ሐጂ ሀሰን ገመዳ አረፉ።
ታላቁ ዓሊም ሐጂ ሀሰን ገመዳ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ታላቁ ዓሊም ሐጂ ሀሰን ገመዳ እድሜያቸውን በዳዕዋ እና ኢልም በማስቀራት ያሳለፉ ሲሆን ለየትኛውም የሀገራችን መንግስት ሳይንበረከኩ በፅናት የዳዕዋ አገልግሎታቸውን ያስቀጠሉና ፍሬ ማፍራት የቻሉ ነበሩ።
ከአፄ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት እስከ ኢህአዴግ ድረስ ለአምስት ያህል ጊዜ ታስረዋል።
ታለቁ ዓሊም ሐጂ ሀሰን ገመዳ ባደረባቸው ህመም የህክምና ክትትል ሲያደረጉ ቆይተው ትላንት ለሊት አርፈዋል። የሐጂ ሀሰን እድሜ ከ120 - 130 ባለው መከከል እንደሆነ ይነገራል።
በቅርቡ " ሂጅራ ባንክ " በሻሸመኔ ከተማ የከፈተውን ቅርጫፍ በስማቸው እንዲሆን አድርጎ ነበር።
ትላንት ለሊት ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት ሐጂ ሀሰን ገመዳ የቀብር ስነስርዓታቸው ዛሬ በሻሸመኔ ከተማ ተፈፅሟል።
በቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ አቶ ጀዋር መሐመድ እና ዶ/ር ጄይላን ከድር ጨምሮ እጅግ በርካታ ሰው ተገኝቶ ነበር።
መረጃው ከሂጅራ ባንክ ፣ ከኡስታዝ አህመዲን ጀበል ፣ ከምእራብ አርሲ ኮሚኒኬሽን ያሰባሰብነው ነው።
https://t.iss.one/tikvahethAFAANOROMOO
@tikvahethiopia
ታላቁ ዓሊም ሐጂ ሀሰን ገመዳ ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
ታላቁ ዓሊም ሐጂ ሀሰን ገመዳ እድሜያቸውን በዳዕዋ እና ኢልም በማስቀራት ያሳለፉ ሲሆን ለየትኛውም የሀገራችን መንግስት ሳይንበረከኩ በፅናት የዳዕዋ አገልግሎታቸውን ያስቀጠሉና ፍሬ ማፍራት የቻሉ ነበሩ።
ከአፄ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት እስከ ኢህአዴግ ድረስ ለአምስት ያህል ጊዜ ታስረዋል።
ታለቁ ዓሊም ሐጂ ሀሰን ገመዳ ባደረባቸው ህመም የህክምና ክትትል ሲያደረጉ ቆይተው ትላንት ለሊት አርፈዋል። የሐጂ ሀሰን እድሜ ከ120 - 130 ባለው መከከል እንደሆነ ይነገራል።
በቅርቡ " ሂጅራ ባንክ " በሻሸመኔ ከተማ የከፈተውን ቅርጫፍ በስማቸው እንዲሆን አድርጎ ነበር።
ትላንት ለሊት ከዚህ ዓለም ድካም ያረፉት ሐጂ ሀሰን ገመዳ የቀብር ስነስርዓታቸው ዛሬ በሻሸመኔ ከተማ ተፈፅሟል።
በቀብር ሥነ ሥርዓታቸው ላይ የሀይማኖት አባቶች፣ አቶ ጀዋር መሐመድ እና ዶ/ር ጄይላን ከድር ጨምሮ እጅግ በርካታ ሰው ተገኝቶ ነበር።
መረጃው ከሂጅራ ባንክ ፣ ከኡስታዝ አህመዲን ጀበል ፣ ከምእራብ አርሲ ኮሚኒኬሽን ያሰባሰብነው ነው።
https://t.iss.one/tikvahethAFAANOROMOO
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱና ባስመዘገቡት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችላቸው ተማሪዎች ከዚህ ቀደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳቸው ይታወቃል። ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች የሚከተሉትን ማስተካከያዎች እንዲያደርጉ ጠይቋል ፦ 1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣…
#MoE
የማመልከቻ ቀኑ ተራዘመ።
የትምህርት ሚኒስቴር ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን እንዲያስተካክሉ የሰጠው ጊዜ ትላንት መጠናቀቁን ተከትሎ ዛሬ ይፋ ባደረገው ማስታወቂያ ለተጨማሪ ቀናት አራዝሟል።
በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ባስመዘገቡት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችላቸው ተማሪዎች ከዚህ ቅደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳቸው ይታወቃል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን ገልጾ የሚከተሉትን መረጃዎች እንዲመለከቱ ጠይቋል ፦
1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት የዩኒቨርሲቲ ምርጫቻውን እስከ መጋቢት 19 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በ https://Portal.neaea.gov.et ገብተው እንዲያስተካክሉ ጠይቋል፤ ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ ሚኒስቴሩ የማናስተናግድ መሆኑን አሳውቋል።
2ኛ. በጤና እና ልዩ ልዩ ጉዳዮች ምደባ በልዩ ሁኔታ እንዲታይላቸው የሚያመለክቱ ተማሪዎች መረጃቸውን እስከ መጋቢት 19 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በ https://student.ethernet.edu.et/ በኩል እንዲልኩ ሚኒስቴሩ ያሳሰበ ሲሆን በአካል የሚቀርብ ምንም ዓይነት ማስረጃ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
@tikvahethiopia
የማመልከቻ ቀኑ ተራዘመ።
የትምህርት ሚኒስቴር ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የሚገቡ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን እንዲያስተካክሉ የሰጠው ጊዜ ትላንት መጠናቀቁን ተከትሎ ዛሬ ይፋ ባደረገው ማስታወቂያ ለተጨማሪ ቀናት አራዝሟል።
በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ባስመዘገቡት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችላቸው ተማሪዎች ከዚህ ቅደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳቸው ይታወቃል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን ገልጾ የሚከተሉትን መረጃዎች እንዲመለከቱ ጠይቋል ፦
1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት የዩኒቨርሲቲ ምርጫቻውን እስከ መጋቢት 19 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በ https://Portal.neaea.gov.et ገብተው እንዲያስተካክሉ ጠይቋል፤ ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ ሚኒስቴሩ የማናስተናግድ መሆኑን አሳውቋል።
2ኛ. በጤና እና ልዩ ልዩ ጉዳዮች ምደባ በልዩ ሁኔታ እንዲታይላቸው የሚያመለክቱ ተማሪዎች መረጃቸውን እስከ መጋቢት 19 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ በ https://student.ethernet.edu.et/ በኩል እንዲልኩ ሚኒስቴሩ ያሳሰበ ሲሆን በአካል የሚቀርብ ምንም ዓይነት ማስረጃ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
@tikvahethiopia
" No to War ! No to NATO ! "
የካናዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ ንግግራቸው በተቃውሞ ተቋረጠ።
በሞንትሪያል የውጭ ግንኙነት ካውንስል ንግግር ሲያደርጉ የነበሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ ንግግራቸው የፖለቲካ እና የፀረ ጦርነት አክቲቪስት እንደሆነ በተነገረለት ካናዳዊው ኢቭ ኢንግለር አማካኝነት ተቋርጧል።
ኢንግለር ፥ ካናዳ ጦርነቱን ከማባባስ ትታቀብ ፤ ዩክሬንን በወታደራዊ ትጥቅ ከመደገፍ ታቀቡ ፤ ወታደሮችን ማሰልጠን አቁሙ ፤ ኬየቭን ለምን ወደ ሚኒስክ ስምምነት አልገፋችሁም ? ለምን ? ፣ ልታፍሩ ይገባል ፤ ' No to War , No to NATO ' ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ልትገፉን ነው ፤ ዩክሬንን በሩስያ ላይ ለእጅ አዙር ጦርነት መጠቀም አቁሙ " ሲል ተደምጧል።
ክስተቱን በእጅ ስልኩ እየቀረፀ ተቃውሞን ያሰማው ኢቭ ኢንግለር በደህንነት ሰዎች እየተገፋ ከአዳራሹ እንዲወጣ ተደርጓል።
ካናዳ ዩክሬንን እያስታጠቁ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት።
@tikvahethiopia
የካናዳ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ ንግግራቸው በተቃውሞ ተቋረጠ።
በሞንትሪያል የውጭ ግንኙነት ካውንስል ንግግር ሲያደርጉ የነበሩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሜላኒ ጆሊ ንግግራቸው የፖለቲካ እና የፀረ ጦርነት አክቲቪስት እንደሆነ በተነገረለት ካናዳዊው ኢቭ ኢንግለር አማካኝነት ተቋርጧል።
ኢንግለር ፥ ካናዳ ጦርነቱን ከማባባስ ትታቀብ ፤ ዩክሬንን በወታደራዊ ትጥቅ ከመደገፍ ታቀቡ ፤ ወታደሮችን ማሰልጠን አቁሙ ፤ ኬየቭን ለምን ወደ ሚኒስክ ስምምነት አልገፋችሁም ? ለምን ? ፣ ልታፍሩ ይገባል ፤ ' No to War , No to NATO ' ወደ ሶስተኛው የዓለም ጦርነት ልትገፉን ነው ፤ ዩክሬንን በሩስያ ላይ ለእጅ አዙር ጦርነት መጠቀም አቁሙ " ሲል ተደምጧል።
ክስተቱን በእጅ ስልኩ እየቀረፀ ተቃውሞን ያሰማው ኢቭ ኢንግለር በደህንነት ሰዎች እየተገፋ ከአዳራሹ እንዲወጣ ተደርጓል።
ካናዳ ዩክሬንን እያስታጠቁ ካሉ ሀገራት መካከል አንዷ ናት።
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
በ 'ኦጋዴን' ተፋሰስ ያለውን የነዳጅና ተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መጠን እና ኢኮኖሚያዊ አዋጭነቱን ለማጥናት የሚያስችል ስምምነት በኢትዮጵያ መንግስትና በአሜሪካ ኔዘርላንድስ ስዌል እና አሶሼት ኢንክ በተባለ ኩባንያ መካከል ትላንት ተፈፅሟል።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን በተገኙበት የኢትዮጵያ ማዕድን ሚኒስትር ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የኩባንያው ምክትል ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ዎልፍ ተፈራርመዋል።
ምክትል ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ዎልፍ ፦
" ... የኢትዮጵያ ህዝብ ከውጭ ከሚመጣ የነዳጅ ምርት አቅርቦት በመላቀቅ የሀገሩን ሀብት መጠቀም እንዲችል የተጀመረውን ጥረት እናደንቃለን።
ከማዕድን ሚኒስቴር ጋር በኦጋዴን ተፋሰስ ያለውን ክምችት እና ሃብት ለማየት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመናል። ይህም ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ ያለውን የነዳጅ ክምችት እና ሃብት መጠን በአግባቡ እንዲረዳና ቀጥሎም ኢኮኖሚያዊ አዋጭነት ባለው መንገድ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል እንዲያቅድ ይረዳዋል።
የጥናት ስራውን በሚቀጥለው ሰኞ / ሳምንት እንጀምራለን። ፕሮጀክቱ የ4 ወር ጊዜ ያለው ሲሆን በዚህ ጊዜ ለማጠናቀቅ ብቁ ሰዎችን እናመጣለን "
ኢ/ር ታከለ ኡማ (የማዕድን ሚኒስትር) ፦
" ... ይሄን የተፈጥሮ ጋዝን ለይቶ አውቆ ፣ ኢኮኖሚያዊ አዋጭነቱን እንዲሁም ለምን እንደምንጠቀም በአራት ወር ጊዜ ውስጥ ለመንግስት ካስረከበ በኃላ የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት በከፊል ለመዳበሪያ ምርት በከፊል ለኢነርጂ የምንጠቀምበት ይሆናል "
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን ፦
" ... ኢትዮጵያ በኦጋዴን ያለው እምቅ ሃብት ለመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ ከሆነው ኩባንያ ጋር በመስራቷ ደስተኛ ነኝ። ኩባንያው ጥልቅ እውቀት ባላቸው ባለሞያዎቹ ብቻ ሳይሆን ለደንበኞቹ ስኬት ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ነው። "
ከዛሬ 4 ዓመት በፊት (ሰኔ 20/2010 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያ በPOLY GCL የተሰኘው የቻይና ኩባንያ አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የድፍድፍ ነዳጅ የሙከራ ምርት እንደምትጀምር ገልፀው እንደነበር ይታወሳል።
ሰኔ 20 /2010 ዓ/ም ላይ ሚዲያዎች በነጋታው ማለትም በ (ሰኔ 21) የድፍድፍ ነዳጅ የሙከራ ምርት እንደሚጀመር ቦታውም በምስራቅ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ኦጋዴን ኤሊሊ አከባቢ መሆኑን መግለፃቸው የሚዘነጋ አይደለም።
በወቅቱ በሙከራ ደረጃ በቀን 450 በርሚል ድፍድፍ ነዳጅ የማውጣት ስራ ይጀመራል ፤ ወደ ጅቡቲም ከመስከረም 2011 ጀምሮ የፕይፕ ዝርጋት ስራ ይጀመራል ሲባል ነበር።
ያንብቡ : telegra.ph/SOMALI---OGADEN-03-23
በ 'ኦጋዴን' ተፋሰስ ያለውን የነዳጅና ተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መጠን እና ኢኮኖሚያዊ አዋጭነቱን ለማጥናት የሚያስችል ስምምነት በኢትዮጵያ መንግስትና በአሜሪካ ኔዘርላንድስ ስዌል እና አሶሼት ኢንክ በተባለ ኩባንያ መካከል ትላንት ተፈፅሟል።
ስምምነቱን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን በተገኙበት የኢትዮጵያ ማዕድን ሚኒስትር ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የኩባንያው ምክትል ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ዎልፍ ተፈራርመዋል።
ምክትል ፕሬዝዳንት ጆሴፍ ዎልፍ ፦
" ... የኢትዮጵያ ህዝብ ከውጭ ከሚመጣ የነዳጅ ምርት አቅርቦት በመላቀቅ የሀገሩን ሀብት መጠቀም እንዲችል የተጀመረውን ጥረት እናደንቃለን።
ከማዕድን ሚኒስቴር ጋር በኦጋዴን ተፋሰስ ያለውን ክምችት እና ሃብት ለማየት የሚያስችል ስምምነት ተፈራርመናል። ይህም ሚኒስቴሩ በሀገሪቱ ያለውን የነዳጅ ክምችት እና ሃብት መጠን በአግባቡ እንዲረዳና ቀጥሎም ኢኮኖሚያዊ አዋጭነት ባለው መንገድ እንዴት መጠቀም እንደሚቻል እንዲያቅድ ይረዳዋል።
የጥናት ስራውን በሚቀጥለው ሰኞ / ሳምንት እንጀምራለን። ፕሮጀክቱ የ4 ወር ጊዜ ያለው ሲሆን በዚህ ጊዜ ለማጠናቀቅ ብቁ ሰዎችን እናመጣለን "
ኢ/ር ታከለ ኡማ (የማዕድን ሚኒስትር) ፦
" ... ይሄን የተፈጥሮ ጋዝን ለይቶ አውቆ ፣ ኢኮኖሚያዊ አዋጭነቱን እንዲሁም ለምን እንደምንጠቀም በአራት ወር ጊዜ ውስጥ ለመንግስት ካስረከበ በኃላ የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት በከፊል ለመዳበሪያ ምርት በከፊል ለኢነርጂ የምንጠቀምበት ይሆናል "
በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ አስፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን ፦
" ... ኢትዮጵያ በኦጋዴን ያለው እምቅ ሃብት ለመጠቀም በዓለም አቀፍ ደረጃ ዝነኛ ከሆነው ኩባንያ ጋር በመስራቷ ደስተኛ ነኝ። ኩባንያው ጥልቅ እውቀት ባላቸው ባለሞያዎቹ ብቻ ሳይሆን ለደንበኞቹ ስኬት ያላሰለሰ ጥረት የሚያደርግ ነው። "
ከዛሬ 4 ዓመት በፊት (ሰኔ 20/2010 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ኢትዮጵያ በPOLY GCL የተሰኘው የቻይና ኩባንያ አማካኝነት ለመጀመሪያ ጊዜ የድፍድፍ ነዳጅ የሙከራ ምርት እንደምትጀምር ገልፀው እንደነበር ይታወሳል።
ሰኔ 20 /2010 ዓ/ም ላይ ሚዲያዎች በነጋታው ማለትም በ (ሰኔ 21) የድፍድፍ ነዳጅ የሙከራ ምርት እንደሚጀመር ቦታውም በምስራቅ ኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ኦጋዴን ኤሊሊ አከባቢ መሆኑን መግለፃቸው የሚዘነጋ አይደለም።
በወቅቱ በሙከራ ደረጃ በቀን 450 በርሚል ድፍድፍ ነዳጅ የማውጣት ስራ ይጀመራል ፤ ወደ ጅቡቲም ከመስከረም 2011 ጀምሮ የፕይፕ ዝርጋት ስራ ይጀመራል ሲባል ነበር።
ያንብቡ : telegra.ph/SOMALI---OGADEN-03-23
Telegraph
Somali Region OGADEN
#ETHIOPIA በኦጋዴን ተፋሰስ ያለውን የነዳጅ እና የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መጠንና እና ኢኮኖሚያዊ አዋጭነቱን ለማጥናት የሚያስችል ስምምነት በኢትዮጵያ መንግስት እና በአሜሪካው ኔዘርላንድስ ስዌል እና አሶሼት ኢንክ በተባለ ኩባንያ መካከል ትላንት ተፈፅሟል። ስምምነቱን በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ ፈፃሚ አምባሳደር ትሬሲ ጃኮብሰን በተገኙበት የኢትዮጵያ ማዕድን ሚኒስትር ኢ/ር ታከለ ኡማ እና የኩባንያው ምክትል…
#Oxfam
" ኦክስፋም " ከአፍሪካ ቀንድ አስከፊ ድርቅ ጋር በተያያዘ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
ኦክስፋም ፥ በአፍሪቃ ቀንድ በተከሰተው አስከፊ ድርቅ ለረሐብ ለተጋለጠው ሕዝብ መርጃ የሚዉል ገንዘብ ካልተገኘ ከፍተኛ ሰብአዊ ድቀት ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቅቋል።
👉ኢትዮጵያን፣
👉 ሶማሊያን
👉 ኬንያን በመታዉ ድርቅ 13 ሚሊዮን ሕዝብ ለረሐብ መጋለጡን WFP ካስታወቀ 2 ወር ሊሞላ ነው።
ድርጅቱ እንዳስታወቀዉ ለረሐብ ለተጋለጠዉ ሕዝብ መርጃ የሚዉል የምግብ እሕል መግዢያ 6 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገዋል።
የብሪታንያዉ ግብረ ሰናይ ድርጅት ኦክስፋም ትናንት እንዳስታወቀዉ ለርዳታ ከተጠየቀዉ ገንዘብ እስካሁን የተገኘዉ 3 ከመቶ ብቻ ነዉ።
የኦክስፋም የበላይ ኃላፊ ጋብርኤላ በቸር እንዳሉት ባሁኑ ወቅት ምስራቅ አፍሪቃ በዓለም አቀፉ መድረክ ርዕስ አለመሆኑ " ጨካኝ " ሐቅ ነዉ። ብለውታል።
" ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በተለይ ምዕራቡ ዓለም ሙሉ ትኩረቱን በዩክሬኑ ጦርነት ላይ በማድረጉ ሌሎች በርካታ ሰብአዊና ፖለቲካዊ ቀዉሶች እየተዘነጉ ነዉ " ያሉት ኃላፊው " ምሥራቅ አፍሪቃን የመታዉ ድርቅ በመዘንጋቱ በያዝነዉ 2022 በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች በረሐብ ሊሞቱ አይገባም። " ብለዋል።
ባሁኑ ወቅት ድፍን ዓለም " የተቃጠለች " ያክል ስሜት ቢኖርም ለጋሾች ሰብአዊ መብትንና ሰብአዊ ቀዉስን በመከላከሉ ረገድ አንዱን ከሌላዉ ሊመርጡ አይገባም ሲሉ በቸር ማስገንዘባቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
" ኦክስፋም " ከአፍሪካ ቀንድ አስከፊ ድርቅ ጋር በተያያዘ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
ኦክስፋም ፥ በአፍሪቃ ቀንድ በተከሰተው አስከፊ ድርቅ ለረሐብ ለተጋለጠው ሕዝብ መርጃ የሚዉል ገንዘብ ካልተገኘ ከፍተኛ ሰብአዊ ድቀት ሊከሰት እንደሚችል አስጠንቅቋል።
👉ኢትዮጵያን፣
👉 ሶማሊያን
👉 ኬንያን በመታዉ ድርቅ 13 ሚሊዮን ሕዝብ ለረሐብ መጋለጡን WFP ካስታወቀ 2 ወር ሊሞላ ነው።
ድርጅቱ እንዳስታወቀዉ ለረሐብ ለተጋለጠዉ ሕዝብ መርጃ የሚዉል የምግብ እሕል መግዢያ 6 ቢሊዮን ዶላር ያስፈልገዋል።
የብሪታንያዉ ግብረ ሰናይ ድርጅት ኦክስፋም ትናንት እንዳስታወቀዉ ለርዳታ ከተጠየቀዉ ገንዘብ እስካሁን የተገኘዉ 3 ከመቶ ብቻ ነዉ።
የኦክስፋም የበላይ ኃላፊ ጋብርኤላ በቸር እንዳሉት ባሁኑ ወቅት ምስራቅ አፍሪቃ በዓለም አቀፉ መድረክ ርዕስ አለመሆኑ " ጨካኝ " ሐቅ ነዉ። ብለውታል።
" ዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ በተለይ ምዕራቡ ዓለም ሙሉ ትኩረቱን በዩክሬኑ ጦርነት ላይ በማድረጉ ሌሎች በርካታ ሰብአዊና ፖለቲካዊ ቀዉሶች እየተዘነጉ ነዉ " ያሉት ኃላፊው " ምሥራቅ አፍሪቃን የመታዉ ድርቅ በመዘንጋቱ በያዝነዉ 2022 በብዙ መቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች በረሐብ ሊሞቱ አይገባም። " ብለዋል።
ባሁኑ ወቅት ድፍን ዓለም " የተቃጠለች " ያክል ስሜት ቢኖርም ለጋሾች ሰብአዊ መብትንና ሰብአዊ ቀዉስን በመከላከሉ ረገድ አንዱን ከሌላዉ ሊመርጡ አይገባም ሲሉ በቸር ማስገንዘባቸውን የጀርመን ድምፅ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#ማጀስቲክ
ማጀስቲክ ኢንቴሪየር ዲዛይን እና የፊኒሺንግ ስራዎች ለቢሮዎች ፤ለሆቴልና ካፌዎች፤ ለተለያዩ የንግድ ሱቆች እና ለመኖሪያ ቤቶች የሚሆኑ ፡-
- Interior design & Architectural planning
- Finishing works
- Wood working & Furniture በማንኛውም ጊዜና ቦታ ካሉበት ሆነው ምን ማሰራት እንደሚፈልጉ በማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ባለሙያዎቻችንን ያማክሩ፡፡ አድራሻዎቻችን፡- 0901911111/0901919991/ 0911253679/89
Telegram:- @majestic_interior
Contact :- @majesticinteriors
📍 A.A,Getu commercial Center,Office 418 & 404
ማጀስቲክ ኢንቴሪየር ዲዛይን እና የፊኒሺንግ ስራዎች ለቢሮዎች ፤ለሆቴልና ካፌዎች፤ ለተለያዩ የንግድ ሱቆች እና ለመኖሪያ ቤቶች የሚሆኑ ፡-
- Interior design & Architectural planning
- Finishing works
- Wood working & Furniture በማንኛውም ጊዜና ቦታ ካሉበት ሆነው ምን ማሰራት እንደሚፈልጉ በማህበራዊ ትስስር ገጾቻችን ባለሙያዎቻችንን ያማክሩ፡፡ አድራሻዎቻችን፡- 0901911111/0901919991/ 0911253679/89
Telegram:- @majestic_interior
Contact :- @majesticinteriors
📍 A.A,Getu commercial Center,Office 418 & 404
#EthiopianAirlines
ላለፉት ሰላሳ ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያገለገሉት አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ከጤናቸው ጋር በተገናኘ በይፋዊ መንገድ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፍቃዳቸው መልቀቃቸውን ኢትዮ ንግድና ኢንስትመንት መድረክ ዘግቧል።
በገዘ ፍቃዳቸው ከኃላፊነታቸው የለቀቁት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወልደ ገ/ማርያም ከስድስት ወራት ላለፈ ጊዜ ህክምናቸውን በአሜሪካ እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል፡፡
አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ላለፉት 11 ዓመታት የኢትዮጵያ አየር መንገድን በዋና ሥራ አስፈፃሚ አሥፈፃሚነት የመሩ ሲሆን፤ ለ37 ዓመታት አየር መንገዱን አገልግለዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢትዮ ንግድና ኢንስትመንት መድረክ
@tikvahethiopia
ላለፉት ሰላሳ ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያገለገሉት አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ከጤናቸው ጋር በተገናኘ በይፋዊ መንገድ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፍቃዳቸው መልቀቃቸውን ኢትዮ ንግድና ኢንስትመንት መድረክ ዘግቧል።
በገዘ ፍቃዳቸው ከኃላፊነታቸው የለቀቁት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወልደ ገ/ማርያም ከስድስት ወራት ላለፈ ጊዜ ህክምናቸውን በአሜሪካ እየተከታተሉ እንደሚገኙም ተገልጿል፡፡
አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ላለፉት 11 ዓመታት የኢትዮጵያ አየር መንገድን በዋና ሥራ አስፈፃሚ አሥፈፃሚነት የመሩ ሲሆን፤ ለ37 ዓመታት አየር መንገዱን አገልግለዋል፡፡
ምንጭ፦ ኢትዮ ንግድና ኢንስትመንት መድረክ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EthiopianAirlines ላለፉት ሰላሳ ሰባት ዓመታት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ያገለገሉት አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ከጤናቸው ጋር በተገናኘ በይፋዊ መንገድ ከኃላፊነታቸው በገዛ ፍቃዳቸው መልቀቃቸውን ኢትዮ ንግድና ኢንስትመንት መድረክ ዘግቧል። በገዘ ፍቃዳቸው ከኃላፊነታቸው የለቀቁት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተወልደ ገ/ማርያም ከስድስት ወራት ላለፈ ጊዜ ህክምናቸውን በአሜሪካ…
#AtoTewoldeGebremariam
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ለመንግስት ያስገቡት የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልፀዋል።
አቶ ተወልደ ይህንን የገለፁት ለ ኢትዮጵያ ቼክ የመረጃ አጣሪ ድረገፅ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም በጤና እክል ምክንያት ቀደም ብለው ጡረታ መውጣታቸውን ገልፀው ፤ ለመንግስት ያስገቡት የመልቀቂያ ጥያቄም ተቀባይነት ማግኘቱን አረጋግጠዋል።
አቶ ተወልደ አየር መንገዱን ለ37 አመት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ያገለገሉ ሲሆን ላለፉት 11 አመታት በዋና ስራ አስፈፃሚነት አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ በአገልግሎት ዘመናቸው " የአመቱ ምርጥ የአፍሪካ ስራ አስፈፃሚ " ን ጨምሮ እጅግ በርካታ ሽልማቶችን ለግላቸው እና ለአየር መንገዱ አስገኝተዋል።
አዲሱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ማን እንደሚሆን እስካሁን አልታወቀም/ ይፋ አልተደረገም።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ለመንግስት ያስገቡት የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልፀዋል።
አቶ ተወልደ ይህንን የገለፁት ለ ኢትዮጵያ ቼክ የመረጃ አጣሪ ድረገፅ ነው።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም በጤና እክል ምክንያት ቀደም ብለው ጡረታ መውጣታቸውን ገልፀው ፤ ለመንግስት ያስገቡት የመልቀቂያ ጥያቄም ተቀባይነት ማግኘቱን አረጋግጠዋል።
አቶ ተወልደ አየር መንገዱን ለ37 አመት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ያገለገሉ ሲሆን ላለፉት 11 አመታት በዋና ስራ አስፈፃሚነት አገልግለዋል።
አቶ ተወልደ በአገልግሎት ዘመናቸው " የአመቱ ምርጥ የአፍሪካ ስራ አስፈፃሚ " ን ጨምሮ እጅግ በርካታ ሽልማቶችን ለግላቸው እና ለአየር መንገዱ አስገኝተዋል።
አዲሱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ ማን እንደሚሆን እስካሁን አልታወቀም/ ይፋ አልተደረገም።
@tikvahethiopia
#HalabaZone📍
ነፍሰ ጡር ሴት፣ ልጅ የተሸከመች እናትን ጨምሮ 7 ሰዎች በደራሽ ውሃ ተወሰዱ።
ትላንት በድንገት የተከሰተ ደራሽ ውሃ የብላቴ ወንዝን ሲያቋርጡ የነበሩ አንዲት ነፍሰ ጡር ሴትን ጨምሮ 7 ሰዎችን ወስዷል።
በሀላባ ዞን ከብላቴ ወንዝ ማዶ የሚገኙ የዌራ ወረዳ እና የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ቀበሌያት ነዋሪ የሆኑ ግለሰቦች ትናንትና ልክ ከምሽቱ 4 ሠዓት አካባቢ ከፋማ ፏፏቴ በላይ የሚገኘውና በተለምዶ " ጣጤ ብላቴ " ተብሎ የሚጠራውን የወንዝ ውሃ አቋርጠው ሲሻገሩ በደራሽ ውሃ ተወስደዋል።
በደራሽ ውሃው ከተወሰዱት መካከል፦
👉 ነፍሰ ጡር ሴት፣
👉 ህፃን ልጅ የተሸከመች እናት
👉 የ9ኛ ክፍል ተማሪ የሚገኙ ሲሆን እስካሁን በሟቾች አስክሬን ዙሪያ የተገኘ የተጣራ መረጃ የለም።
የዌራ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማህበረሰቡ ከበጋ ውጭ በማንኛውም ዝናብ የሚጥልበት ጊዜ በዚህ በኩል ከመሻገር እንዲቆጠብ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
ነፍሰ ጡር ሴት፣ ልጅ የተሸከመች እናትን ጨምሮ 7 ሰዎች በደራሽ ውሃ ተወሰዱ።
ትላንት በድንገት የተከሰተ ደራሽ ውሃ የብላቴ ወንዝን ሲያቋርጡ የነበሩ አንዲት ነፍሰ ጡር ሴትን ጨምሮ 7 ሰዎችን ወስዷል።
በሀላባ ዞን ከብላቴ ወንዝ ማዶ የሚገኙ የዌራ ወረዳ እና የሀላባ ቁሊቶ ከተማ ቀበሌያት ነዋሪ የሆኑ ግለሰቦች ትናንትና ልክ ከምሽቱ 4 ሠዓት አካባቢ ከፋማ ፏፏቴ በላይ የሚገኘውና በተለምዶ " ጣጤ ብላቴ " ተብሎ የሚጠራውን የወንዝ ውሃ አቋርጠው ሲሻገሩ በደራሽ ውሃ ተወስደዋል።
በደራሽ ውሃው ከተወሰዱት መካከል፦
👉 ነፍሰ ጡር ሴት፣
👉 ህፃን ልጅ የተሸከመች እናት
👉 የ9ኛ ክፍል ተማሪ የሚገኙ ሲሆን እስካሁን በሟቾች አስክሬን ዙሪያ የተገኘ የተጣራ መረጃ የለም።
የዌራ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማህበረሰቡ ከበጋ ውጭ በማንኛውም ዝናብ የሚጥልበት ጊዜ በዚህ በኩል ከመሻገር እንዲቆጠብ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia
#BirbirCity📍
የገዛ ልጁን በሽጉጥ በማስፈራራት የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።
በደቡብ ክልል በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ " መንደር ሰባት " ነዋሪ የሆኑት ኢኒስፔክተር ግርማ ጌታቸው የገዛ ልጁን መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በመድፈሩ 9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተቀጣ።
የልጅቷ ዕድሜዋ 20 ሲሆን የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ናት።
ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው በቀን 6 ቀን 6/2014 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ተበዳይ ጩኸት ማሰማቷን ተከትሎ የደረሰው ጎረቤት ለፖሊስ ጥቆማ አድርጓል።
ፖሊስ ጉዳዩን አጣርቶ ካቀረበ በኋላ የጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ተከሳሹ በ9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ፍርድ እንዲቀጣ መወሰኑን ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
More : @tikvahethmagazine
የገዛ ልጁን በሽጉጥ በማስፈራራት የደፈረው ግለሰብ በእስራት ተቀጣ።
በደቡብ ክልል በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ብርብር ከተማ " መንደር ሰባት " ነዋሪ የሆኑት ኢኒስፔክተር ግርማ ጌታቸው የገዛ ልጁን መንግሥት ባስታጠቀው ሽጉጥ በማስፈራራት በመድፈሩ 9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ተቀጣ።
የልጅቷ ዕድሜዋ 20 ሲሆን የዘጠነኛ ክፍል ተማሪ ናት።
ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው በቀን 6 ቀን 6/2014 ዓ/ም ከምሽቱ 2 ሰዓት አካባቢ ሲሆን ተበዳይ ጩኸት ማሰማቷን ተከትሎ የደረሰው ጎረቤት ለፖሊስ ጥቆማ አድርጓል።
ፖሊስ ጉዳዩን አጣርቶ ካቀረበ በኋላ የጋሞ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ ፍ/ቤት በዛሬው ዕለት በዋለው ችሎት ተከሳሹ በ9 ዓመት ከ3 ወር ፅኑ እስራት ፍርድ እንዲቀጣ መወሰኑን ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
More : @tikvahethmagazine
TIKVAH-ETHIOPIA
#AtoTewoldeGebremariam የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም ለመንግስት ያስገቡት የመልቀቂያ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልፀዋል። አቶ ተወልደ ይህንን የገለፁት ለ ኢትዮጵያ ቼክ የመረጃ አጣሪ ድረገፅ ነው። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ተወልደ ገ/ማርያም በጤና እክል ምክንያት ቀደም ብለው ጡረታ መውጣታቸውን ገልፀው ፤ ለመንግስት ያስገቡት…
#Update
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ከጤናቸው ጋር በተያያዘ በገዛ ፍቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቃቸውን አረጋግጧል።
በሌላ በኩል ፤ የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ግርማ ዋቄ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው በቅርቡ መሾማቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል።
አቶ ግርማ ፤ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የካበተ ልምድ ያላቸው ሲሆኑ አየር መንገዱን ዛሬ ለደረሰበት ስኬት መሰረት በጣለ መልኩ ለ7 ዓመታት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው አገልግለዋል።
ቦርዱ በቅርቡ አዲሱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የአቶ ተወልደ ገ/ማርያምን ተተኪ ያሳውቃል ተብሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ አቶ ተወልደ ገብረ ማርያም ከጤናቸው ጋር በተያያዘ በገዛ ፍቃዳቸው ከኃላፊነት መልቀቃቸውን አረጋግጧል።
በሌላ በኩል ፤ የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ግርማ ዋቄ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው በቅርቡ መሾማቸውን አየር መንገዱ አስታውቋል።
አቶ ግርማ ፤ በአየር ትራንስፖርት ዘርፍ የካበተ ልምድ ያላቸው ሲሆኑ አየር መንገዱን ዛሬ ለደረሰበት ስኬት መሰረት በጣለ መልኩ ለ7 ዓመታት ዋና ስራ አስፈፃሚ ሆነው አገልግለዋል።
ቦርዱ በቅርቡ አዲሱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የአቶ ተወልደ ገ/ማርያምን ተተኪ ያሳውቃል ተብሏል።
@tikvahethiopia