#MoE
በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱና ባስመዘገቡት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችላቸው ተማሪዎች ከዚህ ቀደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳቸው ይታወቃል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች የሚከተሉትን ማስተካከያዎች እንዲያደርጉ ጠይቋል ፦
1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም ድረስ በ Portal.neaea.gov.et ገብተው እንዲያስተካክሉ የተባለ ሲሆን ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
2ኛ. በጤና እና ልዩ ልዩ ጉዳዮች ምደባ በልዩ ሁኔታ እንዲታይላቸው የሚያመለክቱ ተማሪዎች መረጃቸውን እስከ መጋቢት 11/2014 ዓ.ም ድረስ በ https://student.ethernet.edu.et/ በኩል እንዲልኩ ማሳሰቢያ የተላለፈ ሲሆን በአካል የሚቀርብ ምንም ዓይነት ማስረጃ ሚኒስቴሩ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
(ትምህርት ሚኒስቴር)
@tikvahethiopia
በ2013 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱና ባስመዘገቡት ውጤት መሠረት በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ምደባ ማግኘት የሚያስችላቸው ተማሪዎች ከዚህ ቀደም የተቋም እና የመስክ ምርጫ ማካሄዳቸው ይታወቃል።
ትምህርት ሚኒስቴር በቅርቡ ምደባ የሚያደርግ መሆኑን ገልጾ ተማሪዎች የሚከተሉትን ማስተካከያዎች እንዲያደርጉ ጠይቋል ፦
1ኛ. የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ አቅም፣ የተማሪዎች አማካይ ውጤት አፈፃፀም፣ ወዘተ ከግንዛቤ በማስገባት የዩኒቨርሲቲ ምርጫቸውን እስከ መጋቢት 13/2014 ዓ.ም ድረስ በ Portal.neaea.gov.et ገብተው እንዲያስተካክሉ የተባለ ሲሆን ከምደባ በኋላ የሚቀርብ ምንም አይነት የምደባ ለውጥ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
2ኛ. በጤና እና ልዩ ልዩ ጉዳዮች ምደባ በልዩ ሁኔታ እንዲታይላቸው የሚያመለክቱ ተማሪዎች መረጃቸውን እስከ መጋቢት 11/2014 ዓ.ም ድረስ በ https://student.ethernet.edu.et/ በኩል እንዲልኩ ማሳሰቢያ የተላለፈ ሲሆን በአካል የሚቀርብ ምንም ዓይነት ማስረጃ ሚኒስቴሩ የማያስተናግድ መሆኑን ገልጿል።
(ትምህርት ሚኒስቴር)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ ለተለያዩ ግለሰቦች የሙሉ አምባሳደርነት እና የአምባሳደርነት ሹመት ሰጡ። በዚህም መሠረትም፡- 1/ አቶ ተፈራ ደርበው 2/ አቶ ደሴ ዳልኬ 3/ ዶክተር ስለሺ በቀለ 4/ ጄኔራል ባጫ ደበሌ 5/ ጄኔራል ሀሰን ኢበራሂም 6/ ወ/ሮ ሽትዬ ምናለ 7/ ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ 8/ አቶ ረሻድ መሀመድ 9/ አምባሳደር ጀማል በከር 10/ አቶ ፈይሰል ኦሊይ…
#Update
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ የተሾሙ አምባሳደሮች የተመደቡባቸው ሀገራት ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
አምባሳደሮቹ የተመደቡባቸውን ሀገራት ፦
1. አምባሳደር ተፈራ ደርበው —ጃፓን
2. አምባሳደር ደሴ ዳልኬ—ደቡብ ኮሪያ
3. አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ—አሜሪካ
4. አምባሳደር ባጫ ደበሌ — ኬንያ
5. አምባሳደር ሀሰን ኢብራሂም–ግብፅ
6. አምባሳደር ዳባ ደበሌ –ሩዋንዳ
7. አምባሳደር ጀማል በከር–ፖኪሲታን
8. አምባሳደር ፈይሰል አሊይ__ኳታር
9. አምባሳደር ኢሳያስ ጎታ—ሞሮኮ
10. አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው–አውስትራሊያ
11. አምባሳደር ምህረተአብ ሙሉጌታ—ስዊዲን
12. አምባሳደር ፍቃዱ በየነ–ኤርትራ
ተቀማጭነታቸው በኢትዮጵያ ሆኖ በተለያዩ ሀገሮች የተሾሙ አምባሳደሮች ፦
13. አምባሳደር ጣፋ ቱሉ–ብራዚል
14. አምባሳደር ዶ/ር ገነት ተሾመ–ኩባ
15. አምባሳደር ሽታዬ ምናለ– ኮትዲቯር
16. እምባሳደር ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ-ኢንዶኔዥያ
17. አምባሳደር ረሻድ መሀመድ– ዝምባብዌ
በቆንስል ጅነራልነት የተመደቡ ፦
18. አምባሳደር አንተነህ ታሪኩን -ገዳሪፍ
19. አምባሳደርአክሊሉ ከበደ–ዱባይ
20. አምባሳደር ሰይድ መሐመድ-ሀርጌሳ
21. አምባሳደር አወል ወግሪስ–ባህሬን
በምክትል የሚሲዮን መሪነት፦
22. አምባሳደር አሳየ አለማየሁ–ጋና
23. አምባሳደር ኃይላይ ብርሃነ–ጀርመን
24. አምባሳደር ብዙነሽ መሠረት–ህንድ
25. አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ–ኒው ዮርክ
26. አምባሳደር ዘላለም ብርሃን–ዋሽንግተን
27. አምባሳደር ፍርቱና ዲባኮ– ቤልጅየም
28. አምባሳደር ወርቃለማሁ ደሰታ –ኬንያ
29. አምባሳደር ውብሸት ደምሴ–እንግሊዝ
30. አምባሳደር ሙሉጌታ ከሊል–ፓኪስታን
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ የተሾሙ አምባሳደሮች የተመደቡባቸው ሀገራት ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
አምባሳደሮቹ የተመደቡባቸውን ሀገራት ፦
1. አምባሳደር ተፈራ ደርበው —ጃፓን
2. አምባሳደር ደሴ ዳልኬ—ደቡብ ኮሪያ
3. አምባሳደር ዶ/ር ስለሺ በቀለ—አሜሪካ
4. አምባሳደር ባጫ ደበሌ — ኬንያ
5. አምባሳደር ሀሰን ኢብራሂም–ግብፅ
6. አምባሳደር ዳባ ደበሌ –ሩዋንዳ
7. አምባሳደር ጀማል በከር–ፖኪሲታን
8. አምባሳደር ፈይሰል አሊይ__ኳታር
9. አምባሳደር ኢሳያስ ጎታ—ሞሮኮ
10. አምባሳደር ፀጋአብ ክበበው–አውስትራሊያ
11. አምባሳደር ምህረተአብ ሙሉጌታ—ስዊዲን
12. አምባሳደር ፍቃዱ በየነ–ኤርትራ
ተቀማጭነታቸው በኢትዮጵያ ሆኖ በተለያዩ ሀገሮች የተሾሙ አምባሳደሮች ፦
13. አምባሳደር ጣፋ ቱሉ–ብራዚል
14. አምባሳደር ዶ/ር ገነት ተሾመ–ኩባ
15. አምባሳደር ሽታዬ ምናለ– ኮትዲቯር
16. እምባሳደር ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ-ኢንዶኔዥያ
17. አምባሳደር ረሻድ መሀመድ– ዝምባብዌ
በቆንስል ጅነራልነት የተመደቡ ፦
18. አምባሳደር አንተነህ ታሪኩን -ገዳሪፍ
19. አምባሳደርአክሊሉ ከበደ–ዱባይ
20. አምባሳደር ሰይድ መሐመድ-ሀርጌሳ
21. አምባሳደር አወል ወግሪስ–ባህሬን
በምክትል የሚሲዮን መሪነት፦
22. አምባሳደር አሳየ አለማየሁ–ጋና
23. አምባሳደር ኃይላይ ብርሃነ–ጀርመን
24. አምባሳደር ብዙነሽ መሠረት–ህንድ
25. አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ–ኒው ዮርክ
26. አምባሳደር ዘላለም ብርሃን–ዋሽንግተን
27. አምባሳደር ፍርቱና ዲባኮ– ቤልጅየም
28. አምባሳደር ወርቃለማሁ ደሰታ –ኬንያ
29. አምባሳደር ውብሸት ደምሴ–እንግሊዝ
30. አምባሳደር ሙሉጌታ ከሊል–ፓኪስታን
@tikvahethiopia
#Bank_of_Abyssinia
የባንካችንን የቴሌግራም ቦት በመጠቀም በአቅራቢያዎ የሚገኙትን የአቢሲንያ ባንክ ኤ.ቲ.ኤም ማሽኖች እና የቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎች ያለምንም መጉላላት በቀላሉ ያግኙ!
የቴሌግራም ቦት ሊንክ : https://t.iss.one/BOA_ATM_bot
የባንካችንን የቴሌግራም ቦት በመጠቀም በአቅራቢያዎ የሚገኙትን የአቢሲንያ ባንክ ኤ.ቲ.ኤም ማሽኖች እና የቨርቹዋል ባንኪንግ ማዕከሎች ያለምንም መጉላላት በቀላሉ ያግኙ!
የቴሌግራም ቦት ሊንክ : https://t.iss.one/BOA_ATM_bot
#WHO
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በላይ የሰዎች ጤና አሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኘው በትግራይ ክልል ውስጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ይህን ያሉት ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
ዶ/ር ቴድሮስ ፥ " "በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በላይ በትግራይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ጤና በአደጋ ላይ ይገኛል" ብለዋል።
"አዎ እኔ ከትግራይ ነኝ። ይህ ቀውስ እኔን፣ ቤተሰቤን እና ጓደኞቼን በግል ይጎዳል። ግን እንደ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር፤ በስጋት ውስጥ ያለን ጤና የመጠበቅ እና የመንከባከብ ኃላፊነት አለብኝ። በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በላይ በትግራይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ጤና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል" ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ፤ በክልሉ ላለው ሰብዓዊ ቀውስ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥታት ይፋዊ ያልሆነ እቀባን ተጠያቂ አድርገዋል።
በተጨማሪ በዚሁ መግለጫቸው ላይ ድርጅታቸው 95 ሺ ሜትሪ ቶን መድኃኒት ወደ ትግራይ ለማድረስ ፍቃድ አለማግኘቱን ተናግረዋል። ላለፉት 500 ቀናት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግሥታት በትግራይ ያሉ 6 ሚሊዮን ሰዎችን ይፋዊ ባልሆነ እቀባ ሥር አድርገዋል ብለዋል።
ዶ/ር ቴድሮስ ላቀረቡት ክስ የኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ የሰጠ ሲሆን ክስ መሰረተ ቢስ ነው ብሎታል።
ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም "መድኃኒቶችን ወደትግራይ ክልል እንዳናስገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ፈቃድ አልሰጠንም" በሚል ያቀረበው ክስ መሰረተ ቢስ ነው ሲል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ፤ ማንም የከለከላቸው የለም ፤ ቀድሞ ፈቃድ እንደተሰጣቸው እየታወቀ መዋሸቱ አግባብ አይደለም ብሏል።
ያንብቡ : telegra.ph/Tigray-03-17
@tikvahethiopia
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በላይ የሰዎች ጤና አሳሳቢ ደረጃ ላይ የሚገኘው በትግራይ ክልል ውስጥ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ይህን ያሉት ትናንት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው።
ዶ/ር ቴድሮስ ፥ " "በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በላይ በትግራይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ጤና በአደጋ ላይ ይገኛል" ብለዋል።
"አዎ እኔ ከትግራይ ነኝ። ይህ ቀውስ እኔን፣ ቤተሰቤን እና ጓደኞቼን በግል ይጎዳል። ግን እንደ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር፤ በስጋት ውስጥ ያለን ጤና የመጠበቅ እና የመንከባከብ ኃላፊነት አለብኝ። በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል በላይ በትግራይ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎችን ጤና አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል" ብለዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ፤ በክልሉ ላለው ሰብዓዊ ቀውስ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ መንግሥታት ይፋዊ ያልሆነ እቀባን ተጠያቂ አድርገዋል።
በተጨማሪ በዚሁ መግለጫቸው ላይ ድርጅታቸው 95 ሺ ሜትሪ ቶን መድኃኒት ወደ ትግራይ ለማድረስ ፍቃድ አለማግኘቱን ተናግረዋል። ላለፉት 500 ቀናት የኢትዮጵያ እና ኤርትራ መንግሥታት በትግራይ ያሉ 6 ሚሊዮን ሰዎችን ይፋዊ ባልሆነ እቀባ ሥር አድርገዋል ብለዋል።
ዶ/ር ቴድሮስ ላቀረቡት ክስ የኢትዮጵያ መንግስት ምላሽ የሰጠ ሲሆን ክስ መሰረተ ቢስ ነው ብሎታል።
ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም "መድኃኒቶችን ወደትግራይ ክልል እንዳናስገባ የኢትዮጵያ መንግሥት ፈቃድ አልሰጠንም" በሚል ያቀረበው ክስ መሰረተ ቢስ ነው ሲል የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።
ኮሚሽኑ ፤ ማንም የከለከላቸው የለም ፤ ቀድሞ ፈቃድ እንደተሰጣቸው እየታወቀ መዋሸቱ አግባብ አይደለም ብሏል።
ያንብቡ : telegra.ph/Tigray-03-17
@tikvahethiopia
#Worebabo📍
በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 609 የብሬን ጥይትና ሌሎችን ህገ ወጥ ቁሳቁሶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረባቦ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ፖሊስ ፤ በወረባቦ ወረዳ በቀን 05/7/2014 ህገ ወጥ መሳሪያዎችና እቃዎች ጭኖ ከጭፉራ አቅጣጫ ወደ ሃይቅ ዋናውን መንገድ ይዞ ሲመጣ የነበረ " ኮድ 3 B38052 AA " የሆነ የጭነት አይሱዙ ቢሲቲማ ከተማ ኬላን በመጣስ ለማምለጥ የሞከረ ቢሆንም የጸጥታ ሃይሎች ባደረጉት ክትትል በ02 ቀበሌ ሃራ መገጠያ አካባቢ ከሌቱ 10:00 አካቢቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስረድቷል።
መኪናው በቁጥጥር ውስጥ ሲውል ፦
👉 39 ካርቶን ጎልዴን ሲጋራ፥
👉 33 ካርቶን የሺሻ አፕል፥
👉 305 የክላሽ ጥይት፥
👉 609 የብሬን ጥይት ፥
👉 10 የቱርክ ጥይት፥
👉 22 የUNHCR የእርዳታ ኬንዳ እና 11 ብርድልሶች በጸጥታ አካሉ ተይዟል ተብሏል።
የመኪና አሽከርካሪ የተሰወረ ሲሆን 3 ተጠርጣሪዎችና መኪናው በቁጥጥር ስር መዋሉም የወረባቦ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።
@tikvahethiopia
በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 609 የብሬን ጥይትና ሌሎችን ህገ ወጥ ቁሳቁሶችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የወረባቦ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታወቀ።
ፖሊስ ፤ በወረባቦ ወረዳ በቀን 05/7/2014 ህገ ወጥ መሳሪያዎችና እቃዎች ጭኖ ከጭፉራ አቅጣጫ ወደ ሃይቅ ዋናውን መንገድ ይዞ ሲመጣ የነበረ " ኮድ 3 B38052 AA " የሆነ የጭነት አይሱዙ ቢሲቲማ ከተማ ኬላን በመጣስ ለማምለጥ የሞከረ ቢሆንም የጸጥታ ሃይሎች ባደረጉት ክትትል በ02 ቀበሌ ሃራ መገጠያ አካባቢ ከሌቱ 10:00 አካቢቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን አስረድቷል።
መኪናው በቁጥጥር ውስጥ ሲውል ፦
👉 39 ካርቶን ጎልዴን ሲጋራ፥
👉 33 ካርቶን የሺሻ አፕል፥
👉 305 የክላሽ ጥይት፥
👉 609 የብሬን ጥይት ፥
👉 10 የቱርክ ጥይት፥
👉 22 የUNHCR የእርዳታ ኬንዳ እና 11 ብርድልሶች በጸጥታ አካሉ ተይዟል ተብሏል።
የመኪና አሽከርካሪ የተሰወረ ሲሆን 3 ተጠርጣሪዎችና መኪናው በቁጥጥር ስር መዋሉም የወረባቦ ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይፈለጋል የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከላይ በምስሉ ላይ ያለውን ግለሰብ በወንጀል እንደሚፈልገው አሳውቋል። ግለሰቡ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎችን በማውጣትና በመጠቀም ከተለያዩ ባንኮች ብር አጭበርብሮ በማውጣት ወንጀል እንደሚፈለግ ነው ፖሊስ የገለፀው። ፌዴራል ፖሊስ ተጠርጣሪውን የሚመለከት ማንኛውም መረጃ ካልዎት እንዲያሳውቁ ጥሪ ያቀረበ ሰሆን ህብረተሰቡ የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግ ጠይቋል። ስልክ…
#ተይዟል
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከጥቂት ቀናት በፊት በጥብቅ ሲፈልገው የነበረ ግለሰብ መያዙን አሳውቋል።
ፖሊስ የካቲት 29 ቀን 2014 ዓ/ም ባወጣው ማስታወቂያ ከላይ በምስሉ ላይ የሚታየውን ግለሰብ በወንጀል እንደሚፈልገው ገልጾ ነበር።
ግለሰቡ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎችን በማውጣትና በመጠቀም ከተለያዩ ባንኮች ብር አጭበርብሮ በማውጣት ወንጀል እንደሚፈለግ ነበር ፖሊስ ገልጾ የነበረው።
ዛሬ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ እንዳሳወቀው ግለሰቡ በተለያዩ ስሞች በመጠቀም ለመሰወር ቢሞክርም በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ከጥቂት ቀናት በፊት በጥብቅ ሲፈልገው የነበረ ግለሰብ መያዙን አሳውቋል።
ፖሊስ የካቲት 29 ቀን 2014 ዓ/ም ባወጣው ማስታወቂያ ከላይ በምስሉ ላይ የሚታየውን ግለሰብ በወንጀል እንደሚፈልገው ገልጾ ነበር።
ግለሰቡ የተለያዩ ሀሰተኛ መታወቂያዎችን በማውጣትና በመጠቀም ከተለያዩ ባንኮች ብር አጭበርብሮ በማውጣት ወንጀል እንደሚፈለግ ነበር ፖሊስ ገልጾ የነበረው።
ዛሬ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ እንዳሳወቀው ግለሰቡ በተለያዩ ስሞች በመጠቀም ለመሰወር ቢሞክርም በህብረተሰቡ ጥቆማ በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል።
@tikvahethiopia
#Tigray
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ከትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ ጋር በተያያዘ መግለጫ አውጥቷል።
ሚኒስቴሩ በመግለጫው የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት የትግራይ ክልልን ሰብአዊ ችግር ለመፍታት በአፋር መስመር የሰብአዊ ድጋፍ የሚያደርሱ ተሽከርካሪዎች በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲንቀሳቀሱ በማመቻቸት ገንቢ የሆነ ሚና ሲጫወት መቆየቱን እና አሁንም ሚናውን መቀጠሉን ገልጿል።
በዚህም መሰረት ዛሬ መጋቢት 17 (እኤአ) 20 የጭነት ተሽከርካሪዎች ምግብ እና 3 ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ከሰመራ ወደ መቐለ መንቀሳቀስ ጀምረዋል ሲል አሳውቋል።
የሰብዓዊ ዕርዳታውን ከፍ ለማድረግ እና የክልሉን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት በየቀኑ ወደ ትግራይ የሚያቀኑት የጭነት ተሽከርካሪዎች ቁጥር 40 ለማድረስ እንደሚሰራ አመልክቷል።
በተጨማሪም 17 አጋሮች መድሃኒትን (ክትባትን ጨምሮ) የህክምና ቁሳቁሶችን እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ወደ ትግራይ ክልል እንዲያስገቡ ፍቃድ አግኝተዋል ብሏል።
ሚኒስቴሩ በመግለጫው 11 አጋሮች 275 ሺ 192 ኪ.ግ የሚመዝኑ የህክምና ግብአቶችን በአየር በረራ ማድረሳቸውን ገልጿል።
ሚኒስቴሩ በአፋር ክልል በድጋሚ በተፈፀመው ጥቃት ከ700,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው እና በአባአላ በኩል ወደ ትግራይ የሚወስደው የሰብአዊ እርዳታ መስመር እንዲዘጋ ማድረጉን አመልክቷል። ጥቃቱ በአፋር ክልል ቂሊቤቲ ረሱ ዞን ወደ 5 ወረዳዎች ከፍ ብሎ ከ300,000 በላይ ሰዎችን እንዲፈናቀሉ ማደረጉን ገልጿል።
ከሰመራ 38 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሰርዶ 43 ምግብ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ቆመው እንደሚገኙም ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
ሆኖም ግን ዛሬ ከተደረጉት ጥብቅ ጥረቶችና ውሳኔዎች በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ያለውን የሰብአዊ ችግር ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ከትግራይ የሰብዓዊ ድጋፍ ጋር በተያያዘ መግለጫ አውጥቷል።
ሚኒስቴሩ በመግለጫው የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት የትግራይ ክልልን ሰብአዊ ችግር ለመፍታት በአፋር መስመር የሰብአዊ ድጋፍ የሚያደርሱ ተሽከርካሪዎች በተቀላጠፈ ሁኔታ እንዲንቀሳቀሱ በማመቻቸት ገንቢ የሆነ ሚና ሲጫወት መቆየቱን እና አሁንም ሚናውን መቀጠሉን ገልጿል።
በዚህም መሰረት ዛሬ መጋቢት 17 (እኤአ) 20 የጭነት ተሽከርካሪዎች ምግብ እና 3 ነዳጅ ጫኝ ተሽከርካሪዎች ከሰመራ ወደ መቐለ መንቀሳቀስ ጀምረዋል ሲል አሳውቋል።
የሰብዓዊ ዕርዳታውን ከፍ ለማድረግ እና የክልሉን መሰረታዊ ፍላጎቶች ለማሟላት በየቀኑ ወደ ትግራይ የሚያቀኑት የጭነት ተሽከርካሪዎች ቁጥር 40 ለማድረስ እንደሚሰራ አመልክቷል።
በተጨማሪም 17 አጋሮች መድሃኒትን (ክትባትን ጨምሮ) የህክምና ቁሳቁሶችን እና የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦትን ወደ ትግራይ ክልል እንዲያስገቡ ፍቃድ አግኝተዋል ብሏል።
ሚኒስቴሩ በመግለጫው 11 አጋሮች 275 ሺ 192 ኪ.ግ የሚመዝኑ የህክምና ግብአቶችን በአየር በረራ ማድረሳቸውን ገልጿል።
ሚኒስቴሩ በአፋር ክልል በድጋሚ በተፈፀመው ጥቃት ከ700,000 በላይ ሰዎች መፈናቀላቸው እና በአባአላ በኩል ወደ ትግራይ የሚወስደው የሰብአዊ እርዳታ መስመር እንዲዘጋ ማድረጉን አመልክቷል። ጥቃቱ በአፋር ክልል ቂሊቤቲ ረሱ ዞን ወደ 5 ወረዳዎች ከፍ ብሎ ከ300,000 በላይ ሰዎችን እንዲፈናቀሉ ማደረጉን ገልጿል።
ከሰመራ 38 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ሰርዶ 43 ምግብ የጫኑ ተሽከርካሪዎች ቆመው እንደሚገኙም ሚኒስቴሩ አመልክቷል።
ሆኖም ግን ዛሬ ከተደረጉት ጥብቅ ጥረቶችና ውሳኔዎች በተጨማሪ የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ያለውን የሰብአዊ ችግር ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ገልጿል።
@tikvahethiopia
#Update
አሜሪካ የሶማሊያን 'የዲሞክራሲ ሂደት አደናቀፉ' ባለቻቸው ተጨማሪ ሶማሊያውያን ላይ የቪዛ ዕገዳ ጥላለች።
ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቷ አማከኝነት ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንክን ትላንት ባወጡት መግለጫ የሶማሊያ መንግሥት የምክር ቤታዊ ምርጫ ሂደቱን ማክሰኞ እአአ መጋቢት 15 /2022 ሊያጠናቅቅ ራሱ ያወጣውን ቀነ ገደብ ተግባራዊ ሳያደርግ መቅረቱን ተከትሎ የዲሞክራሲ ሂደቱን በማደናቀፍ ተጠያቂ ወይም ተመሳጣሪ ናቸው በተባሉ ተጨማሪ ሰዎች ላይ አሜሪካ የቪዛ ማዕቀብ እርምጃ መውሰዷን አሳውቀዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ምንም እንኳን ባለፉት ጥቂት ሳምንታት አበረታች እርምጃ የታየ ቢሆንም አሁንም ያልተያዙ ከሠላሳ ስድስት በላይ ክፍት የምክር ቤት መቀመጫዎች እንዳሉ አመልክተዋል።
የምርጫው ሂደት መዛባት ላይ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊ ተቋማትን የሚደግፉ እና ሂደቱ ግልጽ እንዲሆን የሚጥሩ ጋዜጠኞች እና ተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የወከባ የእስር እና የጥቃት ዒላማ እየተደረጉ መሆኑን የሚያመለክቱ ተዓማኒ ሪፖርቶች መውጣታቸውን ቀጥለዋል ሲሉም አንቶኒ ብሊንከን መግለፃቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
አሜሪካ የሶማሊያን 'የዲሞክራሲ ሂደት አደናቀፉ' ባለቻቸው ተጨማሪ ሶማሊያውያን ላይ የቪዛ ዕገዳ ጥላለች።
ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቷ አማከኝነት ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንክን ትላንት ባወጡት መግለጫ የሶማሊያ መንግሥት የምክር ቤታዊ ምርጫ ሂደቱን ማክሰኞ እአአ መጋቢት 15 /2022 ሊያጠናቅቅ ራሱ ያወጣውን ቀነ ገደብ ተግባራዊ ሳያደርግ መቅረቱን ተከትሎ የዲሞክራሲ ሂደቱን በማደናቀፍ ተጠያቂ ወይም ተመሳጣሪ ናቸው በተባሉ ተጨማሪ ሰዎች ላይ አሜሪካ የቪዛ ማዕቀብ እርምጃ መውሰዷን አሳውቀዋል።
አንቶኒ ብሊንከን ምንም እንኳን ባለፉት ጥቂት ሳምንታት አበረታች እርምጃ የታየ ቢሆንም አሁንም ያልተያዙ ከሠላሳ ስድስት በላይ ክፍት የምክር ቤት መቀመጫዎች እንዳሉ አመልክተዋል።
የምርጫው ሂደት መዛባት ላይ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊ ተቋማትን የሚደግፉ እና ሂደቱ ግልጽ እንዲሆን የሚጥሩ ጋዜጠኞች እና ተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የወከባ የእስር እና የጥቃት ዒላማ እየተደረጉ መሆኑን የሚያመለክቱ ተዓማኒ ሪፖርቶች መውጣታቸውን ቀጥለዋል ሲሉም አንቶኒ ብሊንከን መግለፃቸውን ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ፎቶ : ኩሪፍቱ ሪዞርትስ አዋሽ ፓርክ ውስጥ ያስገነባውን አዲስ ቅርንጫፍ ከትላንትና በስቲያ አስመርቋል።
የአዋሽ ፏፏቴዎች ላይ የተገነባው ይህ የኩሪፍቱ ሪዞርት ለፓርኩ ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
የኩሪፍቱ ሪዞርትስ ባለቤት አቶ ታዲዮስ ጌታቸው ፤ አዲሱ የአዋሽ ሪዞርታቸው እንደከዚህ ቀደሞቹ ሁሉ በአከባቢው ያሉ ተፈጥሯዊ የግንባታ ቁሶችን መጠቀሙን አስረድተውናል።
የግንባታ ሂደቱ 11 ወራት መፍጀቱንም ጠቁመዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በሰው ኃይል ደረጃ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ በአከባቢው ያሉ አቅሙ ያላቸውን ዜጎች መርጦ በማሰልጠን ወደ ሥራ ማስገባታቸውን አቶ ታዲዮስ ገልጸውልናል።
ኩሪፍቱ በስሩ አሁን ላይ ሦስት ሺ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል።
@tikvahethiopia
የአዋሽ ፏፏቴዎች ላይ የተገነባው ይህ የኩሪፍቱ ሪዞርት ለፓርኩ ተጨማሪ የቱሪስት መዳረሻ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
የኩሪፍቱ ሪዞርትስ ባለቤት አቶ ታዲዮስ ጌታቸው ፤ አዲሱ የአዋሽ ሪዞርታቸው እንደከዚህ ቀደሞቹ ሁሉ በአከባቢው ያሉ ተፈጥሯዊ የግንባታ ቁሶችን መጠቀሙን አስረድተውናል።
የግንባታ ሂደቱ 11 ወራት መፍጀቱንም ጠቁመዋል።
ከዚህም በተጨማሪ በሰው ኃይል ደረጃ ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ በአከባቢው ያሉ አቅሙ ያላቸውን ዜጎች መርጦ በማሰልጠን ወደ ሥራ ማስገባታቸውን አቶ ታዲዮስ ገልጸውልናል።
ኩሪፍቱ በስሩ አሁን ላይ ሦስት ሺ ለሚሆኑ ዜጎች የሥራ ዕድል መፍጠር ችሏል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከዓመት በኋላ ከቤታቸው ውጪ መታየታቸው ተሰምቷል። አቶ ዳውድ ዛሬ ረፋድ ላይ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር ስብሰባ ለመቀመጥ ወደ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አምርተው እንደነበር ቢቢሲ ዘግቧል። ምርጫ ቦርድ ከቀናት በፊት የኦነግ የረጅም ጊዜ ሊቀ መንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ አንድ ዓመት ለሚጠጋ ጊዜ ከቤታቸው እንዳይወጡ ተከልክለው በቁም…
#OLF
የኦነግ ከፍተኛ ከፍተኛ አመራር አባል እና የሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር ሽጉጥ ገለታ ለዶቼ ቨለ የተናገሩት ፦
" ... የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከአንድ ዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ በመኖሪያ ቤታቸው ታግተው ሰው ሄዶ ሊጠይቃቸው እንዲሁም እሳቸውም ወጥተው ሰው ማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ነበሩ።
ከረጅም ጊዜ በኋላ ይህንኑን የተረዳው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማጣራት አድርጎ ነገሩ ትክክል አይደለም በማለት መንግስት እንዲፈታቸው መጠየቁ የሚታወስ ነው፡፡
ይህንኑን ሂደት ተከትሎ ይመስላል ከቀናት በፊት ሊቀመንበሩ የካቲት 30 ቀን 2014 ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚያ ከሚኖሩበት ጊቢው ወጥተው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመገኘት ከቦርዱ ሃላፊዎች ጋር የኦነግ ጽ/ቤት ስለመዘጋቱ፣ በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲው አመራሮች ለደህንነታቸው አስጊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን እና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
በመሆኑም ከቀደመው ሁኔታ በተሻለ መንቀሳቀስ ጀምረዋል፡፡ "
@tikvahethiopia
የኦነግ ከፍተኛ ከፍተኛ አመራር አባል እና የሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር ሽጉጥ ገለታ ለዶቼ ቨለ የተናገሩት ፦
" ... የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከአንድ ዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ በመኖሪያ ቤታቸው ታግተው ሰው ሄዶ ሊጠይቃቸው እንዲሁም እሳቸውም ወጥተው ሰው ማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ነበሩ።
ከረጅም ጊዜ በኋላ ይህንኑን የተረዳው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማጣራት አድርጎ ነገሩ ትክክል አይደለም በማለት መንግስት እንዲፈታቸው መጠየቁ የሚታወስ ነው፡፡
ይህንኑን ሂደት ተከትሎ ይመስላል ከቀናት በፊት ሊቀመንበሩ የካቲት 30 ቀን 2014 ለመጀመሪያ ጊዜ ከዚያ ከሚኖሩበት ጊቢው ወጥተው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመገኘት ከቦርዱ ሃላፊዎች ጋር የኦነግ ጽ/ቤት ስለመዘጋቱ፣ በእስር ላይ የሚገኙ የፓርቲው አመራሮች ለደህንነታቸው አስጊ በሆነ ሁኔታ ውስጥ መሆናቸውን እና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይተዋል፡፡
በመሆኑም ከቀደመው ሁኔታ በተሻለ መንቀሳቀስ ጀምረዋል፡፡ "
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#OLF የኦነግ ከፍተኛ ከፍተኛ አመራር አባል እና የሊቀመንበሩ አቶ ዳውድ ኢብሳ ከፍተኛ አማካሪ ዶ/ር ሽጉጥ ገለታ ለዶቼ ቨለ የተናገሩት ፦ " ... የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ ከአንድ ዓመት በላይ ለሚሆን ጊዜ በመኖሪያ ቤታቸው ታግተው ሰው ሄዶ ሊጠይቃቸው እንዲሁም እሳቸውም ወጥተው ሰው ማግኘት በማይችሉበት ሁኔታ ውስጥ ነበሩ። ከረጅም ጊዜ በኋላ ይህንኑን የተረዳው የኢትዮጵያ…
#OLF
አቶ ዳውድ ኢብሳ አሁን ላይ ያገኙት የመንቀሳቀስ ነጻነት ወደ ፈለጉበት መሄድ የሚያስችላቸው እና በስልክ የፈለጉትን ሰው ደውለው የሚገናኙበት ነው ?
የዶ/ር ሽጉጥ ገለታ (የአቶ ዳውድ ከፍተኛ አማካሪ) ለዶቼ ቨለ የሰጡት ምላሽ ፦
" .... እኔ የማውቀው መንቀሳቀሳቸውን እንጂ ከዚህ በፊት የሚጠቀሙበት ስልካቸውን በመቀማታቸው ለጊዜው አግኝተናቸው ማውራት አልቻልንም፡፡
ይሁንና አስፈላጊ የሆኑ አንዳንድ ቦታዎችን ለመድረስ እድሉን እንዳገኙ ነው ለጊዜው የምናውቀው፡፡
ይሄ ለውጥ ምርጫ ቦርዱ ደብዳቤውን ከፃፈ ወዲህ ያየነው መልካም የሚባል ለውጥ ነው፡፡
ከ7 ቀናት በፊት ጀምሮ የተሻለ የመንቀሳቀስ ሁኔታ ቢኖርም ሙሉ በሙሉ በነጻነት የመሄድ ነገር አለ የሚል መደምደሚያ ግን የለንም።
" ... ለውጡ መልካም ነው፡፡ ይህ ቀጥሎ ሊቀመንበሩ ሙሉ በሙሉ ነጻ እስኮሆኑ እና በተለያዩ ህመሞች በእስር ቤት እየተሰቃዩ ያሉት እንደነ ሚካኤል ቦረን፣ ከኔሳ አያና እንዲሁም ከ አቶ ባቴ ዑርጌሣ ጋር በአንድ ስፍራ የነበሩ እንዲሁም ስንቴ ፍርድ ቤት ያሰናበተው እና ከ2 ዓመት በላይ ታስሮ የሚገኘው አብዲ ረጋሳ እና ሁሉም የኦነግ አባላትና አመራሮች ተለቀው ቢሮው ቢንቀሳቀስ ለሁሉም ሰላም መልካም ነው፡፡
የፖለቲካ አውዱንም ያሰፋል፡፡
አሁን የተመለከትነው መነሻ ይመስለናል፡፡ መቀጠል ያለበት ነው ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ሂደት ድምጻችን ላያሰሙልን የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች እና ሚዲያዎች በህዝባችን ስም ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን፡፡ "
@tikvahethiopia
አቶ ዳውድ ኢብሳ አሁን ላይ ያገኙት የመንቀሳቀስ ነጻነት ወደ ፈለጉበት መሄድ የሚያስችላቸው እና በስልክ የፈለጉትን ሰው ደውለው የሚገናኙበት ነው ?
የዶ/ር ሽጉጥ ገለታ (የአቶ ዳውድ ከፍተኛ አማካሪ) ለዶቼ ቨለ የሰጡት ምላሽ ፦
" .... እኔ የማውቀው መንቀሳቀሳቸውን እንጂ ከዚህ በፊት የሚጠቀሙበት ስልካቸውን በመቀማታቸው ለጊዜው አግኝተናቸው ማውራት አልቻልንም፡፡
ይሁንና አስፈላጊ የሆኑ አንዳንድ ቦታዎችን ለመድረስ እድሉን እንዳገኙ ነው ለጊዜው የምናውቀው፡፡
ይሄ ለውጥ ምርጫ ቦርዱ ደብዳቤውን ከፃፈ ወዲህ ያየነው መልካም የሚባል ለውጥ ነው፡፡
ከ7 ቀናት በፊት ጀምሮ የተሻለ የመንቀሳቀስ ሁኔታ ቢኖርም ሙሉ በሙሉ በነጻነት የመሄድ ነገር አለ የሚል መደምደሚያ ግን የለንም።
" ... ለውጡ መልካም ነው፡፡ ይህ ቀጥሎ ሊቀመንበሩ ሙሉ በሙሉ ነጻ እስኮሆኑ እና በተለያዩ ህመሞች በእስር ቤት እየተሰቃዩ ያሉት እንደነ ሚካኤል ቦረን፣ ከኔሳ አያና እንዲሁም ከ አቶ ባቴ ዑርጌሣ ጋር በአንድ ስፍራ የነበሩ እንዲሁም ስንቴ ፍርድ ቤት ያሰናበተው እና ከ2 ዓመት በላይ ታስሮ የሚገኘው አብዲ ረጋሳ እና ሁሉም የኦነግ አባላትና አመራሮች ተለቀው ቢሮው ቢንቀሳቀስ ለሁሉም ሰላም መልካም ነው፡፡
የፖለቲካ አውዱንም ያሰፋል፡፡
አሁን የተመለከትነው መነሻ ይመስለናል፡፡ መቀጠል ያለበት ነው ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ሂደት ድምጻችን ላያሰሙልን የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች እና ሚዲያዎች በህዝባችን ስም ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን፡፡ "
@tikvahethiopia
#ATTENTION
ከ8 ወር በላይ ወደ ቄያቸው ያልተመለሱት የገደማይቱ ተፈናቃዮች የመፍትሄ ያለ እያሉ ነው።
በገደማይቱ ሀምሌ 17 ቀን በነበረው ግጭት ምክንያት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ በርካታ ዜጎች እስካሁን ወደ ቄያቸው መመለስ አልቻሉም።
እነዚህ ዜጎች በየመጠለያው ካምፕ እና በየዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው ወራት ማለፋቸውን ገልፀውልናል።
" ዞር ብሎ የሚያየን እና የሚጠይቀን አጥተናል " ያሉት እነዚሁ ወገኖች ለ20 እና 30 ዓመታት ከኖሩበት ቀያቸው ቢፈናቀሉም አሁን ድረስ ምላሽ የሚሰጥ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በወቅቱ በርካታ ሰዎች መገደላቸውና ሴቶችም ከፍተኛ እንግልት እና ስቃይ እንደደረሰባቸው ያስታወሱት እነኚህ ወገኖች የነበራቸው ሁሉ ንብረት እንደወደመ እና ተዘርፎ በየከተማው ሲሸጥ እንደነበር አስረድተዋል።
የፌዴራል መንግስትን መፍትሄ እንዲሰጠብ ለመጠየቅ ጥረት ብናደርግም አሁን ቆዩኝ ጦርነት ነው እያለን ለወራት በየቤተክርስቲያኑ ፣ በዘመድ አዝማድ ቤት እና በየመጠለያ ጣቢያው በየሜዳው ወድቀን ቆይተናል ብለዋል።
የተፈናቀለው ሰው ቁጥር በርካታ መሆኑን የሚገልፁት እነኚሁ ወገኖች ድምፃቸው እንዲሰማላቸው ፣ ትኩረትም እንዲሰጣቸው፣ የኢትዮጵያ መንግስትም መፍትሄ ይፈልግላቸው ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከወራት በፊት ከነበረው ግጭት ጋር በተያያዘ ሁኔታው ሲከታተል እንደነበረ አስታውሶ ከዛ በኃላ ተፈናቃዮች ስለሚገኙበት ሁኔታ ወቅታዊ መረጃ እንደሚያደርሰን አሳውቋል።
ምላሹ እንደደረሰን የምንልክላችሁ ይሆናል።
@tikvahethiopia
ከ8 ወር በላይ ወደ ቄያቸው ያልተመለሱት የገደማይቱ ተፈናቃዮች የመፍትሄ ያለ እያሉ ነው።
በገደማይቱ ሀምሌ 17 ቀን በነበረው ግጭት ምክንያት ከመኖሪያቸው የተፈናቀሉ በርካታ ዜጎች እስካሁን ወደ ቄያቸው መመለስ አልቻሉም።
እነዚህ ዜጎች በየመጠለያው ካምፕ እና በየዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው ወራት ማለፋቸውን ገልፀውልናል።
" ዞር ብሎ የሚያየን እና የሚጠይቀን አጥተናል " ያሉት እነዚሁ ወገኖች ለ20 እና 30 ዓመታት ከኖሩበት ቀያቸው ቢፈናቀሉም አሁን ድረስ ምላሽ የሚሰጥ እንዳላገኙ ተናግረዋል።
በወቅቱ በርካታ ሰዎች መገደላቸውና ሴቶችም ከፍተኛ እንግልት እና ስቃይ እንደደረሰባቸው ያስታወሱት እነኚህ ወገኖች የነበራቸው ሁሉ ንብረት እንደወደመ እና ተዘርፎ በየከተማው ሲሸጥ እንደነበር አስረድተዋል።
የፌዴራል መንግስትን መፍትሄ እንዲሰጠብ ለመጠየቅ ጥረት ብናደርግም አሁን ቆዩኝ ጦርነት ነው እያለን ለወራት በየቤተክርስቲያኑ ፣ በዘመድ አዝማድ ቤት እና በየመጠለያ ጣቢያው በየሜዳው ወድቀን ቆይተናል ብለዋል።
የተፈናቀለው ሰው ቁጥር በርካታ መሆኑን የሚገልፁት እነኚሁ ወገኖች ድምፃቸው እንዲሰማላቸው ፣ ትኩረትም እንዲሰጣቸው፣ የኢትዮጵያ መንግስትም መፍትሄ ይፈልግላቸው ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከወራት በፊት ከነበረው ግጭት ጋር በተያያዘ ሁኔታው ሲከታተል እንደነበረ አስታውሶ ከዛ በኃላ ተፈናቃዮች ስለሚገኙበት ሁኔታ ወቅታዊ መረጃ እንደሚያደርሰን አሳውቋል።
ምላሹ እንደደረሰን የምንልክላችሁ ይሆናል።
@tikvahethiopia