#ZHAddis
እጆላይ ያለው ካሜራ ጊዜ በሄደ ቁጥር የሚሰጠው ጥቅም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ዝቅ እንደሚል ያቃሉ ከማይፈለግ እቃጋ ሳይመደብ አሁኑኑ እኛ ዘንድ ይዘው ይምጡ እንዳይቆጩ አርገን በጥሩ ዋጋ እንገዞታለን።
ይደውሉልን : 0911156257 ከታች ያለውንlink በመጫን የቴሌግራም አባል ይሁኑ https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEUTeB3LSYVFukiuQw
ቦሌ ወሎሰፈር HMM ህንፃ 2ኛ ፍቅ205
እጆላይ ያለው ካሜራ ጊዜ በሄደ ቁጥር የሚሰጠው ጥቅም ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ዝቅ እንደሚል ያቃሉ ከማይፈለግ እቃጋ ሳይመደብ አሁኑኑ እኛ ዘንድ ይዘው ይምጡ እንዳይቆጩ አርገን በጥሩ ዋጋ እንገዞታለን።
ይደውሉልን : 0911156257 ከታች ያለውንlink በመጫን የቴሌግራም አባል ይሁኑ https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEUTeB3LSYVFukiuQw
ቦሌ ወሎሰፈር HMM ህንፃ 2ኛ ፍቅ205
#ማኪ_ፋሽን
👉 በተመጣጣኝ ዋጋ ይሸምቱ ይዘንጡ ብዙ አማራጮች ስላሉ ሱቃችንን ይጎብኙ ባሉበትም እናደርሳለን።
ስልክ ፦ 0991212121
👉የጫማ ዝርዝሮችን ከነዋጋቸዉ ለማየት ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.iss.one/makkifashionethiopia
እንዲሁም Facebook ፔጃችንን_ይከተሉ
https://www.facebook.com/makkifashionethiopia
📍አድራሻ ቦሌ መድሐኒያለም ሰላም ሲቲ ሞል ምድር ላይ
👉የስራ ሰአት ከሰኞ-እሁድ ከጠዋቱ 3:00- ምሽት 1:30
👉 በተመጣጣኝ ዋጋ ይሸምቱ ይዘንጡ ብዙ አማራጮች ስላሉ ሱቃችንን ይጎብኙ ባሉበትም እናደርሳለን።
ስልክ ፦ 0991212121
👉የጫማ ዝርዝሮችን ከነዋጋቸዉ ለማየት ቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ
https://t.iss.one/makkifashionethiopia
እንዲሁም Facebook ፔጃችንን_ይከተሉ
https://www.facebook.com/makkifashionethiopia
📍አድራሻ ቦሌ መድሐኒያለም ሰላም ሲቲ ሞል ምድር ላይ
👉የስራ ሰአት ከሰኞ-እሁድ ከጠዋቱ 3:00- ምሽት 1:30
#SpecialOlympics
የሚዲያና የኮምንኬሽን ባለሙያዎች ስፔሻል ኦሎምፒክስን እንዲያግዙ ጥሪ ቀርቧል።
የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በልዩ ልዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ተሳታፊ የሚያደርገው ስፔሻል ኦሎምፒክስን የሚድያ ባለሙያዎች እንዲያዙ ጥሪ የቀረበው ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አዳራሽ ለሚድያና ኮምንኬሽን ባለሙያዎች በተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ነው።
የስፔሻል ኦሎምፒክስ ኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ወ/ሮ ምህረት ንጉሴ እንደገለፁት በሀገራችን ከአእምሮ እድገት ውስንነት ጋር የሚኖሩ በርካታ ልጆች ቤት ውስጥ ተዘግቶባቸው እንዳይቀሩና ያላቸውን ልዩ ተሰጥኦ በአደባባይ እንዲያሳዩ ስፔሻል ኦሎምፒክስ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ስለሆነ የሚድያና የኮምንኬሽን ባለሙያዎች ለጉዳዩ ሰፊ የሚድያ ሽፋን በመስጠት አጋር እንዲሆኑ ጠይቀዋል።
በቀዳማዊት እመቤት ክብርት ዝናሽ ታያቸውና አጋር አካላት አነሳሽነት በቅርቡ የተመሰረተው ስፔሻል ኦሎምፒክስ ኢትዮጵያ ፤ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች ኢትዮጵያን በመወከል በዱባይና ግብፅ በተደረጉ የአትሌቲክስ ውድድሮች የወርቅና የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ እንዲሆኑ አስችሏል ።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ማናዬ እውነቱ
@tikvahethiopia
የሚዲያና የኮምንኬሽን ባለሙያዎች ስፔሻል ኦሎምፒክስን እንዲያግዙ ጥሪ ቀርቧል።
የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በልዩ ልዩ ስፖርታዊ ውድድሮች ተሳታፊ የሚያደርገው ስፔሻል ኦሎምፒክስን የሚድያ ባለሙያዎች እንዲያዙ ጥሪ የቀረበው ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደሬሽን አዳራሽ ለሚድያና ኮምንኬሽን ባለሙያዎች በተዘጋጀው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ላይ ነው።
የስፔሻል ኦሎምፒክስ ኢትዮጵያ ፕሬዚደንት ወ/ሮ ምህረት ንጉሴ እንደገለፁት በሀገራችን ከአእምሮ እድገት ውስንነት ጋር የሚኖሩ በርካታ ልጆች ቤት ውስጥ ተዘግቶባቸው እንዳይቀሩና ያላቸውን ልዩ ተሰጥኦ በአደባባይ እንዲያሳዩ ስፔሻል ኦሎምፒክስ ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ስለሆነ የሚድያና የኮምንኬሽን ባለሙያዎች ለጉዳዩ ሰፊ የሚድያ ሽፋን በመስጠት አጋር እንዲሆኑ ጠይቀዋል።
በቀዳማዊት እመቤት ክብርት ዝናሽ ታያቸውና አጋር አካላት አነሳሽነት በቅርቡ የተመሰረተው ስፔሻል ኦሎምፒክስ ኢትዮጵያ ፤ የአእምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ልጆች ኢትዮጵያን በመወከል በዱባይና ግብፅ በተደረጉ የአትሌቲክስ ውድድሮች የወርቅና የነሀስ ሜዳሊያ ተሸላሚ እንዲሆኑ አስችሏል ።
ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ማናዬ እውነቱ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ውሳኔ አሳለፈ። መንግስት ባወጣው መግለጫ ፤ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሰብዓዊ እርዳታን ፍለጋ ወደአጎራባች ክልሎች እየተጓዙ መሆኑን አመልክቷል። እነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታው ከቀያቸው ሳፈናቀሉ ባሉበት እንዲርሳቸው ቢደረግ እንግልታቸውን እንደሚቀንስ በጽኑ እንደሚያምን አሳውቋል። በመሆኑም በከፍተኛ…
" የባንክ፣ የመብራት እና የቴሌኮሚኒኬሽን አገልግሎቶች ወደነበሩበት ይመለሱ " - አቶኒዮ ጉተሬዝ
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም መወሰኑን እንደሚያደንቁ ገልፀዋል ፤ የትግራይ ባለስልጣናትም ግጭት ለማቆም ያሳዩትን ቁርጠኝነትን አድንቀዋል።
ጉተሬዝ ፤ በኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአፋር፣ በአማራ፣ በትግራይ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በኦሮሚያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ላይ አስከፊ ስቃይ አስከትሏል ብለዋል።
አሁን የታዩት አዎንታዊ ለውጦች በፍጥነት ወደ መሬት ወርደው መተርጎም አለባቸው ሲሉም ገልፀዋል።
ዋና ጸሃፊው ፤ በትግራይ ህዝባዊ አገልግሎት ማለትም የባንክ፣ የመብራት እና የቴሌኮሚኒኬሽን ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።
ሁሉም አካላት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አካባቢዎች በሙሉ ሰብአዊ እርዳታዎች ያለመስተጓጎል እንዲገባ እንዲያመቻቹ አሳስበዋል።
ጉረቴዝ ፤ ሁሉም ወገኖች አሁን በሰብዓዊነት ላይ የተመሠረት ግጭት የማቆም ውሳኔያቸውን ወደ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ማሸጋገር አለባቸው ብለዋል።
@tikvahethiopia
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም መወሰኑን እንደሚያደንቁ ገልፀዋል ፤ የትግራይ ባለስልጣናትም ግጭት ለማቆም ያሳዩትን ቁርጠኝነትን አድንቀዋል።
ጉተሬዝ ፤ በኢትዮጵያ ያለው ግጭት በአፋር፣ በአማራ፣ በትግራይ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና በኦሮሚያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች ላይ አስከፊ ስቃይ አስከትሏል ብለዋል።
አሁን የታዩት አዎንታዊ ለውጦች በፍጥነት ወደ መሬት ወርደው መተርጎም አለባቸው ሲሉም ገልፀዋል።
ዋና ጸሃፊው ፤ በትግራይ ህዝባዊ አገልግሎት ማለትም የባንክ፣ የመብራት እና የቴሌኮሚኒኬሽን ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ በድጋሚ ጥሪ አቅርበዋል።
ሁሉም አካላት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አካባቢዎች በሙሉ ሰብአዊ እርዳታዎች ያለመስተጓጎል እንዲገባ እንዲያመቻቹ አሳስበዋል።
ጉረቴዝ ፤ ሁሉም ወገኖች አሁን በሰብዓዊነት ላይ የተመሠረት ግጭት የማቆም ውሳኔያቸውን ወደ ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ማሸጋገር አለባቸው ብለዋል።
@tikvahethiopia
#Tigray #Amhara #Afar #Oromia
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በትግራይ ፣ በአማራ ፣ በአፋር እና በኦሮሚያ ክልሎች በጸጥታ ችግር እና በጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚቀርብ ሰብአዊ ድጋፍ እና የመልሶ ማቋቋም የሚውል 134,884,285 ብር መርሃግብር አስጀምራለች።
ይኸው መርሃግብር ለ227,255 ዜጎች ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችን በአፋጣኝ ለማድረስ የሚውል ሲሆን ከእነዚህም መካከል 9,690 ህፃናት 36,199 ተፈናቃዮች እና ተቀባይ ማህበረሰብ ይገኙበታል።
ፕሮጀክቱ የሚከናወነው በቤተክርስቲያኗ የልማት ኮሚሽን 4 ሀገረስብከቶች አማካኝነት በተጠቀሱት 4 ክልሎች ውስጥ በሚገኙ 7 ዞኖች እና 11 ወረዳዎች ነው።
ገንዘቡን ለማሰባሰብ ድጋፍ ያደረጉት የካሪታስ ዓለም አቀፍ አባል ድርጅቶች እና ሌሎች የቤተክርስቲያን አጋር ድርጅቶች መሆናቸው ተገልፆልናል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በትግራይ ፣ በአማራ ፣ በአፋር እና በኦሮሚያ ክልሎች በጸጥታ ችግር እና በጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው ሰዎች የሚቀርብ ሰብአዊ ድጋፍ እና የመልሶ ማቋቋም የሚውል 134,884,285 ብር መርሃግብር አስጀምራለች።
ይኸው መርሃግብር ለ227,255 ዜጎች ምግብ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎችን በአፋጣኝ ለማድረስ የሚውል ሲሆን ከእነዚህም መካከል 9,690 ህፃናት 36,199 ተፈናቃዮች እና ተቀባይ ማህበረሰብ ይገኙበታል።
ፕሮጀክቱ የሚከናወነው በቤተክርስቲያኗ የልማት ኮሚሽን 4 ሀገረስብከቶች አማካኝነት በተጠቀሱት 4 ክልሎች ውስጥ በሚገኙ 7 ዞኖች እና 11 ወረዳዎች ነው።
ገንዘቡን ለማሰባሰብ ድጋፍ ያደረጉት የካሪታስ ዓለም አቀፍ አባል ድርጅቶች እና ሌሎች የቤተክርስቲያን አጋር ድርጅቶች መሆናቸው ተገልፆልናል።
@tikvahethiopia
#USA
የአሜሪካ ም/ቤት አባሉ ከአንድ አፍሪካዊ ባለሀብት ገንዘብ መቀበላቸው ተረጋገጠ።
ከአንድ አፍሪካዊ ቢሊየነር የገንዘብ ድጋፍ ስለማግኘታቸው ዋሽተዋል የተባሉ የአሜሪካ ም/ቤት አባል ከእንደራሴነታቸው ሊባረሩ እንደሚችሉ ተነገረ።
ጄፍ ፎርተንቤሪ የተባሉት የኔብራስከካ ግዛት የሪፐብሊካን ፓርቲ ተወካይ፣ ከስኬታማው ናይጄሪያዊ የንግድ ሰው ጊልበርት ቻጉሪ ሕገወጥ የገንዘብ ድጋፍ ስለመቀበላቸው ለFBI መዋሸታቸውን የፌደራል ዳኞች እንደደረሱበት ቢቢሲ ፅፏል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በ3 ጥፋቶች አስከ 15 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ለፈረድባቸው ይችላል ተብሏል።
ይህ ጉዳይ የውጭ ተጽእኖ ፈጣሪዎች በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ሊያሳድሩ የሚችሉትን ጫና በተመለከተ ከዚህ በፊት የነበረውን ክርክር መልሶ ቀስቅሶታል።
ምንም እንኳን የውጭ ዜጎች ለፖለቲካ ጉዳዮች የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ባይፈቀድላቸውም የ75 ዓመቱ ናይጄሪያዊ ቢሊየነር በርካታ የገንዘብ ስጦታዎችን ማበርከታቸው ይነገራል።
ግለሰቡ እኤአ በ2016 ላይ አሁን ጥፋተኛ ሆነው ለተገኙት የምክር ቤት አባል ጄፍ ፎርተንቤሪ በበሌሎች ለጋሾች በኩል በሕገወጥ መንገድ የ30,000 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ሰጥተዋል ተብሏል።
እንደራሴው 30,000 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያገኙ የሚገልጽ የተቀረጸ የስልክ ውይይት የተገኘ ቢሆንም፣ ለFBI መርማሪዎች ግን ስለገንዘቡ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ክደዋል።
ሐሙስ በሎስ አንጀለስ ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኞች ፣ ጄፍ ፎርተንቤሪን ሐሰተኛ ቃል በመስጠትና እውነትን ከፌደራል መርማሪዎች በመደበቅ ጥፋተኛ ብለዋቸዋል።
የምክር ቤት አባሉ ላይ የቅጣት ውሳኔ የሚሰጠው ከወራት በኋላ ሰኔ ላይ ሲሆን፣ አስከዚው ድረስ ግን እንደራሴው በውሳኔው ላይ ይግባኝ እንደሚጠይቁ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የአሜሪካ ም/ቤት አባሉ ከአንድ አፍሪካዊ ባለሀብት ገንዘብ መቀበላቸው ተረጋገጠ።
ከአንድ አፍሪካዊ ቢሊየነር የገንዘብ ድጋፍ ስለማግኘታቸው ዋሽተዋል የተባሉ የአሜሪካ ም/ቤት አባል ከእንደራሴነታቸው ሊባረሩ እንደሚችሉ ተነገረ።
ጄፍ ፎርተንቤሪ የተባሉት የኔብራስከካ ግዛት የሪፐብሊካን ፓርቲ ተወካይ፣ ከስኬታማው ናይጄሪያዊ የንግድ ሰው ጊልበርት ቻጉሪ ሕገወጥ የገንዘብ ድጋፍ ስለመቀበላቸው ለFBI መዋሸታቸውን የፌደራል ዳኞች እንደደረሱበት ቢቢሲ ፅፏል።
ከዚህ ጋር ተያይዞ በ3 ጥፋቶች አስከ 15 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት ለፈረድባቸው ይችላል ተብሏል።
ይህ ጉዳይ የውጭ ተጽእኖ ፈጣሪዎች በአሜሪካ ፖለቲካ ውስጥ ሊያሳድሩ የሚችሉትን ጫና በተመለከተ ከዚህ በፊት የነበረውን ክርክር መልሶ ቀስቅሶታል።
ምንም እንኳን የውጭ ዜጎች ለፖለቲካ ጉዳዮች የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ባይፈቀድላቸውም የ75 ዓመቱ ናይጄሪያዊ ቢሊየነር በርካታ የገንዘብ ስጦታዎችን ማበርከታቸው ይነገራል።
ግለሰቡ እኤአ በ2016 ላይ አሁን ጥፋተኛ ሆነው ለተገኙት የምክር ቤት አባል ጄፍ ፎርተንቤሪ በበሌሎች ለጋሾች በኩል በሕገወጥ መንገድ የ30,000 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ሰጥተዋል ተብሏል።
እንደራሴው 30,000 ዶላር የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያገኙ የሚገልጽ የተቀረጸ የስልክ ውይይት የተገኘ ቢሆንም፣ ለFBI መርማሪዎች ግን ስለገንዘቡ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ክደዋል።
ሐሙስ በሎስ አንጀለስ ጉዳዩን የተመለከቱት ዳኞች ፣ ጄፍ ፎርተንቤሪን ሐሰተኛ ቃል በመስጠትና እውነትን ከፌደራል መርማሪዎች በመደበቅ ጥፋተኛ ብለዋቸዋል።
የምክር ቤት አባሉ ላይ የቅጣት ውሳኔ የሚሰጠው ከወራት በኋላ ሰኔ ላይ ሲሆን፣ አስከዚው ድረስ ግን እንደራሴው በውሳኔው ላይ ይግባኝ እንደሚጠይቁ መናገራቸውን ቢቢሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NEBE ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 26 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ማሳሰቡ ይታወሳል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ዛሬ ማብራሪያ ሰጥቷል። በዚህም እስካሁን ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዱ ፓርቲዎች ብልጽግና ፣ ህዳሴ ፣ ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ ፣ ጋህነን መሆናቸውን አመልክቷል። እንደ ምርጫ ቦርድ ማብራሪያ ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ በጊዜ ገደቡ መሰረት ቀን ያሳወቁ 3 ፓርቲዎች አሉ። ቦርድ 12 ፓርቲዎች…
#OFC
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።
የፓርቲው ጉባኤ ዛሬ እና ነገ የሚካሄድ ሲሆን በተለያዩ የፓርቲው ውስጣዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
በዛሬው የፓርቲው ጉባኤ መክፈቻ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ አቶ ጀዋር መሀመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች እና አባላቶች ተገኝተዋል።
የጉባኤውን ሂደት ተከታትለን የምናሳውቅ ይሆናል።
ፎቶ ፦ ኡቡንቲ ሚዲያ እና Tikvah Family
@tikvahethiopia
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) ሁለተኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀመረ።
የፓርቲው ጉባኤ ዛሬ እና ነገ የሚካሄድ ሲሆን በተለያዩ የፓርቲው ውስጣዊ እና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።
በዛሬው የፓርቲው ጉባኤ መክፈቻ ላይ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና፣ አቶ ጀዋር መሀመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች እና አባላቶች ተገኝተዋል።
የጉባኤውን ሂደት ተከታትለን የምናሳውቅ ይሆናል።
ፎቶ ፦ ኡቡንቲ ሚዲያ እና Tikvah Family
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BREAKING የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት ለማቆም ውሳኔ አሳለፈ። መንግስት ባወጣው መግለጫ ፤ በአሁኑ ወቅት በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ክልል ነዋሪዎች የሰብዓዊ እርዳታን ፍለጋ ወደአጎራባች ክልሎች እየተጓዙ መሆኑን አመልክቷል። እነዚህ ዜጎች የሰብዓዊ እርዳታው ከቀያቸው ሳፈናቀሉ ባሉበት እንዲርሳቸው ቢደረግ እንግልታቸውን እንደሚቀንስ በጽኑ እንደሚያምን አሳውቋል። በመሆኑም በከፍተኛ…
#Tigray
የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆመ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።
ከመንግስት ውሳኔ በኃላም ከትግራይ ክልል በኩል በጎ ምላሽ መኖሩ ለበርካታ ወራት አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች እና ከክልሉ ውጭ ላሉ ቤተሰቦች በጎ ተስፋን ያጫረ እንደሆነ ይታመናል።
ነገር ግን ከዚህ በፊት የመከላከያ ኃይል ባለበት ፀንቶ ይቆያል ከሚለው ውሳኔ በምን ይለያል የሚል ጥያቄ የሚነሳ ሲሆን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ከቀናት በፊት ለቪኦኤ በሰጡት ቃል፦
"የመጀመሪያው ወደ ትግራይ አካባቢ አልገባም አለ እንጂ የተለያዩ ትንኮሳዎች ካሉ አፀፋ አልመልስም አላለም።
የተለያዩ አካባቢዎች ላይ አደጋዎች ሊኖሩ ይችላሉ ብሎ በሰጋ በየትኛውም ጊዜ እርምጃ ከመውሰድ የሚያግድ ነገር አልነበረም።
የአሁኑ ግን ለበረራዎች ደህንነት ሲባል፣ የህወሓት ሚሊሻም በተለያየ መልክ ስጋት ውስጥ ገብቶ መንገዱን እንዳይዘጋው የትኛውም አይነት ግጭት ከማድረግ እቆጠባለሁ ነው ያለው" ሲሉ አስረድተዋል።
ከውሳኔው በኃላ እርዳታ አቅርቦት እንዲሻሻል የሚደረግ ጥረት በተመለከተ ዶ/ር ለገሰ፥
"...በሳምንት እስከ3 ጊዜ ይካሄድ የነበረ በረራ አሁን መጠኑን የመጨመር አንዱ ነው።
ሌላው ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የገንዘብ ፍሰት ጋር የተያያዘ የታገዱ ነበሩ እነሱ በተወሰነ ደረጃ የመጨመር እንቅስቃሴ ነው። ገደቦች ነበሩ ገደቦቹን የማሻሻል ስራ ይሰራል" ብለዋል።
ሌላው፥ መንግስት ለሰብዓዊ እርዳታው መቀላጠፍ የህወሓት ኃይሎች በጉልበት ከያዛቸው አካባቢዎች ለቀው እንደሚወጡና ዋናውን የ " አብዓላ ኮሪደር " መስመርን እንዲከፍቱ ጠይቋል፤ ከያዙት ቦታ ባይለቁ ለሚለው ጥያቄ ዶ/ር ለገሰ " እሱን በሂደት ብናየው ይሻላል ከአሁኑ መገመት ተገቢ አይሆንም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግስት ለሰብዓዊነት ሲባል ግጭት የማቆመ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።
ከመንግስት ውሳኔ በኃላም ከትግራይ ክልል በኩል በጎ ምላሽ መኖሩ ለበርካታ ወራት አስከፊ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች እና ከክልሉ ውጭ ላሉ ቤተሰቦች በጎ ተስፋን ያጫረ እንደሆነ ይታመናል።
ነገር ግን ከዚህ በፊት የመከላከያ ኃይል ባለበት ፀንቶ ይቆያል ከሚለው ውሳኔ በምን ይለያል የሚል ጥያቄ የሚነሳ ሲሆን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሚኒስትር ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ከቀናት በፊት ለቪኦኤ በሰጡት ቃል፦
"የመጀመሪያው ወደ ትግራይ አካባቢ አልገባም አለ እንጂ የተለያዩ ትንኮሳዎች ካሉ አፀፋ አልመልስም አላለም።
የተለያዩ አካባቢዎች ላይ አደጋዎች ሊኖሩ ይችላሉ ብሎ በሰጋ በየትኛውም ጊዜ እርምጃ ከመውሰድ የሚያግድ ነገር አልነበረም።
የአሁኑ ግን ለበረራዎች ደህንነት ሲባል፣ የህወሓት ሚሊሻም በተለያየ መልክ ስጋት ውስጥ ገብቶ መንገዱን እንዳይዘጋው የትኛውም አይነት ግጭት ከማድረግ እቆጠባለሁ ነው ያለው" ሲሉ አስረድተዋል።
ከውሳኔው በኃላ እርዳታ አቅርቦት እንዲሻሻል የሚደረግ ጥረት በተመለከተ ዶ/ር ለገሰ፥
"...በሳምንት እስከ3 ጊዜ ይካሄድ የነበረ በረራ አሁን መጠኑን የመጨመር አንዱ ነው።
ሌላው ከእርዳታ ሰጪ ድርጅቶች የገንዘብ ፍሰት ጋር የተያያዘ የታገዱ ነበሩ እነሱ በተወሰነ ደረጃ የመጨመር እንቅስቃሴ ነው። ገደቦች ነበሩ ገደቦቹን የማሻሻል ስራ ይሰራል" ብለዋል።
ሌላው፥ መንግስት ለሰብዓዊ እርዳታው መቀላጠፍ የህወሓት ኃይሎች በጉልበት ከያዛቸው አካባቢዎች ለቀው እንደሚወጡና ዋናውን የ " አብዓላ ኮሪደር " መስመርን እንዲከፍቱ ጠይቋል፤ ከያዙት ቦታ ባይለቁ ለሚለው ጥያቄ ዶ/ር ለገሰ " እሱን በሂደት ብናየው ይሻላል ከአሁኑ መገመት ተገቢ አይሆንም " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
@tikvahethiopia
🌧 ቦረና 🌧
ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ አስከፊ ድርቅ ውስጥ የነበሩ አካባቢዎች ዝናብ ጥሏል።
ይህም ነዋሪዎች ላይ ደስታን ፈጥሯል።
ከሰሞኑን በእነዚህ አከባቢዎች ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ፈጣሪያቸውን በማመስገን ከብቶቻቸው የዝናብ ዉሃ ሲጠጡ የሚያሳይ ፎቶ እና ቪዲዮ በማሕበራዊ ሚዲያ እያጋሩ ይገኛሉ።
ቃላቸውን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ክፍል የሰጡት የቦረና ዞን ኤልዋዬ ወረዳ ነዋሪው አባ ሾባ ሞሉ ዝናብ በማግኘታቸው እጅግ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዝናብ ከረቡዕ ማታ ጀምሮ አንደዘነበ የተናገሩት አባ ሾባ ሁሉም ቦታ ተመሳሳይ እንዳልሆነ ጠቁመዋል። ለኤልዋዬ እና ያቤሎ ግን በጣም መልካም የሚባል ቀን እንደነበር ገልፀዋል።
የቦረና ማህበረሰብ ዝናብ በማጣት በድርቅ እንዳይቸገር አንደሚፈራው ሁሉ ከድርቅ በኃላ ዝናብ ሲገኝም የሚመጣውን ጎርፍ ትኩረት ሰጥቶ ይከታተላል። ለምን ? ከተባለ ከባዱ ዝናብ በድርቅ የተጎዱ ከብቶች ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፤ ሊገላቸው ይችላል በሚል ነው።
ለዚህም ነው " ፎሮሪ ሮቢ ዋቅ / 'forori roobi waaq' " የሚለው፣ ይህ ማለት " ያልበዛ ፣ያላነሰ አድርገህ አዝንብልን " እንደ ማለት ነው።
አባ ሾባም ያሉት ይህንኑ ነው ፤ " ይህ ዝናብ ከባድ ሆኖ ዘንቦ ከብቶችን አልጎዳም። ቀስ እያለ ነበር የዘነበው። አሁንም እየዘነበ ነው ። ጥሩ ደመናም ውጥቷል "
ነገር ግን ከአንድ ወር በፊት አንድ ቀን ብቻ የጣለው ዝናብ ከብቶች ላይ ከባድ ጉዳት አድርሶ ነበር ። በጎርፉ ወደ 13,000 ከብቶች አንዳለቁ ተገልጿል። በሰው ህይወት ላይም ጉዳት አድርሶ ነበር።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BORANA-03-26
@tikvahethiopia
ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ አስከፊ ድርቅ ውስጥ የነበሩ አካባቢዎች ዝናብ ጥሏል።
ይህም ነዋሪዎች ላይ ደስታን ፈጥሯል።
ከሰሞኑን በእነዚህ አከባቢዎች ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ፈጣሪያቸውን በማመስገን ከብቶቻቸው የዝናብ ዉሃ ሲጠጡ የሚያሳይ ፎቶ እና ቪዲዮ በማሕበራዊ ሚዲያ እያጋሩ ይገኛሉ።
ቃላቸውን ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ ክፍል የሰጡት የቦረና ዞን ኤልዋዬ ወረዳ ነዋሪው አባ ሾባ ሞሉ ዝናብ በማግኘታቸው እጅግ መደሰታቸውን ተናግረዋል።
ዝናብ ከረቡዕ ማታ ጀምሮ አንደዘነበ የተናገሩት አባ ሾባ ሁሉም ቦታ ተመሳሳይ እንዳልሆነ ጠቁመዋል። ለኤልዋዬ እና ያቤሎ ግን በጣም መልካም የሚባል ቀን እንደነበር ገልፀዋል።
የቦረና ማህበረሰብ ዝናብ በማጣት በድርቅ እንዳይቸገር አንደሚፈራው ሁሉ ከድርቅ በኃላ ዝናብ ሲገኝም የሚመጣውን ጎርፍ ትኩረት ሰጥቶ ይከታተላል። ለምን ? ከተባለ ከባዱ ዝናብ በድርቅ የተጎዱ ከብቶች ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላል፤ ሊገላቸው ይችላል በሚል ነው።
ለዚህም ነው " ፎሮሪ ሮቢ ዋቅ / 'forori roobi waaq' " የሚለው፣ ይህ ማለት " ያልበዛ ፣ያላነሰ አድርገህ አዝንብልን " እንደ ማለት ነው።
አባ ሾባም ያሉት ይህንኑ ነው ፤ " ይህ ዝናብ ከባድ ሆኖ ዘንቦ ከብቶችን አልጎዳም። ቀስ እያለ ነበር የዘነበው። አሁንም እየዘነበ ነው ። ጥሩ ደመናም ውጥቷል "
ነገር ግን ከአንድ ወር በፊት አንድ ቀን ብቻ የጣለው ዝናብ ከብቶች ላይ ከባድ ጉዳት አድርሶ ነበር ። በጎርፉ ወደ 13,000 ከብቶች አንዳለቁ ተገልጿል። በሰው ህይወት ላይም ጉዳት አድርሶ ነበር።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BORANA-03-26
@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
የብራዚል መንግስት በ" ኮቪድ - 19 ወረርሽኝ " ወቅት በከፍተኛ ሙያዊ ብቃት ብራዚልን አግዘዋል ላላቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ አመራሮች በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት የሚሰጠውን ከፍተኛ የሪዮ ብራንኮ ሜዳይ አበረክቷል።
የአየር መንገዱ የቀድሞ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ከፍተኛውን የክብር ማእረግ ሲበረከትላቸው በብራዚል እና በደቡብ አሜሪካ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ግሩም አበበን ጨምሮ ሁለት የአየር መንገዱ የስራ ሀላፊዎች ደግሞ ሜዳዮ ተበርክቶላቸዋል።
የክብር እና የእውቅና ስነ-ስርዓቱ አዲስ አበባ በሚገኘው በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ሊዊ ኤድዋርዶ መኖሪያ የተካሄደ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ዋቄ እና የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና መፍቲን ጨምሮ በርካታ የክብር እንግዶች ተገኝተው ነበር።
ምንጭ፦ ዋፋ ማርኬቲንግ
@tikvahethmagazine
የብራዚል መንግስት በ" ኮቪድ - 19 ወረርሽኝ " ወቅት በከፍተኛ ሙያዊ ብቃት ብራዚልን አግዘዋል ላላቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ አመራሮች በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት የሚሰጠውን ከፍተኛ የሪዮ ብራንኮ ሜዳይ አበረክቷል።
የአየር መንገዱ የቀድሞ ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ከፍተኛውን የክብር ማእረግ ሲበረከትላቸው በብራዚል እና በደቡብ አሜሪካ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኦፕሬሽን ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ግሩም አበበን ጨምሮ ሁለት የአየር መንገዱ የስራ ሀላፊዎች ደግሞ ሜዳዮ ተበርክቶላቸዋል።
የክብር እና የእውቅና ስነ-ስርዓቱ አዲስ አበባ በሚገኘው በኢትዮጵያ የብራዚል አምባሳደር ሊዊ ኤድዋርዶ መኖሪያ የተካሄደ ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ አቶ ግርማ ዋቄ እና የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና መፍቲን ጨምሮ በርካታ የክብር እንግዶች ተገኝተው ነበር።
ምንጭ፦ ዋፋ ማርኬቲንግ
@tikvahethmagazine