የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ ትላንት በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ መግለጫ አውጥቶ ነበር።
ፓርቲው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ ፤ " የሕግ የበላይነትን እና ሥርአትን ሕግን እየሸራረፉ እና መብቶችን እየጣሱ ማረገገጥ አይቻልም " ያለ ሲሆን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እያከናወነ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ በሕግ አግባብ ብቻ እንዲያከናውን አሳስቧል።
ክልሉ እያከናወናቸው ያሉት የጅምላ እስር ለብልሹ አሰራር እና ለዘፈቀደ ውሳኔ ተጋላጭ በመሆናቸው በአስቸኳይ እንዲቆሙ ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል ፤ የክልሉ መንግሥት እየወሰደ ባለው እርምጃ አብን አመራሮቹ እና አባላቱን ጨምሮ ባላቸው የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ምክንያት በግለሰቦች ላይ እየተፈጸመ ያለው እስር እንዲቆም እና በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት የታሰሩ ሰዎች ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በተጨማሪ አብን የክልሉ መንግስት እየወሰደው ባለው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ሂደት እየታዩ ያሉ ግልፅ ችግሮችን ሰበብ በማድረግ የአማራን ክልል የግጭት ማዕከል ለማድረግ እየሰሩ ያሉ ግለሰቦች እና ቡድኖችን በጽኑ አወግዛለሁ ያለ ሲሆን " ጠላት ጦርነት ለመክፈት በተዘጋጀበት ወቅት የአመጽ ጥሪ ማድረግ ያለንበትን አጠቃላይ የጸጥታ ከባቢያዊ ሁኔታ የዘነጋ እና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ከመሆኑም በላይ ለጠላት የሚደረግ ስልታዊ ድጋፍ በመሆኑ የአመጽ ጥሪ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል በመግለጫው አሳስቧል።
(አብን ትላንት ያወጣው መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ፓርቲው በማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ ፤ " የሕግ የበላይነትን እና ሥርአትን ሕግን እየሸራረፉ እና መብቶችን እየጣሱ ማረገገጥ አይቻልም " ያለ ሲሆን የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት እያከናወነ ያለውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ በሕግ አግባብ ብቻ እንዲያከናውን አሳስቧል።
ክልሉ እያከናወናቸው ያሉት የጅምላ እስር ለብልሹ አሰራር እና ለዘፈቀደ ውሳኔ ተጋላጭ በመሆናቸው በአስቸኳይ እንዲቆሙ ሲልም ጥሪ አቅርቧል።
በሌላ በኩል ፤ የክልሉ መንግሥት እየወሰደ ባለው እርምጃ አብን አመራሮቹ እና አባላቱን ጨምሮ ባላቸው የፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ምክንያት በግለሰቦች ላይ እየተፈጸመ ያለው እስር እንዲቆም እና በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት የታሰሩ ሰዎች ያላንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ጠይቋል።
በተጨማሪ አብን የክልሉ መንግስት እየወሰደው ባለው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ሂደት እየታዩ ያሉ ግልፅ ችግሮችን ሰበብ በማድረግ የአማራን ክልል የግጭት ማዕከል ለማድረግ እየሰሩ ያሉ ግለሰቦች እና ቡድኖችን በጽኑ አወግዛለሁ ያለ ሲሆን " ጠላት ጦርነት ለመክፈት በተዘጋጀበት ወቅት የአመጽ ጥሪ ማድረግ ያለንበትን አጠቃላይ የጸጥታ ከባቢያዊ ሁኔታ የዘነጋ እና ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ከመሆኑም በላይ ለጠላት የሚደረግ ስልታዊ ድጋፍ በመሆኑ የአመጽ ጥሪ የሚያደርጉ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ " ሲል በመግለጫው አሳስቧል።
(አብን ትላንት ያወጣው መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ፤ ከአብን ስራ አስፈፃሚ አባልነት በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን አሳውቀዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የአብን አባሉ ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፤ " አብን ባለፈው የካቲት አካሂዶት በነበረው ጊዜያዊ የአስፈፃሚ ሪፎርም ላይ ንቅናቄው በቀጣይ 3 ወር ውስጥ የሚያካሂደው ሪፎርም ተከናውኖ አዳዲስ አመራሮች እስኪመረጡ ድረስ ከ2 እስከ 3 ወር ላልበለጠ ጊዜ ወደ ስራ አስፈፃሚ እንድመለስ የአብን ማዕከላዊ ኮሚቴ ወስኖ ነበር። " ብለዋል።
አክለውም ፤ " ወደ አመራርነት የመመለስ ፍላጎት ባይኖረኝም የድርጅቴ ውሳኔ ስለነበር ውሳኔውን ተቀብየው ቆይቻለሁ " ሲሉ ገልፀዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ ፤ " ለአጭር ጊዜ ብዬ የተመለስኩበት ጊዜ ስለተጠናቀቀ እንዲሁም ወደፊት ጊዜው ሲደርስ በምገልፃቸው ምክንያቶች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ከአብን ስራ አስፈፃሚ አባልነቴ በፈቃዴ ለቅቂያለሁ " ያሉ ሲሆን በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ግን የአብን ሪፎርም በስኬት እስኪጠናቀቅ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
" የንቅናቄው ሪፎርም በአጭር ጊዜ ተጠናቆ አብን ተጠናክሮ ሲቆም ደግሞ ልክ ከአብን ሊቀ መንበርነቴ በገንዛ ፈቃዴ እንደለቀቅሁት ሁሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቴንም በገዛ ፈቃዴ በመልቀቅ አዳዲስ መሪዎች በማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ እድል እንዲያገኙ ለማድረግ መወሰኔን እገልፃለሁ " ሲሉም አክለዋል።
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የአብን አባሉ ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፤ " አብን ባለፈው የካቲት አካሂዶት በነበረው ጊዜያዊ የአስፈፃሚ ሪፎርም ላይ ንቅናቄው በቀጣይ 3 ወር ውስጥ የሚያካሂደው ሪፎርም ተከናውኖ አዳዲስ አመራሮች እስኪመረጡ ድረስ ከ2 እስከ 3 ወር ላልበለጠ ጊዜ ወደ ስራ አስፈፃሚ እንድመለስ የአብን ማዕከላዊ ኮሚቴ ወስኖ ነበር። " ብለዋል።
አክለውም ፤ " ወደ አመራርነት የመመለስ ፍላጎት ባይኖረኝም የድርጅቴ ውሳኔ ስለነበር ውሳኔውን ተቀብየው ቆይቻለሁ " ሲሉ ገልፀዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ ፤ " ለአጭር ጊዜ ብዬ የተመለስኩበት ጊዜ ስለተጠናቀቀ እንዲሁም ወደፊት ጊዜው ሲደርስ በምገልፃቸው ምክንያቶች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ከአብን ስራ አስፈፃሚ አባልነቴ በፈቃዴ ለቅቂያለሁ " ያሉ ሲሆን በማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት ግን የአብን ሪፎርም በስኬት እስኪጠናቀቅ እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
" የንቅናቄው ሪፎርም በአጭር ጊዜ ተጠናቆ አብን ተጠናክሮ ሲቆም ደግሞ ልክ ከአብን ሊቀ መንበርነቴ በገንዛ ፈቃዴ እንደለቀቅሁት ሁሉ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነቴንም በገዛ ፈቃዴ በመልቀቅ አዳዲስ መሪዎች በማዕከላዊ ኮሚቴ ውስጥ እድል እንዲያገኙ ለማድረግ መወሰኔን እገልፃለሁ " ሲሉም አክለዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA መሳሪያ በታጠቁ ሰዎች በርካቶች በሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ከሰሞኑን ተፈፅመው በነበሩ ጥቃቶች ሰዎች ተገድለዋል ፤ ቆስለዋል። ሰሞኑን በኒው ዮርክ ግዛት በፋሎ ከተማ አንድ ነጭ ታጣቂ ጥቁሮች የሚበረክቱበት መገበያያ ሥፍራ ገብቶ ጥቃት ፈፅሞ 10 ሰዎችን ገድሏል። ይኸው ተጠርጣሪ 18 ዓመቱ ሱሆን ፔይተን ጌንድሮን ይባላል ጥቃቱን 320 ኪሎ ሜትር ተጉዞ መጥቶ መፈፀሙን ፖሊስ ገልጿል። አሜሪካዊው…
#US
በየጊዜው በርካቶች በታጣቁ ሰዎች በሚከፈት ተኩስ የሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ትላንትም እጅግ በጣም ዘግናኝ የሚባል ጥቃት ተፈፅሞ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት ተገድለዋል።
በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት አንድ የ18 ዓመት ወጣት በከፈተው የተኩስ እሩምታ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት መገደላቸውን ተዘግቧል።
ድርጊቱ የተፈፀመው በደቡብ ቴክሳስ ግዛት፣ ዩቫልዲ ከተማ ሮብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ነው አንድ ወጣት ድንገተኛ ተኩስ ከፍቶ ነው 19 ህፃናትን ጨምሮ 2 አዋቂዎችን የገደለው።
ከተገደሉት ሁለት አዋቂዎች አንዷ በዚያው ትምህርት ቤት የምታስተምር መምህርት ነበረች።
ፖሊስ እንዳለው ድርጊቱ የፈፀመው ወጣት የታጠቀው ኤአር-15 ከፊል አውቶማቲክ ጠመንጃ ነበር።
ወጣቱ መጀመርያ ሴት አያቱን ከገደለ በኋላ ነው ሕጻናቱን በግፍ የገደላቸው ተብሏል።
አንዳንድ መገናኛ ብዙኃን ወጣቱ በዚያው አካባቢ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት የ2ኛ ደረጃ ተማሪ እንደሆነ እየዘገቡ ይገኛሉ።
የቴክሳስ ግዛት ገዥ ግሬግ አቦት ወጣቱ " ሳልቫዶር ራሞስ " እንደሚባልና መኪናውን ደጅ አቁሞ ወደ ትምህርት ቅጥር ግቢው ከገባ በኋላ አሰቃቂው ድርጊት እንደፈጸመ ተናግረዋል።
አሶሲየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከትምህርት ቤቱ በቅርብ የነበረ አንድ የድንበር ጠባቂ ፖሊስ የተኩስ ድምጽ ሰምቶ ወደ ትምህርት ቤቱ በመግባት ይህን ወጣት ታጣቂ ተኩሶ ባይገድለው ኖሮ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊሆን ይችል ነበር።
እንደ Gun Violence Archive ድረገፅ መረጃ በአሜሪካ ሀገር ከጦር መሳሪያዎች ጋር በተያያዘ (በመሳሪያ እራሳቸውን የሚያጠፉትን ጨምሮ) በየዓመቱ #አርባ_ሺህ (40,000) ይሞታሉ።
(ኤፒ/ቢቢሲ - ፎቶ - ሶሻል ሚዲያ)
@tikvahethiopia
በየጊዜው በርካቶች በታጣቁ ሰዎች በሚከፈት ተኩስ የሚገደሉባት ሀገረ አሜሪካ ትላንትም እጅግ በጣም ዘግናኝ የሚባል ጥቃት ተፈፅሞ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት ተገድለዋል።
በአሜሪካ ቴክሳስ ግዛት አንድ የ18 ዓመት ወጣት በከፈተው የተኩስ እሩምታ 2 አዋቂዎችን ጨምሮ 19 ሕጻናት መገደላቸውን ተዘግቧል።
ድርጊቱ የተፈፀመው በደቡብ ቴክሳስ ግዛት፣ ዩቫልዲ ከተማ ሮብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ነው አንድ ወጣት ድንገተኛ ተኩስ ከፍቶ ነው 19 ህፃናትን ጨምሮ 2 አዋቂዎችን የገደለው።
ከተገደሉት ሁለት አዋቂዎች አንዷ በዚያው ትምህርት ቤት የምታስተምር መምህርት ነበረች።
ፖሊስ እንዳለው ድርጊቱ የፈፀመው ወጣት የታጠቀው ኤአር-15 ከፊል አውቶማቲክ ጠመንጃ ነበር።
ወጣቱ መጀመርያ ሴት አያቱን ከገደለ በኋላ ነው ሕጻናቱን በግፍ የገደላቸው ተብሏል።
አንዳንድ መገናኛ ብዙኃን ወጣቱ በዚያው አካባቢ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤት የ2ኛ ደረጃ ተማሪ እንደሆነ እየዘገቡ ይገኛሉ።
የቴክሳስ ግዛት ገዥ ግሬግ አቦት ወጣቱ " ሳልቫዶር ራሞስ " እንደሚባልና መኪናውን ደጅ አቁሞ ወደ ትምህርት ቅጥር ግቢው ከገባ በኋላ አሰቃቂው ድርጊት እንደፈጸመ ተናግረዋል።
አሶሲየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከትምህርት ቤቱ በቅርብ የነበረ አንድ የድንበር ጠባቂ ፖሊስ የተኩስ ድምጽ ሰምቶ ወደ ትምህርት ቤቱ በመግባት ይህን ወጣት ታጣቂ ተኩሶ ባይገድለው ኖሮ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊሆን ይችል ነበር።
እንደ Gun Violence Archive ድረገፅ መረጃ በአሜሪካ ሀገር ከጦር መሳሪያዎች ጋር በተያያዘ (በመሳሪያ እራሳቸውን የሚያጠፉትን ጨምሮ) በየዓመቱ #አርባ_ሺህ (40,000) ይሞታሉ።
(ኤፒ/ቢቢሲ - ፎቶ - ሶሻል ሚዲያ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራር የሆነት ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲለቀቁ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ። ኮነሌል ገመቹ አያና በግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ/ም በተከሰሱበት በሽብር ወንጀል በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና የህገመንግክት ጉዳዮች ወንጀል ችሎች በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ በነጋታው ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በር ላይ ሲወጡ በኦሮሚያ…
ኮለኔል ገመቹ አያና ዛሬ ከታሰሩበት ተፈተው ከቤተሰቦቻቸው ጋር መቀላቀላቸው ታውቋል።
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አመራር ኮነሌል ገመቹ አያና በስር ፍርድ ቤት ነጻ ከተባሉበት ግንቦት 9 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ ለ 6 ወራት በኦሮሚያ ፖሊስ ቀሪውን ከህዳር 16 ጀምሮ ደግሞ በፌደራል ፖሊስ በአጠቃላይ ለአንድ አመት ካለፍርድ ቤት ትዛዝ በእስር ላይ እንደነበሩ መግለጻቸውን ተከትሎ የዓቃቤ ህግን የይግባኝ መዝገብን ሲመለከት የነበረው የጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የኦሮማያ ፖሊስ በእስራት ሁኔታቸው ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ታዞ ባለመቅረቡ ካለምክንያት መታሰር የለባቸውም ዜጎች ሰብዓዊ መብት መጣስ የለበትም ሲል ከእስር እንዲፈቱ አዟል።
በትዛዙ መሰረት ኮለኔል ገመቹ ዛሬ ከታሰሩበት ከፌደራል ፖሊስ ተፈተው ቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።
(ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ)
@tikvahethiopia
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር አመራር ኮነሌል ገመቹ አያና በስር ፍርድ ቤት ነጻ ከተባሉበት ግንቦት 9 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ ለ 6 ወራት በኦሮሚያ ፖሊስ ቀሪውን ከህዳር 16 ጀምሮ ደግሞ በፌደራል ፖሊስ በአጠቃላይ ለአንድ አመት ካለፍርድ ቤት ትዛዝ በእስር ላይ እንደነበሩ መግለጻቸውን ተከትሎ የዓቃቤ ህግን የይግባኝ መዝገብን ሲመለከት የነበረው የጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የኦሮማያ ፖሊስ በእስራት ሁኔታቸው ላይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ታዞ ባለመቅረቡ ካለምክንያት መታሰር የለባቸውም ዜጎች ሰብዓዊ መብት መጣስ የለበትም ሲል ከእስር እንዲፈቱ አዟል።
በትዛዙ መሰረት ኮለኔል ገመቹ ዛሬ ከታሰሩበት ከፌደራል ፖሊስ ተፈተው ቤተሰቦቻቸው ጋር ተቀላቅለዋል።
(ጋዜጠኛ ታሪክ አዱኛ)
@tikvahethiopia
#የመኪና_ስርቆት
አዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው ኦፕሬሽን በተለያዩ ጊዜያት የተሰረቁ 22 ተሽከርካሪዎችን እና 33 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ይስተዋል የነበረውን የተሽከርካሪ ስርቆት ለመከላከል እና ወንጀል ፈፃሚዎችን ህግ ፊት ለማቅረብ የአዲስ አበባ ፖሊስ በጥናት ላይ በመመስረት የምርመራ እና የክትትል ቡድን አቋቁሞ ባካሄደው ኦፕሬሽን በተለያዩ ጊዜያት የተሰረቁ 22 ተሽከርካሪዎችን ማስመለሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
ተሽከርካሪዎቹ እየተሰረቁ አብዛኞቹ ወደ #ሃዋሳ ከተማ እንደሚወሰዱ በምርመራ ማረጋገጥ እንደተቻለ የገለፀው ፖሊስ ከተሰረቁት ተሽከርካሪዎች መካከል ሰባቱ በአዲስ አበባ የተገኙ ሲሆን የተቀሩት 15 ተሽከርካሪዎች ደግሞ በሀዋሳ ከተማ እና ከሀዋሳ ከተማ 100 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኝ አነስተኛ ከተማ ተይዘው ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ መደረጉን አሳውቋል።
ተሽከርካሪ በመስረቅ፣ የተሰረቀውን ተሽከርካሪ በመግዛት እና በመደለል ተሳትፎ ያደረጉ ከአዲስ አበባ 19 ከሃዋሳ ደግሞ 14 በአጠቃላይ 33 ግለሰቦች ተይዘው ምርመራው በስፋት መቀጠሉን ፖሊስ አክሎ አመልክቷል።
ተሽከርካሪዎቹን ለጥበቃ ምቹ በሆነ ቦታ ባለማቆም በሚፈጠር ክፍተት እና አሽከርካሪዎች ለልዩ ልዩ ጉዳይ የመኪናቸውን ቁልፍ ተሽከርካሪ ላይ ጥለው ሲወርዱ እና የተሽከርካሪውን ቁልፍ በልዩ ልዩ አጋጣሚ በማስቀረፅ ወንጀል ፈፃሚዎቹ የስርቆት ወንጀሉን ሲፈፅሙ እንደነበር በምርመራ ተረጋግጧል።
አዲስ አበባ ፖሊስ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ አስገንዝቦ ለስራው ስኬታማነት ድጋፍ ላደረጉት የፌዴራል ፖሊስና የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምስጋና አቅርቧል።
Via - AA POLICE
@tikvahethiopia
አዲስ አበባ ፖሊስ ባደረገው ኦፕሬሽን በተለያዩ ጊዜያት የተሰረቁ 22 ተሽከርካሪዎችን እና 33 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ገለፀ፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ ይስተዋል የነበረውን የተሽከርካሪ ስርቆት ለመከላከል እና ወንጀል ፈፃሚዎችን ህግ ፊት ለማቅረብ የአዲስ አበባ ፖሊስ በጥናት ላይ በመመስረት የምርመራ እና የክትትል ቡድን አቋቁሞ ባካሄደው ኦፕሬሽን በተለያዩ ጊዜያት የተሰረቁ 22 ተሽከርካሪዎችን ማስመለሱን የአዲስ አበባ ፖሊስ አሳውቋል።
ተሽከርካሪዎቹ እየተሰረቁ አብዛኞቹ ወደ #ሃዋሳ ከተማ እንደሚወሰዱ በምርመራ ማረጋገጥ እንደተቻለ የገለፀው ፖሊስ ከተሰረቁት ተሽከርካሪዎች መካከል ሰባቱ በአዲስ አበባ የተገኙ ሲሆን የተቀሩት 15 ተሽከርካሪዎች ደግሞ በሀዋሳ ከተማ እና ከሀዋሳ ከተማ 100 ኪሎ ሜትር ርቃ በምትገኝ አነስተኛ ከተማ ተይዘው ዛሬ ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ መደረጉን አሳውቋል።
ተሽከርካሪ በመስረቅ፣ የተሰረቀውን ተሽከርካሪ በመግዛት እና በመደለል ተሳትፎ ያደረጉ ከአዲስ አበባ 19 ከሃዋሳ ደግሞ 14 በአጠቃላይ 33 ግለሰቦች ተይዘው ምርመራው በስፋት መቀጠሉን ፖሊስ አክሎ አመልክቷል።
ተሽከርካሪዎቹን ለጥበቃ ምቹ በሆነ ቦታ ባለማቆም በሚፈጠር ክፍተት እና አሽከርካሪዎች ለልዩ ልዩ ጉዳይ የመኪናቸውን ቁልፍ ተሽከርካሪ ላይ ጥለው ሲወርዱ እና የተሽከርካሪውን ቁልፍ በልዩ ልዩ አጋጣሚ በማስቀረፅ ወንጀል ፈፃሚዎቹ የስርቆት ወንጀሉን ሲፈፅሙ እንደነበር በምርመራ ተረጋግጧል።
አዲስ አበባ ፖሊስ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ አስገንዝቦ ለስራው ስኬታማነት ድጋፍ ላደረጉት የፌዴራል ፖሊስና የሲዳማ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ምስጋና አቅርቧል።
Via - AA POLICE
@tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ #1 ፦
➡️ #ሴኔጋል ፦ በምዕራብ ሴኔጋል ፤ ቲቫዋን በምትሰኝ ከተማ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰ ቃጠሎ 11 አዲስ የተወለዱ ህጻናት መሞታቸውን ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ተናግረዋል።
➡️ #አፍጋኒስታን ፦ በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል እና ሰሜናዊ ከተማ ማዛር ኢ ሻሪፍ ከተከታታይ በደረሱ ፍንዳታዎች ቢያንስ 14 ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። ዳኢሽ ለጥቃቱ ኃላፊነት መውሰዱን ሮይተርስ ዘግቧል።
➡️ #ሩስያ ፦ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ላይ ለሚያካሂዱት ኦፕሬሽን ወታደሮቻቸውን ወደ ሀገሪቱ ከላኩ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዩክሬን ውስጥ በወታደራዊ ዘመቻው ከቆሰሉ ወታደሮች ጋር ተገናኝተዋል። በሌላ የሩስያ ጉዳይ ፤ ሀገሪቱ ያለባትን የውጭ ሀገራት እዳ በራሷ መገበያያ ገንዘብ “ሩብል” ለመክፈል ወስናለች ፤ እዚ ውሳኔ ላይ የደረሰችው የአሜሪካ ግምጃ ቤት ከቀናት በፊት በሩሲያ በአሜሪካ ባንኮች በኩል የምትፈጽመውን የውጭ ዕዳ ክፍያ ፍቃድ መሰረዙን ተከትሎ ነው።
➡️ #ዩክሬን ፦ ወደ ሰቨሮዶንስክ ከተማ የሚወስደውን አውራ ጎዳና ለመቆጣጠር በሩስያ እና ዩክሬን ኃያሎች መካከል ከፍተኛ ጦርነት እየተደረገ ነው። ሩሲያ ይህን ከተማ ለመቆጣጠር ተቃርቢያለሁ ብትልም አንድ ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን ነገሩን አስተባብለዋል። ይህ ጎዳና ዩክሬን የምትቆጣጠራቸውን ከተሞች ሩሲያ ከያዘቻቸው ከተሞች ጋር የሚያገናኝ ከፍ ያለ ወታደራዊ ዋጋ ያለው ነው።
➡️ #ጋምቢያ ፦ የጋምቢያ መንግስት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ከ20 አመታት በላይ በዘለቀው የስልጣን ዘመናቸው ተፈጽመዋል በተባሉ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ማሰቃየት እና ሌሎች ወንጀሎች ላይ ክስ እንደሚመሰርት አስታውቋል።
#አልጀዚራ #ቲአርቲወርልድ #ስፑትኪን #ሮይተርስ
@tikvahethiopia
➡️ #ሴኔጋል ፦ በምዕራብ ሴኔጋል ፤ ቲቫዋን በምትሰኝ ከተማ በአንድ ሆስፒታል ውስጥ በደረሰ ቃጠሎ 11 አዲስ የተወለዱ ህጻናት መሞታቸውን ፕሬዝዳንት ማኪ ሳል ተናግረዋል።
➡️ #አፍጋኒስታን ፦ በአፍጋኒስታን ዋና ከተማ ካቡል እና ሰሜናዊ ከተማ ማዛር ኢ ሻሪፍ ከተከታታይ በደረሱ ፍንዳታዎች ቢያንስ 14 ሰዎች መገደላቸው ተነግሯል። ዳኢሽ ለጥቃቱ ኃላፊነት መውሰዱን ሮይተርስ ዘግቧል።
➡️ #ሩስያ ፦ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በዩክሬን ላይ ለሚያካሂዱት ኦፕሬሽን ወታደሮቻቸውን ወደ ሀገሪቱ ከላኩ በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ዩክሬን ውስጥ በወታደራዊ ዘመቻው ከቆሰሉ ወታደሮች ጋር ተገናኝተዋል። በሌላ የሩስያ ጉዳይ ፤ ሀገሪቱ ያለባትን የውጭ ሀገራት እዳ በራሷ መገበያያ ገንዘብ “ሩብል” ለመክፈል ወስናለች ፤ እዚ ውሳኔ ላይ የደረሰችው የአሜሪካ ግምጃ ቤት ከቀናት በፊት በሩሲያ በአሜሪካ ባንኮች በኩል የምትፈጽመውን የውጭ ዕዳ ክፍያ ፍቃድ መሰረዙን ተከትሎ ነው።
➡️ #ዩክሬን ፦ ወደ ሰቨሮዶንስክ ከተማ የሚወስደውን አውራ ጎዳና ለመቆጣጠር በሩስያ እና ዩክሬን ኃያሎች መካከል ከፍተኛ ጦርነት እየተደረገ ነው። ሩሲያ ይህን ከተማ ለመቆጣጠር ተቃርቢያለሁ ብትልም አንድ ከፍተኛ የዩክሬን ባለሥልጣን ነገሩን አስተባብለዋል። ይህ ጎዳና ዩክሬን የምትቆጣጠራቸውን ከተሞች ሩሲያ ከያዘቻቸው ከተሞች ጋር የሚያገናኝ ከፍ ያለ ወታደራዊ ዋጋ ያለው ነው።
➡️ #ጋምቢያ ፦ የጋምቢያ መንግስት የቀድሞ ፕሬዝዳንት ያህያ ጃሜህ ከ20 አመታት በላይ በዘለቀው የስልጣን ዘመናቸው ተፈጽመዋል በተባሉ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ማሰቃየት እና ሌሎች ወንጀሎች ላይ ክስ እንደሚመሰርት አስታውቋል።
#አልጀዚራ #ቲአርቲወርልድ #ስፑትኪን #ሮይተርስ
@tikvahethiopia
#Motta 📍
የሞጣ ከተማ ሰላም እና ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ፤ በህግ የሚፈለጉ ግለሰቦች በሁለት ቀን ለመንግስት እጅ እንዲሰጡት አሳሰበ።
ኮማንድ ፖስቱ ይህን ያሳሰበው ትላንት ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም በወቅታዊ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ ነው።
በህግ የሚፈለጉ ግለሰቦች ከሁለት ቀን ሞጣ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት በመቅረብ ለመንግስት እጅ እንዲሰጡ ያሳሰበው ኮማንድፖስቱ ግለሰቦቹ በተሰጣቸው እድል ባለመጠቀም ለሚወሰደው ርምጃ ሁሉ ሀላፊነት አልወስድም ብሏል።
በሌላ በኩል ፤ ኮማንድ ፖስቱ ፦
➡️ ማንኛውንም ህ/ሠብ በቡድን መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን ገልጿል።
➡️ ማንኛውም ማህበረሰብ በህግ የሚፈለጉ አካላትን ደብቆ ወይም አከራይቶ ቢገኝ ተጠያቂ መሆኑን አውቆ ችግር ፈጣሪዎችንና ተፈላጊዎችን አጋልጦ እንዲሰጥ አሳስቧል።
➡️ ከጠዋቱ 12:30 በፊትና ከምሽቱ 1: 30 በኋላ ስምሪት ከተሰጣቸው የጸጥታ ሀይሎች ውጭ የእንቅስቃሴ ገደብ ተቀምጧል። ይህ ሳይሆን ቢቀር የጸጥታ ሀይሉ እርምጃ ይወስዳል ተብሏል።
➡️ ስምሪት ከተሰጠው የጸጥታ ሀይል ውጭ የጦር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈጽሞ ተከልክሏል።
(ተጨማሪ ክልከላዎችን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
የሞጣ ከተማ ሰላም እና ፀጥታ ኮማንድ ፖስት ፤ በህግ የሚፈለጉ ግለሰቦች በሁለት ቀን ለመንግስት እጅ እንዲሰጡት አሳሰበ።
ኮማንድ ፖስቱ ይህን ያሳሰበው ትላንት ግንቦት 17 ቀን 2014 ዓ/ም በወቅታዊ ጉዳይ ባወጣው መግለጫ ነው።
በህግ የሚፈለጉ ግለሰቦች ከሁለት ቀን ሞጣ ከተማ ፖሊስ ጽ/ቤት በመቅረብ ለመንግስት እጅ እንዲሰጡ ያሳሰበው ኮማንድፖስቱ ግለሰቦቹ በተሰጣቸው እድል ባለመጠቀም ለሚወሰደው ርምጃ ሁሉ ሀላፊነት አልወስድም ብሏል።
በሌላ በኩል ፤ ኮማንድ ፖስቱ ፦
➡️ ማንኛውንም ህ/ሠብ በቡድን መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን ገልጿል።
➡️ ማንኛውም ማህበረሰብ በህግ የሚፈለጉ አካላትን ደብቆ ወይም አከራይቶ ቢገኝ ተጠያቂ መሆኑን አውቆ ችግር ፈጣሪዎችንና ተፈላጊዎችን አጋልጦ እንዲሰጥ አሳስቧል።
➡️ ከጠዋቱ 12:30 በፊትና ከምሽቱ 1: 30 በኋላ ስምሪት ከተሰጣቸው የጸጥታ ሀይሎች ውጭ የእንቅስቃሴ ገደብ ተቀምጧል። ይህ ሳይሆን ቢቀር የጸጥታ ሀይሉ እርምጃ ይወስዳል ተብሏል።
➡️ ስምሪት ከተሰጠው የጸጥታ ሀይል ውጭ የጦር መሳርያ ይዞ መንቀሳቀስ ፈጽሞ ተከልክሏል።
(ተጨማሪ ክልከላዎችን ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia