TIKVAH-ETHIOPIA
#መልዕክት_2 (ነገ የሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን ሂፍዝ ውድድር) - ፕሮግራሙ ከጠዋቱ 1 ሰዐት ጀምሮ ስለሚካሄድ በጊዜ አዲስ አበባ ስታዲየም እንገኝ። - በ500 ብር ትኬታ የቆረጠ ሁለት ሰው ሆኖ መግባት ይችላሉ። ትኬት ያልገዙ ሰዎች በ200 ብር በር ላይ እንዲገዙ ተመቻችቷል። - ሴቶች ከወጋገን ባንክ ፊት ለፊት ያሉትን በር ቁጥር 8፣ 9 እና 11ን ብቻ ተጠቀሙ። የVIP እንግዶችም በVIP…
ፎቶ ፦ በአሁን ሰዓት በ አዲስ አበባ ስታዲየም " ዓለም ዓቀፍ የቁርአን ሂፍዝ ውድድር " እየተካሄደ ይገኛል።
ፕሮግራሙ በርካታ ህዝበ ሙስሊም በተገኘበት ነው እየተከናወነ የሚገኘው።
በዚህ ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ኢብራሒም አብዱራህማን ኢብራሒም ሀገራችን #ኢትዮጵያን 🇪🇹 ወክሎ የውድድሩ ተሳታፊ ነው።
ፕሮግራሙ እንደተጠናቀቀ ተጨማሪ መረጃዎችን የምንልክላችሁ ይሆናል።
@tikvahethiopia
ፕሮግራሙ በርካታ ህዝበ ሙስሊም በተገኘበት ነው እየተከናወነ የሚገኘው።
በዚህ ዓለም አቀፍ የቁርዓን ውድድር ኢብራሒም አብዱራህማን ኢብራሒም ሀገራችን #ኢትዮጵያን 🇪🇹 ወክሎ የውድድሩ ተሳታፊ ነው።
ፕሮግራሙ እንደተጠናቀቀ ተጨማሪ መረጃዎችን የምንልክላችሁ ይሆናል።
@tikvahethiopia
#አስቸኳይ
ሰኔ 4 ቀን 2014 ዓ/ም በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሜጫ ወረዳ በረዶ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።
በሰሜን ሜጫ ወረዳ ቆለላ ቀበሌ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ፦
- ጋፈራ፣
- አውጣ
- ባችማ
- ተክለድብ በተባሉ ቀበሌዎች 1409 በሚደርሱ የአባወራ ቤቶች ላይ ከባድና ቀላል የንብረት ጉዳት ደርሷል።
በእስሳት እና አትክልት፣ ፍራፍሬ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ለተጎዱ 5 ቀበሌዎች #አስቸኳይ_ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ዝርዝር በዚህ ተያይዟል ፦ https://telegra.ph/North-Mecha-06-13
#ሰሜን_ሜጫ_ወረዳ
@tikvahethiopia
ሰኔ 4 ቀን 2014 ዓ/ም በአማራ ክልል፣ ሰሜን ሜጫ ወረዳ በረዶ ቀላቅሎ የጣለ ዝናብ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።
በሰሜን ሜጫ ወረዳ ቆለላ ቀበሌ በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ፦
- ጋፈራ፣
- አውጣ
- ባችማ
- ተክለድብ በተባሉ ቀበሌዎች 1409 በሚደርሱ የአባወራ ቤቶች ላይ ከባድና ቀላል የንብረት ጉዳት ደርሷል።
በእስሳት እና አትክልት፣ ፍራፍሬ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል።
በረዶ ቀላቅሎ በጣለው ከባድ ዝናብ ለተጎዱ 5 ቀበሌዎች #አስቸኳይ_ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
አጠቃላይ የደረሰው ጉዳት ዝርዝር በዚህ ተያይዟል ፦ https://telegra.ph/North-Mecha-06-13
#ሰሜን_ሜጫ_ወረዳ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ችሎት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ የ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተፈቀደላቸው። የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝና ሰለሞን ሹምዬ እያንዳንዳቸው የ10 ሺ ብር ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ፤ ፖሊስ በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ እና በመስከረም አበራ ላይ እያደረገው ለሚገኘው ምርመራ…
#Update #ችሎት
መምህርት መስከረም አበራ በ30,000 (30 ሺ ብር) ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ።
ትዕዛዙን ዛሬ ያስተላለፈው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መሆኑን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
መምህርት መስከረም አበራ በ30,000 (30 ሺ ብር) ዋስትና ከእስር እንድትለቀቅ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተሰጠ።
ትዕዛዙን ዛሬ ያስተላለፈው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት መሆኑን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somali #Afar #ሰላም #ውይይት
ትላንት የአፋርና የሱማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ኮንፈረንስ በአዳማ ተካሂዶ ነበር።
የሰላም ኮንፈረንሱ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት ዓላማ ያደረገ ነው መሆኑን ሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።
በአካባቢዎቹ የሚታዩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ሰላምን ለማምጣት ወደ ግጭት ለሚያመሩ ጉዳዮችም መፍትሔዎች ተለይተው የተቀመጡበት መድረክ ነው ተብሏል።
የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ፤ በግጭት ምክንያት ከኖሩበት ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው እየኖሩ ችግሮችን እየተጋፈጡ ያሉ ወገኖች ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ሊደረጉ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም በመድረኩ መነሳቱን ከሰላም ሚኒስቴር በኩል የወጣው መረጃ ያሳያል።
ባለፈው ዓመት በተነሳ ግጭት ከዘጠኝ ወር በላይ ቤታቸው ተፈናውለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በየዘመዶቻቸው ቤት የተጠለሉ በርካታ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
ትላንት የአፋርና የሱማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ኮንፈረንስ በአዳማ ተካሂዶ ነበር።
የሰላም ኮንፈረንሱ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት ዓላማ ያደረገ ነው መሆኑን ሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።
በአካባቢዎቹ የሚታዩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ሰላምን ለማምጣት ወደ ግጭት ለሚያመሩ ጉዳዮችም መፍትሔዎች ተለይተው የተቀመጡበት መድረክ ነው ተብሏል።
የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ፤ በግጭት ምክንያት ከኖሩበት ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው እየኖሩ ችግሮችን እየተጋፈጡ ያሉ ወገኖች ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ሊደረጉ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም በመድረኩ መነሳቱን ከሰላም ሚኒስቴር በኩል የወጣው መረጃ ያሳያል።
ባለፈው ዓመት በተነሳ ግጭት ከዘጠኝ ወር በላይ ቤታቸው ተፈናውለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በየዘመዶቻቸው ቤት የተጠለሉ በርካታ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DawitNega በትግርኛ የሙዚቃ ስራዎች በእጅጉ የሚታወቀው አርቲስት ዳዊት ነጋ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰማ። አርቲስት ዳዊት ህመም አጋጥሞት ያለፉትን ቀናት በአዲስ ህይወት ሆስፒታል በህክምና ላይ እንደነበር ተነግሯል። የአርቲስት ዳዊት ነጋ የሙዚቃ ስራዎች የትግርኛ ቋንቋ ከሚያደምጡ ሰዎች ባለፈ ቋንቋውን በማያዳምጡትም ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የነበሩ ናቸው። ከሙዚቃ ስራዎቹ መካከል ፦ ባባ ኢለን፣…
#DawitNega
የአርቲስት ዳዊት ነጋ ቤተሰቦች እና ጓደኞች ለቢቢሲ ትግርኛ የሰጡት ቃል ፦
" ባደረበት ድንገተኛ ህመም ዓርብ ዕለት ነው አዲስ አበባ አዲስ ህይወት ሆስፒታል የገባው።
ባለፈው ሳምንት ሰኞ ዕለት በጉንፋን መልክ የጀመረ ህመሙ ከተባባሰ በኋላ ዓርብ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እስከ ቅዳሜ ድረስ ህክምና ሲደረግለት ቆይቷል።
ትናንት እሁድ ከሰዓት በኋላ ህመሙ ሲጸናበት ወደ ጽኑ ህሙማን ክትትል ክፍል ገብቷል ማታ 1፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ ህይወቱ አልፏል።
ወደሆስፒታሉ ከመምጣቱ በፊት ህመሙን ለማስታገስ በቤት ውስጥ ግሉኮስ ይወሰድ ነበር።
ህመሙ ሲበረታበት ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ የስኳር መጠኑ መጨመሩን እና ህመሙ ወደ የሳንባ ምች (ኒሞኒያ) መቀየሩን ተነግሮታል።
የዳዊት አስከሬን ላይ ተጨማሪ ምርመራ ይደረጋል። "
Via BBC Tigrinya
@tikvahethiopia
የአርቲስት ዳዊት ነጋ ቤተሰቦች እና ጓደኞች ለቢቢሲ ትግርኛ የሰጡት ቃል ፦
" ባደረበት ድንገተኛ ህመም ዓርብ ዕለት ነው አዲስ አበባ አዲስ ህይወት ሆስፒታል የገባው።
ባለፈው ሳምንት ሰኞ ዕለት በጉንፋን መልክ የጀመረ ህመሙ ከተባባሰ በኋላ ዓርብ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እስከ ቅዳሜ ድረስ ህክምና ሲደረግለት ቆይቷል።
ትናንት እሁድ ከሰዓት በኋላ ህመሙ ሲጸናበት ወደ ጽኑ ህሙማን ክትትል ክፍል ገብቷል ማታ 1፡ዐዐ ሰዓት አካባቢ ህይወቱ አልፏል።
ወደሆስፒታሉ ከመምጣቱ በፊት ህመሙን ለማስታገስ በቤት ውስጥ ግሉኮስ ይወሰድ ነበር።
ህመሙ ሲበረታበት ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ የስኳር መጠኑ መጨመሩን እና ህመሙ ወደ የሳንባ ምች (ኒሞኒያ) መቀየሩን ተነግሮታል።
የዳዊት አስከሬን ላይ ተጨማሪ ምርመራ ይደረጋል። "
Via BBC Tigrinya
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ችሎት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ የ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተፈቀደላቸው። የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝና ሰለሞን ሹምዬ እያንዳንዳቸው የ10 ሺ ብር ዋስትና በማስያዝ ከእስር እንዲለቀቁ ትዕዛዝ ሰጠ። ፍርድ ቤቱ ፤ ፖሊስ በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ እና በመስከረም አበራ ላይ እያደረገው ለሚገኘው ምርመራ…
#Update #ችሎት
የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ።
ችሎቱ 7 ቀን የምርመራ ጊዜ የፈቀደው ፖሊስ " በምርመራው የሚያጠናቅቃቸው ነገሮች ካሉ " በሚል ምክንያት መሆኑን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በጋዜጠኛ ያየሰው ሽመልስ ላይ ተጨማሪ የሰባት ቀናት የምርመራ ጊዜ ፈቀደ።
ችሎቱ 7 ቀን የምርመራ ጊዜ የፈቀደው ፖሊስ " በምርመራው የሚያጠናቅቃቸው ነገሮች ካሉ " በሚል ምክንያት መሆኑን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DawitNega የአርቲስት ዳዊት ነጋ ቤተሰቦች እና ጓደኞች ለቢቢሲ ትግርኛ የሰጡት ቃል ፦ " ባደረበት ድንገተኛ ህመም ዓርብ ዕለት ነው አዲስ አበባ አዲስ ህይወት ሆስፒታል የገባው። ባለፈው ሳምንት ሰኞ ዕለት በጉንፋን መልክ የጀመረ ህመሙ ከተባባሰ በኋላ ዓርብ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ እስከ ቅዳሜ ድረስ ህክምና ሲደረግለት ቆይቷል። ትናንት እሁድ ከሰዓት በኋላ ህመሙ ሲጸናበት ወደ ጽኑ ህሙማን ክትትል…
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
አርቲስት ዳዊት ነጋ ማን ነው ?
- ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል ፤ መቐለ ከተማ እንዳማርያም ነው።
- ትምህርቱን የተከታተለው በዓይደር ት/ቤት ነው ፤ የሙዚቃ ስራንም አንድ ብሎ የጀመረው በመቐለ ሲሆን በ15 ዓመቱ የሙዚቃን ስራ መጀመሩን በአንድ ወቅት ተናግሯል።
- በመጀመሪያ ለመዝፈን ' ሰርከስ ትግራይ ' የሄደው ዳዊት አንዳልተቀበሉት ፤ በኃላም ወደ ማርሽ ባንድ ገብቶ በድራመርነት ለ6 ዓመት ተጫውቷል።
- ህይወት ብዙ የፈተነችው ዳዊት ነጋ ፤ መሰናክሎችን አልፎ ስኬታማ ለመሆን ብቅቶ ነበር። እናት እና አባቱን በ10 ዓመቱ ያጣው ዳዊት ህይወቱን ለማስቀጠል ገና በልጅነቱ ትንንሽ እቃዎችን እየሸጠ እራሱን ለመቻል ብዙ ታግሏል።
- ከእናት እና አባቱ ህልፈት በኃላ የእናቱ የቅርብ ሰው ወደሆኑ ጎረቤቱ የገባው ዳዊት በአንድ ወቅት ምግብ የሚበላበትን ፣ የ200 ብር ቤት ክራይ የሚከፍለውን አጥቶ ነበር።
- ከልጅነቱ አንስቶ አስራ አምስት ዓመታትን በሙዚቃ ውስጥ ያሳለፈው ዳዊት 15 ዓመት ሙሉ በዚህ ሞያ ብር ሳያገኝ፣ አንዳንዴም ምግብ ሳይበላ እያደረ ፣ የቤት ኪራይ ሚከፍለው ሲያጣ ለሊት በአጥር ዘሎ እስከመግባት አንዳንዴም ጓደኞቹ ቤት እስከማደር ደርሶ ነበር።
- ምግብ መብያ አጥቶ ብዙ የተቸገረው ዳዊት እንደሱ የተቸገር ኢትዮጵያዊ ስለመኖሩ እንደሚጠራጠር በአንድ ወቅት በሰጠው ቃለ ምልልስ ተናግሮ ነበር።
- ምንም እንኳ ብዙ የህይወት ውጣውረድ ፣ ፈተና ከፊቱ ቢያጋጥመውም ያን ሁሉ ችግር በትጋት አልፎ የወጣበትን የትግራይ ህዝብ ባህል ፣ መዚቃ በስራው ለዓለም አስተዋውቋል። በትግርኛ የሙዚቃ ዘርፍ ውስጥም የራሱን አሻራ አሳርፏል።
አርቲስት ዳዊት ነጋ በትላንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
@tikvahethiopia
- ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል ፤ መቐለ ከተማ እንዳማርያም ነው።
- ትምህርቱን የተከታተለው በዓይደር ት/ቤት ነው ፤ የሙዚቃ ስራንም አንድ ብሎ የጀመረው በመቐለ ሲሆን በ15 ዓመቱ የሙዚቃን ስራ መጀመሩን በአንድ ወቅት ተናግሯል።
- በመጀመሪያ ለመዝፈን ' ሰርከስ ትግራይ ' የሄደው ዳዊት አንዳልተቀበሉት ፤ በኃላም ወደ ማርሽ ባንድ ገብቶ በድራመርነት ለ6 ዓመት ተጫውቷል።
- ህይወት ብዙ የፈተነችው ዳዊት ነጋ ፤ መሰናክሎችን አልፎ ስኬታማ ለመሆን ብቅቶ ነበር። እናት እና አባቱን በ10 ዓመቱ ያጣው ዳዊት ህይወቱን ለማስቀጠል ገና በልጅነቱ ትንንሽ እቃዎችን እየሸጠ እራሱን ለመቻል ብዙ ታግሏል።
- ከእናት እና አባቱ ህልፈት በኃላ የእናቱ የቅርብ ሰው ወደሆኑ ጎረቤቱ የገባው ዳዊት በአንድ ወቅት ምግብ የሚበላበትን ፣ የ200 ብር ቤት ክራይ የሚከፍለውን አጥቶ ነበር።
- ከልጅነቱ አንስቶ አስራ አምስት ዓመታትን በሙዚቃ ውስጥ ያሳለፈው ዳዊት 15 ዓመት ሙሉ በዚህ ሞያ ብር ሳያገኝ፣ አንዳንዴም ምግብ ሳይበላ እያደረ ፣ የቤት ኪራይ ሚከፍለው ሲያጣ ለሊት በአጥር ዘሎ እስከመግባት አንዳንዴም ጓደኞቹ ቤት እስከማደር ደርሶ ነበር።
- ምግብ መብያ አጥቶ ብዙ የተቸገረው ዳዊት እንደሱ የተቸገር ኢትዮጵያዊ ስለመኖሩ እንደሚጠራጠር በአንድ ወቅት በሰጠው ቃለ ምልልስ ተናግሮ ነበር።
- ምንም እንኳ ብዙ የህይወት ውጣውረድ ፣ ፈተና ከፊቱ ቢያጋጥመውም ያን ሁሉ ችግር በትጋት አልፎ የወጣበትን የትግራይ ህዝብ ባህል ፣ መዚቃ በስራው ለዓለም አስተዋውቋል። በትግርኛ የሙዚቃ ዘርፍ ውስጥም የራሱን አሻራ አሳርፏል።
አርቲስት ዳዊት ነጋ በትላንትናው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
@tikvahethiopia
#HoPR
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ ከህ/ተ/ም/ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች 6ኛው ምክር ቤት በ1ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ በሚያካሂደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቃል የሚሰጡትን ምላሽ ያዳምጣል።
ነገ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ መደበኛ ጉባዔ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተያዘው አጀንዳ መሠረትም፤ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ጥያቄዎችን ያቀርባሉ። እንደዚሁም አስተያየታቸውን ይሰነዝራሉ።
ስብሰባው በቀጥታ ለህዝብ ይሰራጫል ተብሏል።
Via HoPR
@tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ ከህ/ተ/ም/ቤት አባላት ለሚነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ እና ማብራሪያ ይሰጣሉ።
የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች 6ኛው ምክር ቤት በ1ኛ ዓመት የሥራ ዘመኑ በሚያካሂደው 13ኛ መደበኛ ስብሰባ፤ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ክቡር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በቃል የሚሰጡትን ምላሽ ያዳምጣል።
ነገ ሰኔ 7 ቀን 2014 ዓ.ም. በሚካሄደው በዚህ መደበኛ ጉባዔ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤት አባላት ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች መልስ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በተያዘው አጀንዳ መሠረትም፤ የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችን በተመለከተ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ጥያቄዎችን ያቀርባሉ። እንደዚሁም አስተያየታቸውን ይሰነዝራሉ።
ስብሰባው በቀጥታ ለህዝብ ይሰራጫል ተብሏል።
Via HoPR
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert ዋስትናው ተሻረ ! ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ እና ጋዜጠኛ መዓዛ መሐመድ የተፈቀደው የ10 ሺህ ብር ዋስትና ተሻረ ። የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደላቸውን የ10 ሺህ ብር ዋስትና ሻረ። ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን የሻረው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዋስትና ትዕዛዙ ላይ ይግባኝ…
#Update
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ነገ ፍ/ ቤት እንዲቀርብ ታዘዘ።
ጋዜጠኛ ተመስገን ፍርድ ቤት ነገ እንዲቀርብ ዛሬ መጥሪያ ደርሶታል።
ጠበቃው አቶ ሄኖክ አክሊሉ እንደተናገሩት " ለነገ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንዲቀርብ መጥሪያ ዛሬ እንደደረሰው አረጋግጫለሁ " በለዋል።
" በዚህ መሰረት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአራዳ ምድብ ቻሎት ነገ ጠዋት 3:00 ሰዓት ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድ ቤት ይቀርባል " ሲሉ መግለፃቸውን ከጋዜጠኛ ተመስገን ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ ለመስማት ተችሏል።
ከቀናት በፊት (ሰኔ 2) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደ የ10 ሺህ ብር ዋስትና መሻሩ እንዲሁም 8 ቀናት ለምርመራ መፍቀዱ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ነገ ፍ/ ቤት እንዲቀርብ ታዘዘ።
ጋዜጠኛ ተመስገን ፍርድ ቤት ነገ እንዲቀርብ ዛሬ መጥሪያ ደርሶታል።
ጠበቃው አቶ ሄኖክ አክሊሉ እንደተናገሩት " ለነገ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንዲቀርብ መጥሪያ ዛሬ እንደደረሰው አረጋግጫለሁ " በለዋል።
" በዚህ መሰረት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአራዳ ምድብ ቻሎት ነገ ጠዋት 3:00 ሰዓት ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድ ቤት ይቀርባል " ሲሉ መግለፃቸውን ከጋዜጠኛ ተመስገን ወንድም ታሪኩ ደሳለኝ ለመስማት ተችሏል።
ከቀናት በፊት (ሰኔ 2) የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደ የ10 ሺህ ብር ዋስትና መሻሩ እንዲሁም 8 ቀናት ለምርመራ መፍቀዱ አይዘነጋም።
@tikvahethiopia