TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ (UAE) ወደ ትግራይ ክልል የምግብ እርዳታ ላከች። ሀገሪቱ 35 ቶን ምግብ የጫነ አውሮፕላን ወደ የትግራይ ክልል መዲና መቐለ በዛሬው እለት መላኳን ገልጻለች፡፡ በኢትዮጵያ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ አምባሳደር ሞሀመድ ሳሊም አልረሽድ ፥ " የተደረገው የምግብ እርዳታ በትግራይ ክልል ያለውን የሰብአዊ ሁኔታ ለመርዳት ነው " ብለዋል፡፡ የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ…
#Tigray , #Mekelle📍
የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ወደ ትግራይ ክልል 30 ቶን የምግብ ድጋፍ ላከች።
የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ለትግራይ ህዝብ አስፈላጊ እርዳታ በአየር ለማጓጓዝ በሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ ጥረት 30 ቶን የምግብ ድጋፍ የጫነ አውሮፕላን ወደ ትግራይ ክልል መዲና መቐለ መለኳ ተሰምቷል።
ድጋፉ 5,600 ሴቶችና ህጻናትን ጨምሮ ከ7,000 በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።
አሁን ባለው ሁኔታ እየጨመረ የመጣውን የቤተሰቦችን በተለይ የሴቶችን እና የህጻናትን ፍላጎት ይደግፋል ተብሏል።
ባለፈው ወር የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ወደ ትግራይ ክልል 35 ቶን የምግብ እርዳታ መላኳ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ወደ ትግራይ ክልል 30 ቶን የምግብ ድጋፍ ላከች።
የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ለትግራይ ህዝብ አስፈላጊ እርዳታ በአየር ለማጓጓዝ በሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ ጥረት 30 ቶን የምግብ ድጋፍ የጫነ አውሮፕላን ወደ ትግራይ ክልል መዲና መቐለ መለኳ ተሰምቷል።
ድጋፉ 5,600 ሴቶችና ህጻናትን ጨምሮ ከ7,000 በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል።
አሁን ባለው ሁኔታ እየጨመረ የመጣውን የቤተሰቦችን በተለይ የሴቶችን እና የህጻናትን ፍላጎት ይደግፋል ተብሏል።
ባለፈው ወር የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ወደ ትግራይ ክልል 35 ቶን የምግብ እርዳታ መላኳ ይታወሳል።
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
መንግሥት ትግራይን ጨምሮ በጦርነት እና ግጭቶች የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ነዋሪዎችን ለማቋቋም ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።
ፕሮጀክቱን ይፋ ያደረገው የገንዘብ ሚኒስቴር ሲሆን ከውጭ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።
አሁን ይፋ የሆነው ለመፈፀም አምስት ዓመታት ይፈጃል የተባለው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን ትግራይ፣ አማራ ፣ አፋር ቅድሚያ ተሰጥቷቸዋል፤ እንዲሁም በምዕራብ ኢትዮጵያ በኩል ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ምዕራብ ኦሮሚያ ቅድሚያ አግኝተዋል።
ይፈጃል ከተባለው ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ከዓለም ባንክ የሚገኝ ሲሆን ቀሪውን የኢትዮጵያ መንግስት ይሸፍነዋል።
በፕሮጀክቶቹ ከታቀዱት ተግባራት መካከል ፦
👉 በግጭት የተጎዱ ወገኖችን አፋጣኝ ፍላጎት ማሟላት፤
👉 ፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ተጎጂዎች እንዲያገግሙ፤ አገልግሎት የሚሰጡ ማዕከላት ማቋቋም፤
👉 መሰረተ ልማቶችን መልሶ ማቋቋም፤
👉 ለመልሶ ሟቋቋም የሚደረገውን ጥረት በዘላቂነት መደገፍ የሚችሉ ተቋማትን ማጠናከር ይገኙበታል።
ፕሮጀክቱን ለማስፈፀምና ለመከታተል የተለያዩ ሚኒስቴር መ/ቤቶችን ያካተተ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን ፕሮጀክቱን ለማስፈፀም ዋና ኃላፊነት የተሰጠው ለገንዘብ ሚኒስቴር ነው።
ፕሮጀክቱ ግጭት እና ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች ላይ ከመንግስት ድጋፍ ውጭ መግባት እና መስራት ከሚችሉ የ3ኛ ወገን አካላት ጋር በመዋዋል ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
ውል የሚገቡት የ3ኛ ወገን አካላት ፕሮጀክቶቹን ግልፅ እና ቀጥተኛ በሆነ መንገድ ተፈፃሚ የማድረግ ኃላፊነት አለባቸው ፤ የአካባቢው አስተዳደር ሚናን በመተካትም የፕሮጀክት ሂደቱን የማመቻቸት እና ውጤታማ የማድረግ ሙሉ ኃላፊነት ይወስዳሉ መባሉን ሪፖርተር አስነብቧል።
@tikvahethiopia
መንግሥት ትግራይን ጨምሮ በጦርነት እና ግጭቶች የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ነዋሪዎችን ለማቋቋም ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል።
ፕሮጀክቱን ይፋ ያደረገው የገንዘብ ሚኒስቴር ሲሆን ከውጭ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው።
አሁን ይፋ የሆነው ለመፈፀም አምስት ዓመታት ይፈጃል የተባለው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን ትግራይ፣ አማራ ፣ አፋር ቅድሚያ ተሰጥቷቸዋል፤ እንዲሁም በምዕራብ ኢትዮጵያ በኩል ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ምዕራብ ኦሮሚያ ቅድሚያ አግኝተዋል።
ይፈጃል ከተባለው ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ከዓለም ባንክ የሚገኝ ሲሆን ቀሪውን የኢትዮጵያ መንግስት ይሸፍነዋል።
በፕሮጀክቶቹ ከታቀዱት ተግባራት መካከል ፦
👉 በግጭት የተጎዱ ወገኖችን አፋጣኝ ፍላጎት ማሟላት፤
👉 ፆታዊ ጥቃት ለደረሰባቸው ተጎጂዎች እንዲያገግሙ፤ አገልግሎት የሚሰጡ ማዕከላት ማቋቋም፤
👉 መሰረተ ልማቶችን መልሶ ማቋቋም፤
👉 ለመልሶ ሟቋቋም የሚደረገውን ጥረት በዘላቂነት መደገፍ የሚችሉ ተቋማትን ማጠናከር ይገኙበታል።
ፕሮጀክቱን ለማስፈፀምና ለመከታተል የተለያዩ ሚኒስቴር መ/ቤቶችን ያካተተ ኮሚቴ የተቋቋመ ሲሆን ፕሮጀክቱን ለማስፈፀም ዋና ኃላፊነት የተሰጠው ለገንዘብ ሚኒስቴር ነው።
ፕሮጀክቱ ግጭት እና ስጋት ባለባቸው አካባቢዎች ላይ ከመንግስት ድጋፍ ውጭ መግባት እና መስራት ከሚችሉ የ3ኛ ወገን አካላት ጋር በመዋዋል ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።
ውል የሚገቡት የ3ኛ ወገን አካላት ፕሮጀክቶቹን ግልፅ እና ቀጥተኛ በሆነ መንገድ ተፈፃሚ የማድረግ ኃላፊነት አለባቸው ፤ የአካባቢው አስተዳደር ሚናን በመተካትም የፕሮጀክት ሂደቱን የማመቻቸት እና ውጤታማ የማድረግ ሙሉ ኃላፊነት ይወስዳሉ መባሉን ሪፖርተር አስነብቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA መንግሥት ትግራይን ጨምሮ በጦርነት እና ግጭቶች የተጎዱ አካባቢዎችን መልሶ ለመገንባት እና ነዋሪዎችን ለማቋቋም ከ19 ቢሊዮን ብር በላይ የሚፈጅ ፕሮጀክት ይፋ አድርጓል። ፕሮጀክቱን ይፋ ያደረገው የገንዘብ ሚኒስቴር ሲሆን ከውጭ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው። አሁን ይፋ የሆነው ለመፈፀም አምስት ዓመታት ይፈጃል የተባለው የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን ትግራይ፣ አማራ ፣…
#ETHIOPIA
IOM (ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት) በመስከረም 2014 ዓ/ም ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ እና በጦርነትና በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለማቋቋም ይፋ በተደረገው ፕሮጀክት ላይ በቀረበው ሰነድ መሰረት ፦
👉 በኢትዮጵያ ከ4.2 ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች አሉ፤ ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለቱይ ተፈናቃዮች መካከል ትልቁ ነው።
👉 ከ4.2 ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች መካከል ከ50 % በላይ ሴቶች ሲሆኑ ቢያንስ 720 ,000 ህፃናትም ተፈናቅለዋል።
👉 ከ4.2 ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች 80 % በግጭት ምክንያት የተፈናቀሉ ናቸው ፤ 50 በመቶዎቹ (2.08 ሚሊዮን ገደማ) ባለፉት 6 እና 7 ወር የተፈናቀሉ ናቸው።
👉 ከአጠቃላይ ተፈናቃዮች ወደ 90 % (1.8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች) በትግራይ ክልል ናቸው።
NB : በሰነዱ ያልተካተቱ ተፈናቃዮች በአፋር እና አማራ ክልሎች የሚገኙ ሲሆን አጠቃላይ የተጎጂዎች ልየታ እና ምዘና በአሁን ወቅት እየተካሄ እንደሚገኝ ሪፖርተር አስነብቧል።
@tikvahethiopia
IOM (ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ድርጅት) በመስከረም 2014 ዓ/ም ላይ ይፋ ባደረገው መረጃ እና በጦርነትና በግጭት የተጎዱ ወገኖችን ለማቋቋም ይፋ በተደረገው ፕሮጀክት ላይ በቀረበው ሰነድ መሰረት ፦
👉 በኢትዮጵያ ከ4.2 ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች አሉ፤ ይህ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ ካለቱይ ተፈናቃዮች መካከል ትልቁ ነው።
👉 ከ4.2 ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች መካከል ከ50 % በላይ ሴቶች ሲሆኑ ቢያንስ 720 ,000 ህፃናትም ተፈናቅለዋል።
👉 ከ4.2 ሚሊዮን በላይ ተፈናቃዮች 80 % በግጭት ምክንያት የተፈናቀሉ ናቸው ፤ 50 በመቶዎቹ (2.08 ሚሊዮን ገደማ) ባለፉት 6 እና 7 ወር የተፈናቀሉ ናቸው።
👉 ከአጠቃላይ ተፈናቃዮች ወደ 90 % (1.8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች) በትግራይ ክልል ናቸው።
NB : በሰነዱ ያልተካተቱ ተፈናቃዮች በአፋር እና አማራ ክልሎች የሚገኙ ሲሆን አጠቃላይ የተጎጂዎች ልየታ እና ምዘና በአሁን ወቅት እየተካሄ እንደሚገኝ ሪፖርተር አስነብቧል።
@tikvahethiopia
#አብን
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዶ/ር በለጠ ሞላን በድጋሚ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ።
አቶ መልካሙ ሹምዬ ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጣሂር መሐመድ ፤ ፓርቲው ለ3 ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ሲያካሂድ እንደቆየና የሥራ አስፈፃሚ አባላቱን በአዲስ በማደራጀት ማጠናቀቁን ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት፦
👉 ዶ/ር በለጠ ሞላ - ሊቀመንበር
👉 አቶ መልካሙ ሹምዬ - ምክትል ሊቀመንበር
👉 ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ - የውጭ ግንኙነት ኃላፊ
👉 አቶ ዩሱፍ ኢብራሒም - የሕግ ጉዳዮች ኃላፊ
👉 አቶ ክርስቲያን ታደለ - የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ክፍል ኃላፊ
👉 አቶ ጋሻው መርሻ - የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ
👉 አቶ ጣሂር መሐመድ - የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ
👉 ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም - የአብን ጽ/ቤት ኃላፊ
👉 አቶ ሐሳቡ ተስፋየ - አደረጃጀት ጉዳዮች ኃላፊ አድርጎ የሥራ አስፈፃሚውን በአዲስ አደራጅቷል።
ከተመረጡት የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚዎች መካከል ሦስቱ አዲስ መሆናቸው ተገልጿል።
ፓርቲው ዛሬ 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር ማካሄድ መጀመሩን #ኢብኮ / #አሚኮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዶ/ር በለጠ ሞላን በድጋሚ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ።
አቶ መልካሙ ሹምዬ ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጣሂር መሐመድ ፤ ፓርቲው ለ3 ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ሲያካሂድ እንደቆየና የሥራ አስፈፃሚ አባላቱን በአዲስ በማደራጀት ማጠናቀቁን ገልጸዋል።
በዚህም መሠረት፦
👉 ዶ/ር በለጠ ሞላ - ሊቀመንበር
👉 አቶ መልካሙ ሹምዬ - ምክትል ሊቀመንበር
👉 ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ - የውጭ ግንኙነት ኃላፊ
👉 አቶ ዩሱፍ ኢብራሒም - የሕግ ጉዳዮች ኃላፊ
👉 አቶ ክርስቲያን ታደለ - የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ክፍል ኃላፊ
👉 አቶ ጋሻው መርሻ - የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ
👉 አቶ ጣሂር መሐመድ - የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ
👉 ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም - የአብን ጽ/ቤት ኃላፊ
👉 አቶ ሐሳቡ ተስፋየ - አደረጃጀት ጉዳዮች ኃላፊ አድርጎ የሥራ አስፈፃሚውን በአዲስ አደራጅቷል።
ከተመረጡት የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚዎች መካከል ሦስቱ አዲስ መሆናቸው ተገልጿል።
ፓርቲው ዛሬ 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር ማካሄድ መጀመሩን #ኢብኮ / #አሚኮ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የነዳጅ ዋጋ አሽቆለቆለ። በዩክሬንና ሩስያ ጦርነት ምክንያት ባለፉት ሳምንታት የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ ማሻቀቡ ፤ በበርሜልም እስከ 140 ዶላር ድረስ ደርሶ ነበር። በዚህ ሳምንት ግን የነዳጅ ዋጋ በእጅጉ መቀነሱ ተነግሯል። አሁን ላይ ፤ የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ በበርሜል 98.50 ዶላር ሲሆን በአሜሪካ ነዳጅ ገበያ እንደመለኪያ በሚታየው ዌስት ቴክሳስ ኢንተርሚዴት 1 በርሜል ነዳጅ 96.14 ዶላር በሆነ…
#Update
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 💵 ፦
🛢️ እ.ኤ.አ. ህዳር አንድ 👉 68 ዶላር
🛢️ እ.ኤ.አ. ታህሳስ አንድ 👉 77 ዶላር
🛢️ እ.ኤ.አ. ጥር አንድ 👉 89 ዶላር
🛢️ እ.ኤ.አ. የካቲት አንድ 👉 97 ዶላር
🛢️ ዛሬ ላይ የአንድ በርሜል የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 👉 108 ዶላር ደርሷል።
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከቀናት በፊት ባለፉት ሳምንታት ከታየው ከፍተኛ ጭማሪ (እስከ 140 ዶላር ድረስ ደርሶ ነበር) ወርዶ ከአንድ መቶ ዶላር በታች የነበር ሲሆን አሁን ወደ ላይ እያሻቀበ ይገኛል።
መረጃው ከቢዝነስ ኢንሳይደር የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 💵 ፦
🛢️ እ.ኤ.አ. ህዳር አንድ 👉 68 ዶላር
🛢️ እ.ኤ.አ. ታህሳስ አንድ 👉 77 ዶላር
🛢️ እ.ኤ.አ. ጥር አንድ 👉 89 ዶላር
🛢️ እ.ኤ.አ. የካቲት አንድ 👉 97 ዶላር
🛢️ ዛሬ ላይ የአንድ በርሜል የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ 👉 108 ዶላር ደርሷል።
የብሬንት ድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ከቀናት በፊት ባለፉት ሳምንታት ከታየው ከፍተኛ ጭማሪ (እስከ 140 ዶላር ድረስ ደርሶ ነበር) ወርዶ ከአንድ መቶ ዶላር በታች የነበር ሲሆን አሁን ወደ ላይ እያሻቀበ ይገኛል።
መረጃው ከቢዝነስ ኢንሳይደር የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
PHOTO : የ2022 የቤል ግሬድ የአለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና እየተካሄደ ይገኛል። ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል። ትላንት ለሊት ላይ በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያዊያን🇪🇹 አትሌቶቻችን ከአንድ እስከ ሶስት ተከታትለው በመግባት አሸንፈዋል። በ1500 ሜትር ሴቶች ውድድር ፦ 1ኛ. አትሌት ጉዳፍ ፀጋይ ወርቅ ለሀገራችን ስታስገኝ ፤ 2ኛ. አክሱማዊት እምባዬ ለሀገራችን የብር ሜዳሊያ አገኝታለች፡ 3ኛ. ሂሩት…
ፎቶ ፦ ሀገራችን ኢትዮጵያ 🇪🇹 የደመቀችበት የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ቀጥሎ የተካሄደ ሲሆን ኢትዮጵያ ተጨማሪ ሜዳሊያዎችን አስመዝግባለች።
ዛሬ በተካሄደ የ3000 ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተከታትለው በመግባት የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።
የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል።
ሁሉንም የስፖርታዊ ጉዳዮችን በ @tikvahethsport ይከታተሉ።
ዛሬ በተካሄደ የ3000 ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ እና ለሜቻ ግርማ ተከታትለው በመግባት የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኝተዋል።
የቤልግሬድ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና ዛሬ ፍፃሜውን ያገኛል።
ሁሉንም የስፖርታዊ ጉዳዮችን በ @tikvahethsport ይከታተሉ።
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍 የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ያናሷቸው ጥያቄዎች ምንድናቸው ? የካማሺ ዞን ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ዓለሙ በሽር ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ በእስር ላይ ያሉ አባሎቻቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል። የዞኑ አስተዳደሮች ይሄ ጥያቄ በዞኑ የሚመለስ እንዳልሆነ አስረድተው፣ በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ንግግር በማድረግ መልስ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።…
#Update
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በጫካ ያሉ ታጣቂዎች ፤ ትጥቃቸውን በሚፈቱበት አካሄድ ላይ ከተወካዮቻቸው ጋር ውይይት ሊደረግ መሆኑ ታውቋል።
የክልሉ መንግስት የተሃድሶ ስልጠና ሃሳቡን ያቀረበው፤ ከጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ታጣቂዎች ጋር ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 10 ቀን 2014 በይፋ ዕርቅ መፈጸሙን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
በጉሙዝ ባህል መሰረት የተከናወነው የዕርቅ ስነ ስርዓት የተካሄደው በካማሺ ዞን፤ ካማሺ ከተማ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽና በካማሺ ወንዝ ዳርቻ ነው።
በዕርቅ ስነ ስርዓቱ ላይ የምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ የክልሉ ም/ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አለምነሽ ይባስ እና የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ ተገኝተው ነበር።
በካማሺ ከተማ የስብሰባ አዳራሽ በተከናወነው ዕርቅ ለአራት ሰዓታት የዘለቀ ነበር።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት እና በጉህዴን አመራሮች መካከል ዕርቅ መውረድ ተከትሎ፤ በጫካ የነበሩ አማጽያን ከእነ ትጥቃቸው ወደ ካማሺ ከተማ ሲገቡ መመልከታቸውን አንድ የከተማውን ነዋሪዎች ዋቢ አድርጎ ድረገፁ አስነብቧል።
የታጣቂዎቹን ወደ ከተማ መግባት የካማሺ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ቦካ አቦሴም አረጋግጠዋል።
ታጣቂዎቹ ለጊዜው የካማሺ ዞን ባዘጋጀላቸው ማረፊያ እንደሚቆዩ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው ገልፀው ፤ በየትኛው የከተማው አካባቢ እንደሚቆዩ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ያንብቡ ፦ telegra.ph/Ethiopia-Insider-03-20
Credit - Ethiopia Insder
@tikvahethiopia
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በጫካ ያሉ ታጣቂዎች ፤ ትጥቃቸውን በሚፈቱበት አካሄድ ላይ ከተወካዮቻቸው ጋር ውይይት ሊደረግ መሆኑ ታውቋል።
የክልሉ መንግስት የተሃድሶ ስልጠና ሃሳቡን ያቀረበው፤ ከጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ታጣቂዎች ጋር ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 10 ቀን 2014 በይፋ ዕርቅ መፈጸሙን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።
በጉሙዝ ባህል መሰረት የተከናወነው የዕርቅ ስነ ስርዓት የተካሄደው በካማሺ ዞን፤ ካማሺ ከተማ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽና በካማሺ ወንዝ ዳርቻ ነው።
በዕርቅ ስነ ስርዓቱ ላይ የምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ የክልሉ ም/ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አለምነሽ ይባስ እና የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ ተገኝተው ነበር።
በካማሺ ከተማ የስብሰባ አዳራሽ በተከናወነው ዕርቅ ለአራት ሰዓታት የዘለቀ ነበር።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት እና በጉህዴን አመራሮች መካከል ዕርቅ መውረድ ተከትሎ፤ በጫካ የነበሩ አማጽያን ከእነ ትጥቃቸው ወደ ካማሺ ከተማ ሲገቡ መመልከታቸውን አንድ የከተማውን ነዋሪዎች ዋቢ አድርጎ ድረገፁ አስነብቧል።
የታጣቂዎቹን ወደ ከተማ መግባት የካማሺ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ቦካ አቦሴም አረጋግጠዋል።
ታጣቂዎቹ ለጊዜው የካማሺ ዞን ባዘጋጀላቸው ማረፊያ እንደሚቆዩ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው ገልፀው ፤ በየትኛው የከተማው አካባቢ እንደሚቆዩ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።
ያንብቡ ፦ telegra.ph/Ethiopia-Insider-03-20
Credit - Ethiopia Insder
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍 የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ያናሷቸው ጥያቄዎች ምንድናቸው ? የካማሺ ዞን ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ዓለሙ በሽር ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ በእስር ላይ ያሉ አባሎቻቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል። የዞኑ አስተዳደሮች ይሄ ጥያቄ በዞኑ የሚመለስ እንዳልሆነ አስረድተው፣ በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ንግግር በማድረግ መልስ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።…
#Kasmashi📍
የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ከዚህ በፊት እርቅ ለመፈፀም ካስቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎች የትኞቹ ተሟሉ ?
👉 የታሰሩ ጉህዴን አመራሮች እንዲፈቱ ጠይቀው፤ በርካታ የታጠቂው ኃይሎች ከእስር ተፈተዋል፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፌደራል መንግስት ጋር በመነጋገር የታሰሩ የጉህዴን አመራሮች የካቲት 17 እንዲፈቱ አድርጓል። ከነዚህ ውስጥ የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ የሚገኙበት ሲሆን ከ20 ቀናት ገደማ በፊት ነው የተፈቱት። ባለፉት 2 ሳምንታት 400 ገደማ የፓርቲው አባላትም ከእስር መፈታታቸውን ጉህዴን አረጋግጧል።
👉 የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና ለሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆኑ ጠይቀው፤ አካባቢው ሰላም ከሆነ የክልሉ መንግስት ነዋሪዎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስና በየትኛውም ቦታ እርዳታ ማቅረብ እንደሚችል ለታጣቂዎቹ ገልጿል።
👉 በካማሺ እና መተከል ዞን ያሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዲሁም የሌሎች ክልል ልዩ ኃይሎች አካባቢዎቹን ለቅቀው እንዲወጡ ጠይቀው፤ ክልሉ የተጠቀሱት የጸጥታ ኃይሎች እንዲወጡ በቅድሚያ ሰላም መምጣት እንዳለበት ከብዙ ውይይት በኋላ ስምምነት ላይ መደረሱን አመልክቷል፤ ጉህዴን ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም አይነት ውይይት አላደረግንም ብሏል፤ ከዕርቁ በኋላ በጉዳዩ ላይ ወይይት እንደሚደረግበት ገልጿል።
🔹 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ታጥቀው በየጫካው ያሉ ታጣቂዎች፤ ትጥቃቸውን ፈትተው የተሃድሶ ስልጠና የሚያገኙበት ሁኔታ ላይ መምከር ከዕርቁ በኋላ የሚኖረው አንዱ ዋነኛ ጉዳይ ነው ብሏል። ጉህዴን በተመሳሳይ ከዕርቁ በኋላ ከክልሉ መንግስት ጋር የሚደረግ ውይይት አለ ያለ ሲሆን ታጣቂዎቹ ትጥቅ መቼ እንደሚፈቱ የሚወሰነው በውይይት ነው ብሏል። እስከዛ ግን ታጥቀው እንደሚቆዩ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ከዚህ በፊት እርቅ ለመፈፀም ካስቀመጡት ቅድመ ሁኔታዎች የትኞቹ ተሟሉ ?
👉 የታሰሩ ጉህዴን አመራሮች እንዲፈቱ ጠይቀው፤ በርካታ የታጠቂው ኃይሎች ከእስር ተፈተዋል፤ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፌደራል መንግስት ጋር በመነጋገር የታሰሩ የጉህዴን አመራሮች የካቲት 17 እንዲፈቱ አድርጓል። ከነዚህ ውስጥ የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ የሚገኙበት ሲሆን ከ20 ቀናት ገደማ በፊት ነው የተፈቱት። ባለፉት 2 ሳምንታት 400 ገደማ የፓርቲው አባላትም ከእስር መፈታታቸውን ጉህዴን አረጋግጧል።
👉 የተፈናቀሉ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንዲመለሱ እና ለሰብዓዊ እርዳታ ተደራሽ እንዲሆኑ ጠይቀው፤ አካባቢው ሰላም ከሆነ የክልሉ መንግስት ነዋሪዎችን ወደ ቀያቸው ለመመለስና በየትኛውም ቦታ እርዳታ ማቅረብ እንደሚችል ለታጣቂዎቹ ገልጿል።
👉 በካማሺ እና መተከል ዞን ያሉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት እንዲሁም የሌሎች ክልል ልዩ ኃይሎች አካባቢዎቹን ለቅቀው እንዲወጡ ጠይቀው፤ ክልሉ የተጠቀሱት የጸጥታ ኃይሎች እንዲወጡ በቅድሚያ ሰላም መምጣት እንዳለበት ከብዙ ውይይት በኋላ ስምምነት ላይ መደረሱን አመልክቷል፤ ጉህዴን ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም አይነት ውይይት አላደረግንም ብሏል፤ ከዕርቁ በኋላ በጉዳዩ ላይ ወይይት እንደሚደረግበት ገልጿል።
🔹 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ታጥቀው በየጫካው ያሉ ታጣቂዎች፤ ትጥቃቸውን ፈትተው የተሃድሶ ስልጠና የሚያገኙበት ሁኔታ ላይ መምከር ከዕርቁ በኋላ የሚኖረው አንዱ ዋነኛ ጉዳይ ነው ብሏል። ጉህዴን በተመሳሳይ ከዕርቁ በኋላ ከክልሉ መንግስት ጋር የሚደረግ ውይይት አለ ያለ ሲሆን ታጣቂዎቹ ትጥቅ መቼ እንደሚፈቱ የሚወሰነው በውይይት ነው ብሏል። እስከዛ ግን ታጥቀው እንደሚቆዩ ገልጿል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አብን የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዶ/ር በለጠ ሞላን በድጋሚ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ። አቶ መልካሙ ሹምዬ ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል። የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጣሂር መሐመድ ፤ ፓርቲው ለ3 ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ሲያካሂድ እንደቆየና የሥራ አስፈፃሚ አባላቱን በአዲስ በማደራጀት ማጠናቀቁን ገልጸዋል። በዚህም መሠረት፦ 👉 ዶ/ር…
" አብን በጠቅላላ ጉባዔው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደመረጠ ተደርጎ የሚሰራጭ መረጃ ሐሰት ነው " - አቶ ጣሂር መሐመድ
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ባለፉት ሁለት ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን አካሂዷል።
ዛሬ ደግሞ ሦስተኛ ድርጅታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን እያካሄደ ነው።
የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጣሂር መሐመድ ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሰጡት ቃል ፤ ትናንት በነበረው #የማዕከላዊ_ኮሚቴ_ስብሰባ በተወሰነ መልኩ የአመራር ሽግሽግ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች እልባት መሰጠቱን ገልፀዋል።
" ነገር ግን የፓርቲውን መመሪያ እና ደንብ በውል ካለመረዳት #በጠቅላላ_ጉባዔው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደተመረጠ የሚናፈሰው ወሬ ትክክል አይደለም " ሲሉ አብራርተዋል።
አቶ ጣሂር ጠቅላላ ጉባዔው የሚመርጠው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ነው ያሉ ሲሆን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የአገልግሎት ዘመን የሚጠናቀቅበት ጊዜ ደግሞ አልደረሰም ብለዋል።
በዚህም በማዕከላዊ ኮሚቴ የተላለፈ ውሳኔ በጠቅላላ ጉባዔ እንደተሻረ ተደርጎ በተለይ በማኅበራዊ የመገናኛ አውታር የሚንሸራሸረው መረጃ መሰረተ ቢስ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ አቶ ጣሂር መሐመድ በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ በጠቅላላ ጉባዔው ምንም አይነት የምርጫ ሂደት እየተደረገ እንዳልሆነ ከሰዓታት በፊት ገልፀዋል።
" ትላንት በተጠናቀቀው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባችን የአመራር መተካካቶችን አድርገናል። " ያሉት አቶ ጣሂር " አሁን ላይ የጠቅላላ ጉባዔያችን በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል " ብለዋል።
@tikvahethiopia
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ባለፉት ሁለት ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን አካሂዷል።
ዛሬ ደግሞ ሦስተኛ ድርጅታዊ ጠቅላላ ጉባዔውን እያካሄደ ነው።
የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ጣሂር መሐመድ ለአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በሰጡት ቃል ፤ ትናንት በነበረው #የማዕከላዊ_ኮሚቴ_ስብሰባ በተወሰነ መልኩ የአመራር ሽግሽግ ለሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች እልባት መሰጠቱን ገልፀዋል።
" ነገር ግን የፓርቲውን መመሪያ እና ደንብ በውል ካለመረዳት #በጠቅላላ_ጉባዔው የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ እንደተመረጠ የሚናፈሰው ወሬ ትክክል አይደለም " ሲሉ አብራርተዋል።
አቶ ጣሂር ጠቅላላ ጉባዔው የሚመርጠው የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ነው ያሉ ሲሆን የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት የአገልግሎት ዘመን የሚጠናቀቅበት ጊዜ ደግሞ አልደረሰም ብለዋል።
በዚህም በማዕከላዊ ኮሚቴ የተላለፈ ውሳኔ በጠቅላላ ጉባዔ እንደተሻረ ተደርጎ በተለይ በማኅበራዊ የመገናኛ አውታር የሚንሸራሸረው መረጃ መሰረተ ቢስ ነው ብለዋል።
በሌላ በኩል ፤ አቶ ጣሂር መሐመድ በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ በጠቅላላ ጉባዔው ምንም አይነት የምርጫ ሂደት እየተደረገ እንዳልሆነ ከሰዓታት በፊት ገልፀዋል።
" ትላንት በተጠናቀቀው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባችን የአመራር መተካካቶችን አድርገናል። " ያሉት አቶ ጣሂር " አሁን ላይ የጠቅላላ ጉባዔያችን በተሳካ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል " ብለዋል።
@tikvahethiopia