TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአዲስ አበባ ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የፊታችን ማክሰኞ በመንበረ ፓትርያርኩ የቋሚ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይገኛሉ። ያሉትን ችግሮች በሰላማዊ መንገድ ለመፍታትም ቀጠሮ ተይዟል። ቅዱስ ሲኖዶስ በመስቀል አደባባይ ጉዳይ እና በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ለመነጋገር ለከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጥሪ ማስተላለፉ ይታወቃል። በስብሰባው ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ…
#Update
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና ካቢኔያቸው ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ እና ካቢኔያቸው ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተገኝተዋል።
ቋሚ ሲኖዶስ የካቲት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ፣ በወይብላ ማርያም ጉዳይ፣ በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት እና በሌሎች የቤተ ክርስቲያን ይዞታዎች ዙሪያ ተወያይቶ አሉ የሚባሉ ችግሮችን በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ለመፍታት ይዞት የነበረው ቀጠሮ በወቅቱ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት ስብሰባ ስለነበረውና ከንቲባዋም በዚያ መገኘታቸው የግድ ስለሆነ ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር የነበረው ቀጠሮ ለዛሬ እንዲተላለፍ የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና ከአስተዳደሩ የተወከሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በአካል ተገኝተው ለቋሚ ሲኖዶስ በገለጹት መሰረት የውይይቱ ጊዜ ለዛሬ እንዲተላለፍ መደረጉ ይታወሳል።
በዚህም መሰረት ከንቲባዋና የካቢኔ አባላቶቻቸው ዛሬ በሰዓቱ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ሲሆን ከቋሚ ሲኖዶስ አባላት በተጨማሪ ሌሎች ብፁአን አባቶች ፣ የህግ ባለሙያዎች ፣ ከመምሪያ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።
በውይይቱ አሉ የሚባሉና ቤተክርስቲያን የምታቀርባቸው ጥያቄዎች ሁሉ ፍጹም ሰላማዊና ህጋዊ በሆነ መንገድ መፍትሔ የሚያገኝበትን ሁኔታ ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚገመት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ገልፃለች።
ከዚህ ቀደም በቋሚ ሲኖዶስ አባላት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መካከል ሊደረግ የታሰበው ውይይት በተለያዩ ምክንያቶች እንቅፋት እየገጠመው መቆየቱ ይታወሳል።
መረጃው ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ነው።
@tikvahethiopia
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና ካቢኔያቸው ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተገኝተዋል።
የአዲስ አበባ ከንቲባ እና ካቢኔያቸው ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተገኝተዋል።
ቋሚ ሲኖዶስ የካቲት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ፣ በወይብላ ማርያም ጉዳይ፣ በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት እና በሌሎች የቤተ ክርስቲያን ይዞታዎች ዙሪያ ተወያይቶ አሉ የሚባሉ ችግሮችን በሰላማዊና በህጋዊ መንገድ ለመፍታት ይዞት የነበረው ቀጠሮ በወቅቱ የከተማ አስተዳደሩ ምክር ቤት ስብሰባ ስለነበረውና ከንቲባዋም በዚያ መገኘታቸው የግድ ስለሆነ ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር የነበረው ቀጠሮ ለዛሬ እንዲተላለፍ የከተማ አስተዳደሩ ምክትል ከንቲባና ከአስተዳደሩ የተወከሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች በአካል ተገኝተው ለቋሚ ሲኖዶስ በገለጹት መሰረት የውይይቱ ጊዜ ለዛሬ እንዲተላለፍ መደረጉ ይታወሳል።
በዚህም መሰረት ከንቲባዋና የካቢኔ አባላቶቻቸው ዛሬ በሰዓቱ በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የተገኙ ሲሆን ከቋሚ ሲኖዶስ አባላት በተጨማሪ ሌሎች ብፁአን አባቶች ፣ የህግ ባለሙያዎች ፣ ከመምሪያ ኃላፊዎች ጋር ውይይት ያደርጋሉ።
በውይይቱ አሉ የሚባሉና ቤተክርስቲያን የምታቀርባቸው ጥያቄዎች ሁሉ ፍጹም ሰላማዊና ህጋዊ በሆነ መንገድ መፍትሔ የሚያገኝበትን ሁኔታ ይፈጥራሉ ተብሎ እንደሚገመት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ገልፃለች።
ከዚህ ቀደም በቋሚ ሲኖዶስ አባላት እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ መካከል ሊደረግ የታሰበው ውይይት በተለያዩ ምክንያቶች እንቅፋት እየገጠመው መቆየቱ ይታወሳል።
መረጃው ፦ የኢኦተቤ ህዝብ ግንኙነት ነው።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#State_of_Emergency ከሳምንታት በፊት የሚኒስትሮች ምክር ቤት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጊዜው ከመጠናቀቁ በፊት ቀሪ እንዲሆን ያቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት ምርምሮ ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል። ም/ ቤቱ ውሳኔውን መርምሮ የሚያፀድቀው ነገ በሚያካሂደው አስቸኳይ ስብሰባ ነው። በውሳኔ ሃሳቡ ላይ ድምጽ ከመስጠቱ በፊት የም/ቤቱ የሕግ፣ ፍትህ እና ዲሞክራሲ ቋሚ ኮሚቴ…
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሳ።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል።
ምክር ቤቱ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የወሰነው።
ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ተወስኗል፡፡
በተመሳሳይ የፍትህ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የጀመሯቸውን ጉዳዮች በመደበኛው የፍትህ አሰጣጥ ስርአት እንዲያጠናቅቁም መወሰኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል።
ምክር ቤቱ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የወሰነው።
ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት ከዛሬ ጀምሮ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት እንዲያደርግ ተወስኗል፡፡
በተመሳሳይ የፍትህ አካላት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ የጀመሯቸውን ጉዳዮች በመደበኛው የፍትህ አሰጣጥ ስርአት እንዲያጠናቅቁም መወሰኑን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
#Oromia , #QelemWollega📍
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር (ERCS) የቄለም ወለጋ ቅርንጫፍ ንብረት የሆኑና ማኅበሩ ለሰብዓዊ አገልግሎት የሚጠቀምባቸው ሁለት የታርጋ ቁጥር ET05-02121 እና ታርጋ ቁጥር ET05-02108 አምቡላንሶቹ ሰሞኑን በቄለም ወለጋ ለሰብዓዊ አገልግሎት ሲንቀሳቀሱ ማህበሩ በውል በማያውቀው ሁኔታ እና በግዳጅ ተወስደዋል።
ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን አለምአቀፍ የጄኔቫ ኮንቬንሽን የሚፃረርና፣ ከማህበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ማኅበሩ ገልጿል።
ከላይ የታርጋ ቁጥራቸው የተገለፁት 2 አምቡላንሶች በማኅበሩ ቁጥጥር ስር የሌሉ መሆኑን ተረድተው ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አምቡላንሶቹን ወደ ማህበሩ ተመልሠው ለህብረተሠቡ የተለመደውን ሰብዓዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንዲሰጡት ማህበሩ በተገልጋይ ወገኖች ስም ጠይቋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር (ERCS) የቄለም ወለጋ ቅርንጫፍ ንብረት የሆኑና ማኅበሩ ለሰብዓዊ አገልግሎት የሚጠቀምባቸው ሁለት የታርጋ ቁጥር ET05-02121 እና ታርጋ ቁጥር ET05-02108 አምቡላንሶቹ ሰሞኑን በቄለም ወለጋ ለሰብዓዊ አገልግሎት ሲንቀሳቀሱ ማህበሩ በውል በማያውቀው ሁኔታ እና በግዳጅ ተወስደዋል።
ድርጊቱ ኢትዮጵያ የፈረመችውን አለምአቀፍ የጄኔቫ ኮንቬንሽን የሚፃረርና፣ ከማህበሩ ዓላማ ውጪ መሆኑን ማኅበሩ ገልጿል።
ከላይ የታርጋ ቁጥራቸው የተገለፁት 2 አምቡላንሶች በማኅበሩ ቁጥጥር ስር የሌሉ መሆኑን ተረድተው ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ አምቡላንሶቹን ወደ ማህበሩ ተመልሠው ለህብረተሠቡ የተለመደውን ሰብዓዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ አስፈላጊውን ሁሉ ድጋፍ እንዲሰጡት ማህበሩ በተገልጋይ ወገኖች ስም ጠይቋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ እና ካቢኔያቸው ጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ተገኝተዋል። የአዲስ አበባ ከንቲባ እና ካቢኔያቸው ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ የቅዱስ ሲኖዶስ መሰብሰቢያ አዳራሽ ተገኝተዋል። ቋሚ ሲኖዶስ የካቲት 4 ቀን 2014 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ፣ በወይብላ ማርያም ጉዳይ፣ በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት እና በሌሎች የቤተ ክርስቲያን ይዞታዎች ዙሪያ…
#Update
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዛሬው እለት የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በመስቀል አደባባይና በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ቦታዎች በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ የጋራ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
ውይይቱ በፍጹም ቅን ልቡና፣ መደማመጥና መግባባት በተሞላበት ስሜት መካሄዱ ተገልጿል።
በውይይቱ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመስቀል አደባባይና የጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀትን በተመለከተ የተነሱትን ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የጋራ ኮሚቴ በማቋቋም ቀጣይ ውይይቶችን መሠረት በማድረግ የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ወደፊት ቤተ ክርስቲያንና የከተማ አስተዳደሩ በልማት፣ በሰላምና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበው እንደሚሰሩ ይፋ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዛሬው እለት የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች በመስቀል አደባባይና በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት ቦታዎች በቀረቡ ጥያቄዎች ላይ የጋራ ውይይት ማድረጋቸውን ገልፀዋል።
ውይይቱ በፍጹም ቅን ልቡና፣ መደማመጥና መግባባት በተሞላበት ስሜት መካሄዱ ተገልጿል።
በውይይቱ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመስቀል አደባባይና የጃንሜዳ ባሕረ ጥምቀትን በተመለከተ የተነሱትን ጥያቄዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ የጋራ ኮሚቴ በማቋቋም ቀጣይ ውይይቶችን መሠረት በማድረግ የማያዳግም ምላሽ ለመስጠት የጋራ ስምምነት ላይ ተደርሷል።
ወደፊት ቤተ ክርስቲያንና የከተማ አስተዳደሩ በልማት፣ በሰላምና በተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ተቀራርበው እንደሚሰሩ ይፋ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
#DStv
🗓ከጥር 2 እስከ መጋቢት 21 ድረስ ብቻ የሚቆይ የደስ ደስ ከዲኤስቲቪ!
⚽️የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎችን የዲኤስቲቪ ደንበኞች በሜዳ ፓኬጅ ላይ በነፃ ማየት እንደሚችሉ ያውቃሉ ?
👉 የሜዳ ፓኬጅ 550ብር ሲከፍሉ ባለ 1,300 ብር የሜዳ ፕላስ ፓኬጅ ስጦታ ያገኛሉ ! ⏰ በዕድሉ ፈጥነው ይጠቀሙ ።
በእርግጥም ከከፈሉት የዲኤስቲቪ ፓኬጅ በላይ ያግኙ!
ክፍያ ለመፈፀም ፣ ፓኬጅዎን ለመቀየር እንዲሁም ሌሎች የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ : https://bit.ly/2WDuBLk
የዲኤስቲቪን ቤተሰብ ይቀላቀሉ: https://bit.ly/3D2O1t4
🗓ከጥር 2 እስከ መጋቢት 21 ድረስ ብቻ የሚቆይ የደስ ደስ ከዲኤስቲቪ!
⚽️የቻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎችን የዲኤስቲቪ ደንበኞች በሜዳ ፓኬጅ ላይ በነፃ ማየት እንደሚችሉ ያውቃሉ ?
👉 የሜዳ ፓኬጅ 550ብር ሲከፍሉ ባለ 1,300 ብር የሜዳ ፕላስ ፓኬጅ ስጦታ ያገኛሉ ! ⏰ በዕድሉ ፈጥነው ይጠቀሙ ።
በእርግጥም ከከፈሉት የዲኤስቲቪ ፓኬጅ በላይ ያግኙ!
ክፍያ ለመፈፀም ፣ ፓኬጅዎን ለመቀየር እንዲሁም ሌሎች የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት የMyDStv Telegram ሊንክ ይጫኑ : https://bit.ly/2WDuBLk
የዲኤስቲቪን ቤተሰብ ይቀላቀሉ: https://bit.ly/3D2O1t4
#መግለጫ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ዛሬ " ለዜጎች መብት መከበር የሚሟገተው ጋዜጠኛ መብት ይከበር " በሚል መግለጫ አውጥቷል።
ማህበሩት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት መሻሻል እያሳየ እንደነበርና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ሲመሰክሩ እንደነበር አስታውሷል።
ይሁንና ይህ መሻሻል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሸረሸረ መሄዱን በብዙ ማሳያዎች መግለጽ እንደሚቻል እና ይህንንም የተለያዩ ማሳያዎች በመጥቀስ አብራርቷል።
(ከማህበሩ የተላከውን ሙሉ መግለጫ በዝርዝር ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ማኅበር ዛሬ " ለዜጎች መብት መከበር የሚሟገተው ጋዜጠኛ መብት ይከበር " በሚል መግለጫ አውጥቷል።
ማህበሩት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት መሻሻል እያሳየ እንደነበርና ዓለም ዓቀፍ ተቋማት ሲመሰክሩ እንደነበር አስታውሷል።
ይሁንና ይህ መሻሻል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እየተሸረሸረ መሄዱን በብዙ ማሳያዎች መግለጽ እንደሚቻል እና ይህንንም የተለያዩ ማሳያዎች በመጥቀስ አብራርቷል።
(ከማህበሩ የተላከውን ሙሉ መግለጫ በዝርዝር ከላይ ያንብቡ)
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ተፈርዶበታል
በጣልያን ሀገር ገጠራማ ስፍራ በሆነችው ፍራሲሎንጎ ከተማ ፍየሎችን እያረባች በአይብና በፍየል ምርቶቿና በጠንካራ ሰራተኝነቷ የታወቀችውን ኢትጵያዊቷን አጊቱ ጉደታን ቤቷ ውስጥ እያለች በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው የ33 ዓመቱ ጋናዊ ስደተኛ ሱሌይማን አዳምስ 20 ዓመት እስር ተፈርዶበታል።
የትሬንቶ ፍርድ ቤት ሰኞ ዕለት በዋለው ችሎት ጋናዊው ሱሌይማንን በነፍስ ማጥፋት ወንጀል 15 ዓመት ከስምንት ወር እንዲሁም አራት ዓመት ከአራት ወር ወሲባዊ ጥቃት በመፈጸም ፍርድ አስተላልፎበታል።
በተወሰነው ቅጣት ቤተሰቧ ደስተኛ አይደለም።
ኢትዮጵያ ውስጥ የምትገኘው የአጊቱ እህት ሀወኒ ኤዳዎ ጉደታ ለቢቢሲ በሰጠችው ቃል ቤተሰቧ ፍርድ ቤቱ በገዳዩ ላይ ያሳለፈው የእስር ቅጣት በቂ ነው ብሎ እያምንም ብላለች።
ሀወኒ ኤዴዎ " ምንም እንኳን ቅጣቱ እሷን የሚመልሳት ባይሆንም፣ ከተፈጸመው ወንጀል አኳያ ውሳኔው በቂ አይደለም። እኛ የእድሜ ልክ አስራት ይፈረዳል ብለን ጠብቀን ነበር" ስትል ለቢቢሲ ተናግራለች።
@tikvahethiopia
በጣልያን ሀገር ገጠራማ ስፍራ በሆነችው ፍራሲሎንጎ ከተማ ፍየሎችን እያረባች በአይብና በፍየል ምርቶቿና በጠንካራ ሰራተኝነቷ የታወቀችውን ኢትጵያዊቷን አጊቱ ጉደታን ቤቷ ውስጥ እያለች በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለው የ33 ዓመቱ ጋናዊ ስደተኛ ሱሌይማን አዳምስ 20 ዓመት እስር ተፈርዶበታል።
የትሬንቶ ፍርድ ቤት ሰኞ ዕለት በዋለው ችሎት ጋናዊው ሱሌይማንን በነፍስ ማጥፋት ወንጀል 15 ዓመት ከስምንት ወር እንዲሁም አራት ዓመት ከአራት ወር ወሲባዊ ጥቃት በመፈጸም ፍርድ አስተላልፎበታል።
በተወሰነው ቅጣት ቤተሰቧ ደስተኛ አይደለም።
ኢትዮጵያ ውስጥ የምትገኘው የአጊቱ እህት ሀወኒ ኤዳዎ ጉደታ ለቢቢሲ በሰጠችው ቃል ቤተሰቧ ፍርድ ቤቱ በገዳዩ ላይ ያሳለፈው የእስር ቅጣት በቂ ነው ብሎ እያምንም ብላለች።
ሀወኒ ኤዴዎ " ምንም እንኳን ቅጣቱ እሷን የሚመልሳት ባይሆንም፣ ከተፈጸመው ወንጀል አኳያ ውሳኔው በቂ አይደለም። እኛ የእድሜ ልክ አስራት ይፈረዳል ብለን ጠብቀን ነበር" ስትል ለቢቢሲ ተናግራለች።
@tikvahethiopia
ሸይኽ ቃሲም ሀጂ አልአሩሲ አርፈዋል።
ታላቁ አሊም ሸይኽ ቃሲም ሀጂ አልአሩሲ በህክምና እርዳታ ላይ እያሉ ማረፋቸው ተሰምቷል።
ሸይኽ ቃሲም ሀጂ አልአሩሲ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለሱናው መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ከሚወስዱት ግንባር ቀደም አሊሞች መካከል እንደነበሩ ተነግሯል።
በተጨማሪ በርካታ ለዲኑ የሚለፉ ወጣቶችን እና አሊሞችን ማፍራት የቻሉ እውቅ አሊም እንደነበሩ ተገልጿል።
በዳዕዋ ጉዟቸውም ብዙ ፈተናዎችን ያስተናገዱ አሊም ነበሩ።
መረጃውን ከኢትዮጵያ እስልምና እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እንዲሁም ከኡስታዝ አቡበከር አህመድ ነው ያገኘነው።
@tikvahethiopia
ታላቁ አሊም ሸይኽ ቃሲም ሀጂ አልአሩሲ በህክምና እርዳታ ላይ እያሉ ማረፋቸው ተሰምቷል።
ሸይኽ ቃሲም ሀጂ አልአሩሲ በሀገራችን ኢትዮጵያ ለሱናው መስፋፋት የአንበሳውን ድርሻ ከሚወስዱት ግንባር ቀደም አሊሞች መካከል እንደነበሩ ተነግሯል።
በተጨማሪ በርካታ ለዲኑ የሚለፉ ወጣቶችን እና አሊሞችን ማፍራት የቻሉ እውቅ አሊም እንደነበሩ ተገልጿል።
በዳዕዋ ጉዟቸውም ብዙ ፈተናዎችን ያስተናገዱ አሊም ነበሩ።
መረጃውን ከኢትዮጵያ እስልምና እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እንዲሁም ከኡስታዝ አቡበከር አህመድ ነው ያገኘነው።
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
3 ጉዳዮች ከዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ፦
1ኛ. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከዛሬ የካቲት 8/2014 ጀምሮ ቀሪ የሚሆንበት የውሳኔ ሃሳብ በ63 ተቃውሞ፣ በ21 ድምፀ ታአቅቦ፣ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል።
2ኛ. የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ በሁለት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እና የግል ድርጅቶች ሰራተኞች ጡረታ ለማደንገግ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በአንድ ተቃውሞ፣ በሶስት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል፡፡
3ኛ. የመንገድ ትራንስፖርት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በአንድ ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ለዝርዝር እይታ ለከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡
@tikvahethiopia
3 ጉዳዮች ከዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ፦
1ኛ. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከዛሬ የካቲት 8/2014 ጀምሮ ቀሪ የሚሆንበት የውሳኔ ሃሳብ በ63 ተቃውሞ፣ በ21 ድምፀ ታአቅቦ፣ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል።
2ኛ. የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ በሁለት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እና የግል ድርጅቶች ሰራተኞች ጡረታ ለማደንገግ የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ በአንድ ተቃውሞ፣ በሶስት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ፀድቋል፡፡
3ኛ. የመንገድ ትራንስፖርት ረቂቅ አዋጅን መርምሮ በአንድ ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ለዝርዝር እይታ ለከተማ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ መርቷል፡፡
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ETHIOPIA 3 ጉዳዮች ከዛሬው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ ፦ 1ኛ. የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ከዛሬ የካቲት 8/2014 ጀምሮ ቀሪ የሚሆንበት የውሳኔ ሃሳብ በ63 ተቃውሞ፣ በ21 ድምፀ ታአቅቦ፣ በአብላጫ ድምፅ ፀድቋል። 2ኛ. የመንግስት ሰራተኞች ጡረታ ለመደንገግ የቀረበ ረቂቅ አዋጅ በሁለት ድምጸ ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ እና የግል ድርጅቶች ሰራተኞች ጡረታ ለማደንገግ የቀረበውን ረቂቅ…
የ #መንግሥት እና የ #ግል ሠራተኞች ጡረታን ለመደንገግ የቀረበው አዋጅ ምን ይዟል ?
ለመንግሥት ሠራተኞች ፦
• የተሻሻለው የጡረታ ዐዋጅ የጡረታ ዕድሜን ጣራ ' 60 ዓመት ' እንዲሆን እና ጡረተኛው በሕይወት ሳለ የሚያገኘው የጡረታ መጠን ሲያልፍ ለትዳር አጋር 50 በመቶ የጡረታው ተጠቃሚ እንዲሆን ይፈቅዳል።
• የፖሊስና መከላከያ መዋጮ ከግለሰቡ የሚደረገው ሌሎች የግልና የመንግሥት ሠራተኞች እንደሚያዋጡት 7 በመቶ ሆኖ ከመንግሥት አካል የሚደረግለት መዋጮ ግን ወደ 33 በመቶ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ለግል ድርጅቶች ሠራተኞች ፦
• በድርጅቶች ምክንያት ሳይዋጣ የቀረን ገንዘብ በሦስት ወር ውስጥ ገቢ ካልተደረገ በቀጥታ ድርጅቱ ካለው ማንኛውም የባንክ አካውንት ገቢ እንዲደረግበት ያስገድዳል።
• የግል ድርጅት ባለቤቶች በድርጅቱ ሠራተኛ ሆነው በጡረታ ማዕቀፉ ውስጥ እንዳይገቡ አዋጁ አግዷል።
• ከ10 ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ ዕድሜው ለጡረታ በሚደርስበት ጊዜ የዕድሜ ልክ ጡረታ ተከፋይ እንዲሆን አዋጁ ይፈቅዳል።
• የሚሰበሰበው የጡረታ መዋጮም ወደ ኢንቨስትመንት በማስገባት ገቢን ማሳደግ ለጡረተኞች የክፍያ ማሻሻያ የሚያደርግበትን እድል ይፈጥራል።
• አንድ አሰሪ የ ግል ድርጅት ፍቃዱን በሚያድስበት ወቅት የሠራተኞቹን መዋጮ ካላስገባ ፍቃዱ የማይታደስበት አስገዳጅ አንቀጽም ተካቷል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
ለመንግሥት ሠራተኞች ፦
• የተሻሻለው የጡረታ ዐዋጅ የጡረታ ዕድሜን ጣራ ' 60 ዓመት ' እንዲሆን እና ጡረተኛው በሕይወት ሳለ የሚያገኘው የጡረታ መጠን ሲያልፍ ለትዳር አጋር 50 በመቶ የጡረታው ተጠቃሚ እንዲሆን ይፈቅዳል።
• የፖሊስና መከላከያ መዋጮ ከግለሰቡ የሚደረገው ሌሎች የግልና የመንግሥት ሠራተኞች እንደሚያዋጡት 7 በመቶ ሆኖ ከመንግሥት አካል የሚደረግለት መዋጮ ግን ወደ 33 በመቶ ከፍ እንዲል ተደርጓል።
ለግል ድርጅቶች ሠራተኞች ፦
• በድርጅቶች ምክንያት ሳይዋጣ የቀረን ገንዘብ በሦስት ወር ውስጥ ገቢ ካልተደረገ በቀጥታ ድርጅቱ ካለው ማንኛውም የባንክ አካውንት ገቢ እንዲደረግበት ያስገድዳል።
• የግል ድርጅት ባለቤቶች በድርጅቱ ሠራተኛ ሆነው በጡረታ ማዕቀፉ ውስጥ እንዳይገቡ አዋጁ አግዷል።
• ከ10 ዓመት በላይ ያገለገለ ሠራተኛ ዕድሜው ለጡረታ በሚደርስበት ጊዜ የዕድሜ ልክ ጡረታ ተከፋይ እንዲሆን አዋጁ ይፈቅዳል።
• የሚሰበሰበው የጡረታ መዋጮም ወደ ኢንቨስትመንት በማስገባት ገቢን ማሳደግ ለጡረተኞች የክፍያ ማሻሻያ የሚያደርግበትን እድል ይፈጥራል።
• አንድ አሰሪ የ ግል ድርጅት ፍቃዱን በሚያድስበት ወቅት የሠራተኞቹን መዋጮ ካላስገባ ፍቃዱ የማይታደስበት አስገዳጅ አንቀጽም ተካቷል።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ተነሳ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ በሃገሪቱ ተጥሎ የቆየውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አንስቷል። ምክር ቤቱ በ63 ተቃውሞ በ21 ተአቅቦ በአብላጫ ድምጽ ነው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ የወሰነው። ይህን ውሳኔ ተከትሎ÷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መርማሪ ቦርድ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አፈጻጸም ጋር ተያይዞ ያላጠናቀቃቸው ጅምር ስራዎች ካሉ ይህ ውሳኔ ከተላለፈበት…
" አሁንም ከእስር ያልተለቀቁ ሰዎች በአፋጣኝ ከእስር ይለቀቁ " - ኢሰመኮ
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየካቲት 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተለይ በሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ እንዲነሳ መወሰኑን ኮሚሽኑ በበጎ መመልከቱን ገልጿል።
ኮሚሽኑ በአስቸኳይ ሁኔታ ወቅት ከአዋጁ አተገባበር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር የዋሉ እና አሁንም ያልተለቀቁ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲለቀቁ በድጋሚ አሳስቧል።
በተጨማሪ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በቁጥጥር ስር ውለው የተለቀቁ ሰዎችም በእስር ስለመቆየታቸው ማረጋገጫ ባለማግኘታቸው ወደ ስራ መመለስ አለመቻልን ጨምሮ ለተለያዩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መጋለጣቸውን ባደረገው ክትትል መገንዘቡን ኮሚሽኑ ገልጿል።
ስለሆነም ሰዎች በእስር የቆዩበትን ጊዜ ማስረጃ እና ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች የመስጠቱን ሂደት እንዲፋጠንና ሰዎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው መመለስ እንዲችሉ እንዲደረግ ኢሰመኮ አሳስቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በየካቲት 8 ቀን 2014 ዓ/ም ከጥቅምት 23 ቀን 2014 ዓ/ም ጀምሮ ተግባራዊ የነበረውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በተለይ በሰብአዊ መብቶች ሁኔታ ላይ ያሳደረውን ተጽዕኖ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ እንዲነሳ መወሰኑን ኮሚሽኑ በበጎ መመልከቱን ገልጿል።
ኮሚሽኑ በአስቸኳይ ሁኔታ ወቅት ከአዋጁ አተገባበር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር የዋሉ እና አሁንም ያልተለቀቁ ሰዎች በአፋጣኝ እንዲለቀቁ በድጋሚ አሳስቧል።
በተጨማሪ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በቁጥጥር ስር ውለው የተለቀቁ ሰዎችም በእስር ስለመቆየታቸው ማረጋገጫ ባለማግኘታቸው ወደ ስራ መመለስ አለመቻልን ጨምሮ ለተለያዩ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መጋለጣቸውን ባደረገው ክትትል መገንዘቡን ኮሚሽኑ ገልጿል።
ስለሆነም ሰዎች በእስር የቆዩበትን ጊዜ ማስረጃ እና ሌሎች አስፈላጊ ሰነዶች የመስጠቱን ሂደት እንዲፋጠንና ሰዎች ወደ መደበኛ ሕይወታቸው መመለስ እንዲችሉ እንዲደረግ ኢሰመኮ አሳስቧል።
@tikvahethiopia