TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
61.5K photos
1.55K videos
215 files
4.26K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ትኩረት📣

የሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎና ከሚሴ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ፤ " የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ወደ ቅዱስ ላልይበላ ዓለም አቀፍ ቅርስ ሊመለከት ይገባል " ሲሉ ጥሪ አቀረቡ።

ብፁዕነታቸው ቅዱስ ላልይበላን በማስመልከት ዛሬ በተሰጠ መግለጫ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እና በነበረው ጦርነት የቅዱስ ላልይበላ ቅርስ የቱሪዝም እና የከተማው እንቅስቃሴ ከፍተኛ ጫና ውስጥ መውደቁን ገልጸዋል፤ በዚህም አገልጋዮች ለከፍተኛ ችግር መጋለጣቸውን አሳውቀዋል።

ቅዱስ ላልይበላ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሐብት እንደመሆኑ አቅም በፈቀደ ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ለድጋፍ እጁን እንዲዘረጋ ጥሪ አቅርበዋል።

ብፁዕነታቸው " ሁላችንም የድርሻችንን በመወጣት ቅርሳችን እንጠብቅ " ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ዜጎች ድጋፋቸውን በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፣ አቢሲኒያ እና ዳሽን ባንኮች በ 👉 0712 የባንክ የሒሳብ ቁጥር ማድረግ ይችላሉ።

ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0911061164 እና 0913912457 መደወል ይቻላል።

ምንጭ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት

@tikvahethiopia
የሲዳማ ክልል ወጣቶች ጥያቄ  💬

(የድምፅ ባለቤት ዶቼ ቨለ ሬድዮ ሲሆን - ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በሚሆን መልኩ በፅሁፍ የተዘጋጀ)

በሀዋሳ ከተማ ፤ የብልፅግና ፓርቲ ከሲዳማ ወጣቶች ጋር ለመምከር የውይይት መድረክ አዘጋጅቶ ነበር።

በዚህ መድረክ የተሳተፉ አብዛኞቹ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች ሲሆኑ ለበርካታ አመታት ያለ ስራ መቀመጣቸውን በመግለፅ ጠንካራ ጥያቄዎችን አንስተዋል።

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ፦

" አሁን ወጣቱን አደራጅተን እንደዚህ እያደረግን ነው ብላችሁ እያወራችሁ ነው። የትኛውን ነው ?

ለምሳሌ ፦ ኮንቴነር በየክፍለ ከተማው ፈትሹ ያለውን ነገር ታያላችሁ ፤ አመራሩ እጅ ነው ያለው ኮንቴነር። አደራጅ እና አስተባባሪ ተብሎ የተቀመጡ ሰዎች እነሱ እጅ ነው ያለው ኮንቴነር ለወጣቱ ይሰጥ ተብሎ የተሰራው ፤ የምን ብልፅግና ነው እናተ ምትመሩት ?

ይህንን ወጣት ፤ በቀን 3 ጊዜ መብላት ያልቻለን ህዝብ እየመራችሁ እንዴት ነው ? እናተ በV8 እና በተለያየ ላንድክሩዘር መኪኖች እየዘነጣችሁ የምትሄዱት ? በምን አግባብ ነው ? "

ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል ፦

" ... ብልፅግና ፓርቲ መነፅር ብቻ ነው የቀየራችሁት ። ሙሉ ኢህአዴግ የነበሩ ናቸው። እነዚህ ሰዎች ደግሞ ለውጡን ለመቀበል ዝግጁ አይደሉም። በሌብነት ፣ በዘረኝነት የተጠመዱ ሰዎች ናቸው።

ብልፅግና ፓርቲ ቢያንስ ወጣቱን የሚሰማ ከሆነ እኛ በትዕግሥት መንግስቱ አልተረጋጋም ፣ ጫና አለበት የውስጥም የውጭም ብለን በትዕግስት ጠብቀናል ሶስት ዓመት ሙሉ አሁን 4ኛ ዓመት ልንይዝ ነው ሁሌ በዚህ ይቀጥላል ? የኛም ዝምታ በዚህ ይቀጥላል ? እሱን ጊዜ የሚፈታው ነገር ነው። "

ከዚህ በተጨማሪ የውይይት ተሳታፊዎች ጥያቄያቸውን በሰላማዊ ሰልፍ ለመጠየቅ ቢጥሩም እንዳልቻሉ ፤ በክልላቸው ዴሞክራሲና ነፃነት የለም ሲሉ ምሬታቸውን ገልፀዋል።

እንዲሁም በክልሉ ፦

👉 ሰብአዊ መብቶች ይጥሳሉ፣
👉 የመልካም አስተዳደር ጉድለት አለ፤
👉 ሙስና ተንሰራፍቷል ፤
👉 ባለስልጣናት ለወጣቶች መገልገያ የተገነቡ ተቋማትን ለዘመዶቻቸዉና ለቤተሰቦቻቸዉ ሰጥተዋል፣
👉 ባለስልጣናት ዉሳኔዎችን የሚያሳልፉት ለእነሱና ለወዳጅ ዘመዶቻቸዉ በሚጠቅም መልኩ ነዉ ብለዋል።

በወጣቶች ለተነሱት ጥያቄዎች በመድረኩ ከተገኙት አንዱ የሲዳማ ብልፅና ፓርቲ ፅ/ቤት የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ አቶ ዘማች እርጥባ ተከታዩን ብለዋል ፦

" ቁጥር ብዙ ለሆነ ወጣት ስራ እድል ያልተፈጠረለት ሁኔታ አለ። እየተፈጠረም ያለው እራሱ የባለሃብት ቤተሰብ ፣ የአመራር ቤተሰብ የሚለው ትክክል ነው።

ምን እያደረጋችሁ ነው ያላችሁት ? ቢሚል ለነሳችሁት መጀመሪያ የሚሆነው ይህን ሲፈፅም የነበረው ሊመራ ኃላፊነት የተሰጠው አመራር በአግባቡ ያልመራውን እርምጃ ወስደናል አሁን።

በዚህ ዓመት አሁን እስካለንበት ከ80 በላይ በሆኑት ላይ እርምጃ ተወስዷል። ይሄ ብቻም አላቆመም ቀጥሎም በኃላፊዎች ላይ እርምጃ እየተወሰደ በከተማ ፓርቲ ደረጃ ፤ በመንግስት ደረጃ የሚኬድበት ሁኔታ ይቀጥላል "

የብልፅግና ወጣቶች ሊግ አመራር አንዱ ታረቀኝ ለገሰ ፦

" የምታነሷቸው ጥያቄዎች በሰፊው አሉ። ስራ አጥነት አለ። የ3 ዓመት ብቻ አይደለም ፤ የ7 ዓመት ስራ ያልተቀጠረ ወጣት ፤ ስራ ያላገኘ ወጣት ያለው እኛ ጋር በዝርዝር አለ። እያንዳንዱን ጥያቄ በዝርዝር ይዘናል ፤ እንደተባለው ቀጥታ ይሄ ለፌዴራል ብልፅግና ፓርቲ ግብአት ሆኖ የሚሄድ ነው። "

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
አሜሪካ ከወራት በፊት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አድርጋ የሾመቻቸው አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ በቅርቡ (ከሰኔ በፊት) ከስልጣናቸው ሊለቁ ነው።

ከስድስት ወር ላነሰ ጊዜ በልዩ መልዕክተኛነት ያገለገሉት ሳተርፊልድ ከስልጣናቸው ሲለቁ ምክትል ልዩ መልዕክተኛ ፔይቶን ኖፕፍ ቦታውን እንደሚረከቡ ለጉዳዩ ቅርበት ካላቸድ ምንጮች መስማቱን ሮይተርስ ዘግቧል።

በቅድሚያ የአምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ በቅርቡ ከኃላፊነታቸው ሊለቁ እንደሚችሉ መረጃውን ያወጣው ፎሬይን ፖሊሲ ሲሆን የእሳቸው ከኃላፊነት መልቀቅ፤ ከፍተኛ የፖለቲካ አለመራጋጋት፣ የጅምላ ጭፍጨፋዎች እና የረሃብ ስጋት ባለበት የአፍሪካ ቀንድ ትልቅ የዲፕሎማሲ ክፍተት የሚፈጥር እንደሆነ አስፍሯል።

በሌላ በኩል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤት አምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ እና ምክትላቸው ኖፕፍ ዛሬ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ አስታውቋል።

2ቱ የአሜሪካ ባለስልጣናት በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጠናት ፣ ከዲፕሎማቲ አጋሮች እና ከረድዔት ድርጅቶች ጋር ተገናኝተው ይመክራሉ ተብሏል።

የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በአምባሳደር ዴቪድ ሳተርፊልድ ከኃላፊነት መነሳት ላይ በይፋ የሰጠው አስተያየት አንደሌለ ሮይተርስ ፅፏል።

@tikvahethiopia
#ዋግኽምራ📍

ጦርነት ክፉኛ ከጎዳቸው የአማራ ክልል አካባቢዎች አንዱ የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ነው።

በእዚህ አካባቢ ያሉ ወገኖች ለከፋ ችግር ተጋልጠው ሜዳ ላይ መውደቃቸው እና አስፈላጊው ድጋፍ ሊደረግላቸው እንደሚገባ ጥሪ ሲቀርብ እንደነበር ይታወሳል።

ምንም እንኳን በቂ ባይሆንም የተለያዩ ድጋፎች ሲደረጉ ተስተውሏል።

ዛሬ ከዋግ ኽምራ ኮሚኒኬሽን በተገኘ መረጃ የወልዲያ ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ሳቢያ ከቤታቸው ተፈናቅለው በሰቆጣ መጠለያ ለሚገኙ የዋግ ተፈናቃዮች 1.3 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የስንዴ (300 ኩንታል) ድጋፍ አድርጓል።

ዩኒቨርሲቲው በችግር ላይ ለወደቁት ወገኖች አስፈላጊውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አሳውቋል።

በተጨማሪ በዞኑ የተለያዩ ምርምሮችን ተግባራዊ በማድረግ የህብረትሰቡን ችግር ለመፍታት የበኩሉን እንደሚወጣ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ምዝገባና ማረጋገጫ ኤጀንሲ በከተማዋ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጳጉሜን 5 ቀን 2014 ዓ.ም የካዳስተር ምዝገባ እና እወጃ ሥራ እንደሚካሄድ አሳውቋል።

ከዚህ ቀደም የመሬት ይዞታቸውን በካዳስተር ያላስመዘገቡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች መረጃዎቻቸውን ለሚቀጥሉት ተከታታይ 15 ቀናት ማዘጋጀት እንደሚችሉ ተነግሯል።

ከተማ አስተዳደሩ ከ10 ዓመት በፊት ጀምሮ ሕጋዊ የመሬት ይዞታ የማረጋገጥ (ካዳስተር) ሥራ እየሠራ ሲሆን በዚህ ዓመት በመዲናዋ የለሚኩራ ክ/ከተማን ሳይጨምር በ10 ክፍለ ከተሞች ውስጥ በሚገኙ 25 ቀጠናዎች ላይ የመሬት ይዞታን የማረጋገጥ እና የእወጃ ሥራ እንደሚሠራ ተገልጿል።

በዚሁ መሰረት ይዞታ የማረጋገጥ እና የእወጃ ሥራው ከዛሬ ጀምሮ እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2014 ዓ.ም ለ5 ወራት እንደሚሠራ ተመላክቷል፡፡

በዚህ ወቅት በሕግ ተይዘው ካሉ የመሬት ጉዳዮች እና የሕግ ክርክሮች ውጪ ምንም ዓይነት #የስም_ዝውውር_እንደማይካሄድ ነው የተገለጸው፡፡

ከተማ አስተዳደሩ ከ2008 ዓ. ም እስከ 2011 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት ከ118 ሺህ በላይ የመሬት ይዞታዎችን እና ከ161 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በካዳስተር መመዝገቡ ተጠቁሟል።

ኤጀንሲው የምዝገባ ሒደቱ ተዓማኒ እንዲሆን ከማህበረሰቡ የተውጣጡ ታዛቢዎች ተሳታፊ ይሆናሉ ማለቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ከተማ መገናኛ እና አንዋር መስጂድ አካባቢ ያሉት ስማርት የመኪና ማቆሚያዎች ጥገና ተደርጎላቸው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸው ተገልጿል።

መገናኛ ስማርት የመኪና ማቆሚያ ከአንድ ዓመት በላይ አገልግሎት ከሰጠ በኋላ ተቋርጦ የነበረ ሲሆን መንስኤው የኤሌክትሪካል ቴክኒክ ችግር ነው ተብሏል።

አንዋር መስጂድ አካባቢ ያለው ስማርት የመኪና ማቆሚያ የኤሌክትሪክ መስመሩ በመቆረጡ አገልግሎት ሳይሰጥ እንደቆየ ተገልጿል።

አሁኑ ላይ ሁለቱም ስማርት የመኪና ማቆሚያዎች ተጠግነው #ለአገልግሎት_ክፍት መሆናቸውን የከተማው ትራንስፖርት ቢሮ አሳውቋል።

መገናኛ ስማርት የመኪና ማቆሚያ 90 መኪኖችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚችል ባለ 15 ደረጃ ያለው ሲሆን፥ ከአጠገቡ 105 መኪናዎችን ማስተናገድ የሚችል የመሬት ላይ መኪና ማቆሚያ አለው፡፡

በተመሳሳይ በአንዋር መስጂድ አካባቢ ለ80 መኪናዎች አገልግሎት መስጠት ይችላል፤ በመሬት ላይ ደግሞ 110 መኪናዎችን የመያዝ አቅም አለው፡፡

#AddisAbaba_Transport_Bureau

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለ38 ዓመታት ያገለገሉት አቶ መስፍን ጣሰው የአየር መንገዱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነዋል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ መምሪያ፣ የጥገናና ኢንጂነሪንግ፣ እንዲሁም ኦፕሬሽን ዳይሬክተር በመሆን ያገለገሉት አቶ መስፍን ጣሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው ተሹመዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርድ ትላንት አዲሱን…
#EthiopianAirlines

በቅርቡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ሆነው የተሾሙት አቶ መስፍን ጣሰው አዲስ የማኔጅመንት ቡድን አዋቅረዋል፡፡

በተዋቀረው በአዲሱ ማኔጅመንት ቡድን ቀደም ሲል በተጠባባቂነት የሃላፊነት ቦታዎች ይዘው ሲያገለግሉ የነበሩ ሀላፊዎች ቦታው ፀድቆላቸዋል።

አንዳንድ ሀላፊዎች ደግሞ ከቦታቸው ተነስተው በሌሎች ባልደረቦቻቸው መተካታቸውን " ኢትዮ የንግድ እና ኢንቨስትመንት መድረክ " ዘግቧል።

(ዝርዝሩ ከላይ በምስሉ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#Gambella

በጋምቤላ ክልል መዠንገር ዞን ፤ ሜጢ ከተማ ከፍርድ ቤት ቀጠሮ ወደ ማረሚያ ቤት 22 እስረኞችን ሲመልስ የነበረ የፖሊስ ተሽከርካሪ ተገልብጦ ከባድ አደጋ መድረሱ ተሰምቷል።

በአደጋው የአንድ እስረኛ ህይወት አልፏል።

አጠቃላይ በተሽከርካሪው 22 እስረኞችና 4 የፖሊስ አባላት (26 ሰዎች) የአደጋው ሰለባ ሲሆኑ በአደጋው የሞት፣ ከባድ ፣እና ቀላል ጉዳት ተመዝግቧል።

የመዠንገር ዞን ፀጥታ መምሪያ ለሸገር ኤፍ ኤም በሰጠው ቃል ፤ መኪናው ከፊት ለፊት ባጃጅ ገብቶበት እሱን አድናለው ሲል መገልበጡን ገልጾ ጉዳት የደረሰባቸው እስረኞች እና የፖሊስ አባላት ቴፒ ሆስፒታል ተወስደዋል።

ከእስረኞች መካከል ያመለጠ እንደሌለ ያሳወቀው ፀጥታ መምሪያው አንድ ታራሚ ህይወቱ እንዳለፈ ሌሎቹ ግን በሆስፒታል ህክምና ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።

22ቱ ግለሰቦች በተለያየ ጥፋት ተጠርጥረው ማረሚያ የወረዱ መሆናቸውን የገለፀው የፀጥታ መምሪያው ከአዲስ አበባ የሚላክ " የስንዴ እርዳታ " ወደ ህዝብ ሳይደርስ መንገድ ላይ ሲሸጡ እና ለግል ጥቅም ሲያውሉ የነበሩ ሰዎች መኖራቸውን መጠቆሙን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA

የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ የሚሆን የ300 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አፅድቋል።

የዓለም ባንክ፥ በኢትዮጵያ በተከሰቱት ግጭቶች የሰው ህይወት መጥፋቱን ፣ ሰብአዊ ቀውሶች መከሰታቸውን፣ የግልና የመንግስት ንብረቶች መውደማቸውን እና ማህበረሰቦች ከፍተኛ ድጋፍ እንዲሹ ማድረጉን ገልጿል።

በተጨማሪ የተከሰቱ ግጭቶች በመላ ሀገሪቱ በሺዎች ለሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀል ምክንያት መሆናቸውን እና ጾታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን (GBV) የበለጠ እንዲባባስ ማድረጉን አመልክቷል።

እነዚህን ተግዳሮቶች ለመፍታት እና ኢትዮጵያን ለመርዳት የዓለም ባንክ በግጭት ለተጎዱ ማህበረሰቦች ምላሽና መልሶ መቋቋም ለሚውል ፕሮጀክት የ300 ሚሊዮን ዶላር ድጋፍ አጽድቋል።

ፕሮጀክቱ የህብረተሰቡን አፋጣኝ ፍላጎቶች ለመቅረፍ፣ በግጭት የወደሙ መሠረተ ልማቶችን መልሶ ለማቋቋም እና በግጭት ሳቢያ የመጡ ተፅእኖዎችን በዘላቂነት ለመቋቋም የሚደረገውን ጥረት ይደግፋል ብሏል።

ፕሮጀክቱ ምንም እንኳን ሀገራዊ መልክ ቢኖረውም ቅድሚያ የሚሰጠው በቅርቡ በተከሰተ ግጭት ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰባቸው እና ከፍተኛ የሆነ የውስጥ ተፈናቃዮች ለሚገኙባቸው የአፋር፣ አማራ፣ ትግራይ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ኦሮሚያ ክልሎች ነው።

ከአካባቢያዊ ሁኔታዎች ጋር የተጣጣመ ፈጣን እና ቀልጣፋ ድጋፍን ለማረጋገጥ ፕሮጀክቱ በፌዴራል፣ በክልልና በማህበረሰብ አቀፍ ድርጅቶች ይተገበራል ተብሏል።

ከፍተኛ የሆነ ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች ደግሞ በገለልተኛ 3ኛ ወገን አካላት ተግባራዊ ይሆናል።

https://www.worldbank.org/en/news/press-release/2022/04/12/world-bank-supports-ethiopia-s-conflict-affected-communities-targets-over-five-million-people

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሩስያ ፥ ስዊድንን እና ፊንላንድን አስጠነቀቀች። የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስዊድን እና ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል ከሞከሩ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ ኢኮኖሚያዊ እና ወታደራዊ ] እንደሚኖሩ አስጠንቅቋል። አሁን በዩክሬን እና ሩስያ መካከል ያለው ጦርነት ተባብሶ በቀጠለበት ሁኔታ ሩስያ ፊንላንድ እና ስዊድንን ማስፈራራቷ ሌላ ዓለም አቀፋዊ ስጋት ፈጥሯል። የኃያላን ሀገራቱ ግብግብ በተለይ…
#Russia #Finland #Sewden

ሩስያ NATOን ለመቀላቀል ከሞከራችሁ እጅግ " ጎጂ " የሆኑ ውጤቶች [ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ] ይኖራል ስትል ካስጠነቀቀቻቸው ስውዲን እና ፊንላንድ መካከል ስውዲን NATOን ለመቀላቀል ለማመልከት መወሰኗ ተሰምቷል።

የስዊዲን ጠ/ሚ ማግዳሌና አንደርሰን ሀገራቸው በሰኔ ወር መጨረሻ ላይ ለNATO ጥምረት አባልነት ለማመልከት መወሰኗን ገልፀዋል።

ፊንላንድ በበኩሏ ፤ አሁን ይኽ ነው የሚባል ውሳኔ ላይ ባትደርስም በሚቀጠሉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ NATOን ለመቀላቀል የማመልከት ውሳኔ ላይ እደርሳለሁ ብላለች።

የፊንላንድ ጠ/ሚ ሳንና ማሪን እና የስዊድን ጠ/ሚ ማግዳሌና አንደርሰን በአካባቢው የጸጥታ ጉዳዮች ላይ ዛሬ በስቶክሆልም ተገናኝተው ተወያይተዋል።

በሩስያ እና ዩክሬን መካከል ያለው ጦርነት አሁንም መፍትሄ የላገኘ ሲሆን ሩስያ ዩክሬን ላይ እርምጃ መውሰድ ከጀመረችባቸው ዋነኛ ምክንያቶች አንዱ NATOን ለመቀላቀል ሙከራ ማድረጓና ለደህንነቷ ስጋትን በመደቀኗ መሆኑ ይታወቃል።

የዩክሬን ጦርነት ከተቀሰቀሰ በኃላ ሩስያ ፤ ስውዲን እና ፊንላድ እንዲህ ያለውን ነገር እንዳይሞክሩት ፤ የሚያደርጉት ከሆነ ግን ወታደራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጎጂ ውጤቶች እንደሚኖሩ አስጠንቅቃቸው ነበር።

አሁን ላይ ስውዲን NATOን ለመቀላቀል ጥያቄ እንደምታቀርብ መወሰኗ ፤ ፊንላንድም በቀጣይ ሳምንታት ውሳኔ ላይ ደርሳለሁ ማለቷ ትልቅ ስጋትን ፈጥሯል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ከኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሽዴ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። ከአሜሪካ ኤምባሲ በኩል ይፋ በሆነ መረጃ ውይይቱ ፥ በአሜሪካ እና ኢትዮጵያ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነቶች ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ እንዲሁም በሀገራቱ መካከል ስላለው ወሳኝ ኢኮኖሚያዊ እና የንግድ ግንኙነት ላይ ትኩረት ያደረገ…
#US

በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈፃሚ ትሬሲ አን ጃኮብሰን ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነርና ምክትል ዋና ኮሚሽነር ጋር ተገናኝተው መወያየታቸው ይታወሳል።

በኃላም ከገንዘብ ሚኒስትር ጋር በኢትዮጵያ እና አሜሪካ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ዙሪያ መክረው ነበር።

ትላንት ከኢትዮጵያ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ ጋር በገለልተኛ የዳኝነት ስርዓት እንዲሁም የሰብአዊ መብት አያያዝ አስፈላጊነት ላይ ተወያይተዋል።

በዛሬው ዕለት ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ጋር ተገናኝተዋል።

ሰላም እና እርቅ እንዲፈጠር እንዲሁም ለተቸገሩ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እርዳታ እንዲደርስ ያላቸውን ተስፋ መጋራታቸውን ከአሜሪካ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ፅ/ቤት ባገኘነው መረጃ ደግሞ ፥ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የአሜሪካን ተጠባባቂ አምባሳደር ጃኮብሰንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው ማነጋገራቸውን ይገልፃል።

አምባሳደር ኣን ጃኮብሰን ፤ ከቅዱስነታቸው ቡራኬ ለመቀበል እና ይፋዊ የሥራ ትውውቅ ለማድረግ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የተገኙ መሆናቸውን መረጃው ይገልፃል።

ቅዱስነታቸው ከአምባሳደሯ ጋር በነበራቸው ቆይታ የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት በማስተላለፍ በኢትዮጵያ የሚቆዩበት ጊዜ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን የሚችሉበት ይሆን ዘንድ አባታዊ ተምኔታቸውን ገልጸው በቡራኬ ሸኝተዋቸዋል።

@tikvahethiopia