አውቶቡስ ተጠቃሚዎች በነጻ ወደሚፈልጉባቸው ቦታዎች መጓጓዝ ይችላሉ።
በተጨማሪም ባንኩ በሁሉም የክልል ዋና ከተሞች በተመረጡ ሆስፒታሎች ለሚወልዱ እናቶች በባንኩ ስም " የእንኳን ደስ አላችሁ " ስጦታ የሚያበረክት ይሆናል።
@tikvahethiopia
የአማራ ባንክ ነገ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም ሥራውን በይፋ ይጀምራል።
ባንኩ ነገ በይፋ ስራ የሚጀምርበትን የምረቃት ስነስርአት ከጥዋት 3:00 ጀምሮ ለገሃር በሚገኘው ዋናው መስሪያ ቤት ያካሂዳል።
ነገ ቅዳሜ ሰኔ 11 ቀን 2014 ዓ.ም የሚያካሂደውን የምርቃ ስነስርዓት በማስመልከት በልዩ ሁኔታ ለአዲስ አበባ እና ዙሪያው #አንበሳ አውቶቡስ ተጠቃሚዎች በሙሉ የሙሉ ቀን (ከጠዋቱ 12፡00 ሰዓት እስከ ምሽቱ 3፡ዐዐ ሠዓት) የጉዞ ክፍያን ሸፍኗል።
የአዲስ አበባ እና የዙሪያዋ የአንበሳ አውቶቡስ ተጠቃሚዎች በነጻ ወደሚፈልጉባቸው ቦታዎች መጓጓዝ ይችላሉ።
በተጨማሪም ባንኩ በሁሉም የክልል ዋና ከተሞች በተመረጡ ሆስፒታሎች ለሚወልዱ እናቶች በባንኩ ስም " የእንኳን ደስ አላችሁ " ስጦታ የሚያበረክት ይሆናል።
@tikvahethiopia