TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59K photos
1.5K videos
211 files
4.08K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ፕሬዜዳንቱ እስክንድር ነጋ ብቻ ሲለቀቁ ሌሎቹ በሙሉ ለእስር ተዳርገዋል " - ባልደራስ ፓርቲ ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ከ25 በላይ አባላቱ እንደታሰሩ አስታወቀ። ይህን ያሳወቀው ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ ነው። ዛሬ የካቲት 26 የሚከበረውን የ " ካራማራ የድል " በዓል ለማክበር በ " ድላችን ሀውልት " የተገኘው የባልደራስ ቡድን ወደ አደባባዩ…
#Update

የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) ከተያዙበት አመራሮች እና አባላት መካከል ከፓርቲው ፕሬዜዳንት አቶ እስክንድር ነጋ በተጨማሪ ፣ አቶ ስንታሁ ቸኮል፣ ወ/ሮ ቀለብ ስዩም እና ወ/ሪይ አስካል ደምሌ ከእስር የተለቀቁ መሆኑን አሳውቋል።

ፓርቲው በአሁን ሰዓት 33 አባለቱ በእስር ላይ እንዳሉ ገልጿል።

ቢኒያም ታደሰ እና ሳሙኤል ዲሚትሪ የሚባሉ አባላቱ ሰግሞ ከሌሎቹ እስረኞች ተነጥለው ጊዮርጊስ የሚገኘው አዲስ አበባ ፖሊስ መወሰዳቸውን አመልክቷል።

በሌላ በኩል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ያሉት እስረኞች እህልና ውሃ እንዳይገባላቸው ተከልክለዋል ሲል ገልጿል። ፖሊስ ይህን ለምን እንደሚያደርግ ሲጠየቅም " ከላይ በመጣ ትዕዛዛ ነው " የሚል ምላሽ እንደሰጠው ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ ጠቅሷል።

(ባልደራስ በአሁን ሰዓት በእስር ላይ ይገኛሉ ያላቸው አባላቱ ከላይ የተዘረዘሩት ናቸው)

@tikvahethiopia
" ሩስያን አውግዙ " - አሜሪካ

አሜሪካ የአፍሪካ ሀገራት ሩሲያ በዩክሬን እያደረገች ያለውን " ወታደራዊ ተልዕኮ " እንዲያወግዙ ጥሪ አቀረበች።

አሜሪካ ፥ ምንም እንኳን የአፍሪካ ሀገራት የተመድን የውሳኔ ሃሳብ ቢደግፉም አሁንም ሌሎች ሀገራት ሩሲያን ማውገዝ አለባቸው ብላለች።

በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ኃላፊ ሞሊ ፊ ዩክሬናውያን የአፍሪካን ድጋፍ እንደሚፈልጉ አስታውቀዋል።

አሜሪካ በዓለም አቀፍ መድረክ የአፍሪካ ድምጽ አስፈላጊ መሆኑን እንደምታምን ገልፃለች።

ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ አሁን ላይ በአንድ ላይ ሆኖ ድምጹን እያሰማ መሆኑን የገለጸችው አሜሪካ፤ ይህም ሉዓላዊነትን፣ ግዛታዊ አንድነትን፣ ግጭቶችን በሰላማዊ መንገድ መፍታትን እንዲሁም የንጹሃንን ህይወት መታደግን የሚጠይቅ እንደሆነ አስታውቃለች፡፡

መረጃውን ቪኦኤን ዋቢ አድርጎ ያስነበበው አል ዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia
#BAANKII_GADAA

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለ " ገዳ ባንክ " በመስራች ባለአክሲዮኖች ጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡትን 11 የቦርድ አባላት ሹመት አጽድቋል።

በዚህም፦
1. ዶ/ር ብርሃኑ አሰፋ
2. አቶ ዋስይሁን አመኑ
3. አቶ ሐምዲኖ ሜዴሶ
4. አቶ ሀይሉ ኢፋ (የኦሮሚያ ክልል የልማት ድርጅት ተቆጣጣሪ ባለሥልጣንን በመወከል)
5. ኢ/ር አብዶ ገለቶ
6. ዶ/ር ሀሰን ሁሴን
7. አቶ ሙለታ ደበል
8. አቶ ሽፈራው ሩፌ
9. ወ/ሮ ሰሚራ አብደላ
10. አቶ አላዛር አዱላ
11. ዶ/ር ደገፋ ዱሬሳ የቦርድ አባላትነታቸው ጸድቋል።

ብሔራዊ ባንክ የቦርድ አባላቱ ሥራ መጀመር የሚችሉ መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን በተቻለ ፍጥነት በባንክ የሥራ አመራር፤ በኮርፖሬት አስተዳደር፤ በውስጥ ቁጥጥር፤ በስጋት አስተዳደር፤ በባንክ ህግ ማዕቀፍ ላይ ተገቢውን ስልጠና እንዲወስዱ አሳስቧል።

More : @tikvahethmagazine
የጋራ ግብረ ኃይሉ ማሳሰቢያ ሰጠ።

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል አንዳንድ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ቡድኖችና ግለሰቦች ሰሞኑን በሀገሪቱ በታላቅ ድምቀት በተከበሩ የአድዋ ድል በዓልን እና በዛሬው ዕለት ተከብሮ በዋለው የካራማራ ድል በዓል ላይ በመገኘት በሀገራችን ብሄር ብሄረሰቦችና በህዝብ መካከል ግጭት ለመቀስቀስ ሞክረዋል አለ።

ይህን ያለው ዛሬ ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ነው።

ግብረኃይሉ ፥ " ደከመን ሰለቸን ሳይሉ የህዝቡን ሰላምና ደህንነት ሌት ተቀን የሚጠብቁ የፀጥታ አካላትን ክብር አስፀያፊ ስድቦችን በመሳደብ ደፍረዋል " ብሏል።

ከፀጥታ ኃይሎች ጋር አላስፈላጊ ግጭት ውስጥ ለመግባት ያልፈነቀሉት ድንጋይ አልነበረም ሲል ገልጿል።

ነገር ግን የፀጥታ ኃይሎች ሁሉንም ትንኮሳዎች በትግስት በማለፍ በዓላቱ በሰላምና በድምቀት እንዲከበሩ ማድረጋቸውን ገልጿል።

ግብረ ኃይሉ ውስን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ቡድኖች እና ግለሰቦች የሚፈልጉትን በግልፅ ህግና ስርዓት ተከትለው ማድረግና ሐሳባቸውን በነፃና በዴሞክራሲያዊ መንገድ በተፈቀደላቸው ስፍራ ማራመድና መፈፀም ሲችሉ ብሄርን ከብሄር፣ ሀይማኖትን ከሀይማኖት ጋር ለማጋጨት ስራዬ ብለው ሌት ተቀን በህቡዕ እና በግልጽ ጭምር እየተንቀሳቀሱ መሆናቸውን ደርሼበታለሁ ብሏል።

እነዚህ ውስን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ቡድኖችና ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ሲል ግብረ-ኃይሉ አሳስቧል።

ማንም ከህግ በላይ ስላልሆነ ህግ ጥሰን ድርጊታችንን እንቀጥላለን የሚሉ ከሆነ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድ እንዲሁም በህግ ተጠያቂ እንደሚያደርጋቸው የጋራ ግብረኃይሉ አስጠንቅቋል።

የጋራ ግብረ ኃይሉ በመግለጫው ላይ ውስን የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ቡድኖችና ግለሰቦች ያላቸውን በስም አልገለፀም።

@tikvahethiopia
#CBE

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዚህ ቀደም በተቀመጠው ቀነ ገደብ መረጃቸውን ያላሟሉ ደንበኞቹን ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ አደረገ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያወጣውን መመሪያ ተከትሎ መረጃቸውን ያላሟሉ ደንበኞቹን ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ አግዷል።

ባንኩ የደንበኞቹን መረጃ የማደራጀት እና የማጥራት ስራ እ.ኤ.አ እስከ የካቲት 27 ቀን 2022 ድረስ መሰራቱ እና በርካታ ደንበኞቹም መረጃቸውን ወቅታዊ ማድረጋቸውን ገልጿል።

ቀሪ መረጃቸውን ወቅታዊ ያላደረጉ ደንበኞቹ ወደ ማንኛውም የባንኩ ቅርንጫፍ እስከ አርብ መጋቢት 2 ቀን 2014 ብቻ በመሄድ ሒሳባቸውን ማንቀሳቀስ የሚያስችል መረጃ እንዲሰጡ ጠይቋል።

ከመጋቢት 2 ቀን 2014 ዓ.ም በኋላ ባሉት ቀናት ማንኛውንም የባንክ አገልግሎት (የሞባይል ባንኪንግ ፣ የኢንተርኔት ባንኪንግ እንዲሁም የኤቲኤም እንዲሁም የፖስ አገልግሎት) ማግኘት አይችሉም ብሏል።

Via : @tikvahethmagazine
#UKRAINE #NATO

የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ ዛሬ በመዲናቸው ኬዬቭ ሆነው በቴሌቪዥን ለህዝባቸው ባሰሙት ንግግር ላይ የተናገሩት ፦

" ...ምዕራባውያን መሪዎች ሩሲያ አገራችንን ልትወር መሆኗን ያውቁ ነበር፤ ፑቲን ከተሞቻችንን በቦምብ እንዲደበድቡ ፈቅደዋል።

በዩክሬን ላይ ጥቃት እንደሚፈጸም እና ጉዳትም የማይቀር መሆኑን እያወቀ NATO ሆን ብሎ የዩክሬን ሰማይ ለበረራ ዝግ እንዳይሆን አድርጓል።

የNATO መሪዎች ዛሬም ከበረራ ነጻ የሆነ ቀጠና ውሳኔን ባለማሳለፋቸው ምክንያት ተጨማሪ የዩክሬን ከተሞች እና መንደሮች በቦምብ እንዲደበደቡ ፈቅደዋል።

NATO ዩክሬንን ለመከላከል እርምጃ ባለመውሰዱ በጦርነቱ ምክንያት ለሚሞቱ የአገራችን ዜጎች ሕይወት ተጠያቂ ነው። "

ለምንድነው NATO የዩክሬንን አየር ማይዘጋው ?

NATO በምድርም ሆነ በአየር ወደ ዩክሬን የመግባት ፍላጎት የለውም።

ለNATO ውሳኔ ምዕራባውያን ባለሥልጣናት እንደምክንያት የሚያስቀምጡት በዩክሬን ከበረራ ነጻ የሆነ ቀጠና ከተከለለ የNATO አውሮፕላኖች ጥሰት በሚፈጽሙ የሩሲያ ተዋጊ አውሮፕላኖች ላይ ጥቃት መሰንዘር ይችላሉ።

ይህ ደግሞ 3ኛው የዓለም ጦርነት ሊቀሰቀስ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UKRAINE #NATO የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ ዛሬ በመዲናቸው ኬዬቭ ሆነው በቴሌቪዥን ለህዝባቸው ባሰሙት ንግግር ላይ የተናገሩት ፦ " ...ምዕራባውያን መሪዎች ሩሲያ አገራችንን ልትወር መሆኗን ያውቁ ነበር፤ ፑቲን ከተሞቻችንን በቦምብ እንዲደበድቡ ፈቅደዋል። በዩክሬን ላይ ጥቃት እንደሚፈጸም እና ጉዳትም የማይቀር መሆኑን እያወቀ NATO ሆን ብሎ የዩክሬን ሰማይ ለበረራ ዝግ እንዳይሆን…
" ዩክሬን በዚሁ ከቀጠለች ሀገርነቷን ልታጣ ትችላለች " - ቭላድሚር ፑቲን

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዛሬ በነበራቸው ስብሰባ የዩክሬንን አመራሮች " አሁን እያደረጉ ያሉትን ድርጊት ማድረጋቸውን ከቀጠሉ ዩክሬን ሀገርነቷን ልታጣ ትችላለች " ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ፑቲን ፥ " አሁን ያሉት አመራሮች እየሰሩት ያለውን ስራዎች ከቀጠሉ የዩክሬን ግዛትን የወደፊት ሁኔታ አደጋ ላይ እንደሚጥሉ መረዳት አለባቸው " ያሉ ሲሆን " ይህ ከሆነ እራሳቸው ተጠያቂ ሊሆኑ ይገባል " ብለዋል።

ዛሬ በነበራቸው በዚሁ ስብሰባ ላይ ቭላድሚር ፑቲን ምዕራባውያን አገሮች በሩሲያ ላይ የጣሉትን ማዕቀቦች " ጦርነት ከማወጅ ጋር ተመሳሳይ ነው " ብለውታል።

በሌላ በኩል ፑቲን በዩክሬን ሰማይ ላይ የበረራ ክልከላን ለመጣል የሚደረግ ሙከራ በዓለም ላይ አስከፊ የሆነ መዘዝ ያስከትላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ፕሬዜዳንቱ ፤ በዩክሬን ሰማይ የበረራ ክልከላ ለማድረግ የሚሞክር የትኛውም ኃይል በጦርነቱ ውስጥ ተሳትፎ እንዳደረገ እንደሚታይ እና እንዲህ ያለው እርምጃ ለአውሮፓ እና ለዓለም አስከፊ መዘዝ የሚያስከትል መሆኑን ነው የገለፁት።

ፕሬዜዳንት ፑቲን ፤ በድጋሜ አላማቸው የሩሲያኛ ተናጋሪ ማህበረሰቦችን ከጥቃት መከላከል፤ ዩክሬን ገለልተኝት እንዲሁም ለሩሲያ ስጋት እንዳትሆን ማድረግ መሆኑ አስታውቀዋል።

@tikvahethiopia
#SPHMMC

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ሕክምና ኮሌጅ የ75 ዓመት ክብረ በዓል እና የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8 ) ቀንን ምክንያት በማድረግ የካቲት 29 ቀን ሙሉ ለሙሉ አገልግሎት የሚሰጠው በሴቶች የቀዶ ሕክምና ቡድን አባላት #ብቻ እንደሚሆን አሳውቆናል።

ኮሌጁ በላከል መልዕክት ፤ በተለያዩ የሕክምና ዘርፍ የሰለጠኑ እና ልምድ ያላቸው ቀዶ ሐኪሞቹ በልዩ ልዩ የባለሙያዎች ቡድናቸው ታግዘው አገልግሎት ይሰጣሉ ብሏል።

ይህም የኮሌጁን ሴት ባለሙያዎች የላቀ አገልግሎት እንደሚሰጡ ይህ ጥሩ ማሳያ እንደሆነም አሳውቆናል።

@tikvahethiopia
ከቀረጥ ነፃ የሚገቡ ምርቶችን የሚያመጡ ነጋዴዎችን የሚቆጣጠር አዲስ መመርያ ማዘጋጀቱን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

በኢትዮጵያ እየታየ ባለው ከፍተኛ የዋጋ ንረት ሳቢያ እንደ ስኳር፣ የምግብ ዘይት፣ስንዴ፣ፓስታና ማካሮኒ የመሳሰሉ መሠረታዊ ምርቶች ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ ባለፈው ዓመት መፈቀዱ ይታወሳል።

ነገር ግን ነጋዴዎች የተሰጠውን ዕድል በሕገወጥ መንገድ እየተጠቀሙበት በመሆኑ አዲስ መመርያ ማዘጋጀት ማስፈለጉን ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አሳውቋል።

ሚስቴሩ ከቀረጥ ነፃ እንዲገቡ የተፈቀዱ የፍጆታ ምርቶች ታሪፍ የማይከፈልባቸው በመሆናቸው ኅብረተሰቡ በቅናሽ ዋጋ እንዲገዛ ለማድረግና የተከሰተውን የዋጋ ንረት ለመቀነስ ቢሆንም አስመጪዎች ግን በከፍተኛ ዋጋ እየሸጡ መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል ብሏል።

ከቀረጥ ነፃ ዕድልን የሚጠቀሙ አስመጪዎች በተጠበቀው መሠረት እየሠሩ እንዳልሆነ የገለፀው ሚኒስቴሩ ምርቶቹን ያለ ደረሰኝና በከፍተኛ ዋጋ እየሸጡ እንደሆነ ገልጿል።

ይህን መሠረት በማድረግ አስመጪዎችን የሚቆጣጠር መመርያ ተዘጋጅቷል።

አዲሱ መመርያ አስመጪዎች ያስመጡትን የምርት መጠን፣ ዓይነትና ያስመጡበትን ጊዜ ጉምሩክ ኮሚሽን መዝግቦ ለንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ለክልል ንግድ ቢሮዎች የሚያስተላልፍበትን አሠራር ይዟል።

ጉምሩክ ኮሚሽን በሚሰጠው መረጃ መሠረት የክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ንግድ ቢሮዎች ምርቱ ለማን እንደተከፋፈለ፣ በምን ያህል ዋጋ እንደተሸጠና በሕጋዊ መንገድ መሸጡን ያረጋግጣሉ።

ይህ አዲስ መመሪያ ከ2 ሳምንት በኋላ ተግባራዊ እንደሚደረግ ይጠበቃል። አስመጪዎቹ ከቀረጥ ነፃ የገቡ ምርቶችን ለኅብረት ሥራ ማኅበራትና ለሸማቾች ማኅበራት ቅድሚያ ሰጥተው እንዲያቀርቡ ያዛል።

ምንጭ፦ሪፖርተር (telegra.ph/RE-03-06-2)

@tikvahethiopia
" የምግብ ዘይት የለም ይሉናል፤ አለ የሚባልባት ደግሞ በከፍተኛ ዋጋ ነው የሚሸጠው "

በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚኖሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የምግብ ዘይት አለመኖር ቢኖርም ደግሞ ዋጋው የሚቀመስ እንዳልሆነ ገልፀዋል።

ለአብነት ከአዲስ አበባ ቲክቫህ አባላት በመጣው መልዕክት በተለያዩ አካባቢዎች ባለ5 ሊትር የምግብ ዘይት ካለ እንኳን ከ850-950 ብር ድረስ እንደሚሸጥ ጠቁመዋል። ባለ አንድ ሊትር ከ165-180 ብር ድረስ እንደሚሸጥ ገልፀዋል።

በተለያዩ ክልል ከተሞች ያሉ የቲክቫህ አባላት የምግብ ዘይት የዋጋ ጭማሪ እንደተደረገበት ጠቁመው 5 ሊትሩ የለም እንደሚባሉ ካለም ከ750-900 ብር ድረስ እንደሚሸጥ ገልፀዋል።

በአንዳንድ ቦታዎች ደግሞ ዘይት ተወደደ የሚለውን ሲሰሙ ያላቸውን ዘይት የመደበቅ ድርጊት የሚፈፅሙም አካላት ሊኖሩ ስለሚችሉና ክትትል እንደሚያስፈልገው ጠቁመዋል።

መልዕክታቸውን የላኩ ነዋሪዎች መንግስት ችግሩን መርምሮ እጅግ በጣም አስቸኳይ መፍትሄ እንዲሰጥና ገበያውን እንዲያረጋጋ ጠይቀዋል።

በሌላ ተያያዥ ጉዳይ፦

የባህር ዳር ከተማ በበላየነህ ክንዴ ለከተማው የሚቀርበው የፊቤላ ዘይት በወቅቱና በበቂ መጠን እየቀረበ ባለመሆኑ ከክልሉ ንግድ ቢሮ ጋር በመነጋገር 883,000 ሊትር ፓልም ዘይት ከውጭ ተገዝቶ በ " አለ በጅምላ " በኩል መቅረቡን አሳውቋል።

በነገው ዕለት በሁሉም ክፍለ ከተሞችና የገጠር ቀበሌዎች በተመጣጣኝ ዋጋ የዘይት ስርጭት ያካሄዳል ብሏል።

በአ/አ ከተማ ደግሞ የምግብ ዘይት በድብቅ ይዘው ለማሸሽ የሞከሩ ህገወጦች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ከተማው አሳውቋል።

መንግስትንና ህብረተሰቡን ለማጋጨትና አርቴፊሻል የዋጋ ንረትን በመፍጠር ህዝቡን ለማስጨነቅ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ሃይሎች በመኖራቸው ህብረተሰቡ ጥቆማ ይስጠኝ ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" የምግብ ዘይት የለም ይሉናል፤ አለ የሚባልባት ደግሞ በከፍተኛ ዋጋ ነው የሚሸጠው " በተለያዩ የሀገሪቱ ከተሞች የሚኖሩ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የምግብ ዘይት አለመኖር ቢኖርም ደግሞ ዋጋው የሚቀመስ እንዳልሆነ ገልፀዋል። ለአብነት ከአዲስ አበባ ቲክቫህ አባላት በመጣው መልዕክት በተለያዩ አካባቢዎች ባለ5 ሊትር የምግብ ዘይት ካለ እንኳን ከ850-950 ብር ድረስ እንደሚሸጥ ጠቁመዋል። ባለ አንድ ሊትር…
#BahirDar📍

በባህር ዳር የምግብ ዘይት መሸጫ ዋጋ ይፋ ሆነ።

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ንግድ መምሪያ የምግብ ዘይት መሸጫ ዋጋ ይፋ አድርጓል።

ከነገ ከ28/06/2014 ዓ.ም ጀምሮ መሰራጨት የሚጀምረው ፓልም ዘይት መግዣና መሸጫ ዋጋ መረጃ ይህንን ይመስላል ፦

ቸርቻሪዎች / ሸማቾች ህ/ስ/ማ ከአለ በጅምላ የሚገዙበት የጅምላ ዋጋ ፦

1. ባለ 20 ሊትር 👉 1575.6 ብር ፣
2. ባለ 5 ሊትር 👉 408.6 ብር፣
3. ባለ 3 ሊትር 👉 251.10 ብር ሲሆን፣

ቸርቻሪዎች / ሸማቾች ህ/ስ/ማ #ለተጠቃሚው_ማህበረሰብ የሚያሰራጩበት ዋጋ ደግሞ ፦

1. ባለ 20 ሊትር 👉 1641.80 ብር ፣
2. ባለ 5 ሊትር 👉 425.80 ብር፣
3. ባለ 3 ሊትር 👉 261.70 ብር መሆኑ ተገልጿል።

ምንጭ፦ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር

@tikvahethiopia
ሳፋየር አዲስ ሆቴል ተከፍቷል።

"በወቅታዊ ጉዳዮች" ምክንያት በሚል ለ3 ወር ተዘግቶ የነበረው በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ከቦሌ መድሃኒዓለም ወደ አትላስ በሚወስደው መንገድ ላይ የሚገኘው ባለ አራት ኮከቡ " ሳፋየር አዲስ ሆቴል " ተከፈተ።

ሆቴሉ ባለፈው ማክሰኞ መከፈቱን ሪፖርተር ያስነበበ ሲሆን ሶስት ወር ተዘግቶ ከቆየ በኃላ “ምንም ችግር የለበትም” በመባሉ መከፈቱ ነው የተነገረው።

ሳፋየር አዲስ ህዳር 24 ቀን 2014 ዓ/ም ከመታሸጉ በፊት ከ3 ጊዜ በላይ በፀጥታ ኃይሎች ተፈትሾ የነበረ ሲሆን ህዳር 21 ላይ የመጨረሻ ፍተሻ ተደርጎበት በሁለተኛው ቀን ታሽጓል።

የሆቴሉ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮናስ ወርቁ፣ ሆቴሉ ሲዘጋም ሆነ ሲከፈት ምንም ዓይነት ገለጻ ለሆቴሉ አስተዳደር እንዳልተደረገ እና ሆቴሉ በተዘጋባቸው ያለፉት ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ክስ እንዳልተመሠረተ አስታውቀዋል፡፡

በሆቴሉ ውስጥ በተደረጉት ሁሉም ፍተሻዎች ምንም ነገር አለመገኘቱንና ይኼንን የሚገልጽ ፊርማ ፍተሻውን ያካሄዱ አካላትና የሆቴሉ አስተደዳር መፈራረማቸውን ያስታውሰዋል። በዚህም ምክንያት " በቶሎ ይከፈታል " በሚል ጉዳዩን ሲከታተሉ መቆየታቸውን አስረድተዋል፡፡

ነገር ግን ሆቴሉ ታሽጎ ከቆየ 3 ወር በኃላ ሊከፈት ችሏል።

የወረዳው ንግድና ኢንደስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት ሆቴሉን የከፈተው የከተማ አስተዳደሩ ውሳኔ በክፍለ ከተማው በኩል በደብዳቤ ስለደረሰው መሆኑን ለሪፖርተር ገልጿል።

በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ባለ ኮከብ ሆቴሎች ከወራት በፊት በተለያዩ ምክንያቶች እንዲዘጉ መደረጋቸው ይታወሳል።

በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ከተዘጉት ሆቴሎች መካከል ካሌብና ሀርመኒ ሆቴሎች ይገኙበታል፡፡

ተጨማሪ : telegra.ph/Reporter-03-06

@tikvahethiopia
#Dessise #Kombolcha

በዛሬው ዕለት አቶ ሳሙኤል ሞላልኝ የ #ደሴ ከተማ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ሆነው ሲሾሙ አቶ መሀመድ አሚን ደግሞ የ #ኮምቦልቻ ከተማ ከንቲባ ሆነው ተሹመዋል።

የደሴ ከተማ አሰተዳደር ምክር ቤት ባካሄደው 4ኛ ዙር 9ኛ ዓመት 31ኛ መደበኛ ጉባኤ አቶ ሳሙኤል ሞላልኝን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አድርጎ ሾሟል።

በሌላ በኩል የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ባካሄደው 3ኛ አስቸኳይ ጉባኤ አቶ መሀመድ አሚን ኮምቦልቻ ከተማን በከንቲባነት እንዲመሩ ሾሟቸዋል።

@tikvahethiopia