" ሁሌም ግጭቱ እንዲቆም ፣ ሰብአዊ እርዳታ በሁሉም ቦታ እንዲዳረስ እንዲሁም ሰላምን የሚያመጣ ውጤታማ ድርድር እንዲደረግ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ " - አንቶኒዮ ጉተሬዝ
የተባበሩተ መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንዲያበቃ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በርካታ ግንኙነቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ይህን የተናገሩት በዚህ ሳምንት የምዕራብ አፍሪካ አገራት በሆኑት በሴኔጋል፣ በኒጀር እና በናይጄሪያ ጉብኝት ባደረጉበት ጊዜ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ነው።
ዋና ፀሀፊው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ከህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ጋር ግንኙነቶችን በመፍጠር ጦርነቱ መቋጫ እንዲያገኝ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በዚህም የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብአዊ እርዳታ ለማቅረብ አመቺ ሁኔታ እንዲፈጠርና በመጨረሻም በውይይት ሰላም እንዲወርድ አዘውትረው ሲጥሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
ጉተሬዝ ፥ " ሁሌም ግጭቱ እንዲቆም፣ ሰብአዊ እርዳታ በሁሉም ቦታ እንዲዳረስ እንዲሁም ሰላምን የሚያመጣ ውጤታማ ድርድር እንዲደረግ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ " ሲሉ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
የተባበሩተ መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት እንዲያበቃ ከሁለቱም ወገኖች ጋር በርካታ ግንኙነቶችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ይህን የተናገሩት በዚህ ሳምንት የምዕራብ አፍሪካ አገራት በሆኑት በሴኔጋል፣ በኒጀር እና በናይጄሪያ ጉብኝት ባደረጉበት ጊዜ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ነው።
ዋና ፀሀፊው ከጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ እና ከህወሓት ሊቀመንበር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል (ዶ/ር) ጋር ግንኙነቶችን በመፍጠር ጦርነቱ መቋጫ እንዲያገኝ ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸዋል።
በዚህም የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የሰብአዊ እርዳታ ለማቅረብ አመቺ ሁኔታ እንዲፈጠርና በመጨረሻም በውይይት ሰላም እንዲወርድ አዘውትረው ሲጥሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።
ጉተሬዝ ፥ " ሁሌም ግጭቱ እንዲቆም፣ ሰብአዊ እርዳታ በሁሉም ቦታ እንዲዳረስ እንዲሁም ሰላምን የሚያመጣ ውጤታማ ድርድር እንዲደረግ ጥረት ሳደርግ ቆይቻለሁ " ሲሉ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።
@tikvahethiopia
የዜጎች መረጃን የማግኘት መብት እስከምን ድረስ ነው?
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት ረ/ፕሮፌሰር ዶ/ር ሙላቱ አለማየሁ ፦
" ለሀገራዊ ደኅንነት ከሚያሰጉና በልዩነት ከሚቀመጡት ውጪ ያለ ማንኛውም መረጃ የህዝብ መረጃ ነው ተብሎ ይታሰባል።
ይህ ሕግ ከላይ ከተጠቀሱት ውስን ገደቦች ውጭ ማንኛውም ሰው መረጃ ጠይቆ የማግኘት መብትን ያጎናጽፋል።
ለምሳሌ ፦ አንድ ግለሰብ የህ/ተ/ምክር ቤት የተወያዩበትን ቃለ ጉባዔ አሳዩኝ ብሎ የመጠየቅ መብት ጭምር አለው። ይህ በግለሰብ ደረጃ መተግበር የሚገባው ሕግ ለሚዲያዎች እንኳን ተፈጻሚ አይሆንም። "
◾️
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ ፦
" የመረጃ መዛባት አንደኛው መንስዔ የመረጃ እጦት ነው።
መረጃ አሰጣጡ ተቋማዊ ቅርጽ አለመያዙና በግለሰቦችና በኃላፊዎች ፈቃድ መወሰኑ የመረጃ ነጻነትን የሚጋፋ ጉዳይ ሆኗል። ለዚህም መረጃ በመስጠት የሚሞገስ፤ መረጃ ባለመስጠት የሚወቀስበት ዘመን መምጣት አለበት።
'መረጃ ከልካዮች ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚያደርጉት ይመስላቸዋል። የመንግሥት ተቋማት የህዝብ ሀብትን መሰረት አድርገው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው ይህንን በግልጽና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ ለህብረተሰቡ ማቅረብ በሕግ ይገደዳሉ "
ያንብቡ 👉 https://telegra.ph/Tikvah-Family-05-06
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት ረ/ፕሮፌሰር ዶ/ር ሙላቱ አለማየሁ ፦
" ለሀገራዊ ደኅንነት ከሚያሰጉና በልዩነት ከሚቀመጡት ውጪ ያለ ማንኛውም መረጃ የህዝብ መረጃ ነው ተብሎ ይታሰባል።
ይህ ሕግ ከላይ ከተጠቀሱት ውስን ገደቦች ውጭ ማንኛውም ሰው መረጃ ጠይቆ የማግኘት መብትን ያጎናጽፋል።
ለምሳሌ ፦ አንድ ግለሰብ የህ/ተ/ምክር ቤት የተወያዩበትን ቃለ ጉባዔ አሳዩኝ ብሎ የመጠየቅ መብት ጭምር አለው። ይህ በግለሰብ ደረጃ መተግበር የሚገባው ሕግ ለሚዲያዎች እንኳን ተፈጻሚ አይሆንም። "
◾️
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ ፦
" የመረጃ መዛባት አንደኛው መንስዔ የመረጃ እጦት ነው።
መረጃ አሰጣጡ ተቋማዊ ቅርጽ አለመያዙና በግለሰቦችና በኃላፊዎች ፈቃድ መወሰኑ የመረጃ ነጻነትን የሚጋፋ ጉዳይ ሆኗል። ለዚህም መረጃ በመስጠት የሚሞገስ፤ መረጃ ባለመስጠት የሚወቀስበት ዘመን መምጣት አለበት።
'መረጃ ከልካዮች ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለማዳን የሚያደርጉት ይመስላቸዋል። የመንግሥት ተቋማት የህዝብ ሀብትን መሰረት አድርገው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው ይህንን በግልጽና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ ለህብረተሰቡ ማቅረብ በሕግ ይገደዳሉ "
ያንብቡ 👉 https://telegra.ph/Tikvah-Family-05-06
@tikvahethiopia
" ልጆቻችን እንዳይራቡ እና ቤተሰብም ችግር ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ችግር እየየን እየሰራን ነው " - የባለ ሶስት እግር (ባጃጅ) አሽከርካሪዎች
በተለያዩ ከተሞች በባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ እና ኑሯቸውን በዛ ያደረጉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በነዳጅ (ቤንዚን) እጥረት እና አለመገኘት ሳቢያ ከፍተኛ ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
ለአብነት በሀዋሳ ከተማ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ችግሩ ወራትን ማስቆጠሩን ፤ ነገር ግን አሁንም ነዳጅ (ቤንዚን) ማግኘት ፈተና እንደሆነ መቀጠሉን ገልፀዋል።
" ነዳጅ (ቤንዚን) የለም ይባላል ፤ ሱቅ ውስጥ እና በየመንገዱ በህገወጥ መልኩ ከዋናው ዋጋ በእጥፍ ጨምሮ ሲሸጥ ይውላል፤ ነዳጅ (ቤንዚን) ከማደያ እየወጣ በየግለሰብ እጅ ገብቶ እና በየሱቁ ሲሸጥ የሚቆጣጠር እና መፍትሄ የሚሰጥ አካል አልተገኘም። በዚህ ላይ የተለያዩ አካላትም እጃቸውን ሊኖርበት ይችላል " ሲሉ ገልፀዋል።
ከማደያ ውጭ አንድ ሊትር እስከ 70 ብር ድረስ ነው የሚሸጠው ፤ እነዚህ አካላት እንደልብ ነዳጅ እያገኙ እና እየሸጡ ነዳጅ (ቤንዚን) ጠፋ ማለት ተቀባይነት የለውም ብለዋል።
" ልጆቻችን እንዳይራቡ እና ቤተሰብ ችግር ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ችግር እየየን እየሰራን ነው በዚህ ጉዳይ መፍትሄ እንሻለን " ሲሉ ገልፀዋል።
በመንግስት መዋቅር ውስጥና በነዳጅ ማደያዎች ይህ ችግር እንዳይፈታ የሚፈልጉ የህገወጥ ድርጊቱ የጥቅም ተጋሪዎች ስለሚኖሩ አስፈላጊው እርምት ሊደርግ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
ውድ ቤተሰቦቻች እናተስ በአካባቢያዎችሁ ላይ ተመሳሳይ ችግር አለ ? መልዕክታችሁ በዚህ አስቀምጡልን @tikvahethiopiaBOT
በተለያዩ ከተሞች በባለሶስት እግር ተሽከርካሪዎች (ባጃጅ) የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ እና ኑሯቸውን በዛ ያደረጉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት በነዳጅ (ቤንዚን) እጥረት እና አለመገኘት ሳቢያ ከፍተኛ ችግር እየገጠማቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
ለአብነት በሀዋሳ ከተማ በዚህ ስራ ላይ የተሰማሩ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ችግሩ ወራትን ማስቆጠሩን ፤ ነገር ግን አሁንም ነዳጅ (ቤንዚን) ማግኘት ፈተና እንደሆነ መቀጠሉን ገልፀዋል።
" ነዳጅ (ቤንዚን) የለም ይባላል ፤ ሱቅ ውስጥ እና በየመንገዱ በህገወጥ መልኩ ከዋናው ዋጋ በእጥፍ ጨምሮ ሲሸጥ ይውላል፤ ነዳጅ (ቤንዚን) ከማደያ እየወጣ በየግለሰብ እጅ ገብቶ እና በየሱቁ ሲሸጥ የሚቆጣጠር እና መፍትሄ የሚሰጥ አካል አልተገኘም። በዚህ ላይ የተለያዩ አካላትም እጃቸውን ሊኖርበት ይችላል " ሲሉ ገልፀዋል።
ከማደያ ውጭ አንድ ሊትር እስከ 70 ብር ድረስ ነው የሚሸጠው ፤ እነዚህ አካላት እንደልብ ነዳጅ እያገኙ እና እየሸጡ ነዳጅ (ቤንዚን) ጠፋ ማለት ተቀባይነት የለውም ብለዋል።
" ልጆቻችን እንዳይራቡ እና ቤተሰብ ችግር ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ችግር እየየን እየሰራን ነው በዚህ ጉዳይ መፍትሄ እንሻለን " ሲሉ ገልፀዋል።
በመንግስት መዋቅር ውስጥና በነዳጅ ማደያዎች ይህ ችግር እንዳይፈታ የሚፈልጉ የህገወጥ ድርጊቱ የጥቅም ተጋሪዎች ስለሚኖሩ አስፈላጊው እርምት ሊደርግ ይገባል ሲሉ አስገንዝበዋል።
ውድ ቤተሰቦቻች እናተስ በአካባቢያዎችሁ ላይ ተመሳሳይ ችግር አለ ? መልዕክታችሁ በዚህ አስቀምጡልን @tikvahethiopiaBOT
#EKA_KOTEBE
ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ትላንትና #የመጨረሻውን የኮቪድ-19 ታካሚ በሰላም ወደ ቤቱ መሸኘቱን እና ሆስፒታሉ በሁለት አመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ኮቪድ19 ታካሚ ውሎ ማደሩን ስራ አስኪያጁ ዶ/ር ያሬድ አግደው ገልፀዋል።
ዶ/ር ያሬድ አግደው፤ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ላለፉት ሁለት አመታት የኮቪድ-19 ህክምና መዕከል ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንዳለን አስታውሰዋል።
" በትናንትናው ዕለት የመጨረሻውን ታካሚ ወደ ቤቱ በሰላም ሸኝተናል " ያሉት ስራ አስኪያጁ " በሁለት አመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሆስፒታላችን ያለ ኮቪድ19 ታካሚ ውሎ አድሯል " ሲሉም ገልፀዋል።
" ከዚህ በኋላ ሀገርን በሚጎዳ መልኩ የኮቪድ19 ማዕበል በሀገራችን በድጋሚ እንዳይከሰት ሁላችንም የድርሻችን መወጣት ይኖርብናል " ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
@tikvahethiopia
ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ትላንትና #የመጨረሻውን የኮቪድ-19 ታካሚ በሰላም ወደ ቤቱ መሸኘቱን እና ሆስፒታሉ በሁለት አመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ኮቪድ19 ታካሚ ውሎ ማደሩን ስራ አስኪያጁ ዶ/ር ያሬድ አግደው ገልፀዋል።
ዶ/ር ያሬድ አግደው፤ በተረጋገጠ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ላለፉት ሁለት አመታት የኮቪድ-19 ህክምና መዕከል ሆኖ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንዳለን አስታውሰዋል።
" በትናንትናው ዕለት የመጨረሻውን ታካሚ ወደ ቤቱ በሰላም ሸኝተናል " ያሉት ስራ አስኪያጁ " በሁለት አመት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ሆስፒታላችን ያለ ኮቪድ19 ታካሚ ውሎ አድሯል " ሲሉም ገልፀዋል።
" ከዚህ በኋላ ሀገርን በሚጎዳ መልኩ የኮቪድ19 ማዕበል በሀገራችን በድጋሚ እንዳይከሰት ሁላችንም የድርሻችን መወጣት ይኖርብናል " ሲሉም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
@tikvahethiopia
#Tigray
የዓለም ምግብ ፕሮግራም እንዳሳወቀው በዚህ ሳምንት እስካሁን 16 የሰብዓዊ ድጋፍ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ትግራይ፣ መቐለ የደረሱ ሲሆን ሌላ ኮንቮይ 64 ተሽከርካሪዎች በጉዞ ላይ ይገኛሉ ይህ በ2022 6ኛው ኮንቮይ ነው።
ድርጅቱ ፥ በሚያዚያ ወር በሸራሮ ወረዳ ለሚገኙ 45,000 ሰዎች ምግብ ማቅረቡን የገለፀ ሲሆን የተመጣጠነ የምግብ ችግር ያለባቸውን 11,000 ሴቶች እና ህፃናትን መድረስ መቻሉን ገልጿል።
በትግራይ ክልል ያለው የሰብዓዊ ሁኔታን ምላሽ ለመስጠት በየዕለቱ ወደ ክልሉ 100 ሰብዓዊ ድጋፍ የጫኑ ተሽከርካሪዎች መግባት ያለባቸው መሆኑን ከዚህ ቀደም የዓለም ምግብ ፕሮግራም መግለፁ ይታወሳል።
ከወራቶች በፊት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ በፊት ከነበረው የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መሻሻሎች ቢታዩም አሁንም ካለው ፍላጎት ጋር ሲነፃፀር አነስተኛና የተቸገሩ ወገኖችን ሰብዓዊ ፍላጎት ለማሟላት ሰፊ ስራ እንደሚጠብቅ የሚገልፁ በርካቶች ናቸው።
@tikvahethiopia
የዓለም ምግብ ፕሮግራም እንዳሳወቀው በዚህ ሳምንት እስካሁን 16 የሰብዓዊ ድጋፍ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ትግራይ፣ መቐለ የደረሱ ሲሆን ሌላ ኮንቮይ 64 ተሽከርካሪዎች በጉዞ ላይ ይገኛሉ ይህ በ2022 6ኛው ኮንቮይ ነው።
ድርጅቱ ፥ በሚያዚያ ወር በሸራሮ ወረዳ ለሚገኙ 45,000 ሰዎች ምግብ ማቅረቡን የገለፀ ሲሆን የተመጣጠነ የምግብ ችግር ያለባቸውን 11,000 ሴቶች እና ህፃናትን መድረስ መቻሉን ገልጿል።
በትግራይ ክልል ያለው የሰብዓዊ ሁኔታን ምላሽ ለመስጠት በየዕለቱ ወደ ክልሉ 100 ሰብዓዊ ድጋፍ የጫኑ ተሽከርካሪዎች መግባት ያለባቸው መሆኑን ከዚህ ቀደም የዓለም ምግብ ፕሮግራም መግለፁ ይታወሳል።
ከወራቶች በፊት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆም ውሳኔ ከተላለፈ በኃላ በፊት ከነበረው የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት መሻሻሎች ቢታዩም አሁንም ካለው ፍላጎት ጋር ሲነፃፀር አነስተኛና የተቸገሩ ወገኖችን ሰብዓዊ ፍላጎት ለማሟላት ሰፊ ስራ እንደሚጠብቅ የሚገልፁ በርካቶች ናቸው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
' የትምህር ቤት ክፍያ ' የአዲስ አበባ የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን የ2015 የትምህርት ዘመንን የክፍያ ጭማሪ አስመልክቶ ከትምህርት ቤቶች ጋር ምክክር አድርጎ ነበር። በዚህም ፥ በ2014 ዓ/ም ጭማሪ ያደረጉ ትምህርት ቤቶች በ2015 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ምንም አይነት ጭማሪ ማድረግ እንደማይችሉ ተገልጿል። ነገር ግን ላለፉት 2 እና 3 አመታት ጭማሪ ሳያደርጉ የቆዩ ትምህርት ቤቶች…
#ክፍያ
የአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በቀጣይ የትምህርት ዘመን (2015 ዓ/ም) ክፍያ መጨመር የሚችሉት የግል ትምህርት ቤቶች መለየታቸውን እና ጭማሪውም ከወላጆች ጋር መክረው የሚያደርጉት መሆኑን አስታውቋል።
ጭማሪ ማድረግ የሚችሉ ት/ቤቶች በ2014 ዓ/ም ምንም አይነት የክፍያ ጭማሪ ያላደረጉ ናቸው።
የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ህይወት ጉግሳ ጉዳዩን ከተመለከተ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጡት ቃል፥ " ጭማሪ ማድረግ የሚችሉት በ2014 ምንም አይነት ጭማሪ ያላደረጉ ብቻ ናቸው። ጭማር ማድረግ ይችላሉ ሲባል ደግሞ ቀጥታ ይጨምራሉ ማለት ሳይሆን ከወላጆች ጋር መክረው / ከወላጅ ኮሚቴ ጋር መክረው ሲተማመኑ ነው " ብለዋል።
ወ/ሮ ህይወት ጭማሪ የሚደረገው ክፍያ ተፈፃሚ የሚሆነው ወላጆች እና የወልጅ ኮሚቴ ያመነበት ብቻ እንደሆነም አክለዋል።
ወላጆችና ትምህርት ቤቶች ባይስማሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጣልቃ ገብቶ ሁለቱን አካላት የማግባባት ስራ የሚሰራ ሲሆን መንግስት ያስቀመጠውን መመሪያ ሳይከተል ወላጆች ያልተስማሙበት ወርሃዊ ክፍያ እጨምራለሁ የሚል ትምህርት ቤት ካለ እውቅና ፍቃዱ ይሰረዛል ፤ ትምህርት ቤቱ ይታሸጋል ለዚህም የተዘጋጀ በቂ መመሪያ መኖሩን የአዲስ አበባ ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል።
በሌላ በኩል፤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአዲስ አበባ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከተማሪ ወላጆች ጋር ምክክር ለማድረግ ቀድመው ቀጠሮ የያዙ ሲሆን ሁሉም ወላጆች በት/ቤት ተገኝተው የተማሪዎች መመዝገቢያ እና የወርሃዊ ክፍያ ላይ በንቃት ተሳትፈው የጋራ ውሰኔ እንዲያሳልፉ የከተማው ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጥሪ ማቅረቡን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በቀጣይ የትምህርት ዘመን (2015 ዓ/ም) ክፍያ መጨመር የሚችሉት የግል ትምህርት ቤቶች መለየታቸውን እና ጭማሪውም ከወላጆች ጋር መክረው የሚያደርጉት መሆኑን አስታውቋል።
ጭማሪ ማድረግ የሚችሉ ት/ቤቶች በ2014 ዓ/ም ምንም አይነት የክፍያ ጭማሪ ያላደረጉ ናቸው።
የባለስልጣን መ/ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ህይወት ጉግሳ ጉዳዩን ከተመለከተ ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ በሰጡት ቃል፥ " ጭማሪ ማድረግ የሚችሉት በ2014 ምንም አይነት ጭማሪ ያላደረጉ ብቻ ናቸው። ጭማር ማድረግ ይችላሉ ሲባል ደግሞ ቀጥታ ይጨምራሉ ማለት ሳይሆን ከወላጆች ጋር መክረው / ከወላጅ ኮሚቴ ጋር መክረው ሲተማመኑ ነው " ብለዋል።
ወ/ሮ ህይወት ጭማሪ የሚደረገው ክፍያ ተፈፃሚ የሚሆነው ወላጆች እና የወልጅ ኮሚቴ ያመነበት ብቻ እንደሆነም አክለዋል።
ወላጆችና ትምህርት ቤቶች ባይስማሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጣልቃ ገብቶ ሁለቱን አካላት የማግባባት ስራ የሚሰራ ሲሆን መንግስት ያስቀመጠውን መመሪያ ሳይከተል ወላጆች ያልተስማሙበት ወርሃዊ ክፍያ እጨምራለሁ የሚል ትምህርት ቤት ካለ እውቅና ፍቃዱ ይሰረዛል ፤ ትምህርት ቤቱ ይታሸጋል ለዚህም የተዘጋጀ በቂ መመሪያ መኖሩን የአዲስ አበባ ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል።
በሌላ በኩል፤ ነገ እና ከነገ በስቲያ በአዲስ አበባ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከተማሪ ወላጆች ጋር ምክክር ለማድረግ ቀድመው ቀጠሮ የያዙ ሲሆን ሁሉም ወላጆች በት/ቤት ተገኝተው የተማሪዎች መመዝገቢያ እና የወርሃዊ ክፍያ ላይ በንቃት ተሳትፈው የጋራ ውሰኔ እንዲያሳልፉ የከተማው ትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ጥሪ ማቅረቡን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#MoE
ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት አምጥተው በየዩኒቨርሲቲው የተመደቡ ተማሪዎች ምደባውን እና የተለያዩ ጉዳዮችን ተከትሎ ያላቸውን ቅሬታ በኦንላይን ሲቀበል መቆየቱን ገልጾ ለቀረቡት ቅሬታዎች በሙሉ ተገቢውን ምላሽ ሰጥቶ መጨረሱን ዛሬ አሳውቋል።
ይህን ተከትሎ ወደ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች በሙሉ ዩኒቨርሲቲዎቹ በሚያደርጉት የጥሪ መርሃ-ግብር መሰረት በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ አስፈላጊውን መረጃ አሟልተው እንዲገኙ አሳስቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከሳምንታት በፊት የተማሪዎችን ምደባ ይፋ ማድረጉ ፤ ይህንን ተከትሎም ቅሬታ ያላቸው ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ ጥሪ ማቅርቡ ይታወሳል።
በሌላ በኩል እስካሁን የመግቢያ ቀን ያሳወቁ ዩኒቨርሲቲዎችን ዝርዝር በዚህ ማግኘት ይቻላል : https://t.iss.one/TikvahUniversity/3708
@tikvahethiopia
ትምህርት ሚኒስቴር ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ውጤት አምጥተው በየዩኒቨርሲቲው የተመደቡ ተማሪዎች ምደባውን እና የተለያዩ ጉዳዮችን ተከትሎ ያላቸውን ቅሬታ በኦንላይን ሲቀበል መቆየቱን ገልጾ ለቀረቡት ቅሬታዎች በሙሉ ተገቢውን ምላሽ ሰጥቶ መጨረሱን ዛሬ አሳውቋል።
ይህን ተከትሎ ወደ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ ተማሪዎች በሙሉ ዩኒቨርሲቲዎቹ በሚያደርጉት የጥሪ መርሃ-ግብር መሰረት በየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ አስፈላጊውን መረጃ አሟልተው እንዲገኙ አሳስቧል።
ትምህርት ሚኒስቴር ከሳምንታት በፊት የተማሪዎችን ምደባ ይፋ ማድረጉ ፤ ይህንን ተከትሎም ቅሬታ ያላቸው ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ ጥሪ ማቅርቡ ይታወሳል።
በሌላ በኩል እስካሁን የመግቢያ ቀን ያሳወቁ ዩኒቨርሲቲዎችን ዝርዝር በዚህ ማግኘት ይቻላል : https://t.iss.one/TikvahUniversity/3708
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የዋጋ ግሽበት📈 መቆሚያ ያልተገኘለት የዋጋ ግሽበት አሁንም ማሻቀቡን እንደቀጠለ ነው። የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ እንደሚያሳየው የመጋቢት ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ34.7 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡ የምግብ ዋጋ ግሽበት የመጋቢት ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ43.4…
የዋጋ ግሽበት📈
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የሚያዝያ ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 36.6 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
ምግብና ምግብ-ነክ ያልሆኑ የኢንዴክሱ ክፍሎች በሁለት ትልልቅ የሃይማኖት በዓላት ምክንያት በያዝነው ወር ወቅታዊ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡
የምግብ ዋጋ ግሽበት የሚያዝያ ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ42.9 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በያዝነው ወር በተደራራቢ የሃይማኖት በዓላት መከበር ምክንያት በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ መታየቱን ካፒታል ጋዜጣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት በየወሩ የሚያወጣው የዋጋ ግሽበት መረጃ የሚያዝያ ወር 2014 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር 36.6 ከመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
ምግብና ምግብ-ነክ ያልሆኑ የኢንዴክሱ ክፍሎች በሁለት ትልልቅ የሃይማኖት በዓላት ምክንያት በያዝነው ወር ወቅታዊ ጭማሪ አሳይተዋል፡፡
የምግብ ዋጋ ግሽበት የሚያዝያ ወር 2014 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር በ42.9 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በያዝነው ወር በተደራራቢ የሃይማኖት በዓላት መከበር ምክንያት በእህሎች የዋጋ ጭማሪ የታየ ሲሆን የአትክልት ዋጋም ላይ መጠነኛ ጭማሪ መታየቱን ካፒታል ጋዜጣ የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎትን ዋቢ አድርጎ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
#ESP2022
በአ/አ የአሜሪካ ኤምባሲ ለEducationUSA Scholars Program (ESP) 2022 ማመልከቻ ክፍት መደረጉን ዛሬ አሳውቋል።
ኤምባሲው ፤ ESP የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት በአካዳሚክ የላቁ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በአሜሪካ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች በማመልከት የሰለጠኑ እና በደንብ የተማሩ መሪዎችን ለማፍራት የሚረዳ የ4 ሳምንት የስልጠና ፕሮግራም መሆኑን አስታውሷል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃንና የማመልከቻ ቅፆችን በዚህ https://ow.ly/B6b750J0X7q ማግኘት ይቻላል።
ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም ስለ ፕሮግራሙ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፊታችን ማክሰኞ ግንቦት 2/2014 ዓ/ም የኦንላይን መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
በዚሁ ላይ ለመሳተፍ የሚከተለውን ሊንክ https://ow.ly/6e4w50J0X7s 👉Meeting ID 160 083 5437 መጠቀም እንደሚቻል በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በአ/አ የአሜሪካ ኤምባሲ ለEducationUSA Scholars Program (ESP) 2022 ማመልከቻ ክፍት መደረጉን ዛሬ አሳውቋል።
ኤምባሲው ፤ ESP የነገዋን ኢትዮጵያ ለመገንባት በአካዳሚክ የላቁ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በአሜሪካ ኮሌጆችና ዩኒቨርሲቲዎች በማመልከት የሰለጠኑ እና በደንብ የተማሩ መሪዎችን ለማፍራት የሚረዳ የ4 ሳምንት የስልጠና ፕሮግራም መሆኑን አስታውሷል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃንና የማመልከቻ ቅፆችን በዚህ https://ow.ly/B6b750J0X7q ማግኘት ይቻላል።
ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ተጨማሪ መረጃዎችን ለመስጠት እንዲሁም ስለ ፕሮግራሙ የሚነሱ ጥያቄዎችን ለመመለስ የፊታችን ማክሰኞ ግንቦት 2/2014 ዓ/ም የኦንላይን መርሃ ግብር ተዘጋጅቷል።
በዚሁ ላይ ለመሳተፍ የሚከተለውን ሊንክ https://ow.ly/6e4w50J0X7s 👉Meeting ID 160 083 5437 መጠቀም እንደሚቻል በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ አሳውቋል።
@tikvahethiopia