TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.3K photos
1.51K videos
212 files
4.11K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Audio
AudioLab
የኢትዮጵየ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድን መግለጫ በቀጥታ መከታተል ላልቻላችሁ ቤተሰቦቻችን የድምፅ ቅጂውን አያይዘነዋል (9 MB) ።

የተነሱ ዋና ጉዳዮች ያልናቸውን በፅሁፍ የምናጋራችሁ ይሆናል።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

ምርጫ ከተደረገባቸው 440 ምርጫ ክልሎች ውስጥ 221 የሚሆኑ የምርጫ ክልሎች ውጤቶቻቸውን መለጠፋቸውን ወይዘሪት ሶሊያና አሳውቀዋል።

ከምርጫ ክልሎቹ መካከል ከ50 % በላይ የሚሆኑት ናቸው ጊዜያዊ የምርጫ ውጤቶቻቸውን የለጠፉት።

በአማራ ክልል 40 የምርጫ ክልሎች ውጤት የለጠፉ ሲሆን በኦሮሚያ 125 የምርጫ ክልሎች ውጤት ለጥፈዋል ተብሏል።

አዲስ አበባ ከተማ ባሉ 10 የምርጫ ክልሎች ውጤት አሳውቀዋል፤ በከተማ ያሉ ሌሎች የምርጫ ክልሎች ቆጠራ አለመጠናቀቁ ተገልጿል።

በሌላ በኩል ፦ በደቡብ ክልል በቁጫ የምርጫ ክልል ሲካሄድ የነበረው ቆጠራ እንዲቆም ተወስኗል።

ቆጠራው እንዲቆም የተወሰነው በነበረው ተገቢ ያልሆነ አሰራር እና የጸጥታ ችግር ምክንያት እንደሆነ ወ/ሪት ሶልያና ሽመልስ ገልጸዋል።

ቦርሩ በቁጫ የምርጫ ክልል በሂደቱ ላይ ተገቢ ያልሆኑ አሰራሮች እንደነበሩ ቅሬታዎች ለቦርዱ ሲቀበል የነበረ ሲሆን ጉዳዩ እስኪጣራ ቆጠራ እንዲቆም ተወስኗል።

በምርጫ ክልሉ ሲቀርቡ ከነበሩት ቅሬታዎች በተጨማኢ የጸጥታ ችግር እንዳለ ቦርዱ መረጃ ስለደረሰው ቆጠራው ቆሞ የምርጫ ቁሳቁሶች ባለበት ታሽጎ እንዲቀመጥ ወስኗል።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013

በድሬደዋ በ6 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ችግር እንዳጋጠመው ቦርዱ ገለጸ።

በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ስድስት የምርጫ ጣቢያዎች የክልል ምክር ቤት ምርጫ ሳይካሄድ እንደቀረ እንዲሁም ከስድስቱ በአንዱ ጣቢያ የህዝብ ተወካዮች ምርጫ ጭምር ሳይካሄድ መቅረቱን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ገልጿል።

ሪፖርቱ አሁን እንደደረሳቸው የገለጹት የቦርዱ የኮሚውኒኬሽን አማካሪ ሶልያና ሽመልስ ''የክልል ምክር ቤት የድምጽ መስጫ ወረቀት አልደረሰንም'' በሚል ምርጫው ሳይካሄድ እንደቀረ የምርጫ ክልሉ ኃላፊ መግለጹን የጠቆሙ ሲሆን ይህንን ግን አስቀድመው ሪፖርት አለማድረጋቸውን ነው ያነሱት።

በእነዚህ ጣቢያዎች ላይ ምን ይሆናል የሚለውን ቦርዱ መመልከቱን አንስተው ''እነዚህ ጣቢያዎች ላይ አንድ ፖርቲ ብቻ ነው የሚወዳደረው። የአንድ ፖርቲ ውድድር ስለሆኑ በክልል ምክር ቤት ደረጃ የሚኖረውን ውጤት አይቀይሩትም ስለዚህ ምንም አይነት ተጨማሪ ምርጫ ማድረግ አያስፈልግም ብሎ ቦርዱ ወስኗል'' ብለዋል።

ከስድስቱ አንዱ ጣቢያ ላይ ከክልል ተወካዮች ምክር ቤት በተጨማሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም አለመካሄዱን ያነሱት ወ/ሪት ሶልያና ''...በአጠቃላይ የተወካዮች ምክር ቤት ውጤት ታይቶ ውጤቱን የሚቀይር ከሆነ ተጨማሪ ውሳኔ ቦርዱ የሚወስን ይሆናል።'' ሲሉ ገልጸዋል።

6ቱ ጣቢያዎች ከዚህ ቀደም የመራጮች ምዝገባ በትክክል ያልተካሄደባቸው ተብለው የተለዩ እንደሆኑ ያስታወሱት ወ/ሪት ሶሊያና ለዚህ ችግር መፈጠር ኃላፊነት የሚወስደው አካል የቱ ነው የሚለውን እያጣሩ መሆኑንም ገልጸዋል።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

የ24 ሰዓት የኮቪድ ሪፖርት :

• የላብራቶሪ ምርመራ - 5,307
• ቫይረሱ የተገኘባቸው - 112
• ህይወታቸው ያለፈ - 7
• ከበሽታው ያገገሙ 288

አጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 275,881 የደረሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 4,309 ህይወታቸው ሲያልፍ 258,491 ሰዎች አገግመዋል። ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,988,902 ደርሰዋል።

@tikvahethiopia
#ምርጫ2013_እና_አዲስአበባ

ምርጫ ቦርድ ከሰሞኑን በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው ምርጫ ሂደት ላይ በፓርቲዎች (በተለይ ደግሞ በባልደራስ ፓርቲ) ሲነሱ ለነበሩ ቅሬታዎች እና አቤቱታዎች በተወሰኑት ላይ ምላሽ ሰጥቷል።

ለቅሬታዎቹ እና አቤቱታዎቹ ምላሽ እና ማብራሪያ የሰጡት የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ ናቸው።

ማህበራዊ ሚዲያ ላይ በየምርጫ ጣቢያው በተለጠፈው የውጤት መግለጫ ወረቀት ላይ ተሰረዟል/ተደልዟል ስለሚባለው ጉዳይ ?

ወ/ሪት ሶሊያና : ምርመራ አድርገናል ፤ የየምርጫ ክልል ኃላፊዎች ስርዝ ድልዝ ተደረገበት የተባለውን ጣቢያ ተመልከትው ችግር ይኑርበት አይኑርበት የሚለውን ድጋሚ ቆጥረው እያረጋገጡልን ነው፤ የውጤት ማሳወቅ ሂደት ላይ ስርዝ ድልዝ መኖሩ ነው እንጂ ችግር ያለበት አልተገኘም፤ በቆጠራው ላይ ያለው እና የተፃፈው ቁጥር ትክልል ነው የሚል ሪፖርት ደርሶናል።

የምርጫ ቆጠራው ችግር አለበት ስለሚባለው ጉዳይ ? (ባልደራስ ፓርቲ ያቀረበው ቅሬታ)

ወ/ሪት ሶሊያና : በአዲስ አበባ አብዛኛዎቹ የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የሁሉም ፓርቲ ወኪሎች ተገኝተው ነው ቆጠራ የተደረገው ፤ አ/አ ላይ የፓርቲ ወኪል ለምርጫ ጣቢያ ልኮ የምርጫ ጣቢያ አልቀበልም ያለበት ምንም አይነት ምርጫ ጣቢያ የለንም ፤ ሁሉም ቦታዎች የፓርቲ ወኪሎች ተገኝተዋል ፤ እራሳቸው ወኪሎቻቸውን እስከላኩና አቅማቸው ፈቅዶ ከ1 ሺህ በላይ ጣቢያዎች ላይ እስካስቀመጡ ድረስ። ወኪሎቹ የምርጫ ሂደቱ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ተከታትለው ውጤቱ ላይ ፈርመዋል ሁሉም ቦታዎች ላይ ማለት ይቻላል። ወኪሎች ያሉባቸው ፊርማዎች ኖረውን ነው የመጣነው የምርጫ ሂደቱን ስናደርግ።

ይቀጥላል👇
#ምርጫ2013_እና_አዲስአበባ

ማንነታቸው የማይታወቁ ጣቢያዎች ተከፍተው ነበር ? (ባልደራስ ፓርቲ ያቀረበው ቅሬታ)

ወ/ሪት ሶሊያና : ፍፁም ሀሰት ነው። አዲስ አበባ ላይ ማንነታቸው የማይታወቁ ጣቢያዎች የሉንም። ሁሉም ጣቢያዎች ኮድ አላቸው፤ ኮድ የሌላቸው ያገኘናቸው 2 ጣቢያዎችን እንኳን ድጋሚ ኮድ ሰጥተን ምርጫ እንዲካሄድ አድርገናል።

አንዳንድ የምርጫ ጣቢያዎች የባልደራስ ፓርቲን ውጤት እያሳነሱ እንዲፅፉ ተደርገዋል ? (የባልደራስ ፓርቲ ቅሬታ)

ወ/ሪት ሶሊያና : ይህ ፍፁም ሀሰት ነው። ፓርቲ ወኪሎች ያሉባቸው ቦታዎች ከሆኑ የፓርቲ ወኪሎቻቸው እራሳቸው ይህን አይተው ዝም አይሉም። ወኪሎቹ እራሳቸው እንደዚህ ያለ አቤቱታ አቅርበው (በእኔ ፓርቲ ላይ ያለው ውጤት በትክክል አልተቆጠረም/በትክክል አልተፃፈም ብለው) ያቀረቡት ሪፖርት የለም። ያን አይነት አቤቱታ የቀረበበት የምርጫ ጣቢያም የለንም።

በወረቀት እጥረት የተነሳ ደጋፊዎቻችን ወደቤቶቻቸው ሄደዋል ተብሎ ስለተነሳው ቅሬታ ?

ወ/ሪት ሶሊያና : እስከ ለሊቱ 7 ሰዓት ከ10 ድረስ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት አከናውነናል። የድምፅ መስጫ ወረቀት ባለመኖሩ የተቋረጠብን ምርጫ ጣቢያ የለም። ምርጫ ጣቢያዎች ላይ የድምፅ መስጫ ወረቀት እጥረት ነበር ነገር ግን ባለው እያካሄዱ እያለ ተጨማሪ ወረቀቶችን ማድረስ ችለናል። ስለዚህ መሰረታዊ የሆነ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ተቋርጦ የድምፅ መሥጫ ወረቀት ባለመኖሩ የተነሳ ሰው ተበትኖ/ተመልሶ ኑ ወረቀት መጥቷል እና ድምፃችሁን ስጡ የተባለበት አንድም ቦታ የለም፤ ስለዚህ ወረቀት አልቆ ደጋፊዎቼ ተመለሱ የሚለው በከፍተኛ ደረጃ #የተሳሳተ መረጃ ነው።

ይቀጥላል👇
#ምርጫ2013_እና_አዲስአበባ

በአዲስ አበባ ድምፅ ሰጪው ረጅም ሰልፍ ነበረበት የሚልም ቅሬታ ነበር ፤ይሄ ጉዳይ እንዴት ይታያል ?

ወ/ሪት ሶሊያና : ምንም ጥያቄ የለውም ፤ በተወሰነ ደረጃ የድምፅ ሰጪዎች መንገላታት ቢያሳዝንም በሌላ በኩል ሲታይ ድምፅ ሰጪዎች በድምፅ መስጠት ሂደቱ ላይ ለመሳተፍ ረጅም ሰዓት ወስደው በከፍተኛ Trunout ወጥተው ድምፅ መስጠታቸው በጣም የሚያስደስት ነው፤ ይህም በቦርዱ በጥሩ ጎኑ የታየ ነው።

በአጠቃላይ በአ/አ የነበረው ምርጫ በወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ ፦

"... አዲስ አበባ በጣም ጥቂት ችግር ካለባቸው ፤ አብዛኛው የምርጫ ሂደት (ሁሉም ማለት ይቻላል) ፓርቲዎች ሆኑ የግል ተወዳዳሪዎች ወኪሎቻቸውን ያስቀመጡበት ፤ በቆጠራ ሂደቱ ላይ አብዛኛዎቹ ከመጀመሪያው ጀምሮ ሂደቱ እስኪጠናቀ ድረስ ታዝበው #ፈርመው የሄዱበት የቆጠራ ሂደት ያካሄድንበት ነው። በእርግጥ በአዲስ አበባ ጣቢያዎቹ ብዙ ቢሆኑም በከፍተኛ ደረጃ የፓርቲ ወኪሎች የተገኙበት ፣ ታዛቢዎች የተገኙበት፣ ዜጎች በጣም በረጅም ሰልፍ ሰዓት ወስደው የመረጡበት ፣ እስከ ለሊቱ 7 ሰዓት ሰፍል ላይ ያለው ሰው እንዳይቋረጥ ብለን ማንኛውም ድምፅ ሰጪ ድምፁን እንዲሠጥ ያደረግንበት ፣ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ከልሎች ቦታዎች በተሻለ ሁኔታ ግልፅ የሆነበት እና ሚዲያን የሲቪክ ማህበራትም ፣ የፓርቲ ወኪሎች እኛም እራሳችን እየዞርን ያየንበት ነው።"

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ አካባቢዎች በውሃ እጥረት ምክንያት ነዋሪዎች እየተቸገሩ ነው።

ከዚህ ቀደም ፕሮግራም ውሃ የሚመጣባቸው አካባቢዎች ላለፉር ተከታታይ ቀናት ውሃ ማግኘት አልቻሉም፤ ይህም ደግሞ በኑሯቸው ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ እያደረሰ መሆኑን ጠቁመዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ ከሰሞኑ እየታየ ካለው የውሃ እጥረት ጋር በተያያዘ የከተማው ውሃ እና ፍሳሽ ባለስልጣን ምላሽ ሠጥቷል።

ባለስልጣኑ እንደሚለው ከሆነ ሰሞኑን በመዲናይቱ በተፈጠረ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ የውሃ ምርት እና ስርጭት ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው።

የኤሌትሪክ መቆራረጥ ችግሩ በአቃቂ ጉድጓዶች እና ግፊት መስጫ ጣቢያዎች ላይ መፈጠሩንም ገልጿል፤ ይህ ሁኔታ ውሃ ለደንበኞቹ በወጣው መረሀ ግብር መሰረት እንዳይሰጥ ችግር እንደፈጠረበት አስውቋል።

በዚህም ፦
- ገላን አካባቢ፣
- ሳሪስ፣
- ሀና ማርያም፣
- ሀይሌ ጋርመንት፣
- ላፍቶ፣
- ጀሞ፣
- ቆሬ፣
- ሳር ቤት፣
- ሜክሲኮ፣
- ልደታ፣
- ጌጃ ሰፈርና ቤቴል አካባቢዎች ውሃ ለማሰራጨት #አልተቻለም ተብሏል።

በተጨማሪ ፥ በለገዳዲ ጉድጓዶች ላይ በየሰዓቱ የሚከሰተው የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በባለስልጣኑ አገልግሎት ላይ ጫና እያሳደረ መሆኑን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የችግሩን ስፋት በመረዳት አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠው በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ላይ ባሰራጨው ፅሁፍ ጠይቋል፡፡

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በሳዑዲ አረቢያ በስደት ላይ የነበሩ 380 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ገቡ። ኢትዮጵያውያኑ ቦሌ ኤርፖርት ሲደርሱ የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲና የሠላም ሚኒስትር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬአለም ሽባባው አቀባበል አድርገውላቸዋል። አሁን የገቡትን ጨምሮ 2 ሺህ የሚሆኑ ከስደት ተመላሾች ዛሬ ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል። በሁለት ሳምንት ጊዜ…
#Update

ኢትዮጵያ ከሳዑዲ አረቢያ 1931 ዜጎቿን ወደ አገራቸው መልሳለች።

በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ 40 ሺህ ዜጎችን በቀጣይ ሁለት ሳምንታት ወደ አገራቸው ለመመለስ እየተሰራ መሆኑ መገለፁ አይዘነጋም።

በዚህ መሰረትም ትላንት 1,252 ከሪያድ እና 679 ከጂዳ በአጠቃላይ 1931 ዜጎች በስድስት በረራዎች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።

መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አስቸኳይ የሳዑዲ አረቢያ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነና ዜጎች ተገቢውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ መልዕክት ተላልፎ ነበር። የሳዑዲ ፀጥታ ኃይሎች በሰሩት ኦፕሬሽን ተይዘው በሹሜሲ የማቆያ ጣብያ የሚገኙ ዜጎች ከፍተኛ የውሃ የምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች እጥረት እንዳጋጠማቸው ተሰምቷል።…
#Update #SaudiArabia

በሹሜሲ የማቆያ ጣብያ ለሚገኙ ዜጎች የሚደረገው የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲቆም ተወሰነ።

ውሳኔው የተላለፈው ማህበረሰቡ ባለፉት ጥቂት ቀናት እጅግ በሚያኮራ መልኩ ፈጣን ድጋፍ በማድረግ በቂ የሆኑ ቁሳቁሶች በመለገዙ፤ ለግዜው እነዚህን ቁሳቁሶች በአግባቡ መጠቀም ስለሚያስፈልግ መሆኑን በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅህፈት ቤት አሳውቋል።

ነገር ግን እንደ አስፈላጊነቱ ቆንስላው በድጋሜ የቁሶች ድጋፍ ካስፈለገው ጥያቄውን ሊያቀርብ እንደሚችል ጠቁሟል።

በቀጣይ ቀናት በማቆያ ጣብያ ለሚገኙ ዜጎች #የምግብ አገልግሎት ሲያስፈልግ ከቁጥጥር ከደህንነትና ከተገቢ የስራ ዕቅድና አፈፃፀም አኳያ አመቺ እንዲሆን ከቆንስላ ጽ/ቤቱ እና ከኮሚኒቲው ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር ብቻ ድጋፉ እንዲቀርብ ጥሪ ቀርቧል።

የሳዑዲ የፀጥታ አስከባሪ አካላት በሳዑዲ የተለያዩ ከተሞች ላይ የመኖርያ ፈቃድ ባላቸውም ይሁን በሌላቸው ነዋሪዎች ላይ የፍተሻና የአፈሳ እርምጃ እየወሰዱ እንደሆነና በዚህ ኦፕሬሽን ተይዘው በሹሜሲ የማቆያ ጣብያ ለሚገኙ ዜጎች የውሃ የምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ ቁሶች እጥረት በመከሰቱ ዕርዳታ ማድረግ የሚችሉ ካሉ እንዲያቀርቡ መጠየቁ አይዘነጋም።

@tikvahethiopia
የሶማሊያ ጦር 41 የአልሸባብ ታጣቂዎችን ገደለ።

ጦሩ በዛሬው ዕለት በመዱግ ክልል ውስጥ የወሲል ከተማን ሊያጠቁ ነበር / ጥቃት ሊከፍቱ ነበር ያላቸውን 41 የአልሸባብ ታጣቂዎችን ገድሏል።

በነበረው ግጭት 3 ከሶማሊያ ጦር እንዲሁም 5 ከጋልሙዱግ የዳርዊሽ ኃይሎች መገደላቸው ተሰምቷል።

በሌላ መረጃ የሶማሊያዋ #ፑንትላንድ ዛሬ 21 የአልሸባብ አባላትን ዛሬ ረሽናለች።

አባላቱ ጋልካዮ፣ ቃርዶ እና ጋሮዊ በተባሉ የተለያዩ ሶስት አካባቢዎች ላይ መረሸናቸውን የፑንትላንድ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኛ ጄነራል መሃሙድ አብዲ መሃመድ አረጋግጠዋል፡፡

በፍርድ ቤቱ ውሳኔ የተገደሉት የአል ሸባብ አባላቱ ባለፉት 13 ዓመታት ውስጥ በተለያዩ የፑንትላንድ አካባቢዎች በተፈጸሙ ግድያዎች ጥፋተኛ ነበሩ ተብሏል፡፡

ከጎሳ መሪዎችን፣ ጋዜጠኞች፣ ከመንግስት ባለስልጣናት ግድያ ጀርባ እንደነበሩ ፍርድ ቤት ገልጿል።

መረጃው ከጎብጆግ ፣ አልዓይን ኒውስ ፣ SNTV (የሶማሊያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን) የተውጣጣ ነው።

@tikvahethiopia
#Ethiopia

ኢትዮጵያ በየዕለቱ ሪፖርት የምታደርጋቸው የ #COVID19 ታማሚዎች ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ እያሽቆለቆለ እየመጣ ነው፤ በአንፃሩ ከበሽታው የሚያገግሙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው።

ከረጅም ወራቶች በኃላ ዝቅተኛው የኮቪድ-19 ታማሚዎች ቁጥር ዛሬ ሪፖርት ተደርጓል።

በዛሬው ዕለት የጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው የ24 ሰዓታት ሪፖርት 54 ሰዎች ብቻ ናቸው በኮቪድ-19 እንደተያዙ የተገለፀው።

ከ100 መቶ በታች የኮቪድ-19 ታማሚዎች ቁጥር ሪፖርት ሲደረግ ከወራቶች በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካሁን 275,935 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን ከነዚህ መካከል 259,044 ሰዎች አገግመዋል።

በአሁን ሰዓት በኢትዮጵያ ኮሮና ቫይረስ የሚገኝባቸው ሰዎች ቁጥር 12,575 ነው።

@tikvahethiopia
አሜሪካ የአየር ድብደባ ፈፀመች።

አሜሪካ በኢራን የሚደገፉ ሚሊሻዎችን ዒላማ ያደረገ የአየር ድብደባ በኢራቅ እና በሶሪያ ውስጥ መፈጸሟን የመከላከያ መሥሪያ ቤቷ ፔንታገን አስታወቀ።

ጥቃቱ ሚሊሻዎቹ በአሜሪካ ወታደሮች ሰው አልባ አውሮፕላን ላይ ለፈጸሙት ጥቃት ምላሽ "በጦር መምሪያ እና በጦር መሣሪያ ማከማቻ ተቋማታቸው ላይ" የተፈጸመ ነው ተብሏል።

"ፕሬዝዳንት ባይደን የአሜሪካን ወታደሮችን ለመጠበቅ እርምጃ እንደሚወስዱ ግልጽ ነው" ብሏል ፔንታገን።

ጆ ባይደን ስልጣን ከያዙ ወዲህ በኢራን በሚደገፉ ሚሊሻዎች ላይ የአየር ድብደባ እንዲፈጸም ሲፈቅዱ ይህ ሁለተኛው ነው።

ባለፉት ጥቂት ወራት መቀመጫቸውን ኢራቅ ባደረገው የአሜሪካ ጦር ሠራዊት ላይ በሰው አልባ አውሮፕላን ተደጋጋሚ ጥቃቶች ተሰንዝሮባቸዋል።

ኢራን በጥቃቶቹ እጇ እንደሌለበት ገልጻለች።

2,500 የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች አይ ኤስ የሚዋጋ ዓለም አቀፍ ጥምረት አካል ሆነው ኢራቅ ውስጥ ይገኛሉ።

ፔንታገን ፥ በመከላከያ ዒላማቸውን በጠበቁ የአየር ጥቃቶች በሶሪያ ውስጥ 2 ፤ 1 ደግሞ በኢራቅ ውስጥ የሚገኙ ዒላማዎች ተመተዋል ብሏል፡፡ ካታብ ሂዝቦላህ እና ካታይብ ሰይድ አል ሹሃዳን ጨምሮ በኢራን የሚደገፉ የሚሊሺያ ቡድኖች ዒላማ የተደረትን ተቋማት ይጠቀሙባቸዋል ተብሏል።

አሜሪካ እአአ ከ2009 ጀምሮ ካታይብ ሂዝቦላህ የኢራቅን ሠላምና መረጋጋት አደጋ ላይ ጥሏል በሚል በሽብርተኛነት ፈርጃለች።

የፔንታገን መግለጫ አሜሪካ ራሷን በመከላከል እርምጃ ወስዳለች ብሏል።

አደጋ ለመገደብ የታቀደ "አስፈላጊ፣ ተገቢ እና ሆን ተብሎ የተወሰደ እርምጃን ወስዳለች። ግልጽና ግልጽ ያልሆነ መልዕክት ለመማስተላለፍም ነው" ብሏል።

ፔንታገን በጥቃቱ የሞተ ወይም የቆሰለ ሰው ስለመኖሩን አልገለጸም። 

#BBC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
አሜሪካ የአየር ድብደባ ፈፀመች። አሜሪካ በኢራን የሚደገፉ ሚሊሻዎችን ዒላማ ያደረገ የአየር ድብደባ በኢራቅ እና በሶሪያ ውስጥ መፈጸሟን የመከላከያ መሥሪያ ቤቷ ፔንታገን አስታወቀ። ጥቃቱ ሚሊሻዎቹ በአሜሪካ ወታደሮች ሰው አልባ አውሮፕላን ላይ ለፈጸሙት ጥቃት ምላሽ "በጦር መምሪያ እና በጦር መሣሪያ ማከማቻ ተቋማታቸው ላይ" የተፈጸመ ነው ተብሏል። "ፕሬዝዳንት ባይደን የአሜሪካን ወታደሮችን ለመጠበቅ…
#Update

ትላንት አሜሪካ በኢራቅ እና በሶሪያ ውስጥ በፈፀመችው የአየር ድብደባ የሰዎች ህይወት አልፏል።

ኤሜሪካ በፈፀመችው የአየር ድብደባ አምስት ሚሊሻዎች ሶሪያ ውስጥ ስለመገደላቸው ሶሪያን ኦብዘርቫቶሪ ፎር ሒውማን ራይትስ አሳውቋል።

የሶርያ የመንግሥት የዜና ወኪል (ሳና) በበኩሉ አንድ ህጻን መሞቱን እና ቢያንስ 3 ሰዎች መቁሰላቸውን ዘግቧል።

መረጃው የኤኤፍፒ / ቢቢሲ ነው።

Photo Credit : Joe Truzman

@tikvahethiopia
#BREAKING

የእነ ጀነራል ሰአረ መኮንን ገዳይ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጣ።

የእነ ጀነራል ሰአረ መኮንን ገዳይ አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ በእድሜ ልክ ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኖበታል።

አቃቤ ህግ በሞት እንዲቀጣ ጥያቄ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም 4 የቅጣት ማቅለያ በማቅረቡ ቅጣቱ በእድሜ ልክ እስራት እንዲቀል ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የጸረ ሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት ነው የቅጣት ውሳኔውን ያስተላለፈው ሲል ኢብኮ ዘግቧል።

አስር አለቃ መሳፍንት ጥጋቡ በግንቦት 2011 ዓ/ም በጎንደር ከተማ ከ ብ/ጄ አሳምነው ፅጌ ጋር በመገናኘት ተልኮ ተቀብሎ የቀድሞ ጠቅላይ ኢታማዡር ሹም ጄኔራል ሰአረ መኮንን እና ጓደኛቸው ብ/ጄ ገዛኢ አበራን በሽጉጥ ገሏል ተብሎ መከሰሱ ይታወቃል፡፡

@tikvahethiopia
አቶ ጃዋር መሃመድ ፣ አቶ በቀለ ገርባ ፣ አቶ ሀምዛ አዳነ እና አቶ ደጀኔ ጣፋ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ጸረ ሽብርና ህገ መንግሥታዊ ወንጀሎች ችሎት በፃፉት ደብዳቤ ከዛሬ ጀምሮ በፍቃዳቸው ችሎት ላይ ለመቅረብ እንደማይችሉ ገለፁ።

በደብዳቤያቸው ላይ ፤ "መንግስት ከፊቱ ይጠብቀው ከነበረው ምርጫ ጠንካራ ተፎካካሪ ፓርቲዎችን ከወዲሁ ለማስወገድ አስቀድሞ ወጥኖ በነበረው ዕቅድ መሠረት የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ በማሳበብ እሥር ቤት ካጎረን እነሆ አንድ አመት ሆኖታል" ብለዋል።

በዚህ ጊዜ ለሀገሪቱ የፍትህ ተቋም ክብር በመስጠት የቀረበብንን ክስ ህጋዊ በሆነ መንገድ ተከራክረን ንጽህናችንን ለማረጋገጥ በችሎት እየተገኘን በትዕግስት እና አርአያነት ባለው መልኩ ህግ አክባሪ ዜጎች መሆናችንን ለማስመስከር ሞክረናል ብለዋል።

ይህንን ስናደርግ የነበረው በችሎቱ ለተሰየሙት ዳኞች ፣ ለሚያጅቡን ፖሊሶች እና ለምንገኝበት ማረሚያ ቤት ተገቢውን ክብር በመስጠት ሲሆን በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ የሚሰጠውን ውሳኔ አስፈጻሚው የመንግስት አካል ተግባራዊ ያደርጋል በሚል ጽኑ እምነት ነበር ሲሉ ገልፀዋል።

ነገር ግንበሂደቱ እንደተረዳነው ፍ/ቤቶች የሚሰጡት ውሳኔ በህገወጥ መንገድ እየተጣሰ በነፃ የተሰናበቱ ዜጎች በመንግስት ኃይሎች እየተጠለፉ ወደ ሌላ እስር ቤት ሲወሰዱ አንዳንዴም ደብዛቸው ሲጠፋ ተመልክተናል ብለዋል።

ያንብቡ : telegra.ph/OPPDT-06-28

@tikvahethiopia