TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
58.9K photos
1.5K videos
211 files
4.07K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#WFP

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለትግራይ ክልል ሰብዓዊ ዕርዳታ ለማቅረብ ዛሬ ወደ መቐለ በረራ ጀምሯል።

ተቋሙ በረራውን ያደረገው ያቀረበው ጥያቄ በመንግስት ተቀባይነት አግኝቶ መሆኑ ነው የተገለፀው።

ከአዲስ አበባ ስድስት ሰዎችን ይዞ ወደ መቐለ የበረረው አውሮፕላን ንብረትነቱ የተባበሩት መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም ነው።

ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ የተደረገው በረራ ድጋፉ በምግብ እና ስነ-ምግብ አቅርቦት የሚሳተፉ በክልሉ በ21 ወረዳዎች ለሚሰሩ ሰራተኞች ደመወዝ፣ ለስራ ማስኬጃ፣ ለምግብ ቁሳቁስ መጫኛና ማውረጃ የሚውል ገንዘብ መሆኑ ተጠቁሟል።

አውሮፕላኑ በዛሬው እለት መቐለ ደርሶ ወደ አዲስ አበባ መመለሱ ተገልጿል።

መንግስት የሰብዓዊ ድጋፉ በአውሮፕላን ማከናወን ለሚፈልጉ አካላት ሲወጡም ሆነ ሲገቡ የቦሌ አውሮፕላን ማረፊያን ብቻ እንዲጠቀሙ መመሪያ ማውጣቱ አይዘነጋም። #ENA

@tikvahethiopia
#Update

ደቡብ አፍሪካ ለምትገኙ የቲክቫህ አባላት :

በደ/አፍሪካ ሰሞኑን አመፅ የነበረባቸው ቦታዎች በአንፃራዊ ሁኔታ መረጋጋት እየታየ ይገኛል።

የኩዋዙሉ - ናታል አስተዳደር (Town of KwaNongoma) በተፈፀመዉ ጥፋት ምክንያት የንግድ ተቋማት አለመከፈታቸዉን አስታዉቋል።

የህግ አካላቶች በማንኛዉንም የትራንስፖርት መንገዶች በፒተርማርስበርግ ፍተሻ እያደረጉ ሲሆን በበርገር መንገድ ዘራፊዎችን ከነ መረጃ ማሠራቸዉን ገልፀዋል።

ከመንገድ ትራንስፖርት ባገኘነዉ መረጃ በፑማላንጋ R40 የማርሼ (R40 to Marite area.) መንገድ ላይ በሚያልፋ መኪናዎች ላይ ድንጋይ እየተወረወረ ስለሚገኝ ባትጠቀሙ ይከመራል።

በዚያዉ አካባቢ ሀዚቪዉ አቀጣጫም ቡሽባክ እሪጅ ተመሳሳይ ችግር እንዳለ ከስፍራዉ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።

ከቅዳሜ ጠዋት ጀምሮ በዘረፋዉ በብርቱ ተሳትፈዋል ከሚባሉት በጆርጅ ጎሽ ሆስፒታል ጆሐንስበርግ (George Goch Hostel) አካባቢ የህግ አካላቶች ተደራጅተዉ የቤት ለቤት አሰሳ አድርገዉ የነበረ ቢሆንም አንድም ሰዉ እንኳን አለማግኘታዉ አግርሞትን የፈጠረ ሲሆን ማምሻዉን በድጋሚ በተከናወነ ፍተሻ ፖሊስ 20 ተጠርጣሪዎችን ማሠሩን ከኤስ.ኤ.ቢ.ሲ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

Faya (Tikvah-Family)
Limpopo
South Africa

@tikvahethiopia
"...ሰዎቹን በህይወት የማግኘት እድሉ ጠባብ ነው" - ፖሊስ

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ምስራቅ ደንቢያ ወረዳ 13 የሚደርሱ ሰዎችን አሳፍራ በጣና ሃይቅ ጉዞ የጀመረች አነስተኛ ጀልባ ተሰወረች።

የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት ሃላፊ ምክትል ኮማንደር ቸርነት አስማረ ጀልባዋ የተሰወረችው በወረዳው አዲሰጌ ድንጌ ተብሎ ከሚጠራ ቀበሌ አባን ላይ ጎጥ መነሻቸውን በማድረግ ወደ ጎርጎራ ወደብ ጉዞ ከጀመረች በኋላ ነው ብለዋል።

ተጓዥቹ ሐምሌ 9 ቀን 2013 ዓም ለሊት ድንች ጭነው ጉዞ መጀመራቸውን ከቤተሰቦቻቸው መረጃው ለፖሊስ መድረሱን ገልፀዋል።

ተሳፋሪዎቹ ከ10 እስከ 13 እንደሚደርሱና አብዛኞቹም በስም ዝርዝር መለየታቸውን የገለፁት ምክትል ኮማንደሩ ተሳፋሪዎቹ ከመዳረሻው ጎርጎራ ወደብ እንዳልደረሱ መረጋገጡን ተናግረዋል።

ከትናንት እኩለ ቀን ጀምሮ በሁለት ቡድን የተዋቀረ የፖሊስና የባለሙያዎች ቡድን ፍለጋ እያካሄደ መሆኑን አመልክተው እስካሁን ምንም አይነት ፍንጭ ማግኘት እንዳልተቻለ አስታውቀዋል።

በዛሬው እለት ፍለጋው መቀጠሉን ጠቁመው ተጓዦቹ ክረምት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወይ በማዕበል ተወስደዋል፤ አለበለዚያም ከአቅም በላይ በሆነ ጭነት ጀልባዋ ሰምጣለች የሚል ድምዳሜ ላይ መደረሱን አብራርተዋል።

ተጓዦቹ የተነሱበት ሰዓት ለሊት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ፍለጋውን አስቸጋሪ እንዳደረገው ጠቅሰው ከዚህ በኋላ ሰዎችን በህይወት የማግኘት እድሉ ጠባብ እንደሆነም አመልክተዋል።

ከመነሻው እስከ መዳረሻው ድረስ ያለው የውሀ ላይ ጉዞ የ15 ኪሎ ሜትር ርቀት እንዳለው አመልክትው በፍለጋው የሚገኘውን ዝርዝር ውጤት በቀጣይ ህዝቡ እንዲያውቀው እንደሚደረግ አስታውቀዋል። #ኢዜአ

@tikvahethiopia
#EMA

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን (ኢመብባ) በኢትዮጵያ ውስጥ የሚሰሩ ሁሉም መገናኛ ብዙሃን የሀገሪቱን ሉዓላዊ ግዛት ጥያቄ ውስጥ የሚከቱ ስያሜዎችን ከመጠቀም እንዲቆጠቡ አሳሰበ።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰሜን የኢትዮጵያ ክፍል የሚደረገውን ኦፕሬሽን ጋር ተያይዞ በመደበኛም ሆነ በበየነመረብ የሚሰሩ ዜናዎች እና ፕሮግራሞች ላይ ክትትል ማድረጉን የገለፀ ሲሆን በክትትሉ ወቅት ህግን ያላከበሩ አዘጋገቦችን ተመልክቻለሁ ብሏል።

በዋነኝነት በኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሽብርተኛ ተብሎ የተፈረጀውን ህወሓትን የትግራይ መከላከያ ሰራዊት / ኃይል / የሚል ስያሜ መጠቀም መሆኑን አንስቷል።

በክልል ደረጃ "የመከለከያ ሰራዊት" የሚባል ኃይል አለመኖሩን የገለፀው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ እንዲህ አይነት ስያሜ የኢትዮጵያን ሉዓላዊ ግዛት ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ የሀገር ደህንነትን እና የኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም የሚጎዳ ነው ብሏል።

የህዝብ ተወካዮች ም/ ቤት ጥቅምት 2013 ዓ/ም የቀድሞው የትግራይ ክልል መንግስት በህገ - መንግስት ሽሮ አዲሱን ግዚያዊ አስተዳደር አቋቁሟል ሲል ያስታወሰው ኢመብባ ምርጫ ቦርድ በክልሉ ምርጫ አካሂዱ ክልሉን የሚያስተዳድረው አካል እስኪመረጥ ድረስ በአንዳንድ ሚዲያዎች ዘገባ ውስጥ እምደሚታየው "የትግራይ ክልል መንግስት" የሚባል አካል የለም ብሏል።

በክልሉ ምርጫ እስኪካሄደ ድረስ ትግራይን እንዲመራ ስልጣን የተሰጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ ነው ሲልም አክሏል።

የኢመብባ ፥ መደበኛ ሆኑ የበየነ መረብ ሚዲያዎች "የትግራይ መከላከያ ሰራዊት/ኃይል/" እንዲሁም "የትግራይ ክልል መንግስት" የሚል ስያሜ ከመጠቀም ተቆጠቡ ሲል አሳስቧል።

መ/ ቤቱ ስያሜዎቹን ሲጠቀም በተገኘ የመገናኛ ብዙሃን ተቋም ላይ ጠንካራ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

@tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Update

ደ/አፍሪካ ነዋሪ ለሆናችሁ የቲክቫህ አባላት :

በፕሪቶሪያ #ሞሬሌታ_ፖርክ የሚገኘዉ ፕላስቲክ ቪዉ ድርጅት ለሊቱን በተነሳ እሳት ዉድመት ደርሶበታል።

ፓርክ ቪው ሰሞኑን በደ/አፍሪካ በነበረው አመፅ እና ዘረፋ ጉዳት ያልደረሰበት አካባቢ ነበር። ሆኖም በአሳዛኝ ሁኔታ ምክንያቱ ባልታወቀ መነሻ ትላንት ለሊቱን በእሳት አደጋ ጉዳት ደርሶበታል።

በቃጠሎዉ የተነሳ ሰዎች ላይም ጉዳት መድረሱን ከአካባቢዉ የሚወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ ።

በአካባቢው የምትገኙ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች ጥንቃቄ አይለያቹ።

በሌላ በኩል በደ/አፍሪካ ፍትህ ሚኒስቴር ዘረፋዉ ላይ የተሳተፉ ግለሠቦችን ለመዳኘት የሚያስችል ከመደበኛዉ የሕግ ስርዓት በተለየ የሚሰራ ፍርድ ቤት እና የፍርድ አሠጣጥ ህግ በኩዋዙሉ ናታል ተግባራዊ አድርጓል።

Video credit : Ek media

Faya (Tikvah-Family)
Limpopo
South Africa

@tikvahethiopia
#TokyoOlympics2020

የቶኪዮ ኦሊምፒክስ ከመጀመሩ ከ5 ቀናት በፊት በአትሌቶች መንደር ውስጥ 2 ስፖርተኞቸ ኮሮና ቫይረስ ተገኘባቸው።

ስፖርተኞቹ ለቫይረሱ ታጋላጭ የሆኑ የመጀመሪያዎቹ ተወዳዳሪዎች ሆነዋል፡፡

2ቱ ስፖርተኞች ቅዳሜ ዕለት ተመርምረው ቫይረሱ ከተገኘባቸው ባለሥልጣን ጋር በተመሳሳይ ቡድንና ስፖርት ዘርፍ የሚገኙ ናቸው ሲሉ አዘጋጆቹ አሳውቀዋል።

ሌሎች የቡድኑ አባላት በክፍላቸው ተለይተው እንዲቀመጡ ተደርጓል።

በመንደሩ ቫይረሱ የተገኘባቸው #የመጀመሪያዎቹ ስፖርተኞቹ ሲሆኑ ሌላ ቦታ አንድ ተጨማሪ ስፖርተኛ እሑድ ዕለት በተመሳሳይ ቫይረሱ ተገኝቶበታል፡፡

በአጠቃላይ እሁድ ዕለት ጋዜጠኞች፣ ተባባሪ አካላትን እና ሌሎች ሠራተኞችን ጨምሮ ከኦሎምፒክ ጋር የተገናኙ 10 አዳዲስ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች አዘጋጆቹ ሪፖርት አድርገዋል፡፡

በቶኪዮ የቫይረሱ ስርጭት መጠን እየጨመረ ሲሆን ለአራት ተከታታይ ቀናት ከ 1 ሺህ በላይ አዳዲስ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ተመዝግበዋል፡፡

ብዙ ጃፓናዊያን በዚህ ወቅት ይህ ውድድር መካሄዱን እንደሚቃወሙ የተደረጉ ጥናቶች እንደሚያሳዩ ቢቢሲ በድረገፁ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#Update

ሁሉም ክልሎች በሚባል ደረጃ (የድሬዳዋ ከተማን ጨምሮ) የፀጥታ ኃይላቸውን ወደሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል እያሰማሩ ይገኛሉ።

የጋምቤላ፣ ሀረሪ እና ሱማሌ ክልል የፀጥታ ኃይሎች የተመደበላቸውን የግዳጅ ቀጠና መነቅሳቀሳቸው ታውቋል።

የየክልሉ ልዩ ኃይሎች ወደግዳጅ ቀጠና ከመሄዳቸው ቀደም ብሎ በየክልላቸው መንግስት የሽኝት መርሃግብር ተደርጎላቸው።

የኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት እንደሳወቀው ከሆነ የፌዴራሉ ፀጥታ ኃይሎች እንዲሁም የክልል የፀጥታ ኃይሎች በተመደቡበት ቦታ ቦታቸውን እየያዙ ናቸው።

@tikvahethiopia
ሼይኽ መሐመድ ሁሴን አሊ አል አሙዲ በችግር ላይ ላሉና ለአቅመ ደካሞች ድጋፍ አደረጉ።

#ኢትዮጵያዊው ባለሃብት ሼይኽ መሐመድ ሁሴን አሊ አል አሙዲ ለመጪው የኢድ አል አድሃ አረፋ በዓል በወሎ በተለያዩ አካባቢዎች በችግር ላይ ላሉ እና በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ አቅመ ደካሞች የሚከፋፈል 106 በሬዎችን እና 100 በግ እና ፍየሎችን ለኡዱሂያ ድጋፍ አድርገዋል።

ሼይኽ መሀመድ አል አሙዲ ለኡዲሂያ እንዲሆን በማሰብ ድጋፍ ያደረጓቸው በሬዎች ፣በጎች እና ፍየሎች በወሎ በችግር ላይ ለሚገኙ ወገኖች እና በአዲስ አበባ ለሚገኙ አቅመ ደካሞችም በተለያዩ መስጂዶች እና ተቋማት በኩል እንዲከፋፈል መደረጉ ተገልጿል።

መረጃው የተገኘው ከኡስታዝ አቡበክር አህመድ ነው።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት 4,102 የኮቪድ-19 ላብራቶሪ ምርመራ ያከናወነች ሲሆን 81 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተግኝተዋል፤ ሶስት ሰው ህይወቱ ያለፈ ሲሆን 49 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአፋር ክልል "ህወሓት" ጦርነት ከፈተብኝ አለ። የአፋር ክልላዊ መንግስት ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው 'ህወሓት' ፥ "የሽብር ድርጊቱን ወደ አፋር በማስፋት የአፋር አርብቶ አደር ህዝብ ላይ ጦርነት ከፍቷል" ሲል ገልጿል። ክልሉ "ህወሓት" ጦርነት ከፈተብኝ ያለው በፈንቲ ረሱ ዞን ያሎ ወረዳ በኩል ነው። አፋር ክልል በመግለጫው ላይ ፥…
#Afar

ትላንት የአፋር ክልላዊ መንግስት በህ/ተ/ምክር ቤት ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው 'ህወሓት'፥ "የሽብር ድርጊቱን ወደ አፋር በማስፋት የአፋር አርብቶ አደር ህዝብ ላይ #ጦርነት ከፍቷል" ማለቱ ይታወሳል።

ክልሉ 'ህወሓት' ጦርነት ከፈተብኝ ያለው ፈንቲ ረሱ ዞን ያሎ ወረዳ በኩል ነው ፤ የክልሉ መንግስት የተከፈተበትን ጦርነት ከህዝብ ጋር በመተባበር እንደሚመክት መግለፁ አይዘነጋም።

የአፋር ክልል ሰላም እና አስተዳደር ቢሮም ትላንት ጧቱ 2 ሰአት ጀምሮ "ህወሓት" በያሎ ወረዳ በንጹሃን አርብቶአደሮች ላይ በከፈተዉ ድንገተኛ ጥቃት በሰዉና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ሪፖርት አድርጓል።

ቢሮው፥ ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ አርብቶ አደሮች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ያሳወቀ ሲሆን ቡድኑ የተለያዩ የግለሰብ ቤቶችን ላይ ዝርፊያ መፈፀሙን ገልጿል።

ህወሓት የከፈተውን ጥቃት ተከትሎ ወደስፋራዉ የደረሰዉ የአፋር ልዩ ሃይልና የአካባቢዉ ህብረተሰብ የመከላከል እርምጃዎችን በመውሰድ የቡድኑን አላማ ማክሸፍ መቻሉን አስረድቷል።

'ህወሓት' በአፋር ክልል በከፈተው ጥቃት ወደክልሉ ይጓጓዝ የነበረው የሰብዓዊ ድጋፍ ተስተጓጉሏል።

የህ/ተ/ም/ቤት ሽብርተኛ ብሎ የፈረጀው 'ህወሓት' አፋር ውስጥ ጥቃት መፈፀሙን አምኗል። ቡድኑ ጥቃት ፈፅመኩኝ ያለው የመንግሥት ደጋፊ ወታደሮች ላይ ነው።

አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ለAFP በሰጡት ቃል አፋር ክልል ውስጥ ጥቃት መፈፀማቸውን ገልፀው ጥቃቱ "ውስን ርምጃ ነበር" ብለዋል።

ጥቃቱ ያነጣጠረው በትግራይ እና አፋር ድንበር አካባቢ ተሰባስበው የነበሩ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ላይ ነበር ያሉት አቶ ጌታቸው፥ "ርምጃውን የወሰድነው እነዚህን ሃይሎች ወደ ኦሮሚያ እንዲመለሱ ለማድረግ ነበር፤ ይህም ተሳክቶልናል" ብለዋል።

telegra.ph/Afar-07-18

@tikvahethiopia
* Addis Ababa Police

የአዲስ አበባ ፖሊስ ወንጀልና ሊያጋጥሙ የሚችሉ ሌሎች የፀጥታ ችግሮችን አስቀድሞ ለመከላከል እንዲቻል መኖሪያ ቤት እና የመኝታ አገልግሎት የሚሰጡ ልዩ ልዩ ድርጅቶችና ግለሰቦች የተከራዮችን ማንነት እንዲያረጋግጡ አሳስቧል።

በአ/አ በተለያዩ አካባቢዎች ማንነታቸውን ሰውረው መኖሪያ ቤቶችን እና መኝታ ቤቶችን በመከራየት የወንጀል ተግባራትን ለመፈፀም አቅደው የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ስለመኖራቸው የፖሊስ የምርመራ መዛግብት እንደሚያስረዱ ገልጿል።

በዋናነት ፦
- የመኖሪያ ቤት የሚያከራዩ ግለሰቦች ፤
- የመኝታ አገልግሎት በሚሰጡ ሆቴሎች፣
- ፔንሰሊዮኖችና ተመሣሣይ አገልግሎት የሚሰጡ የንግድ ቤቶች ማንነታቸው በግልፅ ላልታወቁ ሰዎች ቤት እንዳያከራዩ እንዲሁም በሚያከራዩበት ወቅት የተከራዩን ማንነት የሚገልፁ የነዋሪነት መታወቂያና ሌሎች ሰነዶችን በሚገባ አረጋግጠው በመመዝገብ ይህንንም በየአቅራቢያቸው ለሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸው ፖሊስ ዛሬ ባሠራጨው መልዕክት አሳስቧል፡፡

☎️ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙ ለፖሊስ ጥቆማ መስጫ ስልክ ቁጥሮች ከላይ ባለው ምስል ላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

''አመጽና ጦርነት ለማቆም መቼም ቢሆን አይረፍድም። ለህዝብ ጥቅም ልንይዘው የሚገባን ብቸኛው መንገድ የእርቅ እና ሰላም አማራጭ ነው'' - የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጳጳሳት መልእክት

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ጳጳሳት ከሐምሌ 6 እስከ ሐምሌ 9 2013 ዓ.ም. በሞጆ የኮንሰላታ አባቶች ካቶሊክ ገዳም መደበኛ ጉባኤ አካሂደዋል።

በተለያዩ የቤተክርስቲያንና የሀገር ውስጥ ጉዳዮች ጥልቅ ውይይቶችን ማድረጋቸውንም ከጉባኤው በኋላ ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።

በመልዕክቱ የተነሱ አንኳር ነጥቦች መካከል ፦

- ጦርነት ላይ የሚሳትፉ ሁሉ ጦርነት ሕይወት የማጥፋት ፣ ንብረት ከማውደም ሀገርን ከማደህየት ያለፈ ውጤት እንደሌለው ተረድተው የህዝባችን የመኖር ምርጫ ሁሉ የሠላም ግንባታና የእርቅ ሥራ እንዲሆንና እንዲቀጥል አሁንም ደግመን ደጋግመን እንማፀናለን።

- የህዝብን ስቃይ ሊያቃልሉ በሚችሉ ሰብአዊ ድጋፎች የምትሳተፉ ሁላችሁም ማንም የድጋፉ ተጠቃሚ ሳይሆን ወደኋላ እንዳይቀር እንማጸናለን። ለዚህም መሠረታዊ ሰብአዊ ደጋፍ ለሁሉም ወገኖች እንዲዳረስ ሁሉም ወገኖች ያልተገደበ ጥረትና ቀናተኛነት እንዲያሳዩ እናሳስባለን።

- ወደጦርነት መግባት ለተፈጠሩ ስህተቶች ማረሚያ ወይም ለተፈጠረው አለመግባባት መልስ ሊሰጥ በፍጹም እንደማይችል በሁሉም ዘንድ የታወቀ ይሆናል። ምክንያቱም ጦርነት መቼም የሰላም መፈለጊያ መንገድ ሆኖ አያውቅም።

- እኛ እንደእረኞች ለህዝባችን ልንሰጣችሁ የምንችለው ብቸኛ ነገር በክርስቶስ አማካይነት በእግዚአብሔር ያለን እምነት የሚመነጭ ተስፋ ነው። አመጽና ጦርነት ለማቆም መቼም ቢሆን አይረፍድም። ለህዝብ ጥቅም ልንይዘው የሚገባን ብቸኛው መንገድ የእርቅ እና ሰላም አማራጭ ነው።

@tikvahethiopia
#ItsMyDam

የግድባችን ሁለተኛው ዙር ውሃ ሙሌት እየተከናወነ ነው።

ግብፅ እና ሱዳን የግድባችንን ጉዳይ ወደተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ይዘውት ቢሄዱም ይህን ነው የሚባል ለውጥ አላመጡም ይልቁንም አብዛኛው የምክር ቤቱ ሀገራት ከሁለቱ ሀገራት በተቃራኒ የግድቡ ጉዳይ በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት መፍትሄ እንዲፈለግለት የሚል አቋም አንፀባርቀዋል።

ከምክር ቤቱ ስብሰባ በኃላ ግብፆቹም ሆኑ ሱዳኖቹ አላረፉም፤ ከተለያዩ ሀገራት ጋር በግድቡ ጉዳይ ሃሳባቸውን ለማስረፅ እና ለማሳመን እየተነጋገሩ ነው።

ለአብነት ዛሬ የግብፁ ፕሬዜዳንት ከቻይናው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ስለግድቡ መክረዋል።

የግብፅ እና ሱዳን ሚዲያዎችም ቢሆኑ በየቀኑ ስለግድባችን ሳያነሱ አያልፉም። አሁንም ስለግድባችን የተሳሳቱ መረጃዎች ከማሰራጨት አልተቆጠቡም።

Egyptian Independent በተባለው ሚዲያ ብቻ ባለፉት 4 ቀናት ውስጥ ሰባት (7) የታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ ያተኮሩ ዘገባቸው ተሰርተዋል። በሌሎች ሚዲያዎች እንደነ Egypt Today ፣ Al-Ahram ፣ Daily News Egypt ላይ በርካታ ዘገባዎች ሲሰሩ ነበር።

ከፍተኛ መነጋገሪያ የነበረው ግን በ #Egypt_Today ላይ የወጣውና በሀገራችን ሚዲያዎች ተተርጉሞ የተሰራጨው ፕሬዜዳንት አል ሲ ሲ ሃያ ከሪማ ብሄራዊ ኮንፈረንስ ላይ ያደረጉት ንግግር ነው።

ንግግራቸው በሀገራችን ግዙፍ የሆኑ የሚዲያ ተቋማት ከአውድ ውጭ ተተርጉሞ/ሆን ተብሎ ብዙዎችን አሳስቷል። አንዳንዶች ግብፅ አቋም የቀየረች እንዲመስላቸው ሆኗል።

በእርግጥ የግብፁ ፕሬዜዳንት አል ሲ ሲ ምንድነው ያሉት ? ያንብቡ telegra.ph/Grand-Ethiopian-Renaissance-Dam-07-18

@tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ሁለተኛው ዙር ሙሌት #ዛሬ_ለሊት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተሰምቷል።

የውሀው መጠን ግንባታው የደረሰበት ከፍታ ላይ ደርሶ ዛሬ ለሊት ሞልቶ ይፈሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው "የሪፖርተር ጋዜጣ ድረገፅ" ሲሆን መረጃውን ከፕሮጀክቱ ስፍራ ማግኘቱን ገልጿል።

@tikvahethiopia