TIKVAH-ETHIOPIA
የዋጋ ግሽበት📈 መቆሚያ ያልተገኘለት የዋጋ ግሽበት አሁንም ማሻቀቡን እንደቀጠለ ነው። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ እንደሚያሳየው የመጋቢት ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ34.7 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ የምግብ ዋጋ ግሽበት የመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ43.4…
የዋጋ ግሽበት📈
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የሚያዝያ ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 36.6 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
ምግብና ምግብ-ነክ ያልሆኑ የኢንዴክሱ ክፍሎች በሁለት ትልልቅ የሃይማኖት በዓላት ምክንያት በያዝነው ወር ወቅታዊ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡
የምግብ ዋጋ ግሽበት የሚያዝያ ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ42.9 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በያዝነው ወር በተደራራቢ የሃይማኖት በዓላት መከበር ምክንያት በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ መታየቱን ካፒታል ጋዜጣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የሚያዝያ ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 36.6 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
ምግብና ምግብ-ነክ ያልሆኑ የኢንዴክሱ ክፍሎች በሁለት ትልልቅ የሃይማኖት በዓላት ምክንያት በያዝነው ወር ወቅታዊ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡
የምግብ ዋጋ ግሽበት የሚያዝያ ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ42.9 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በያዝነው ወር በተደራራቢ የሃይማኖት በዓላት መከበር ምክንያት በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ መታየቱን ካፒታል ጋዜጣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
#ESP2022
በአ/አ የአሜሪካ ኤምባሲ ለEducationUSA Scholars Program (ESP) 2022 ማመልከቻ ክፍት መደረጉን ዛሬ አሳውቋል።
ኤምባሲው ፤ ESP የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት በአካዳሚክ የላቁ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በአሜሪካ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች በማመልከት የሰለጠኑ እና በደንብ የተማሩ መሪዎችን ለማፍራት የሚረዳ የ4 ሳምንት የስልጠና ፕሮግራም መሆኑን አስታውሷል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃንና የማመልከቻ ቅፆችን በዚህ https://ow.ly/B6b750J0X7q ማግኘት ይቻላል።
ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም ስለ ፕሮግራሙ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፊታችን ማክሰኞ ግንቦት 2/2014 ዓ/ም የኦንላይን መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
በዚሁ ላይ ለመሳተፍ የሚከተለውን ሊንክ https://ow.ly/6e4w50J0X7s 👉Meeting ID 160 083 5437 መጠቀም እንደሚቻል በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በአ/አ የአሜሪካ ኤምባሲ ለEducationUSA Scholars Program (ESP) 2022 ማመልከቻ ክፍት መደረጉን ዛሬ አሳውቋል።
ኤምባሲው ፤ ESP የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት በአካዳሚክ የላቁ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በአሜሪካ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች በማመልከት የሰለጠኑ እና በደንብ የተማሩ መሪዎችን ለማፍራት የሚረዳ የ4 ሳምንት የስልጠና ፕሮግራም መሆኑን አስታውሷል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃንና የማመልከቻ ቅፆችን በዚህ https://ow.ly/B6b750J0X7q ማግኘት ይቻላል።
ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም ስለ ፕሮግራሙ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፊታችን ማክሰኞ ግንቦት 2/2014 ዓ/ም የኦንላይን መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
በዚሁ ላይ ለመሳተፍ የሚከተለውን ሊንክ https://ow.ly/6e4w50J0X7s 👉Meeting ID 160 083 5437 መጠቀም እንደሚቻል በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#ፓስፖርት
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፥ የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት በኦንላይን ላይ ቀጠሮ አስይዘው በተለያየ ምክንያት የቀጠሮ ጊዜ ያለፈባቸው ተገልጋዮች ከዚህን ቀደም በቅጣት በማንኛውም የስራ ቀን አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን ገልጾ ከፊታችን ሰኞ ግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ግን በስራ ሰዓት አርብ አርብ ቀን ብቻ በቅጣት አገልገሎት የሚያገኙ መሆኑን አሳውቋል።
ተገልጋዮች ይህን አውቀው በዕለቱ ብቻ እንዲገኙ መልዕክት አስተላልፏል።
በተጨማሪም ፦ የቀጠሮ ጊዜያቸው ከ1 ወር በላይ ያለፈባቸው ተገልጋዮች #በኦንላይን ላይ ዳግም ማመልከት እንዳለባቸው ገልጿል።
#ማስታወሻ፦ ከዚህ ቀደም " የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ " ይባል የነበረው ተቋም ስያሜው የፌዴራል መንግስት አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ 1263/2014 ዓ.ም መሠረት " የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት / Immigration and citizenship service " በሚል ስያሜ ተቀይሯል።
@tikvahethiopia
የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ፥ የፓስፖርት አገልግሎት ለማግኘት በኦንላይን ላይ ቀጠሮ አስይዘው በተለያየ ምክንያት የቀጠሮ ጊዜ ያለፈባቸው ተገልጋዮች ከዚህን ቀደም በቅጣት በማንኛውም የስራ ቀን አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን ገልጾ ከፊታችን ሰኞ ግንቦት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ግን በስራ ሰዓት አርብ አርብ ቀን ብቻ በቅጣት አገልገሎት የሚያገኙ መሆኑን አሳውቋል።
ተገልጋዮች ይህን አውቀው በዕለቱ ብቻ እንዲገኙ መልዕክት አስተላልፏል።
በተጨማሪም ፦ የቀጠሮ ጊዜያቸው ከ1 ወር በላይ ያለፈባቸው ተገልጋዮች #በኦንላይን ላይ ዳግም ማመልከት እንዳለባቸው ገልጿል።
#ማስታወሻ፦ ከዚህ ቀደም " የኢሚግሬሽን ዜግነትና ወሳኝ ኩነት ኤጀንሲ " ይባል የነበረው ተቋም ስያሜው የፌዴራል መንግስት አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር ለመወሰን በወጣው አዋጅ 1263/2014 ዓ.ም መሠረት " የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት / Immigration and citizenship service " በሚል ስያሜ ተቀይሯል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈጸም የሚገኝ ገንዘብን/ ንብረትን በተለያየ ዘዴ በህጋዊ መንገድ እንደተገኘ አስመስሎ ለመጠቀም መሞከር ነው፡፡
በሀገራችን ህገወጥ ገንዘብ/ንብረት ማመንጫ ወንጅሎች ተብለው ከተለዩት መካከል ፦
👉 ሙስና፣
👉 ግብርን ማጭበርበር፣
👉 ህገወጥ የውጪ ምንዛሬ፣
👉 ህገወጥ ሀዋላ፣
👉 ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ፣
👉 አደንዛዥ ዕጽ ዝውውር፣
👉 ሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ህትመት እና ሌሎች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
እነዚህን ወንጀሎች የፈጸመ አካል ወንጀሎቹን በመፈጸሙ ለእያንዳንዶቹ ወንጀሎች በህግ በተደነገገው መሰረት ቅጣት ይጣልበታል።
በተጨማሪ ወንጀሎቹን በመፈጸም ያገኘውን ሀብት/ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ለማቅረብ ወይም ለመጠቀም በመሞከሩ በአዋጅ 780/2005 መሰረት ንብረቱን ሙሉ ለሙሉ መውረስ እንደተጠበቀ ሆኖ የበርካታ አመታት እሰራት እንዲፈረድበት ይደነግጋል፡፡
ምንጭ፦ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት
@tikvahethiopia
በወንጀል ድርጊት የተገኘ ገንዘብ ወይም ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ ወንጀል የተለያዩ ወንጀሎችን በመፈጸም የሚገኝ ገንዘብን/ ንብረትን በተለያየ ዘዴ በህጋዊ መንገድ እንደተገኘ አስመስሎ ለመጠቀም መሞከር ነው፡፡
በሀገራችን ህገወጥ ገንዘብ/ንብረት ማመንጫ ወንጅሎች ተብለው ከተለዩት መካከል ፦
👉 ሙስና፣
👉 ግብርን ማጭበርበር፣
👉 ህገወጥ የውጪ ምንዛሬ፣
👉 ህገወጥ ሀዋላ፣
👉 ህገወጥ የጦር መሳሪያ ዝውውር ፣
👉 አደንዛዥ ዕጽ ዝውውር፣
👉 ሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ህትመት እና ሌሎች የሚጠቀሱ ናቸው፡፡
እነዚህን ወንጀሎች የፈጸመ አካል ወንጀሎቹን በመፈጸሙ ለእያንዳንዶቹ ወንጀሎች በህግ በተደነገገው መሰረት ቅጣት ይጣልበታል።
በተጨማሪ ወንጀሎቹን በመፈጸም ያገኘውን ሀብት/ንብረት ህጋዊ አስመስሎ ለማቅረብ ወይም ለመጠቀም በመሞከሩ በአዋጅ 780/2005 መሰረት ንብረቱን ሙሉ ለሙሉ መውረስ እንደተጠበቀ ሆኖ የበርካታ አመታት እሰራት እንዲፈረድበት ይደነግጋል፡፡
ምንጭ፦ የፋይናንስ ደህንነት አገልግሎት
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛው የት ነው ያለው ?
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ከቀናት በፊት ማንነታቸውን ባልገለጹ የመንግስት ሰዎች ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ውስጥ ተይዞ መወሰዱንና የት እንዳለ አለመታወቁ መግለፁ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ጋዜጠኛው የት እና በምን ሁኔታ እንዳለ ግልፅ እንዲደረግ እየጠየቁ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከልም የጋዜጠኛው የት እንዳለ አለመታወቅ እንዳሳሰበው ገልጿል።
ማዕከሉ ፤ መንግስት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ የት እንዳለ እንዲያሳውቅ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል ፤ ከ2019 ጀምሮ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጉዳዮችን የሚሟገቱ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችንና ጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት፣ ከለላ በመስጠት እና በማስተዋወቅ ላይ የሚገኝ ለትርፍ ያልተቋቋመ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ነው።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ከቀናት በፊት ማንነታቸውን ባልገለጹ የመንግስት ሰዎች ተከራይቶ ከሚኖርበት ቤት ውስጥ ተይዞ መወሰዱንና የት እንዳለ አለመታወቁ መግለፁ ይታወሳል።
ይህንን ተከትሎ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ጋዜጠኛው የት እና በምን ሁኔታ እንዳለ ግልፅ እንዲደረግ እየጠየቁ ይገኛሉ።
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከልም የጋዜጠኛው የት እንዳለ አለመታወቅ እንዳሳሰበው ገልጿል።
ማዕከሉ ፤ መንግስት ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ የት እንዳለ እንዲያሳውቅ አሳስቧል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ማዕከል ፤ ከ2019 ጀምሮ በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ጉዳዮችን የሚሟገቱ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችንና ጋዜጠኞችን አቅም በመገንባት፣ ከለላ በመስጠት እና በማስተዋወቅ ላይ የሚገኝ ለትርፍ ያልተቋቋመ መንግስታዊ ያልሆነ ተቋም ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ነዋሪዎችን ያማረሩት ጫኝ እና አውራጆች ፦ ከቲክቫህ ቤተሰብ አባል ፦ " ... በአዲስ አበባ ከተማ ላይ በሁሉም ሰፈር ማለት ይቻላል በህገወጥ ጫኝና አውራጆች በሚጠየቅ የተጋነነ ክፍያ ምክንያት ዕቃ መኪና ላይ መጫንም ሆነ ማውረድ አዳጋች ሆኗል፡፡ የአዲስ አበባ ፖሊስ እነዚህ ህገ ወጦች ላይ እርምጃ በመውሰድ ህብረተሰቡን ሊታደግ ይገባል። ሰው ተሰቃይቷል ፤ ህዝቡ ተበሳጭቷል ፤ ጉረቤትህ እና ልጆችህ…
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ ጫኝና አውራጆች ያለአግባብ ገንዘብ በመጠየቅ ነዋሪዎችን እያማረሩ ነው።
የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር በመዲናዋ ከሚገኙ የጫኝና አውራጅ ማህበራት ጋር ምክክር አድርገዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ዳይሬክተር ኮማንደር ሰለሞን ፋንታሁን ህብረተሰቡ ንብረቱን ከቦታ ቦታ ሲያንቀሳቅስ በጫኝና አውራጅ ያለአግባብ ገንዘብ እየተጠየቀ በመሆኑ ነዋሪዎች ለምሬት ተዳርገዋል ብለዋል።
ንብረቱ ከሚገዛበት ዋጋ በላይ ህብረተሰቡ እንዲከፍል እየተጠየቀ መሆኑ ንብረታቸውን በለሊት ፈረቃ እንዲያጓጉዙ ተገደዋል ሲሉም ገልፀዋል።
ጫኝና አውራጆች ያልተደራጁበት ቦታ ላይ በመምጣት እናወርዳለን በማለት ግጭት የሚፈጠርበት ሁኔታ መኖሩን አክለዋል፡፡
አቅመ ደካሞች ገንዘብ የለንም ሲሉ ፍቃደኛ አለመሆን በጉልበት ለማስገደድ መሞከር፣ጠጥተው በመምጣት ከማህበረሰቡ ጋር መጋጨት፣ ገንዘብ አስገድዶ መቀበል የሚሉት ዋናነት የሚታዩ ችግሮች መሆናቸዉን አንስተዋል፡፡
በህጋዊ መንገድ የተደራጁ ጫኝና አውራጆች ደግሞ ከስራ አድል ፈጠራ ባሻገር #መብትና_ግዴታቸውን_ያለማወቅ ችግር እንዳለባቸዉ የጠቀሱት ኮማንደር ሰለሞን መሰል ሕገወጥ ድርጊቶችን መከላለል የሁሉም ኃላፊነት በመሆኑ ህብረተሰቡም ሊተባበር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ዛሬ በተካሄደው መድረክ በከተማዋ 1072 ህጋዊና 577 ህገወጥ ጫኝና አውራጅ ማህበራት ይገኛሉ መባሉን አዲስ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
#ማስታወሻ ፦ ያልተገባ ስራ የሚሰሩ ጫኝ እና ወራጆችን ወደ ህግ ከማቅረብ ይልቅ #ተስማሙ የሚሉ የፖሊስ አባላትን ህብረተሰቡ ሲመለከት በ991 ነፃ የስልክ መስመር እና በ 0111110111 በመደወል ለፖሊስ መጠቆም ይቻላል።
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ጫኝና አውራጆች ያለአግባብ ገንዘብ በመጠየቅ ነዋሪዎችን እያማረሩ ነው።
የአዲስ አበባ ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጋር በመተባበር በመዲናዋ ከሚገኙ የጫኝና አውራጅ ማህበራት ጋር ምክክር አድርገዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የማህበረሰብ አቀፍ ዳይሬክተር ኮማንደር ሰለሞን ፋንታሁን ህብረተሰቡ ንብረቱን ከቦታ ቦታ ሲያንቀሳቅስ በጫኝና አውራጅ ያለአግባብ ገንዘብ እየተጠየቀ በመሆኑ ነዋሪዎች ለምሬት ተዳርገዋል ብለዋል።
ንብረቱ ከሚገዛበት ዋጋ በላይ ህብረተሰቡ እንዲከፍል እየተጠየቀ መሆኑ ንብረታቸውን በለሊት ፈረቃ እንዲያጓጉዙ ተገደዋል ሲሉም ገልፀዋል።
ጫኝና አውራጆች ያልተደራጁበት ቦታ ላይ በመምጣት እናወርዳለን በማለት ግጭት የሚፈጠርበት ሁኔታ መኖሩን አክለዋል፡፡
አቅመ ደካሞች ገንዘብ የለንም ሲሉ ፍቃደኛ አለመሆን በጉልበት ለማስገደድ መሞከር፣ጠጥተው በመምጣት ከማህበረሰቡ ጋር መጋጨት፣ ገንዘብ አስገድዶ መቀበል የሚሉት ዋናነት የሚታዩ ችግሮች መሆናቸዉን አንስተዋል፡፡
በህጋዊ መንገድ የተደራጁ ጫኝና አውራጆች ደግሞ ከስራ አድል ፈጠራ ባሻገር #መብትና_ግዴታቸውን_ያለማወቅ ችግር እንዳለባቸዉ የጠቀሱት ኮማንደር ሰለሞን መሰል ሕገወጥ ድርጊቶችን መከላለል የሁሉም ኃላፊነት በመሆኑ ህብረተሰቡም ሊተባበር እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።
ዛሬ በተካሄደው መድረክ በከተማዋ 1072 ህጋዊና 577 ህገወጥ ጫኝና አውራጅ ማህበራት ይገኛሉ መባሉን አዲስ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
#ማስታወሻ ፦ ያልተገባ ስራ የሚሰሩ ጫኝ እና ወራጆችን ወደ ህግ ከማቅረብ ይልቅ #ተስማሙ የሚሉ የፖሊስ አባላትን ህብረተሰቡ ሲመለከት በ991 ነፃ የስልክ መስመር እና በ 0111110111 በመደወል ለፖሊስ መጠቆም ይቻላል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba 🪪 " ላልተወሰነ ጊዜ አዲስ መታወቂያ መስጠት አቁመናል " - የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ የአዲስ አበባ ከተማ ወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ላልተወሰነ ጊዜ " አዲስ መታወቂያ " የመስጠት አገልግሎት ማቆሙን አስታውቋል። ኤጀንሲው የመታወቂያ ፣ የልደት ፣ የጋብቻና የሞት ማስረጃዎችን ይመዘግባል ፤ ዜጎች በሚፈልጉበት ወቅትም አገልግሎቱን ይሰጣል፡፡ በአገልግሎት አሰጣቱ…
#መታወቂያ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተበራከተ የመጣዉን ሰነድ እና የነዋሪነት መታወቂያ አስመስሎ የመስራት /ፎርጀሪ/ ወንጀል ተጋላጭነትን ለመከላከል አዲስ የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት ከሚያዚያ 21፣ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ግዜ እንዲቆም መደረጉ ይታወሳል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ እድሚያቸው 18 ዓመት ሞልቶ የነዋሪነት መታወቂያ ያላወጡ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመደቡ ተማሪዎች ፦
* በከተማዉ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ መሆኑን የሚያስረዳ የ12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ እና
* ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያለፉበትን ዉጤት በማቅረብ በነዋሪነት የቤተሰብ ቅጽ ዉሰጥ አስቀድሞ የተመዘገቡ መሆኑ ሲረጋገጥ አገልግሎቱን እንዲያገኙ ተፈቅዷል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ወ/ኩ/ም/ኤጀንሲ
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እየተበራከተ የመጣዉን ሰነድ እና የነዋሪነት መታወቂያ አስመስሎ የመስራት /ፎርጀሪ/ ወንጀል ተጋላጭነትን ለመከላከል አዲስ የነዋሪነት መታወቂያ አገልግሎት ከሚያዚያ 21፣ 2014 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ግዜ እንዲቆም መደረጉ ይታወሳል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ እድሚያቸው 18 ዓመት ሞልቶ የነዋሪነት መታወቂያ ያላወጡ ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተመደቡ ተማሪዎች ፦
* በከተማዉ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ መሆኑን የሚያስረዳ የ12ኛ ክፍል የትምህርት ማስረጃ እና
* ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያለፉበትን ዉጤት በማቅረብ በነዋሪነት የቤተሰብ ቅጽ ዉሰጥ አስቀድሞ የተመዘገቡ መሆኑ ሲረጋገጥ አገልግሎቱን እንዲያገኙ ተፈቅዷል።
ምንጭ፦ የአዲስ አበባ ወ/ኩ/ም/ኤጀንሲ
@tikvahethiopia
#ሌተናል_ኮሎኔል_ፍሥሐ_ደስታ
በድረግ ዘመነ መንግስት ኢትዮጵያን በምክትል ፕሬዝዳንትነት የመሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የቀድሞው መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማሪያም ምክትል በመሆን የኢሕዲሪ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ፣ ኢሕአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ለ20 ዓመታት ያህል በእስር ቆይተዋል።
ቤተሰቦቻቸው ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ የልብ ሕመም የነበረባቸው ሲሆን ለዚህም በአገር ውስጥና በውጪ ክትትል ሲያደርጉ ነበር።
ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት የነበሩት ፍሰሐ ሕይወታቸው ያለፈው አርብ ሚያዚያ 28/2014 ዓ. ም. እኩለ ሌሊት አካባቢ ሲሆን የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው እሁድ ሚያዚያ 30/2014 ዓ. ም. በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ተገልጿል።
ከእስር ከወጡ በኋላ በሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ስላለፉባቸው ሁኔታዎች የሚተርክ "አብዮቱና ትዝታዬ" የሚል መጽሐፍ ያበረከቱ ሲሆን፣ በዚህም "ደርግ በወሰዳቸው በጎ ዕርምጃዎች እንደምደሰት ሁሉ በማወቅ፣ በድፍረት፣ ባለማወቅና በስህተት ለተፈጸሙት ደግሞ ሙሉ ኃላፊነት በመውሰድ በበኩሌ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ብለው ነበር።
ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ከመጀመሪያው መጽሐፋቸው በተጨማሪ 2ኛ መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ እንደነበሩ ቢቢሲ ቤተሰቦቻቸውን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
ትግራይ አድዋ ውስጥ የተወለዱት ሌፍተናንት ኮሎኔል ፍሰሐ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአደዋ ንግሥተ ሳባ እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃን አዲግራት ውስጥ በሚገኘው አግአዚ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-05-07
@tikvahethiopia
በድረግ ዘመነ መንግስት ኢትዮጵያን በምክትል ፕሬዝዳንትነት የመሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ በ81 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
የቀድሞው መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ ኃ/ማሪያም ምክትል በመሆን የኢሕዲሪ ምክትል ፕሬዝዳንት የነበሩት ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ደስታ፣ ኢሕአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ለ20 ዓመታት ያህል በእስር ቆይተዋል።
ቤተሰቦቻቸው ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ፤ ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ የልብ ሕመም የነበረባቸው ሲሆን ለዚህም በአገር ውስጥና በውጪ ክትትል ሲያደርጉ ነበር።
ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት የነበሩት ፍሰሐ ሕይወታቸው ያለፈው አርብ ሚያዚያ 28/2014 ዓ. ም. እኩለ ሌሊት አካባቢ ሲሆን የቀብር ሥነ ሥርዓታቸው እሁድ ሚያዚያ 30/2014 ዓ. ም. በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ተገልጿል።
ከእስር ከወጡ በኋላ በሥልጣን ላይ በነበሩበት ወቅት ስላለፉባቸው ሁኔታዎች የሚተርክ "አብዮቱና ትዝታዬ" የሚል መጽሐፍ ያበረከቱ ሲሆን፣ በዚህም "ደርግ በወሰዳቸው በጎ ዕርምጃዎች እንደምደሰት ሁሉ በማወቅ፣ በድፍረት፣ ባለማወቅና በስህተት ለተፈጸሙት ደግሞ ሙሉ ኃላፊነት በመውሰድ በበኩሌ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ብለው ነበር።
ሌ/ኮሎኔል ፍሰሐ ከመጀመሪያው መጽሐፋቸው በተጨማሪ 2ኛ መጽሐፍ በማዘጋጀት ላይ እንደነበሩ ቢቢሲ ቤተሰቦቻቸውን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
ትግራይ አድዋ ውስጥ የተወለዱት ሌፍተናንት ኮሎኔል ፍሰሐ፣ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በአደዋ ንግሥተ ሳባ እንዲሁም ሁለተኛ ደረጃን አዲግራት ውስጥ በሚገኘው አግአዚ ትምህርት ቤት ተከታትለዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-05-07
@tikvahethiopia
አዲሱ_የሒሳብ_መዝገብ_አያያዝ_መመሪያ.pdf
1.1 MB
#እንድታውቁት
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦዲት የቅሬታ ምንጭ ሆኖ የቆየው " የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 " ን በአዲስ መመሪያ እንዲተካ ማድረጉን አሳውቋል።
መመሪያውን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት የታክስ አስተዳደሩን ቀልጣፋ ለማድረግ እና ግልጽነት የጎደላቸውን አሰራሮች ግልጽ ለማድረግ ነው ብሏል ሚኒስቴሩ።
አዲሱ መመሪያ ቁጥር 176/2014 በሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 ላይ የነበረውን አሰራር ያሻሽላል ተብሏል።
አዲሱ ወይም የተሻሻለው የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 ከላይ በPDF ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ኦዲት የቅሬታ ምንጭ ሆኖ የቆየው " የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 " ን በአዲስ መመሪያ እንዲተካ ማድረጉን አሳውቋል።
መመሪያውን ማሻሻል ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት የታክስ አስተዳደሩን ቀልጣፋ ለማድረግ እና ግልጽነት የጎደላቸውን አሰራሮች ግልጽ ለማድረግ ነው ብሏል ሚኒስቴሩ።
አዲሱ መመሪያ ቁጥር 176/2014 በሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 152/2011 ላይ የነበረውን አሰራር ያሻሽላል ተብሏል።
አዲሱ ወይም የተሻሻለው የሒሳብ መዝገብ አያያዝ መመሪያ ቁጥር 176/2014 ከላይ በPDF ተያይዟል።
@tikvahethiopia
#ጥንቃቄ
በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ሦስት መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እናዳይጠቀም ማሳሰቢያ ተላልፏል።
በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ጥራታቸው፣ ደህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጠ እና በጤና ላይ ከቀላል እስከ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ፦
👉 Titan gel፣
👉 Mara Moja
👉 Relief የተባሉ መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አሳስቧል።
መድኃኒቶቹ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ያልተመዘገቡና በህጋዊ መንገድም ወደ አገር ዉስጥ ያልገቡ ናቸው።
Titan gel የተባለው መድኃኒት በሐኪም ብቻ በመታዘዝ ጥቅም ላይ መዋል ያለበት ሲሆን ነገር ግን በድብቅና በህገወጥ መንገድ ገበያ ላይ አንደሚገኝ ታውቋቃ።
መድኃኒቶቹን ማንኛውም ግለሰብ ወይም አካል በህጋዊ ተቋማት ሆነ በህገወጥ መንገድ ሲያገኛቸው እንዳይጠቀማቸውና በባለስልጣን መስሪያቤቱ ነጻ የስልክ መስመር 8482 በአቅሪያባቸው ለሚገኙ የክልል ተቆጣጠሪዎች ወይም ለጸጥታ አካላት በመጠቆም አስፈላጊዉን ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።
#ሼር #Share
@tikvahethiopia
በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ሦስት መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እናዳይጠቀም ማሳሰቢያ ተላልፏል።
በህገወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ጥራታቸው፣ ደህንነታቸውና ፈዋሽነታቸው ያልተረጋገጠ እና በጤና ላይ ከቀላል እስከ ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ የሚችሉ ፦
👉 Titan gel፣
👉 Mara Moja
👉 Relief የተባሉ መድኃኒቶችን ህብረተሰቡ እንዳይጠቀም የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አሳስቧል።
መድኃኒቶቹ በኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን ያልተመዘገቡና በህጋዊ መንገድም ወደ አገር ዉስጥ ያልገቡ ናቸው።
Titan gel የተባለው መድኃኒት በሐኪም ብቻ በመታዘዝ ጥቅም ላይ መዋል ያለበት ሲሆን ነገር ግን በድብቅና በህገወጥ መንገድ ገበያ ላይ አንደሚገኝ ታውቋቃ።
መድኃኒቶቹን ማንኛውም ግለሰብ ወይም አካል በህጋዊ ተቋማት ሆነ በህገወጥ መንገድ ሲያገኛቸው እንዳይጠቀማቸውና በባለስልጣን መስሪያቤቱ ነጻ የስልክ መስመር 8482 በአቅሪያባቸው ለሚገኙ የክልል ተቆጣጠሪዎች ወይም ለጸጥታ አካላት በመጠቆም አስፈላጊዉን ትብብር እንዲያደርግ ተጠይቋል።
#ሼር #Share
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሚያዚያ የቤንዚን እና የናፍጣ ምርቶች ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር ፥ የሚያዚያ ወር የቤንዚን እና የናፍጣ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በመጋቢት ወር ላይ ሲሸጥበት በነበረው እንደሚቀጥል አስታውቋል። የአውሮፕላን ነዳጅ ፣ የከባድ ጥቁር ናፍጣ እና የቀላል ጥቁር ናፍጣ የመሸጫ ዋጋ በዓለም አቀፍ ዋጋ መሰረት ተሰልቶ የመጣው ወደ ተጠቃሚው እንዲተላለፍ መወሰኑን ኤፍ ቢ…
#የነዳጅ_ዋጋ_ጭማሪ
ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
በዚህም ፦
👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣
👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣
👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም
👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም እንዲሆን መወሰኑን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ : https://telegra.ph/ETHIOPIA-05-07
@tikvahethiopia
ከነገ ሚያዚያ 30 ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደርጓል።
በዚህም ፦
👉 ቤንዚን በሊትር 36 ብር ከ87 ሳንቲም ፣
👉 ነጭ ናፍጣ በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ኬሮሲን በሊትር 35 ብር ከ43 ሳንቲም፣
👉 ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 52 ብር ከ45 ሳንቲም፣
👉 ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 51 ብር ከ78 ሳንቲም
👉 የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 78 ብር ከ87 ሳንቲም እንዲሆን መወሰኑን የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።
ዝርዝሩን ያንብቡ : https://telegra.ph/ETHIOPIA-05-07
@tikvahethiopia