#Sudan | የሱዳን ጦር መሪ ሌ/ ጀነራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን የተባበሩት መንግሥታት (UN) የሽግግር መንግሥቱን እንዲደግፍ ጥሪ አቀረቡ።
ሌ/ጀነራል አል-ቡርሃን ጥያቄውን ያቀረቡት የተመድ የሱዳን ተወካይ የሆኑትን ቮልከር ፔርዝስ አግኝተው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።
ቮልከር ፔርዝስ ከአል-ቡርሃን ጋር መገናኘታቸውን በተረጋገጠ የትዊተር ገጻቸው የገለጹ ሲሆን፤ ምንም አንኳ ሱዳን ሕገ መንግሥታዊው ሥርዓት እንዲመለስ ብትስማም፤ ሌሎች ቁልፍ የሆኑ ጉዳዮች መከናወን አለባቸው ብለዋል።
ጀነራል አል-ቡርሃን ወደ ሥልጣናቸው እንዲመለሱ ከተደረጉት የሲቪል መንግሥት መሪ ጠ/ሚ አብደላ ሐምዶክ ጋር አብሮ ለመሥራት እና ምርጫ እስኪከናወን ድረስ አብደላ ሐምዶክ ለሚመሰርቱት የሽግግር መንግሥት ድጋፍ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
የሱዳን የሽግግር ምክር ቤት በ18 ወራት ውስጥ ምርጫ እንዲያካሂድ ጫና እየተደረገበት መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
ሌ/ጀነራል አል-ቡርሃን ጥያቄውን ያቀረቡት የተመድ የሱዳን ተወካይ የሆኑትን ቮልከር ፔርዝስ አግኝተው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።
ቮልከር ፔርዝስ ከአል-ቡርሃን ጋር መገናኘታቸውን በተረጋገጠ የትዊተር ገጻቸው የገለጹ ሲሆን፤ ምንም አንኳ ሱዳን ሕገ መንግሥታዊው ሥርዓት እንዲመለስ ብትስማም፤ ሌሎች ቁልፍ የሆኑ ጉዳዮች መከናወን አለባቸው ብለዋል።
ጀነራል አል-ቡርሃን ወደ ሥልጣናቸው እንዲመለሱ ከተደረጉት የሲቪል መንግሥት መሪ ጠ/ሚ አብደላ ሐምዶክ ጋር አብሮ ለመሥራት እና ምርጫ እስኪከናወን ድረስ አብደላ ሐምዶክ ለሚመሰርቱት የሽግግር መንግሥት ድጋፍ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
የሱዳን የሽግግር ምክር ቤት በ18 ወራት ውስጥ ምርጫ እንዲያካሂድ ጫና እየተደረገበት መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
#SituationReport | #Amhara #Tigray #Afar
የ #UN_OCHA በአፋር ፣ ትግራይ እና አማራ ክልል ስላለው ሁኔታ እና እየተደረገ ስላለው የሰብዓዊ ድጋፍ እንቅስቃሴ ሪፖርት አውጥቷል።
ዋና ዋና ነጥቦች ፦
- በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት 9.4 ሚሊዮን የሚገመቱ ሰዎች የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
- እኤአ ከህዳር 20 ጀምሮ ከትግራይ ምዕራብ ዞን ወደ ማይ-ፀብሪ፣ ሸራሮ እና ደደቢት ወረዳዎች በርካቶች ተፈናቅለው የገቡ ሲሆን የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት እንደሚያሳየው ከሽሬ በስተ ምዕራብ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ደደቢት ብዙ ሺህ ሰዎች ደርሰዋል፤ አዲስ ተፈናቃዮች ፍሰት የቀጠለ በመሆኑ ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል።
- በትግራይ ክልል 5.2 ሚሊዮን ህዝብ ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ቢያንስ 400,000 ያህሉ በርሃብ መሰል ሁኔታ ላይ ያሉ ናቸው።
- በአፋር ክልል በዚህ ዙር በተደረገ ድጋፍ ከ86,000 በላይ ሰዎች ምግብ አግኝተዋል።
- በአማራ ክልል 3.7 ሚሊዮን ዜጎች አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
- በአማራ ክልል በሰ/ወሎ፣ ዋግ ኽምራና ከፊል ደቡብ ወሎ እንዲሁም በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ በተለይ በአኗኗር ፣ በገበያ መቋረጥ እና የሰብዓዊ ዕርዳታ ለማድረስ ባለመቻሉ አሳሳቢ ነው።
- በአማራ ክልል አዲስ ተፈናቃዮች አሁንም አሉ። በደብረ ብርሃን ከተማ ተፈናቃዮችን የሚያስተናግዱ የጋራ ቦታዎች ቁጥር ከስድስት ወደ 10 ከፍ ብሏል፣በተመሳሳይ በኮምቦልቻ ከ2 ወደ 17 ከፍ ብሏል።
ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/
@tikvahethiopoa
የ #UN_OCHA በአፋር ፣ ትግራይ እና አማራ ክልል ስላለው ሁኔታ እና እየተደረገ ስላለው የሰብዓዊ ድጋፍ እንቅስቃሴ ሪፖርት አውጥቷል።
ዋና ዋና ነጥቦች ፦
- በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት 9.4 ሚሊዮን የሚገመቱ ሰዎች የምግብ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
- እኤአ ከህዳር 20 ጀምሮ ከትግራይ ምዕራብ ዞን ወደ ማይ-ፀብሪ፣ ሸራሮ እና ደደቢት ወረዳዎች በርካቶች ተፈናቅለው የገቡ ሲሆን የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት እንደሚያሳየው ከሽሬ በስተ ምዕራብ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ደደቢት ብዙ ሺህ ሰዎች ደርሰዋል፤ አዲስ ተፈናቃዮች ፍሰት የቀጠለ በመሆኑ ቁጥሩ ሊጨምር ይችላል።
- በትግራይ ክልል 5.2 ሚሊዮን ህዝብ ሰብአዊ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን ከእነዚህ ውስጥ ቢያንስ 400,000 ያህሉ በርሃብ መሰል ሁኔታ ላይ ያሉ ናቸው።
- በአፋር ክልል በዚህ ዙር በተደረገ ድጋፍ ከ86,000 በላይ ሰዎች ምግብ አግኝተዋል።
- በአማራ ክልል 3.7 ሚሊዮን ዜጎች አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ ያስፈልጋቸዋል።
- በአማራ ክልል በሰ/ወሎ፣ ዋግ ኽምራና ከፊል ደቡብ ወሎ እንዲሁም በአፋር ክልል ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች ያለው ሰብዓዊ ሁኔታ በተለይ በአኗኗር ፣ በገበያ መቋረጥ እና የሰብዓዊ ዕርዳታ ለማድረስ ባለመቻሉ አሳሳቢ ነው።
- በአማራ ክልል አዲስ ተፈናቃዮች አሁንም አሉ። በደብረ ብርሃን ከተማ ተፈናቃዮችን የሚያስተናግዱ የጋራ ቦታዎች ቁጥር ከስድስት ወደ 10 ከፍ ብሏል፣በተመሳሳይ በኮምቦልቻ ከ2 ወደ 17 ከፍ ብሏል።
ሙሉ ሪፖርት : https://reports.unocha.org/en/country/ethiopia/
@tikvahethiopoa
" 19 ሰዎች ሕክምና አጥተው ሕይወታቸው አልፏል " - ዶ/ር ብርሃኑ ዓለሙ
የአምደወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሽብርተኛው ህወሓት ባደረሰው ውድመት ምክንያት 19 ሰዎች ህክምና በማጣት ህይወታቸው ማለፉን ሪፖርት አደረገ።
የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ዓለሙ ለአሚኮ በሰጡት ቃል ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ጀምሮ ያከማቻቸው የሕክምና መሳሪያዎች፣ መድኃኒቶች እና ሌሎች ግብዓቶች ወድመዋል።
በሆስፒታሉ ክትትል ላይ የነበሩ 19 ሰዎች ሕክምና አጥተው ሕይወታቸው አልፏል።
በህክምና እጦት ህይወታቸው ያለፈው 7 ነፍሰጡር፣ 5 ሕጻናት እና 7 ተመላላሽ ታካሚዎች መሆናቸውን ዶ/ር ብርሃኑ አሳውቀዋል።
ህወሓት በሆስፒታሉ ንብረት ላይ ያደረሰው ጉዳት ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መሆኑንን ዶ/ር ብርሃኑ ጨምረው ተናግረዋል።
አምደወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከ150,000 በላይ ሕዝብ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሆስፒታል መሆኑን ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
@tikvahethiopia
የአምደወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሽብርተኛው ህወሓት ባደረሰው ውድመት ምክንያት 19 ሰዎች ህክምና በማጣት ህይወታቸው ማለፉን ሪፖርት አደረገ።
የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ዓለሙ ለአሚኮ በሰጡት ቃል ሆስፒታሉ ከተመሰረተ ጀምሮ ያከማቻቸው የሕክምና መሳሪያዎች፣ መድኃኒቶች እና ሌሎች ግብዓቶች ወድመዋል።
በሆስፒታሉ ክትትል ላይ የነበሩ 19 ሰዎች ሕክምና አጥተው ሕይወታቸው አልፏል።
በህክምና እጦት ህይወታቸው ያለፈው 7 ነፍሰጡር፣ 5 ሕጻናት እና 7 ተመላላሽ ታካሚዎች መሆናቸውን ዶ/ር ብርሃኑ አሳውቀዋል።
ህወሓት በሆስፒታሉ ንብረት ላይ ያደረሰው ጉዳት ከ95 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት መሆኑንን ዶ/ር ብርሃኑ ጨምረው ተናግረዋል።
አምደወርቅ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከ150,000 በላይ ሕዝብ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ ሆስፒታል መሆኑን ከአሚኮ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ፦
ከሐምሌ 5/2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጠው ከነበሩ አገልግሎቶች መካከል የብድር ውልን የማረጋገጥ አገልግሎት ብቻ ከነገ ህዳር 25 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት መሰጠት ይጀምራል።
@tikvahethiopia
ከሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ ፦
ከሐምሌ 5/2013 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ተቋርጠው ከነበሩ አገልግሎቶች መካከል የብድር ውልን የማረጋገጥ አገልግሎት ብቻ ከነገ ህዳር 25 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት መሰጠት ይጀምራል።
@tikvahethiopia
#እንድታውቁት
ታርጋዎችን ይመለከታል ፦
የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት አጠቃላይ ለልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎች እና ክልሎች አገልግሎት የሚውል 18,027 ታርጋዎችን አምርቶ ለስርጭት ዝግጁ አድርጓል።
ከዚህ መካከል ለአዲስ አበባ ከተማ አገልግሎት የሚውል 4,225 ታርጋዎች ያካትታል።
ይህን አገልግሎት የሚሰጡ ክልሎችና ከተማ አሰተዳደሮች ለስርጭት የተዘጋጁትን ታርጋዎች በመውሰድ ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እንዲያደርሱ ተጠይቋል።
ተገልጋዮች ጥያቄያቸውን በማቅረብ እንዲገለገሉ ተብሏል።
(የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር)
@tikvahethiopia
ታርጋዎችን ይመለከታል ፦
የፐብሊክ ሰርቪስ ትራንስፖርት አገልግሎት አጠቃላይ ለልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎች እና ክልሎች አገልግሎት የሚውል 18,027 ታርጋዎችን አምርቶ ለስርጭት ዝግጁ አድርጓል።
ከዚህ መካከል ለአዲስ አበባ ከተማ አገልግሎት የሚውል 4,225 ታርጋዎች ያካትታል።
ይህን አገልግሎት የሚሰጡ ክልሎችና ከተማ አሰተዳደሮች ለስርጭት የተዘጋጁትን ታርጋዎች በመውሰድ ለተጠቃሚው ህብረተሰብ እንዲያደርሱ ተጠይቋል።
ተገልጋዮች ጥያቄያቸውን በማቅረብ እንዲገለገሉ ተብሏል።
(የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር)
@tikvahethiopia
#ETHIOPIA
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሰጠው መግለጫ ኢትዮጵያ ላይ እየተደረገ ነው ያለው አውድን ያላገናዘበ ፣ አሳሳች የዲፕሎማሲ፣ የሚዲያና የወትዋቾች ዘመቻ በቃ ሊባል ይገባል ሲል አሳውቋል።
ጉባኤው በመግለጫው ፥ ወቅታዊ ሀገራዊ ችግርን መነሻ በማድረግ አንዳንድ የምዕራቡ ሀገራት መንግስታት የያዙትን አቋም ተገቢ አለመሆኑን በመግለፅ አውግዟል።
ድርጊታቸው የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ወዳጅነት እና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ታሳቢ ያላደረገ መሆኑንም አንስቷል።
ከዚህ በተጨማሪ በሀገራዊ የውስጥ ጉዳዮች የሚታዩትን ግልፅ ተፅእኖ እና ጣልቃ ገብነትን እንዲያቆሙና የኢትዮጵያ እውነት ድምፅ እንዲሰማ ጥሪ አቅርቧል።
የምዕራቡ መንግስታት ከተሳሳተ አቋማቸው እንዲመለሱም ጉባኤው ጠይቋል።
ጉባኤው የኢትዮጵያ ጉዳይ አስጨንቋቸው ብሄራዊ ጥቅሟ ሳይሸራረፍ ሀገራዊ ሉኣላዊነት እና ክብሯ እንዲጠበቅ ከጎኗ ለቆሙ ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በሰጠው መግለጫ ኢትዮጵያ ላይ እየተደረገ ነው ያለው አውድን ያላገናዘበ ፣ አሳሳች የዲፕሎማሲ፣ የሚዲያና የወትዋቾች ዘመቻ በቃ ሊባል ይገባል ሲል አሳውቋል።
ጉባኤው በመግለጫው ፥ ወቅታዊ ሀገራዊ ችግርን መነሻ በማድረግ አንዳንድ የምዕራቡ ሀገራት መንግስታት የያዙትን አቋም ተገቢ አለመሆኑን በመግለፅ አውግዟል።
ድርጊታቸው የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ ወዳጅነት እና የዲፕሎማሲ ግንኙነት ታሳቢ ያላደረገ መሆኑንም አንስቷል።
ከዚህ በተጨማሪ በሀገራዊ የውስጥ ጉዳዮች የሚታዩትን ግልፅ ተፅእኖ እና ጣልቃ ገብነትን እንዲያቆሙና የኢትዮጵያ እውነት ድምፅ እንዲሰማ ጥሪ አቅርቧል።
የምዕራቡ መንግስታት ከተሳሳተ አቋማቸው እንዲመለሱም ጉባኤው ጠይቋል።
ጉባኤው የኢትዮጵያ ጉዳይ አስጨንቋቸው ብሄራዊ ጥቅሟ ሳይሸራረፍ ሀገራዊ ሉኣላዊነት እና ክብሯ እንዲጠበቅ ከጎኗ ለቆሙ ሁሉ ምስጋና አቅርቧል።
@tikvahethiopia
" አዲስ አበባ #ሰላማዊ የአፍሪካ ከተማ ናት " - አውሪሊያ ካላብሮ
በኢትዮጵያ የተመድ (UN) የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠናዊ ቢሮ ዳይሬክተሯ ሚስ አውሪሊያ ካላብሮ አዲስ አበባ እጅግ ሰላማዊዋ የአፍሪካ ከተማ ናት ብለዋል።
ዳይሬክተሯ ይህንን የተናገሩት በአፍሪካ ሌዘር ፣ ጨርቃ ጨርቅ ፣ ፋሽን እና የዘርፉ ቴክኖሎጂዎች ኤግዚቢሽን መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
አውሪሊያ ካላብሮ ፥ " አዲስ አበባ ከተማ ከሚወራው እጅግ ተቃራኒ በሆነ ሁኔታ በአፍሪካ እጅግ ሰላማዊ ከሆኑ ከተሞች አንዷ ናት " ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህም ዓለም አቀፍ የቆዳና የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪና የዘርፉ ነጋዴዎች እዚህ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ላይ መገኘታቸውን ገልፀዋል።
ኤግዚቢሽኑ ባለፉት 3 ዓመታት የኮቪድ 19 ካደረሰው ጫና በኋላ አዲስ የንግድ ስልቶችን በመማር የተዘጋጀ ነውም ብለዋል።
ምንጭ፦ አሻም ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
በኢትዮጵያ የተመድ (UN) የኢንዱስትሪ ልማት ቀጠናዊ ቢሮ ዳይሬክተሯ ሚስ አውሪሊያ ካላብሮ አዲስ አበባ እጅግ ሰላማዊዋ የአፍሪካ ከተማ ናት ብለዋል።
ዳይሬክተሯ ይህንን የተናገሩት በአፍሪካ ሌዘር ፣ ጨርቃ ጨርቅ ፣ ፋሽን እና የዘርፉ ቴክኖሎጂዎች ኤግዚቢሽን መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው።
አውሪሊያ ካላብሮ ፥ " አዲስ አበባ ከተማ ከሚወራው እጅግ ተቃራኒ በሆነ ሁኔታ በአፍሪካ እጅግ ሰላማዊ ከሆኑ ከተሞች አንዷ ናት " ሲሉ ተናግረዋል።
በዚህም ዓለም አቀፍ የቆዳና የጨርቃ ጨርቅ ኢንዱስትሪና የዘርፉ ነጋዴዎች እዚህ ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን ላይ መገኘታቸውን ገልፀዋል።
ኤግዚቢሽኑ ባለፉት 3 ዓመታት የኮቪድ 19 ካደረሰው ጫና በኋላ አዲስ የንግድ ስልቶችን በመማር የተዘጋጀ ነውም ብለዋል።
ምንጭ፦ አሻም ቴሌቪዥን
@tikvahethiopia
#Update
ባለፉት 2 ተከታታይ ቀናት በተደረገው ኦፐሬሽን በሸዋ ግንባር የቀወት ወረዳ፣ ለምለም አምባ፣ ጀውሐ፣ ሰንበቴ፣ አጣየ እና ካራ ቆሬ ከተሞችና አካባቢዎች ከህወሓት እጅ ነፃ መውጣታቸውን በጋሸና ግንባር ደግሞ ኮን እና ዳውንት ሙሉ በሙሉ ከአሸባሪው መፅዳታቸውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ አስታወቀ።
ዕዙ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በወረኢሉ ግንባር ልጓማ ከተማ ነጻ መውጣቷን የገለፀ ሲሆን " በተወረሩት አካባቢዎች የጸጥታ ኃይሎች የጋራ ጥምረት ባካሄዱት ኦፐሬሽን በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪው ሕወሐት ጀሌዎች እጃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ " ብሏል።
ዕዙ " አሸባሪው ሕወሐት እየተሸነፈ በመሆኑ በግንባር ያጣውን ድል በሐሰት መረጃ ለመሸፈን እየጣረ ነው " ያለ ሲሆን " አሸባሪው ሕወሐት የኢትዮጵያ ልጆችን ብርቱ ክንድ መቋቋም አቅቶት ሲፍረከረክ፣ የአሸባሪው አመራሮች መሸነፋቸውን ላለማመንና ወጣቶችን ውጤት በሌለው ጦርነት አሁንም ለመማገድ በማሰብ፣ ስልታዊ ማፈግፈግ አድርገናል በማለት ራሱንና ተስፈኛ ጋላቢዎቹን በማጽናናት ላይ ይገኛል " ሲል ገልጿል።
አክሎም፥ " አሸባሪው ሕወሓት ከዚህ በኋላ ለወረራ የገቡ ጀሌዎቹን የሚያድንበት ዐቅም የለውም፡፡ ወደተወረሩ አካባቢዎች የገባው የአሸባሪው ሕወሐት ጀሌ ሁሉም የመውጫ በሮች ተዘግተውበታል። " ሲል አሳውቋል።
" ወራሪው ኃይል በከንቱ ያሰለፋችሁ ወጣቶች ከዚህ በኋላ ማምለጫ እንደሌላችሁ ተገንዝባችሁ፣ እጃችሁን ለጸጥታ አካላት በመስጠት፣ ራሳችሁን እንድታድኑ መንግሥት ያሳስባል " ብሏል ዕዙ።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት ነጻ ያልወጡ አካባቢዎችን በተሟላ መልኩ ነጻ ለማውጣት በተጋድሎ ላይ እንደገሚገኙም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
ባለፉት 2 ተከታታይ ቀናት በተደረገው ኦፐሬሽን በሸዋ ግንባር የቀወት ወረዳ፣ ለምለም አምባ፣ ጀውሐ፣ ሰንበቴ፣ አጣየ እና ካራ ቆሬ ከተሞችና አካባቢዎች ከህወሓት እጅ ነፃ መውጣታቸውን በጋሸና ግንባር ደግሞ ኮን እና ዳውንት ሙሉ በሙሉ ከአሸባሪው መፅዳታቸውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ አስታወቀ።
ዕዙ ዛሬ ባወጣው መግለጫ በወረኢሉ ግንባር ልጓማ ከተማ ነጻ መውጣቷን የገለፀ ሲሆን " በተወረሩት አካባቢዎች የጸጥታ ኃይሎች የጋራ ጥምረት ባካሄዱት ኦፐሬሽን በሺዎች የሚቆጠሩ የአሸባሪው ሕወሐት ጀሌዎች እጃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ " ብሏል።
ዕዙ " አሸባሪው ሕወሐት እየተሸነፈ በመሆኑ በግንባር ያጣውን ድል በሐሰት መረጃ ለመሸፈን እየጣረ ነው " ያለ ሲሆን " አሸባሪው ሕወሐት የኢትዮጵያ ልጆችን ብርቱ ክንድ መቋቋም አቅቶት ሲፍረከረክ፣ የአሸባሪው አመራሮች መሸነፋቸውን ላለማመንና ወጣቶችን ውጤት በሌለው ጦርነት አሁንም ለመማገድ በማሰብ፣ ስልታዊ ማፈግፈግ አድርገናል በማለት ራሱንና ተስፈኛ ጋላቢዎቹን በማጽናናት ላይ ይገኛል " ሲል ገልጿል።
አክሎም፥ " አሸባሪው ሕወሓት ከዚህ በኋላ ለወረራ የገቡ ጀሌዎቹን የሚያድንበት ዐቅም የለውም፡፡ ወደተወረሩ አካባቢዎች የገባው የአሸባሪው ሕወሐት ጀሌ ሁሉም የመውጫ በሮች ተዘግተውበታል። " ሲል አሳውቋል።
" ወራሪው ኃይል በከንቱ ያሰለፋችሁ ወጣቶች ከዚህ በኋላ ማምለጫ እንደሌላችሁ ተገንዝባችሁ፣ እጃችሁን ለጸጥታ አካላት በመስጠት፣ ራሳችሁን እንድታድኑ መንግሥት ያሳስባል " ብሏል ዕዙ።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ የሚመሩት የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት ነጻ ያልወጡ አካባቢዎችን በተሟላ መልኩ ነጻ ለማውጣት በተጋድሎ ላይ እንደገሚገኙም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዕዝ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።
* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
#GONDAR
ዛሬ ከሁመራ አድርጎ ወደ ጎንደር ከተማ በመግባት ላይ ያለ ተሳቢ መኪና ተገልብጦ ሹፌሩን ጨምሮ የ5 ሰዎች ህይወት ጠፋ።
አደጋው በጎንደር ከተማ በፋሲል ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ኩረበረብ ተብሎ እሚጠራው አካባቢ ቀን 8:30 ገደማ የደረሰ ሲሆን 2 ወንድ እና 3 ሴቶች ህይወታቸው ሲያልፍ 3 ሰዎች ላይ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሷል።
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ የአንደኛ ፖሊስ ጣቢያ የማህበሰረብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ም/ ኢንስፔክተር ስማቸው ፈንቴ አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia
ዛሬ ከሁመራ አድርጎ ወደ ጎንደር ከተማ በመግባት ላይ ያለ ተሳቢ መኪና ተገልብጦ ሹፌሩን ጨምሮ የ5 ሰዎች ህይወት ጠፋ።
አደጋው በጎንደር ከተማ በፋሲል ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ኩረበረብ ተብሎ እሚጠራው አካባቢ ቀን 8:30 ገደማ የደረሰ ሲሆን 2 ወንድ እና 3 ሴቶች ህይወታቸው ሲያልፍ 3 ሰዎች ላይ ከባድ የመቁሰል አደጋ ደርሷል።
የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ እንደሚገኝ የአንደኛ ፖሊስ ጣቢያ የማህበሰረብ አቀፍ ፖሊስ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ም/ ኢንስፔክተር ስማቸው ፈንቴ አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia
#EthiopianFederalPolice
መነሻቸውን ብራዚል ሳኦፖሎ መዳረሻቸውን ደግሞ ዱባይና ናይጄሪያ በማድረግ በአውሮፕላን ሲጓዙ የነበሩ የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎች በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ 🇪🇹 ፌደራል ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎቹ 2 ናይጄሪያዊያንና አንዲት ብራዚላዊት ሲሆኑ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተደረገባቸው ፍተሻ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል።
ግለሰቦቹ አደገኛ ዕፁን በውስጣዊ የሻንጣ አካል በመደበቅና ውጠው በሆዳቸው በመያዝ ለማሳለፍ ሙከራ ቢያደርጉም የፌደራል ፖሊስ አባላት ባደረጉት የተጠናከረ ፍተሻ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት 3 የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎቹ መካከል በብራዚላዊቷ ላይ በተደረገ ፍተሻ ከ13 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን 666 ጥቅል ፍሬና በዱቄት መልክ የተዘጋጀ ከ17 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን 11 እሽግ ኮኬይን የተሰኘ አደገኛ ዕፅ በሻንጣዋ ይዛ መገኘቷን ተረጋግጧል።
ሁለቱ ናይጄሪያዊያን አደገኛ ዕፁን በሆዳቸው ይዘው ሊያዘዋውሩ እንደሚችሉ በመጠራጠር በፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል በተደረገላቸው የኤክስ ሬይ ምርመራ የተገኘባቸው ሲሆን 1,650 ግራም የሚመዝን 83 ፍሬ ኮኬይን ከሆዳቸው እንዲወጣ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአሁኑ ወቅት ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጨማሪ ምርመራ እያካሄደ መሆኑ ታውቋል፡፡
@tikvahethiopia
መነሻቸውን ብራዚል ሳኦፖሎ መዳረሻቸውን ደግሞ ዱባይና ናይጄሪያ በማድረግ በአውሮፕላን ሲጓዙ የነበሩ የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎች በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ 🇪🇹 ፌደራል ፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎቹ 2 ናይጄሪያዊያንና አንዲት ብራዚላዊት ሲሆኑ በቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በተደረገባቸው ፍተሻ እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል።
ግለሰቦቹ አደገኛ ዕፁን በውስጣዊ የሻንጣ አካል በመደበቅና ውጠው በሆዳቸው በመያዝ ለማሳለፍ ሙከራ ቢያደርጉም የፌደራል ፖሊስ አባላት ባደረጉት የተጠናከረ ፍተሻ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት 3 የአደገኛ ዕፅ አዘዋዋሪዎቹ መካከል በብራዚላዊቷ ላይ በተደረገ ፍተሻ ከ13 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን 666 ጥቅል ፍሬና በዱቄት መልክ የተዘጋጀ ከ17 ኪሎግራም በላይ የሚመዝን 11 እሽግ ኮኬይን የተሰኘ አደገኛ ዕፅ በሻንጣዋ ይዛ መገኘቷን ተረጋግጧል።
ሁለቱ ናይጄሪያዊያን አደገኛ ዕፁን በሆዳቸው ይዘው ሊያዘዋውሩ እንደሚችሉ በመጠራጠር በፌደራል ፖሊስ ሆስፒታል በተደረገላቸው የኤክስ ሬይ ምርመራ የተገኘባቸው ሲሆን 1,650 ግራም የሚመዝን 83 ፍሬ ኮኬይን ከሆዳቸው እንዲወጣ ተደርጓል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በአሁኑ ወቅት ግለሰቦቹን በቁጥጥር ስር በማዋል ተጨማሪ ምርመራ እያካሄደ መሆኑ ታውቋል፡፡
@tikvahethiopia
የቤህነን ታጣቂ ቡድን መሪ በቁጥጥር ስር ዋለ።
በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ የቤህነን ታጣቂ ቡድን መሪ የሆነው ህድር መሐመድ አሊ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ኢፕድ ዘግቧል።
ግለሰቡ በመንጌ ወረዳ፣ ጎልሞሶ ቀበሌ ነው በቁጥጥር ሥር መዋሉ የተገለፀው።
የታጣቂ ቡድኑ መሪ በቁጥጥር ሥር በዋለ ጊዜ ፦
- 1 ክላሽ
- 2 ካርታ
- 60 የክላሽ ጥይት
- 5 የጭስ ቦምብ
- 1 ሞቶሮላ ሬዲዮ መገናኛ
- የሱዳን ወታደራዊ ልብስ አብሮ ተይዟል።
@tikvahethiopia
በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ የቤህነን ታጣቂ ቡድን መሪ የሆነው ህድር መሐመድ አሊ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ኢፕድ ዘግቧል።
ግለሰቡ በመንጌ ወረዳ፣ ጎልሞሶ ቀበሌ ነው በቁጥጥር ሥር መዋሉ የተገለፀው።
የታጣቂ ቡድኑ መሪ በቁጥጥር ሥር በዋለ ጊዜ ፦
- 1 ክላሽ
- 2 ካርታ
- 60 የክላሽ ጥይት
- 5 የጭስ ቦምብ
- 1 ሞቶሮላ ሬዲዮ መገናኛ
- የሱዳን ወታደራዊ ልብስ አብሮ ተይዟል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
በጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በህወሓት ተይዘው የነበሩ ተጨማሪ ቦታዎች ነፃ ማውጣቱ ተገልጿል።
የፀጥታ ኃይሎች ጥምረቱ ፦
- የመሐል ሜዳ፣
- ጨፋ ሮቢት፣
- ሐርቡና መኮይ ከተሞችና አካባቢውን ነጻ እንዳወጣ የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አሳውቋል።
የኢትዮጵየ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ " ጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ በጥልቀት ገብተው በየቦታው የተበተነውን የአሸባሪውን ጀሌ በመልቀም ላይ ናቸው " ብሏል።
አክሎም ፥ " በጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ የተመታው አሸባሪ ኃይል ዘርፎና አውድሞ፣ መሣሪያውንም ይዞ እንዳይወጣ የየአካባቢው ሕዝብ ተደራጅቶ መንገድ በመዝጋት ፣ የአሸባሪውን ጀሌዎች በመማረክ ፣ እምቢ ባሉትም ላይ ርምጃ በመውሰድ የተለመደ ጀግንነቱን እንዲደግም " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
በጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የሚመራው የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት በህወሓት ተይዘው የነበሩ ተጨማሪ ቦታዎች ነፃ ማውጣቱ ተገልጿል።
የፀጥታ ኃይሎች ጥምረቱ ፦
- የመሐል ሜዳ፣
- ጨፋ ሮቢት፣
- ሐርቡና መኮይ ከተሞችና አካባቢውን ነጻ እንዳወጣ የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት አሳውቋል።
የኢትዮጵየ የመንግስት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፥ " ጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ በጥልቀት ገብተው በየቦታው የተበተነውን የአሸባሪውን ጀሌ በመልቀም ላይ ናቸው " ብሏል።
አክሎም ፥ " በጥምር የጸጥታ ኃይሎቹ የተመታው አሸባሪ ኃይል ዘርፎና አውድሞ፣ መሣሪያውንም ይዞ እንዳይወጣ የየአካባቢው ሕዝብ ተደራጅቶ መንገድ በመዝጋት ፣ የአሸባሪውን ጀሌዎች በመማረክ ፣ እምቢ ባሉትም ላይ ርምጃ በመውሰድ የተለመደ ጀግንነቱን እንዲደግም " ሲል ጥሪ አቅርቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት በሸዋሮቢት ከተማ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ አገልግሎት መመለሱን ዛሬ አሳውቋል። በተጨማሪ በደብረሲና አካባቢ ያሉ አርማንያ፣ አስፋቸውና ጭራ ሜዳ የተባሉ የገጠር ከተሞች ዛሬ የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ የተደረገ መሆኑን አሳውቋል። ደብረሲናና ሌሎች ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያገኙ ለማደረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጿል። የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ…
#Update
በዛሬው ዕለት ደብረ ሲና፣ ጣርማ በር፣ የለን፣ ተሬ፣ ራሳ፣ ኩማሜ እና ሌሎች በሸዋ ሮቢት ዙሪያ ያሉት የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘታቸውን የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።
@tikvahethiopia
በዛሬው ዕለት ደብረ ሲና፣ ጣርማ በር፣ የለን፣ ተሬ፣ ራሳ፣ ኩማሜ እና ሌሎች በሸዋ ሮቢት ዙሪያ ያሉት የገጠር ከተሞች የኤሌክትሪክ ኃይል ማግኘታቸውን የአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት አሳውቋል።
@tikvahethiopia