TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የኬንያው ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታን ጨምሮ የውጭ ልዑካን እና መሪዎች በሚያደርጉት ጥረት የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት የተኩስ አቁም ውሳኔ ላይ ሊደርሱ እንደሚችሉ ኬንያ እምነት እንዳላት የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አመለከቱ።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሪቼል ኦሞሞ እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር በጋራ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥተዋል።

ሪቼል አሞሞ ኢትዮጵያ ለዚህ ቀውስ መፍትሄ የመፈለግ አቅም እንዳላት እና የተኩስ አቁም ሊደረግ እንደሚችል እንደሚያምኑ ተናግረዋል።

ኦሞሞ በዚህ ንግግራቸው የገለጹት ተስፋ ፕሬዝደንት ኡሁሩ ኬንያታ እሁድ ዕለት ካደረጉት ድንገተኛ የኢትዮጵያ ጉብኝት ጋር ሊገናኝ እንደሚችል ዘገባዎች አመልክተዋል።

ብሊንከን በበኩላቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ኢትዮጵያ ውስጥ ተኩስ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።

የአፍሪካ ሕብረት በልዩ መልእክተኛው ኦሊሴንጎን ኦባሳንጆ አማካኝነት ኢትዮጵያ ላይ የጀመረውን የሰላም ጥረት እንደሚደግፉም መግለፃቸውን ዶቼ ቨለ ሬድዮ ዘግቧል።

ዛሬ ኬንያ የገቡት የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከመግለጫው ቀደም ብሎ ከሀገሪቱ ፕሬዝዳንት አሁሩ ኬንያታ ጋር ተገናኝተው ተወያይተዋል። 

@tikvahethiopia
#Somali : የሶማሌ ክልል የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ በማሰራጨት በህብረተሰቡ መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የተንቀሳቀሱ ሚዲያዎች እና ግለሰቦች ላይ እርምጃ መውሰዱን ገለፀ።

የክልሉ መንግስት ኮሚዮኒኬሽን ቢሮ በህዝቡ መካከል የጥላቻ እና ሀሰተኛ መረጃዎችን የሚያሰራጩ አካላት ከዚህ በኋላ ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ አሣስቧል።

የሶማሌ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ሀላፊ አብዲቃድር ረሺድ ዱዓሌ ፥ " እነኚህ አካላት ለረዥም ዘመናት በመከባበርና አብሮ በኖሩ ማህበረሰብ መካከል የጥላቻ ንግግር እና ሀሰተኛ መረጃን በማሰራጨት ግጭት መቀስቀስን ዓላማቸው አድርገው ሲንቀሳቀሱ ቆይተዋል " ብለዋል።

የጥላቻ ንግግር እና ሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከል የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1185/2012 ተላልፈው በመገኘታቸው ምክንያት እነኚህን አካላት ለህግ ማቅረብ መቻሉን ኃላፊው አስታውቀዋል።

" እነኚህ አካላት ብሄርን ከብሄር ማጋጨት አላማቸው አድርገው ቢንቀሳቀሱም የሶማሌ ህዝብ ከመንግስት፣ ከሀገር ሽማግሌዎች፣ ከሀይማኖት አባቶች እና ከጎሳ መሪዎች ጋር በጋራ የሚሰራ በመሆኑ የታሰበው ግጭት ሳይከሰት ቀርቷል " ሲሉ ሀላፊው አክለዋል።

ድርጊቱ በተለይ ሀገሪቷ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ላይ ባለችበት ሰዓት መፈፀሙ ደግሞ ጉዳዩን አሳሳቢ እንደሚያደርገው ገልፀው መንግስት ከዚህ በኋላ በመሰል ተግባር ተሰማርተው የሚንቀሳቀሱ አካላትን እንደማይታገስ ሀላፊው መናገራቸው የክልሉ መንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ዘግቧል።

የክልሉ ኮሚኒኬሽን እርምጃ ተውስዶባቸዋል ስለተባሉት ሚዲያዎች እና ግለሰቦች በግልፅ ያሰፈረው ነገር ያለው የለም።

@tikvahethiopia
ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽህፈት ቤት በዛሬው ዕለት አስታወቀ።

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ፥ የሲዳማ ጌዲዮ አማሮና ቡርጂ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለኢኦተቤ ቴሌቭዥን እንደገለጹት ብፁዕ አቡነ ባርናባስ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኙና ቀደም ሲል በማኅበራዊ ሚዲያ ሲባል እንደነበረው ክፉ እንዳልገጠማቸው አስታውቀዋል።

ምንጭ፦ EOTC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Uganda: ዛሬ በኡጋንዳ በደረሱ 2 የሽብር አደጋዎች 3 ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆሰሉ፡፡ ካምፓላ ሁለት ቦታዎች በደረሱ የአጥፍቶ ጠፊዎች የሽብር ጥቃት ይ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ፖሊስ አስታቋል፡፡ በአደጋው ከቆሰሉት 33 ሰዎች ውስጥ አምስቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል፡፡ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል፡፡…
#UGANDA

የኢትዮጵያ መንግስት በዩጋንዳ መዲና ካማፓላ ከተማ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት አወገዘ፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን አስመልክቶ ባወጣው መግለጫ÷ በትናንትናው ዕለት በካምፓላ ሁለት ቦታዎች ላይ በተፈጸመው የሽብር ጥቃት በንጹሃን ዜጎችና ፖሊስ ባልደረቦች ላይ በደረሰው የሞትና የአካል ጉዳት ማዘኑን ገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ የተፈጸመውን የሽብር ጥቃት በጥብቅ እንደምታወግዝም ነው በመግለጫው የተመላከተው።

ኢትዮጵያና ዩጋንዳ በጋራ ሽብርተኝነትን የመዋጋት ልምድ እንዳላቸው በመጥቀስ ጥቃቱ ዩጋንዳም ሆነ ሌሎች የአፍሪካ አገራት ሽብርተኝነትን የበለጠ በቁርጠኝነት ከመዋጋት እንደማያግዳቸው የኢትዮጵያ መንግስት ገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ ለኡጋንዳ ህዝብና መንግስት እንዲሁም ለሟች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።

ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ/ የውጭ ጉዳዩ ሚኒስቴር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Uganda: ዛሬ በኡጋንዳ በደረሱ 2 የሽብር አደጋዎች 3 ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ቆሰሉ፡፡ ካምፓላ ሁለት ቦታዎች በደረሱ የአጥፍቶ ጠፊዎች የሽብር ጥቃት ይ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰዎች ሲሞቱ 33 ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸውን የከተማይቱ ፖሊስ አስታቋል፡፡ በአደጋው ከቆሰሉት 33 ሰዎች ውስጥ አምስቱ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸውም ተገልጿል፡፡ የተጎጂዎች ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅብ ይችላል፡፡…
ኬንያ በተጠንቀቅ ላይ ናት።

ኬንያ፣ ትናንት በኡጋንዳ ሽብርተኞች ጥቃት መፈጸማቸውን ተከትሎ ዜጎቿ ሁኔታዎችን በንቃት እንዲከታተሉ አሳስባለች።

ናይሮቢ የትኛውንም ዐይነት የሽብር ጥቃት ለመከላከል በሚያስችል ተጠንቀቅ ላይ መሆኗን አስታውቃለች፡፡

በትናንቱ የካምፓላ ፍንዳታ አጥፍቶ ጠፊዎቹን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች ቆስለዋል፡፡

ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ ዝርዝር ማብራሪያን የሰጡት የኡጋንዳ ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ካጉታ ሙሴቬኒ ጥቃቱ በሽብርተኝነት በተፈረጀው አሊያንስ ፎር ዴሞክራሲ (ADF) ሶስት አጥፍቶ ጠፊዎች መፈጸሙን ተናግረዋል፡፡

የኬንያ መንግስት ቃል አቀባይ የሃገራቸው የጸጥታ አካላት በተጠንቀቅ ላይ መሆናቸውንና አጎራባች በሆኑ የድንበር አካባቢዎች ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኬንያውያን ነቅተው አካባቢቺውን እንዲጠብቅና አዳዲስ ነገሮችን ሲመለከቱ ለፖሊስ እንዲያስታውቁም ኮሎኔል ሳይረስ ኦጉና በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ አል ዓይን ኒውስ

@tikvahethiopia
Ethiopian Human Rights Commission - 1.pdf
265.7 KB
ኢሰመኮ፦

የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ከታወጀበት ጊዜ ጀምሮ ከአዋጁ ጋር በተያያዘ በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን አያያዝ የእስር ሁኔታና የታሳሪዎችን ሁኔታ ለመከታተል በሚያስችለው መልኩ መረጃ ማሰባበሰብ አለመቻሉን አሳውቋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በቂርቆስ እና በየካ ክ/ ከተሞች የሚገኙ ፖሊስ ጣቢያዎችንና ማቆያዎችን ጎብኝቷል፤ ታሳሪዎችንና ቤተሰቦቻቸውን አነጋግሯል፤ በክፍለ ከተማና በወረዳ ደረጃ ካሉ ከፖሊስ አባላት እና አመራሮች ጋር ውይይት በማድረግ መረጃዎችን አሰባስቧል፡፡

በአንጻሩ የአዲስ ከተማ፣ የልደታ፣ የጉለሌ፣ የቦሌ እና የአራዳ ክፍለ ከተማ ኃላፊዎች ከበላይ ትእዛዝ ካልመጣልን መረጃ አንሰጥም፣ እስረኛም መጎብኘት አትችሉም በማለታቸው ኮሚሽኑ በአዋጅ የተሰጠውን ተግባር እና ኃላፊነት እንዳይወጣ ምክንያት ሆነዋል፡፡

በኮሚሽኑ ክትትል የታሰሩ ሰዎችን ብዛት በሚመለከት የተሟላ መረጃ ለማግኘት እንዳልቻለ አሳውቋል።

ኮሚሽኑ በአንጻራዊነት የተሟላ መረጃ ያገኘው ከቂርቆስ ክ/ከተማ ሲሆን መረጃው በተሰጠበት ኅዳር 2/2014 ዓ.ም በክፍለ ከተማው ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ጋር በተያያዘ 714 ሰዎች መታሰራቸውንና ከነዚህ ውስጥ 124ቱ ሴቶች እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።

በሌሎች ክ/ከተሞች በተመሳሳይ ሁኔታ እስሮች ሲከናወኑ ስለነበርና በቁጥጥር ስር የማዋሉ ሂደት አሁንም የቀጠለ በመሆኑ በአዲስ አበባ ብቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መታሰራቸው ይገመታል።

በድሬዳዋ ደግሞ እስከ 300 የሚሆኑ ሰዎች ታስረዋል።

የተወሰኑ ሰዎች በሚመለከታቸው የፀጥታ አካላት መረጃ መሰረት የሚታሰሩ ሲሆን አብዛኛዎቹ ግን ከህብረተሰቡ ተገኘ በተባለ ጥቆማ መሰረት በቁጥጥር ስር እንደሚውሉና ከመካከላቸው የትግራይ ተወላጆች የሆኑ ሰዎች ብዛት ከፍተኛ ነው።

* ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል (PDF)

@tikvahethiopia
#Somalia #Ethiopia #Sudan #SouthSudan

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን እና የኢጋድ ዋና ፀሀፊ ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ሶማሊያ ባሉ አሁናዊ ሁኔታዎች ዙሪያ ላይ ተወያይተዋል።

ውይይቱን በተመለከተ አንቶኒ ብሊንከን በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው ላይ ፥ ውጤታማ ውይይት መደረጉን ገልፀዋል ።

ዶ/ር ወርቅነህ ገበየሁ በበኩላቸው ቀጠናዊ ሰላም እና ደህንነት፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በሌሎችም ቀጠናዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ከአንቶኒ ብሊንከን ጋር መወያየታቸውን በይፋዊ የፌስቡክ ገፃቸው ላይ ገልፀዋል።

ዶ/ር ወርቅነህ ፥ " በቀጣይም ከአሜሪካ ጋር በበርካታ ዘርፎች አብረን እንሰራለን " ያሉ ሲሆን " አሜሪካ የኢጋድ ወሳኝ አጋር ናት "ብለዋል።

Photo : Secretary Antony Blinken

@tikvahethiopia
የልዩ ዕድል ሎተሪ የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች ፦

1ኛ. 20,000,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 1535477

2ኛ. 10,000,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 0165840

3ኛ. 5,000,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 0411256

4ኛ. 3,000,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 1543809

5ኛ. 1,500,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 0503560

6ኛ. 750,000 ብር የሚያስገኘው የ6ኛ ዕጣ ቁጥር 0837825

7ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ7ኛ ዕጣ ቁጥር 1907437

8ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 20,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 30688

9ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 10,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 02294

10ኛ. 20 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 5,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 96608

11ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 2,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 3696

12ኛ. 200 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,000 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 5789

13ኛ. 2,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 500 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 846

14ኛ. 20,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 300 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 67

15ኛ. 200,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 100 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 4 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡

ምንጭ፦ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

4 ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ በንብረት ግምጃ ቤት ውስጥ የተቀመጡ ከ 1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ህዳር 8 ቀን 2014 ዓ/ም በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 በሚገኘው ጠቅላይ ቤተ ክህነት ግቢ ውስጥ በህዝብ ጥቆማ እና ፖሊስ ባደረገው ብርበራ ከ1 ሺህ 800 በላይ ጥይቶች በቁጥጥር ስር መዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ።

በቤተ ክህነቱ ግቢ በሚገኝ የንብረት ግምጃ ቤት በሚገኝ የፅህፈት እና የፅዳት እቃዎች ማስቀመጫ ውስጥ በተደረገው ብርበራ የተገኙት 1ሺህ 363 የብሬን እና 493 የሽጉጥ ጥይቶች ናቸው፡፡

በተጨማሪም 2 የጥይት ማስቀመጫ ሳጥኖች እና 1 የክላሽን-ኮቭ ጠብመንጃ ካዝና ተይዟል፡፡

ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ 1 ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራ ሲሆን ህብረተሰቡ በስልክ፣ በአካል እና ሌሎች የመገናኛ አማራጮችን በመጠቀም እየሰጠ የሚገኘው ጥቆማ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፥ " አሸባሪው የህወሃት ቡድን ለሽብር ተግባሩ የሚጠቀምባቸውን የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች በተለያዩ የኃይማኖት ተቋማት ውስጥ ሲያከማች እና በኃይማኖት ሽፋን የሚንቀሳቀሱ አንዳንድ ግለሰቦችን በተላላኪነት እያሰማራ በበርካታ ንፁሃን ላይ አሰቃቂ እልቂት ሲፈፅም እንደቆየ ይታወሳል " ብሏል።

@tikavhethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Sidama ከነገ ጀምሮ በሲዳማ ክልል የሰአት እላፊ ገደብን ጨምሮ ሌሎች ክልከላዎች ተላለፉ። የሲዳማ ክልል ኮማንድ ፖስት ከነገ ጀምሮ ገደብ የተጣለባቸውን የሰአት እላፊ፣ የእንቅስቃሴዎች ገደብ እና ክልከላዎችን ይፋ አድርጓል። በዚህ መሰረት ፦ - ባለሁለት እግር ተሽከርካሪ ሞተር ሳይክል (ታርጋ ያለው ብቻ) አንድ ሰው ጭኖ ከጠዋት 12 ሰዓት እስከ ምሽቱ 1 ሰዓት ባለ ሦስት እግር ተሽከርካሪ…
#Oromia

በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚኖረውን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ለማስቀጠል ሲባል በክልሉ የሰዎችና ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱ ተገልጿል።

የክልሉ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሰዎችም ሆኑ ተሸከርካሪዎች ሕግና ስርዓትን አክብረው በማንኛውም ሰዓት መንቀሳቀስ እንደሚችሉ አሳውቋል።

በተለያዩ ቦታዎች ላይ ፍተሻዎች ስለሚኖሩ ማንኛውም በክልሉ የሚዘዋወር ሰው መታወቂያ መያዝ እንዳለበት ማሳሰቢያ ተላልፏል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
" የትምህርት ስራ ከብሔርና ከፖለቲካ ነፃ ማድረግ ይገባል " ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ማህብርሰብ ጋር እየተወያዩ ነው ።

ሚኒስተሩ ከዩንቨርስቲው ማህበረሰብ ጋር የሚደርጉት ውይይት የአዲስአበባ ዮንቨርስቲን ችግሩች ለመፍታትና በቀጠይ የዩንቨርስቲውን አቅም ለማሳደግ ስራ ለመስራት እንደሆነ ተገልጿል።

ፕ/ር ብርሃኑ ፤ የትምህርት ስራ ከብሔርና ከፖለቲካ ነፃ ማድረግ እንደሚገባ በመድረኩ ላይ ተናግረዋል።

በውይይት መድረኩ ከዩንቨርስቲው የተለያዩ የትምህርት ክፍል የመጡ ተወካዩች ለትምህርት ሚኒስተሩ በቀጣይ መደርግ ያለባቸውን እና የነበሩ ከፍተቶች ተነስቷል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ትምህርት ቴሌቪዥን(ጋዜጠኛ ነፃነት ጌታቸው)

@tikvahethiopia