'ኸልት ፕራይዝ'
' ዓለም አቀፍ አሸናፊዎች 1 ሚሊዮን ዶላር 💵 ሽልማት ይበረከትላቸዋል '
የዓለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ውድድር " ኸልት ፕራይዝ " በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከየካቲት 5 ጀምሮ መካሄድ ጀምሯል።
"ኸልት ፕራይዝ" ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገው እና በዓለም ላይ ላሉ የተለያዩ ማህበራዊ ተግዳሮቶች መፍትሄ ይሰጣሉ ተብለው የሚታሰቡ የቢዝነስ ሃሳቦች ላይ የሚያተኩር ዓለም አቀፍ ፕሮግራም ነው።
ይህ ፕሮግራም በተለይ የተለያዩ የቢዝነስ ሃሳብ እና የስራ ፈጠራ ችሎታ ያላቸውን ተማሪዎች ዓላማቸውን ማሳካት እንዲችሉ ይረዳል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተሳታፊነት ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋከው ውድድር ከካዛና ግሩፕ ጋር በመተባበር ሲሆን እስከ መጋቢት 17 ቀን 2014 ዓ.ም ይካሄዳል።
ከ100 በላይ ቡድኖች ተመዝግበው 35 ቡድኖች ተመርጠዋል።
በቀጣይ ስልጠና መርሀግብር ያለ ሲሆን ከስልጠናው በኃላ ለዳኞች ቀርበው የተመረጡ በአፍሪካ ደረጃ ኢትዮጵያንና አ/አ ዩኒቨርሲቲን ወክለው ይወዳደራሉ።
ቲክቫህ "ኸልት ፕራይዝ" አስተባባሪዎች እንደሰማው ለውድድር ለሚሳተፉ የምዝገባ ጊዜ ቢጠናቀቅም የተደራጀ ሀሳብ በቡድን ይዘው ለሚመጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ተማሪዎች ብቻ ቀሪ ጥቂት ቦታዎች አሉ።
በተጨማሪ የቢዝነስ ሃሳብና የስራ ፈጠራ ላይ ያተኮረ ስልጠና በቅርቡ የሚጀምር ሲሆን መሳተፍ የሚፈልጉ የማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
ስልጠናው በአካል በአ/አ ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች ነው የሚሰጠው።
የተደራጀ ሀሳብ ያላቸው የAAUና AASTU ተማሪዎች ለመመዝገብ👇
forms.gle/vtUQb5meNevymea87
ስልጠናውን መሳተፍ የሚፈልጉ👇
forms.gle/7sXqfktgrVzU1SpDA
@tikvahethiopia
' ዓለም አቀፍ አሸናፊዎች 1 ሚሊዮን ዶላር 💵 ሽልማት ይበረከትላቸዋል '
የዓለም አቀፍ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ውድድር " ኸልት ፕራይዝ " በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከየካቲት 5 ጀምሮ መካሄድ ጀምሯል።
"ኸልት ፕራይዝ" ተማሪዎችን ማዕከል ያደረገው እና በዓለም ላይ ላሉ የተለያዩ ማህበራዊ ተግዳሮቶች መፍትሄ ይሰጣሉ ተብለው የሚታሰቡ የቢዝነስ ሃሳቦች ላይ የሚያተኩር ዓለም አቀፍ ፕሮግራም ነው።
ይህ ፕሮግራም በተለይ የተለያዩ የቢዝነስ ሃሳብ እና የስራ ፈጠራ ችሎታ ያላቸውን ተማሪዎች ዓላማቸውን ማሳካት እንዲችሉ ይረዳል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተሳታፊነት ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ የተዘጋከው ውድድር ከካዛና ግሩፕ ጋር በመተባበር ሲሆን እስከ መጋቢት 17 ቀን 2014 ዓ.ም ይካሄዳል።
ከ100 በላይ ቡድኖች ተመዝግበው 35 ቡድኖች ተመርጠዋል።
በቀጣይ ስልጠና መርሀግብር ያለ ሲሆን ከስልጠናው በኃላ ለዳኞች ቀርበው የተመረጡ በአፍሪካ ደረጃ ኢትዮጵያንና አ/አ ዩኒቨርሲቲን ወክለው ይወዳደራሉ።
ቲክቫህ "ኸልት ፕራይዝ" አስተባባሪዎች እንደሰማው ለውድድር ለሚሳተፉ የምዝገባ ጊዜ ቢጠናቀቅም የተደራጀ ሀሳብ በቡድን ይዘው ለሚመጡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ለአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ተማሪዎች ብቻ ቀሪ ጥቂት ቦታዎች አሉ።
በተጨማሪ የቢዝነስ ሃሳብና የስራ ፈጠራ ላይ ያተኮረ ስልጠና በቅርቡ የሚጀምር ሲሆን መሳተፍ የሚፈልጉ የማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም ተማሪዎች መመዝገብ ይችላሉ ተብሏል።
ስልጠናው በአካል በአ/አ ዩኒቨርሲቲ ካምፓሶች ነው የሚሰጠው።
የተደራጀ ሀሳብ ያላቸው የAAUና AASTU ተማሪዎች ለመመዝገብ👇
forms.gle/vtUQb5meNevymea87
ስልጠናውን መሳተፍ የሚፈልጉ👇
forms.gle/7sXqfktgrVzU1SpDA
@tikvahethiopia
#የካቲት2010
የ2010 ዓ/ም በተለይም የካቲት ወር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በርካታ ክስተቶች የተስተናገዱበት ፤የካቲት 8 ደግሞ ታሪካዊ ቀን ተብሎ ሊመዘገብ የሚችል ነው።
ለረጅም ዓመታት በእስር ቤት እንዲማቅቁ የተፈረደባቸው ፖለቲከኞች ፣ የሃይማኖት አስተማሪዎች፣ በርካታ ወጣቶች ከእስር እንዲፈቱ የተደረገበት ፤ የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የስልጣን መልቀቂያ ያስገቡበት ወር ነው።
ከብዙ ትውስታዎች በጥቂቱ ፦
- መላው ሀገሪቱ ከፍተኛ ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ የነበረችበት ወቅት ነበር።
- በበርካታ ከተሞች በተለይ በኦሮሚያ ክልል እና አማራ ክልል እንዲሁም በደቡብ ክልል የወጣቶች የ #ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ላይ ተቃውሞ እጅግ የበረታበት ነበር። ተቃውሞው እስረኞች እንዲለቀቁ፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ መንግስት ዜጎችን መግደል እንዲያቆም ሲጠየቅበት የነበረ ነው።
- በተለይ በኦሮሚያ ክልል እጅግ በርካታ ከተሞች ፣ በአማራ ፣ በደቡብ ክልሎች በሚገኙም ከተሞች መንግስትን በመቃወም የስራ ማቆም እና ቤት የመቀመጥ አድማ የተደረገበት ወር ነበር።
- መንግስት እስረኞችን ለመፍትታ የወሰነበት በዚህም ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ (በወቅቱ) ጉዳያቸው በህግ ተይዞ የነበሩ 329 ተጠርጣሪዎች ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ የወሰነበት በአጠቃላ 746 እንዲፈቱ የተባለበት ወር ነበር።
- እነ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ፣ አቶ አንዱአለም አራጌ፣ አቶ አበበ ቀስቶ እና አቶ እስክንድር ነጋ የይቅርታ መጠየቂያ ደብዳቤ አንፈርምም ያሉበት ወር ነው።
- ከሰባት እስከ ሃያ ሁለት አመታት እስር የተበየነባቸው የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት አንዳችም ያጠፋነው ጥፋት የለም በሚል "የምንጠይቀውም ይቅርታ የለም " የይቅርታ ፎርም አንፈርምም ያሉበትም ወር ነው።
- የ2010 የካቲት ወር የኦፌኮው ከፍተኛ አመራር አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ጉርሜሳ አያና፣ አቶ አዲሱ ቡላላ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ ጌቱ ጋሩማ፣ አቶ ተስፋዬ ሊበን እና አቶ በየነ ሩዳ ከእስር የተለቀቁበት ነው።
- የዞን ዘጠኞቹ (የቀድሞ) እነ አቶ በፍቃዱ ኃይሉ ፣ አቶ አጥናፍ ብርሃኔ እና አቶ ናትናኤል ፈለቀ ክስ የተቋረጠበት ወር ነበር የካቲት 2010 ዓ/ም።
- እነ አቶ አዱአለም አራጌ ፣ አቶ እስክንድር ነጋ ፣ ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ፣ አቶ ኦልባና ለሌሳ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታየ ፣ አርቲስት ሴና ሰለሞን ፣ አርቲስት ኤልያስ ክፍሉ ፣ ወ/ሮ ጫልቱ ታከለ ፣ ወ/ሮ እማዋይሽ ፣ አቶ ማሙሸት አማረ፣ ኦኬሎ አኳይ (የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዘዳንት)፣ አቶ አንዱአለም አያሌው ፣ እነ አቶ ብርሀኑ ተክለያሬድ ከእስር የተለቀቁበት ወር ነበር።
* የካቲት 8 / 2010 (በዛሬዋ ቀን) የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከኢህአዴግ ሊቀመንበርነት እና ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተርነት ለመልቀቅ ጥያቄ ያቀረቡበትና ይህንኑም በመግለጫ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያሳወቁበት ቀን ነበር።
- በ2010 የካቲት ወር የሚንስትሮች ምክር ቤት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ በሁሉም ሀገሪቱ ክፍል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ የወሰነበት እና ወደ ምክር ቤት የመራበት ነበር።
- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአስቸኳይ ስብሰባ የካቲት 23/2010 ዓ/ም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በ395 ድጋፍ፣ በ88 ተቃውሞ እና በ7 ድምጸ ታእቅቦ ያፀደቀበት። በኃላም የተፈጠረው የቁጥር ስህተት መነጋገሪያ ነበረበት በወቅቱ አፈጉባኤ የነበሩት አቶ አባዱላ ገመዳ ህዝብን " ይቅርታ " የጠየቁበት ወር ነበር።
- የአዋጁ መታወጅ ከፍተኛ ተቃውሞ እንዲከሰት ያደረገም ነበር። በነበሩ ግጭቶች ቀደም ብሎ በወሩ ውስጥ በነበሩ ተቃውሞዎች በርካታ ወጣቶች የተገደሉበት ነበር።
- የአማራ ክልል በጎንደርና ጭልጋ ማረሚያ ቤቶች የሚገኙ የ224 ተጠርጣሪዎች ክስ ያቋረጠበት።
- የጎንደሯ ወጣት ንግስት ይርጋ ከእስር የተፈታችበት ወር ነው (የካቲት 13 ቀን 2010) ።
- የኢትዮጵያ መንግስት ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ፣ ብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ፅጌን (አሁን በህይወት የሉም) ጨምሮ 18 ሰዎች በይቅርታ እንዲፈቱ የወስነበት ወር ነው።
- የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አደርገዋል ተብለው የተከሰሱት ኮሎኔል አንተነህ ደምስ፣ ኮሎኔል አለሙ ጌትነት፣ ብ/ጀነራል አሳምነው ፅጌ (አሁን በህይወት የሉም)፣ ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ ከእስር የተፈቱት በዚሁ የካቲት ወር ነው።
- የኦህዴድ (የቀድሞ የኢህአዴግ አባል ድርጅት) ማዕከላዊ ኮሚቴ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ሊቀመንበር አድርጎ የመረጠበት ወር ነው። (ዶክተር ዐቢይ የአሁን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር /የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት ናቸው)
- ሱማሌ ክልል 1500 እስረኞችን ከእስር የፈታበት ነው።
- የቀድሞው ሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበሩት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ከእስር የተፈቱበት ወር ነው። እሳቸው ሁለት ጊዜ "ፈርመው እንዲወጡ" ተብሎ ሲጠየቁ ወንጀል እንዳልፈፀሙ በመግለፅ የይቅርታ ፎርም ላይ አልፈርምም ብለው ነበር። (አሁን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ናቸው)
(ከላይ የዘረዘርናቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ ገፃችን በየካቲት ወር 2010 ላይ ከተለዋወጥናቸው በርካታ መረጃዎች / በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት በወሩ ውስጥ ከታዩ ክስተቶች ጥቂቶቹን ያስታወስንበት ነው)
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
የ2010 ዓ/ም በተለይም የካቲት ወር በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ በርካታ ክስተቶች የተስተናገዱበት ፤የካቲት 8 ደግሞ ታሪካዊ ቀን ተብሎ ሊመዘገብ የሚችል ነው።
ለረጅም ዓመታት በእስር ቤት እንዲማቅቁ የተፈረደባቸው ፖለቲከኞች ፣ የሃይማኖት አስተማሪዎች፣ በርካታ ወጣቶች ከእስር እንዲፈቱ የተደረገበት ፤ የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የስልጣን መልቀቂያ ያስገቡበት ወር ነው።
ከብዙ ትውስታዎች በጥቂቱ ፦
- መላው ሀገሪቱ ከፍተኛ ጭንቀት እና ውጥረት ውስጥ የነበረችበት ወቅት ነበር።
- በበርካታ ከተሞች በተለይ በኦሮሚያ ክልል እና አማራ ክልል እንዲሁም በደቡብ ክልል የወጣቶች የ #ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ላይ ተቃውሞ እጅግ የበረታበት ነበር። ተቃውሞው እስረኞች እንዲለቀቁ፣ ፍትህ እንዲሰፍን፣ መንግስት ዜጎችን መግደል እንዲያቆም ሲጠየቅበት የነበረ ነው።
- በተለይ በኦሮሚያ ክልል እጅግ በርካታ ከተሞች ፣ በአማራ ፣ በደቡብ ክልሎች በሚገኙም ከተሞች መንግስትን በመቃወም የስራ ማቆም እና ቤት የመቀመጥ አድማ የተደረገበት ወር ነበር።
- መንግስት እስረኞችን ለመፍትታ የወሰነበት በዚህም ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ (በወቅቱ) ጉዳያቸው በህግ ተይዞ የነበሩ 329 ተጠርጣሪዎች ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር እንዲለቀቁ የወሰነበት በአጠቃላ 746 እንዲፈቱ የተባለበት ወር ነበር።
- እነ ኡስታዝ አሕመዲን ጀበል ፣ አቶ አንዱአለም አራጌ፣ አቶ አበበ ቀስቶ እና አቶ እስክንድር ነጋ የይቅርታ መጠየቂያ ደብዳቤ አንፈርምም ያሉበት ወር ነው።
- ከሰባት እስከ ሃያ ሁለት አመታት እስር የተበየነባቸው የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት አንዳችም ያጠፋነው ጥፋት የለም በሚል "የምንጠይቀውም ይቅርታ የለም " የይቅርታ ፎርም አንፈርምም ያሉበትም ወር ነው።
- የ2010 የካቲት ወር የኦፌኮው ከፍተኛ አመራር አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ጉርሜሳ አያና፣ አቶ አዲሱ ቡላላ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ ጌቱ ጋሩማ፣ አቶ ተስፋዬ ሊበን እና አቶ በየነ ሩዳ ከእስር የተለቀቁበት ነው።
- የዞን ዘጠኞቹ (የቀድሞ) እነ አቶ በፍቃዱ ኃይሉ ፣ አቶ አጥናፍ ብርሃኔ እና አቶ ናትናኤል ፈለቀ ክስ የተቋረጠበት ወር ነበር የካቲት 2010 ዓ/ም።
- እነ አቶ አዱአለም አራጌ ፣ አቶ እስክንድር ነጋ ፣ ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ፣ አቶ ኦልባና ለሌሳ፣ ጋዜጠኛ ውብሸት ታየ ፣ አርቲስት ሴና ሰለሞን ፣ አርቲስት ኤልያስ ክፍሉ ፣ ወ/ሮ ጫልቱ ታከለ ፣ ወ/ሮ እማዋይሽ ፣ አቶ ማሙሸት አማረ፣ ኦኬሎ አኳይ (የቀድሞ የጋምቤላ ክልል ፕሬዘዳንት)፣ አቶ አንዱአለም አያሌው ፣ እነ አቶ ብርሀኑ ተክለያሬድ ከእስር የተለቀቁበት ወር ነበር።
* የካቲት 8 / 2010 (በዛሬዋ ቀን) የቀድሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ሀይለማሪያም ደሳለኝ ከኢህአዴግ ሊቀመንበርነት እና ከኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስተርነት ለመልቀቅ ጥያቄ ያቀረቡበትና ይህንኑም በመግለጫ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያሳወቁበት ቀን ነበር።
- በ2010 የካቲት ወር የሚንስትሮች ምክር ቤት ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ በሁሉም ሀገሪቱ ክፍል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ እንዲታወጅ የወሰነበት እና ወደ ምክር ቤት የመራበት ነበር።
- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአስቸኳይ ስብሰባ የካቲት 23/2010 ዓ/ም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን በ395 ድጋፍ፣ በ88 ተቃውሞ እና በ7 ድምጸ ታእቅቦ ያፀደቀበት። በኃላም የተፈጠረው የቁጥር ስህተት መነጋገሪያ ነበረበት በወቅቱ አፈጉባኤ የነበሩት አቶ አባዱላ ገመዳ ህዝብን " ይቅርታ " የጠየቁበት ወር ነበር።
- የአዋጁ መታወጅ ከፍተኛ ተቃውሞ እንዲከሰት ያደረገም ነበር። በነበሩ ግጭቶች ቀደም ብሎ በወሩ ውስጥ በነበሩ ተቃውሞዎች በርካታ ወጣቶች የተገደሉበት ነበር።
- የአማራ ክልል በጎንደርና ጭልጋ ማረሚያ ቤቶች የሚገኙ የ224 ተጠርጣሪዎች ክስ ያቋረጠበት።
- የጎንደሯ ወጣት ንግስት ይርጋ ከእስር የተፈታችበት ወር ነው (የካቲት 13 ቀን 2010) ።
- የኢትዮጵያ መንግስት ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ፣ ብርጋዴር ጄነራል አሳምነው ፅጌን (አሁን በህይወት የሉም) ጨምሮ 18 ሰዎች በይቅርታ እንዲፈቱ የወስነበት ወር ነው።
- የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አደርገዋል ተብለው የተከሰሱት ኮሎኔል አንተነህ ደምስ፣ ኮሎኔል አለሙ ጌትነት፣ ብ/ጀነራል አሳምነው ፅጌ (አሁን በህይወት የሉም)፣ ብ/ጀነራል ተፈራ ማሞ ከእስር የተፈቱት በዚሁ የካቲት ወር ነው።
- የኦህዴድ (የቀድሞ የኢህአዴግ አባል ድርጅት) ማዕከላዊ ኮሚቴ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን ሊቀመንበር አድርጎ የመረጠበት ወር ነው። (ዶክተር ዐቢይ የአሁን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር /የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት ናቸው)
- ሱማሌ ክልል 1500 እስረኞችን ከእስር የፈታበት ነው።
- የቀድሞው ሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ የነበሩት አቶ ዮናታን ተስፋዬ ከእስር የተፈቱበት ወር ነው። እሳቸው ሁለት ጊዜ "ፈርመው እንዲወጡ" ተብሎ ሲጠየቁ ወንጀል እንዳልፈፀሙ በመግለፅ የይቅርታ ፎርም ላይ አልፈርምም ብለው ነበር። (አሁን የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ናቸው)
(ከላይ የዘረዘርናቸው በቲክቫህ ኢትዮጵያ ገፃችን በየካቲት ወር 2010 ላይ ከተለዋወጥናቸው በርካታ መረጃዎች / በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሂደት በወሩ ውስጥ ከታዩ ክስተቶች ጥቂቶቹን ያስታወስንበት ነው)
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት.pdf
1.4 MB
#ሪፖርት
የህወሓት /TPLF/ ኃይሎች ወደ አማራ ክልል ገብተው በቆዩባቸው ጊዜያት ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ በሲቪሎች ላይ ግድያ እና የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶችን መፈጸማቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው አዲስ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ከሐምሌ 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ተቆጣጥረዋቸው በነበሩ አካባቢዎች፤ ከጦር እና በሰብዓዊነት ላይ ከሚፈጸም ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ ወንጀሎችን ስለመፈጸማቸው የሚያመለክቱ ማስረጃዎች መኖራቸውን አምነስቲ ገልጿል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል " የትግራይ ኃይሎች በአማራ ክልል ከተሞች የሚገኙ በርካታ ንጹሃን ሰዎችን ሆነ ብለው ገድለዋል ፣ ሴቶች እና ታዳጊዎችን አስገድደው በቡድን ደፍረዋል፤ እንዲሁም የግል እና የሕዝብ ንብረት አውድመዋል " ብሏል።
የህወሓት ታጣቂዎች በጭና እና ቆቦ ከተሞች እንዲሁም በአካባቢው በሚገኙ ስፍራዎች ላይ ጥቃት ያደረሱት ከነሐሴ 2013 ዓ.ም. አጋማሽ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጀመሪያ ባሉት ጊዜያት ነው።
ታጣቂዎቹ በአካል ላይ ከሚደርሱት ጥቃቶች በተጨማሪ የግድያ ማስፈራሪያዎች፣ ብሔር ተኮር ስድቦች እና ማንቋሸሾች በተጠቂዎች ላይ ሲደርሱ ነበር።
ቆቦ ላይ ከታጣቂ ነዋሪዎች እና ከሚሊሻዎች የገጠማቸውን መገዳደር ለመበቀለ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የበቀል እርምጃ ሲወስዱ እንደነበር አምነስቲ ሪፖርት አድርጓል።
የህወሓት/TPLF/ታጣቂዎች ተቆጣጥረዋቸው በነበሩ በእንዚህ የአማራ ክልል አካባቢዎች ዓለም አቀፍ መሠረታዊ የሆኑ የሰብዓዊ ሕጎችን አለማክበራቸውን ገልጿል።
(ሙሉ ሪፖርት በPDF ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
የህወሓት /TPLF/ ኃይሎች ወደ አማራ ክልል ገብተው በቆዩባቸው ጊዜያት ከጦር ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ በሲቪሎች ላይ ግድያ እና የአስገድዶ መድፈር ጥቃቶችን መፈጸማቸውን አምነስቲ ኢንተርናሽናል ባወጣው አዲስ ሪፖርት ይፋ አድርጓል።
ከሐምሌ 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ተቆጣጥረዋቸው በነበሩ አካባቢዎች፤ ከጦር እና በሰብዓዊነት ላይ ከሚፈጸም ወንጀል ጋር የሚስተካከሉ ወንጀሎችን ስለመፈጸማቸው የሚያመለክቱ ማስረጃዎች መኖራቸውን አምነስቲ ገልጿል።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል " የትግራይ ኃይሎች በአማራ ክልል ከተሞች የሚገኙ በርካታ ንጹሃን ሰዎችን ሆነ ብለው ገድለዋል ፣ ሴቶች እና ታዳጊዎችን አስገድደው በቡድን ደፍረዋል፤ እንዲሁም የግል እና የሕዝብ ንብረት አውድመዋል " ብሏል።
የህወሓት ታጣቂዎች በጭና እና ቆቦ ከተሞች እንዲሁም በአካባቢው በሚገኙ ስፍራዎች ላይ ጥቃት ያደረሱት ከነሐሴ 2013 ዓ.ም. አጋማሽ እስከ መስከረም 2014 ዓ.ም. መጀመሪያ ባሉት ጊዜያት ነው።
ታጣቂዎቹ በአካል ላይ ከሚደርሱት ጥቃቶች በተጨማሪ የግድያ ማስፈራሪያዎች፣ ብሔር ተኮር ስድቦች እና ማንቋሸሾች በተጠቂዎች ላይ ሲደርሱ ነበር።
ቆቦ ላይ ከታጣቂ ነዋሪዎች እና ከሚሊሻዎች የገጠማቸውን መገዳደር ለመበቀለ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የበቀል እርምጃ ሲወስዱ እንደነበር አምነስቲ ሪፖርት አድርጓል።
የህወሓት/TPLF/ታጣቂዎች ተቆጣጥረዋቸው በነበሩ በእንዚህ የአማራ ክልል አካባቢዎች ዓለም አቀፍ መሠረታዊ የሆኑ የሰብዓዊ ሕጎችን አለማክበራቸውን ገልጿል።
(ሙሉ ሪፖርት በPDF ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ሪፖርት.pdf
#ሪፖርት
ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል (የፆታዊ ጥቃት) ፦
(ቢቢሲ)
ከሐምሌ ወር 2013 ዓ/ም ጀምሮ በጭና እና በዙሪያዋ እድሜያቸው 14 የሚሆኑ ሴት ታዳጊዎችን ጨምሮ የህወሓት ታጣቂዎች በርካታ ሴቶችን በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ መድፈራቸውንና አስገድደው ምግብ እንዲያበስሉላቸው አድርገዋል።
ቃላቸውን የሰጡት 14 የጾታዊ ጥቃት ሰለባዎች በቡድን፤ አንዳንዶቹ ልጆቻቸው ፊት መደፈራቸውን ተናግረዋል።
አንዲት የ7ኛ ክፍል ተማሪ እና 14 ዓመት ታዳጊ ከእናቷ ጋር በመኖሪያቸው ድር-ባሕር በህወሓት ታጣቂዎች መደፈሯን ተናግራለች።
ይህች ታዳጊ ፥ "ረፋድ 5 ሰዓት አካባቢ መሳሪያ የያዙ ሁለት ወጣቶች ወደ ቤታችን ሲመጡ ከእናቴ እና ከአያቴ ጋር ነበርኩ። አንደኛው የወታደር ልብስ ነው የለበሰው ሌላኛው ደግሞ የሲቪል ልብስ። ትግርኛ እና አማርኛ እየቀላቀሉ ነው የሚያወሩት። 'ቤተሰቦቻችን ተደፍረዋል አሁን እናንተን የምንደፍርበት ተራ ነው' አሉን። አንደኛው ከቤት ውጪ እኔን ደፈረኝ። ሌላኛው ደግሞ ቤት ውስጥ እናቴን ደፈረ። እናቴ አሁን ታማለች። . . . ምን እንደተፈጠረ አናወራም" ስትል ተናግራለች።
የ29 ዓመቷ ሰላም ለ15 ሰዓታት በዘለቀ ቆይታ እንዴት 4 የህወሓት ታጣቂዎች እየተፈራረቁ አስገድደው እንደደፈሯት ተናግራለች።
@tikvahethiopia
ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል (የፆታዊ ጥቃት) ፦
(ቢቢሲ)
ከሐምሌ ወር 2013 ዓ/ም ጀምሮ በጭና እና በዙሪያዋ እድሜያቸው 14 የሚሆኑ ሴት ታዳጊዎችን ጨምሮ የህወሓት ታጣቂዎች በርካታ ሴቶችን በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ መድፈራቸውንና አስገድደው ምግብ እንዲያበስሉላቸው አድርገዋል።
ቃላቸውን የሰጡት 14 የጾታዊ ጥቃት ሰለባዎች በቡድን፤ አንዳንዶቹ ልጆቻቸው ፊት መደፈራቸውን ተናግረዋል።
አንዲት የ7ኛ ክፍል ተማሪ እና 14 ዓመት ታዳጊ ከእናቷ ጋር በመኖሪያቸው ድር-ባሕር በህወሓት ታጣቂዎች መደፈሯን ተናግራለች።
ይህች ታዳጊ ፥ "ረፋድ 5 ሰዓት አካባቢ መሳሪያ የያዙ ሁለት ወጣቶች ወደ ቤታችን ሲመጡ ከእናቴ እና ከአያቴ ጋር ነበርኩ። አንደኛው የወታደር ልብስ ነው የለበሰው ሌላኛው ደግሞ የሲቪል ልብስ። ትግርኛ እና አማርኛ እየቀላቀሉ ነው የሚያወሩት። 'ቤተሰቦቻችን ተደፍረዋል አሁን እናንተን የምንደፍርበት ተራ ነው' አሉን። አንደኛው ከቤት ውጪ እኔን ደፈረኝ። ሌላኛው ደግሞ ቤት ውስጥ እናቴን ደፈረ። እናቴ አሁን ታማለች። . . . ምን እንደተፈጠረ አናወራም" ስትል ተናግራለች።
የ29 ዓመቷ ሰላም ለ15 ሰዓታት በዘለቀ ቆይታ እንዴት 4 የህወሓት ታጣቂዎች እየተፈራረቁ አስገድደው እንደደፈሯት ተናግራለች።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሳ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል። ምክር ቤቱ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የወሰነው። ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት…
#USA
አሜሪካ በኢትዮጵያ ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ ጊዙ አዋጅ እንዲነሳ መወሰኑን በመልካም ጎኑ እንደምትቀበል ገልፃለች።
ውሳኔው እየቀጠለ ያለውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለሚደረገው ጥረት በኢትዮጵያ መንግሥት የተወሰደ አንድ አዎንታዊ እና በጎ እርምጃ ነው ብላዋለች።
አሜሪካ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤቷ ባወጣችው መግለጫ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደመነሳቱ አዋጁን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር የዋሉ እና ክስ ያልተመሰረተባቸው ሰዎች በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቃለች።
የእስረኞች መፈታት ሁሉን አካታችና ውጤታማ ብሔራዊ ምክክር ለማድረግ ያስችላልም ብላለች።
አሜሪካ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ፣ ያልተቋረጠ የሰብአዊ አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ፣ በሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና ጥቃቶች ላይ ግልፅ ምርመራዎች እንዲደረጉ እና ግጭቱን በድርድር እንዲፈታ ከሁሉም አካላት ጋር መነጋገሯንና መጣሯን እንደምትቀጥል ገልፃለች።
@tikvahethiopia
አሜሪካ በኢትዮጵያ ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ ጊዙ አዋጅ እንዲነሳ መወሰኑን በመልካም ጎኑ እንደምትቀበል ገልፃለች።
ውሳኔው እየቀጠለ ያለውን ግጭት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ለሚደረገው ጥረት በኢትዮጵያ መንግሥት የተወሰደ አንድ አዎንታዊ እና በጎ እርምጃ ነው ብላዋለች።
አሜሪካ በውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤቷ ባወጣችው መግለጫ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንደመነሳቱ አዋጁን ተከትሎ በቁጥጥር ሥር የዋሉ እና ክስ ያልተመሰረተባቸው ሰዎች በአፋጣኝ ከእስር እንዲለቀቁ ጠይቃለች።
የእስረኞች መፈታት ሁሉን አካታችና ውጤታማ ብሔራዊ ምክክር ለማድረግ ያስችላልም ብላለች።
አሜሪካ ግጭቱ በአስቸኳይ እንዲቆም ፣ ያልተቋረጠ የሰብአዊ አገልግሎት ተደራሽ እንዲሆን ፣ በሁሉም የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እና ጥቃቶች ላይ ግልፅ ምርመራዎች እንዲደረጉ እና ግጭቱን በድርድር እንዲፈታ ከሁሉም አካላት ጋር መነጋገሯንና መጣሯን እንደምትቀጥል ገልፃለች።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሳ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል። ምክር ቤቱ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የወሰነው። ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት…
#UN
" ውሳኔውን በጣም ነው የምናደንቀው " - ተመድ
የተባበሩት መግሥታት ድርጅት (UN) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳቱን በጣም እንደሚያደንቀው አሳውቋል።
የድርጅቱ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱያሪች ፤ ትላንት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳትና የድርጅቱ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ስላላቸው አቋም ተጠይቀው ድርጅቱ ውሳኔውን " በጣም እንደሚያደንቀው " ተናግረዋል።
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ውስጥ የተያዙ እና የታሠሩ ሰዎች እንዲለቀቁ ፣ አሁንም ግጭት መቆም እንዳለበት ፣ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና ተደራሽነት እንዲሁም ደግሞ ተጠያቂነት መስፈን እንዳለበት ቃል አቀባዩ አንስተዋል።
@tikvahethiopia
" ውሳኔውን በጣም ነው የምናደንቀው " - ተመድ
የተባበሩት መግሥታት ድርጅት (UN) የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳቱን በጣም እንደሚያደንቀው አሳውቋል።
የድርጅቱ ቃል አቀባይ ስቴፋን ዱያሪች ፤ ትላንት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳትና የድርጅቱ ዋና ፀሃፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ ስላላቸው አቋም ተጠይቀው ድርጅቱ ውሳኔውን " በጣም እንደሚያደንቀው " ተናግረዋል።
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ውስጥ የተያዙ እና የታሠሩ ሰዎች እንዲለቀቁ ፣ አሁንም ግጭት መቆም እንዳለበት ፣ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦትና ተደራሽነት እንዲሁም ደግሞ ተጠያቂነት መስፈን እንዳለበት ቃል አቀባዩ አንስተዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሳ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል። ምክር ቤቱ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የወሰነው። ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት…
#Turkey
" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳቱ ሰላም እና መረጋጋት ለማምጣት ወሳኝ እርምጃ ነው " - ቱርክ
ቱርክ የኢትዮጵያ ፓርላማ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን በበጎ እንደምትቀበል ገልፃለች።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳት በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት ትክክለኛ እርምጃ ነው ስትልም ገልፃለች።
በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የሚደረጉ ሁሉንም ጥረቶች መደገፏን እንደምትቀጥል የገለፀችው ቱርክ ለስኬታማነቱም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እሰራለሁ ብላለች።
@tikvahethiopia
" የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳቱ ሰላም እና መረጋጋት ለማምጣት ወሳኝ እርምጃ ነው " - ቱርክ
ቱርክ የኢትዮጵያ ፓርላማ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን በበጎ እንደምትቀበል ገልፃለች።
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መነሳት በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት ትክክለኛ እርምጃ ነው ስትልም ገልፃለች።
በኢትዮጵያ ሰላምና መረጋጋትን ለማምጣት የሚደረጉ ሁሉንም ጥረቶች መደገፏን እንደምትቀጥል የገለፀችው ቱርክ ለስኬታማነቱም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እሰራለሁ ብላለች።
@tikvahethiopia
#NEBE
ትላንትና ህ/ተ/ም/ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ 13 ሀገራዊ እና 13 ክልላዊ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያከናውኑ እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንዲያስገቡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ አሳስቧል።
ማሳሰቢያው ከተሰጣቸው ፓርቲዎች መካከል ፦ ብልፅግና፣ ኦፌኮ፣ አብን ፣ ኦነግ ፣ ነእፓ፣ ኦብነግ፣ መኢአድ ይገኙበታል።
(አጠቃላይ ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ትላንትና ህ/ተ/ም/ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ 13 ሀገራዊ እና 13 ክልላዊ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያከናውኑ እንዲሁም አስፈላጊ የሆኑ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንዲያስገቡ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ አሳስቧል።
ማሳሰቢያው ከተሰጣቸው ፓርቲዎች መካከል ፦ ብልፅግና፣ ኦፌኮ፣ አብን ፣ ኦነግ ፣ ነእፓ፣ ኦብነግ፣ መኢአድ ይገኙበታል።
(አጠቃላይ ዝርዝሩ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#UAE #Turkey #Kenya
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የሁለት ቀናት ጉብኝት አድርገዋል።
ኤርዶጋን ጉብኝቱ ስኬታማ ነበር ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አስራ ሶስት ስምምነቶችን የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቶቹ በሀገራቱ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያዳብርና ኢንቨስትመንቶችን የሚያሳድግ እንዲሁም ግንኙነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑ ተነግሯል።
በሌላ መረጃ የጎረቤት ሀገር #ኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ዛሬ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ይገኛሉ። ፕሬዝዳንት ኬንያታ ከአቡዳቢ አልጋወራሽ እና ከዩኤኢ ምክትል ጦር አዛዥ ከሆኑት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ውይይታቸው በአካባቢያዊ ፣ በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፋዊ አጀንዳዎች ዙሪያ እንደነበር አል አይን ኒውስ ዘግቧል።
የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ባለፈው ጥር ወር እንዲሁም አሁን ባለንበት የየካቲት ወር ውስጥ በአጠቃላይ የስድስት ሀገራት መሪዎችን ማለትም ፦
- የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ
- የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
- የእስራኤል ፕሬዜዳንት አይዛክ ሄርዞግ
- የሶማሊያ ጠ/ሚር መሀመድ ሁሴን ሮበል
- የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን
- የኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገሯ አስተናግዳ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክራለች።
@tikvahethiopia
የቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ የሁለት ቀናት ጉብኝት አድርገዋል።
ኤርዶጋን ጉብኝቱ ስኬታማ ነበር ብለዋል።
ሁለቱ ሀገራት አስራ ሶስት ስምምነቶችን የተፈራረሙ ሲሆን ስምምነቶቹ በሀገራቱ መካከል ያለውን ግንኙነት የሚያዳብርና ኢንቨስትመንቶችን የሚያሳድግ እንዲሁም ግንኙነታቸውን የበለጠ የሚያጠናክር መሆኑ ተነግሯል።
በሌላ መረጃ የጎረቤት ሀገር #ኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ዛሬ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ይገኛሉ። ፕሬዝዳንት ኬንያታ ከአቡዳቢ አልጋወራሽ እና ከዩኤኢ ምክትል ጦር አዛዥ ከሆኑት ሼክ መሀመድ ቢን ዛይድ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ውይይታቸው በአካባቢያዊ ፣ በአህጉራዊ እና በዓለም አቀፋዊ አጀንዳዎች ዙሪያ እንደነበር አል አይን ኒውስ ዘግቧል።
የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ባለፈው ጥር ወር እንዲሁም አሁን ባለንበት የየካቲት ወር ውስጥ በአጠቃላይ የስድስት ሀገራት መሪዎችን ማለትም ፦
- የግብፅ ፕሬዜዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ
- የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ
- የእስራኤል ፕሬዜዳንት አይዛክ ሄርዞግ
- የሶማሊያ ጠ/ሚር መሀመድ ሁሴን ሮበል
- የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን
- የኬንያ ፕሬዜዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገሯ አስተናግዳ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክራለች።
@tikvahethiopia
#Freedom_and_Equality
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና ማጎሪያ ካምፖች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንዲለቀቁ ጠየቀ፡፡
ነእፓ አዲስ አበባ ለሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኤምባሲ በጻፈው ደብዳቤ እጅግ አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ በእስር ቤትና ማቆያ ካምፖች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአስቸኳይ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር ተለቀው ወደ ሀገራቸው መምጣት የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችላቸው ጠይቋል፡፡
በፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር አብዱልቃደር አደም ለአምባሳደሩ የተላከው መልእክት የሁለቱን ሀገሮች ከሺህ ዓመት በላይ የዘለቀ ግንኙነት አስታውሶ፣ ኢትዮጵያውያን ያሉበት እጅግ ዘግናኝ ሁኔታ የፍትህ እና የነጻነት መለያ ለሆነችው ቅድስት ሀገር የማይመጥን በመሆኑ እስረኞቹ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡
የደብዳቤው ቅጂ ለኢፌድሪ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እና ሳዑዲ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተላልፏል፡፡
(ሙሉ መልእክቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) በሳዑዲ አረቢያ በእስር ቤት እና ማጎሪያ ካምፖች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን እንዲለቀቁ ጠየቀ፡፡
ነእፓ አዲስ አበባ ለሚገኘው የሳዑዲ ዓረቢያ ኤምባሲ በጻፈው ደብዳቤ እጅግ አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ በእስር ቤትና ማቆያ ካምፖች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአስቸኳይ እና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከእስር ተለቀው ወደ ሀገራቸው መምጣት የሚችሉበት ሁኔታ እንዲመቻችላቸው ጠይቋል፡፡
በፓርቲው ሊቀመንበር ዶክተር አብዱልቃደር አደም ለአምባሳደሩ የተላከው መልእክት የሁለቱን ሀገሮች ከሺህ ዓመት በላይ የዘለቀ ግንኙነት አስታውሶ፣ ኢትዮጵያውያን ያሉበት እጅግ ዘግናኝ ሁኔታ የፍትህ እና የነጻነት መለያ ለሆነችው ቅድስት ሀገር የማይመጥን በመሆኑ እስረኞቹ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠይቋል፡፡
የደብዳቤው ቅጂ ለኢፌድሪ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር እና ሳዑዲ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተላልፏል፡፡
(ሙሉ መልእክቱ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
#AddisAbaba
በአዲስ አበባ በስድስት ወራት በተከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች የደረሰ ጉዳት [ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገለፀው ] ፦
• 24 ሺህ ያህል የትራፊክ አደጋዎች ተከስተዋል።
• 210 ዜጎች ሞተዋል።
• 946 ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
• 575 ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
• 14 ሺህ 168 ያህል አደጋዎች በንብረት ላይ ጉዳት አድርሰዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደሚለው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተከሰተው የትራፊክ አደጋ በ5 ሺህ ያህል 📉 ቀንሷል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ በስድስት ወራት በተከሰቱ የትራፊክ አደጋዎች የደረሰ ጉዳት [ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደገለፀው ] ፦
• 24 ሺህ ያህል የትራፊክ አደጋዎች ተከስተዋል።
• 210 ዜጎች ሞተዋል።
• 946 ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል።
• 575 ቀላል የአካል ጉዳት ደርሷል።
• 14 ሺህ 168 ያህል አደጋዎች በንብረት ላይ ጉዳት አድርሰዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደሚለው ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የተከሰተው የትራፊክ አደጋ በ5 ሺህ ያህል 📉 ቀንሷል።
ምንጭ፦ ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ
@tikvahethiopia
#ቅጥር
የአዲስ አበባ አስተዳደር የጤና ቢሮ በስሩ ላሉት ተቋማት ሰራተኞችን አወዳድሮ በቋሚ ቅጥር ለማሰራት ይፈልጋል።
መስፈርቶቹን የምታሟሉ ከ8/06/2014 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት 10 የስራ ቀናት መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።
ሁሉም የስራ መደብ የስራ ልምድ #ዜሮ ዓመት ነው።
ከፍተኛ ባለሞያ የተፈለገበት የስራ መደብ - ጠቅላላ ሀኪም ሲሆን በመጀመሪያ ዲግሪ በ9,056 ብር ደመወዝ አጠቃላይ 150 ሰው ይፈለጋል።
በተጨማሪ በ ዘO (ጤና መኮንን) በተመሳሳይ የመጀመሪያ ዲግሪ በ7,071 ብር ደመወዝ 50 ሰው ይፈለጋል።
እንዲሁም በደረጃ 4 ጤና ኤክስቴንሽን (ዲፕሎማ / ሌቭል 4) በ5,358 ብር ደመወዝ ፣ በደረጃ 4 ነርስ (ዲፕሎማ / ሌቭል 4) በ4,609 ደመወዝ ፣ በሚድዋይፈሪ ፕሮፌሽናል (የመጀመሪያ ዲግሪ) በ6,193 ብር ደመወዝ ፣ በፋርማሲ ፕሮፌሽናል (የመጀመሪያ ዲግሪ) በ7,071 ብር ደመወዝ በተጠቀሱት እያንዳንዱ የስራ መደቦች 30 ሰዎች ይፈለጋሉ።
በሌሎችም የስራ መደቦች ላይ ያሉ ቦታዎችን ፣ የደመወዝ መጠን ፣ የትምህርት ደረጃ ከላይ በተያያዘው ምስል ይመልከቱ።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ አስተዳደር የጤና ቢሮ በስሩ ላሉት ተቋማት ሰራተኞችን አወዳድሮ በቋሚ ቅጥር ለማሰራት ይፈልጋል።
መስፈርቶቹን የምታሟሉ ከ8/06/2014 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት 10 የስራ ቀናት መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሏል።
ሁሉም የስራ መደብ የስራ ልምድ #ዜሮ ዓመት ነው።
ከፍተኛ ባለሞያ የተፈለገበት የስራ መደብ - ጠቅላላ ሀኪም ሲሆን በመጀመሪያ ዲግሪ በ9,056 ብር ደመወዝ አጠቃላይ 150 ሰው ይፈለጋል።
በተጨማሪ በ ዘO (ጤና መኮንን) በተመሳሳይ የመጀመሪያ ዲግሪ በ7,071 ብር ደመወዝ 50 ሰው ይፈለጋል።
እንዲሁም በደረጃ 4 ጤና ኤክስቴንሽን (ዲፕሎማ / ሌቭል 4) በ5,358 ብር ደመወዝ ፣ በደረጃ 4 ነርስ (ዲፕሎማ / ሌቭል 4) በ4,609 ደመወዝ ፣ በሚድዋይፈሪ ፕሮፌሽናል (የመጀመሪያ ዲግሪ) በ6,193 ብር ደመወዝ ፣ በፋርማሲ ፕሮፌሽናል (የመጀመሪያ ዲግሪ) በ7,071 ብር ደመወዝ በተጠቀሱት እያንዳንዱ የስራ መደቦች 30 ሰዎች ይፈለጋሉ።
በሌሎችም የስራ መደቦች ላይ ያሉ ቦታዎችን ፣ የደመወዝ መጠን ፣ የትምህርት ደረጃ ከላይ በተያያዘው ምስል ይመልከቱ።
@tikvahethiopia
#NCDO
በወሎ እና በአፋር በጦርነቱ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ተደረገ።
#ነሲሓ_የበጎ_አድራጎትና_የልማት_ድርጅት (NCDO) በወሎ እና በአፋር በጦርነቱ ምክንያት ይበልጥ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።
ድርጅቱ ከሳምንት በፊት በአፋር ክልል ከሰመራ ከተማ በ270 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው ኢሪብቲ ከተማና በጭፍራ ከተማ በመገኘት በጀርመን ኮሎን ኤን አር ቬ የባርባሮሳ ፕላትስ ጓደኛማማቾች ጋር በመተባበር በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ እና ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።
ወሎ ውስጥ ከዓለም አቀፍ የሐረሪ ተወላጆችና ሐረሪ ደርሲ ጋር በመተባበር በኩታበር ወረዳ፣ በቦሩ ሜዳ፣ በሐይቅ ከተማ፣ በወረባቦና ቢስቲማ ከተማ በመገኘት ላለፉት ተከታታይ 3 ቀናት ከበጎ አድራጊ ግለሰቦች ያሰባሰበውን ድጋፍ ለተጎጂዎች አከፋፍለዋል። በወሎ ውስጥ ብቻ በጠቅላላ ለ1 ሺህ አባወራዎች የአንድ ወር አስቤዛ የተሰጠ ሲሆን፤
ለአንድ አባወራ፦
1) ዘይት: 1 ሊትር
2) ዱቄት: 10 ኪሎ
3) ሩዝ: 4 ኪሎ
4) ፓስታ: 4 እሽግ
5) መኮረኒ: 4 ኪሎ
6) የህፃናት አልሚ ምግብ እና ብስኩት
7) የተለያዩ ያገለገሉ አልባሳት ተበርክተዋል።
ጉዳቱ እጅግ የከፋ በመሆኑ የተነሳ ሌሎችም አካላት ርብርብ ያደርጉ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
@tikvahethiopia
በወሎ እና በአፋር በጦርነቱ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ተደረገ።
#ነሲሓ_የበጎ_አድራጎትና_የልማት_ድርጅት (NCDO) በወሎ እና በአፋር በጦርነቱ ምክንያት ይበልጥ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።
ድርጅቱ ከሳምንት በፊት በአፋር ክልል ከሰመራ ከተማ በ270 ኪሎ ሜትር ርቀት በምትገኘው ኢሪብቲ ከተማና በጭፍራ ከተማ በመገኘት በጀርመን ኮሎን ኤን አር ቬ የባርባሮሳ ፕላትስ ጓደኛማማቾች ጋር በመተባበር በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ እና ከፍተኛ የሆነ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች ድጋፍ አድርጓል።
ወሎ ውስጥ ከዓለም አቀፍ የሐረሪ ተወላጆችና ሐረሪ ደርሲ ጋር በመተባበር በኩታበር ወረዳ፣ በቦሩ ሜዳ፣ በሐይቅ ከተማ፣ በወረባቦና ቢስቲማ ከተማ በመገኘት ላለፉት ተከታታይ 3 ቀናት ከበጎ አድራጊ ግለሰቦች ያሰባሰበውን ድጋፍ ለተጎጂዎች አከፋፍለዋል። በወሎ ውስጥ ብቻ በጠቅላላ ለ1 ሺህ አባወራዎች የአንድ ወር አስቤዛ የተሰጠ ሲሆን፤
ለአንድ አባወራ፦
1) ዘይት: 1 ሊትር
2) ዱቄት: 10 ኪሎ
3) ሩዝ: 4 ኪሎ
4) ፓስታ: 4 እሽግ
5) መኮረኒ: 4 ኪሎ
6) የህፃናት አልሚ ምግብ እና ብስኩት
7) የተለያዩ ያገለገሉ አልባሳት ተበርክተዋል።
ጉዳቱ እጅግ የከፋ በመሆኑ የተነሳ ሌሎችም አካላት ርብርብ ያደርጉ ዘንድ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።
@tikvahethiopia