#ሪፖርት
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።
በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።
ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።
ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።
ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።
* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱን በተመለከተ ቃላቸውን ሰጥተውናል።
በአጠቅላይ ምርጫው ሰላማዊ መሆኑን መታዘብ እንደተቻለ ፣ የተለያየ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውድድሩን ህግ በማክበር ፍፁም ነው ባይባልም የተሻለ ውድድር ስሜት የተፈጠረበት እና የህዝብ መነሳሳት የታየበት አበረታች የሚባል ሂደት ነበር ብለዋል።
ነገር ግን ምርጫው እንከን አልባ እና ፍፁም ነበር ማለት እንዳልሆነ ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ አሳውቀውናል።
ምርጫው ላይ የተለያዩ ችግሮች የነበሩ እንደሆነም አንስተዋል።
ተጠባባቂ ዳይሬክተሩ ፥ "የትኛውም ምርጫ ፍፁም ሆኖም አያውቅም፣ ሊሆንም አይችልም፤ ምርጫ ሂደት ነው የምንማርበት ነው ከዚህ ምርጫ የተሻለ አፈፃፀም ደግሞ በሚቀጥለው ይታያል ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።
* የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርቱ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia
Audio
AudioLab
#ምርጫ2013
ምርጫውን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የሰጡን አጭር ገለፃ።
@tikvahethiopia
ምርጫውን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶች ሕብረት ለምርጫ (CECOE) ተጠባባቂ ዳይሬክተር አበራ ኃይለማርያም የሰጡን አጭር ገለፃ።
@tikvahethiopia
#EthiopianAirlines
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ' ሙሉ በሙሉ ' የኮቪድ-19 ክትባት በወሰዱ ሰራተኞች በረራ ማድረግ መጀመሩን ዛሬ አሳውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ተወልደ ገብረማርያም ፥ በረራዎችን ሙሉ በሙሉ ክትባት በወሰዱ ሠራተኞች በማድረጋችን ተደስተናል ብለዋል።
አክለውም ፥ "ይህንን ማድረጋችን የሰራተኞቻችንን እና የደንበኞቻችንን የጤና ደህንነት በመጠበቅ ረገድ ትልቅ እርምጃ ነው" ሲሉ ገልፀዋል።
አቶ ተወልደ፥ በመላው ዓለም በኮቪድ-19 ክትባት በመተማመን ለንግድ ፣ ለቪኤፍአር እና ለቱሪዝም የሚጓዙ መንገደኞች ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ተበረታተናል ብለዋል።
አየር መንገዱ ለሰራተኞቹ እንዲሁም ለባለድርሻ አካላቱ ከ37,000 በላይ የክትባቶችን ገዝቶ ማስገባቱን አቶ ተወልደ አሳውቀዋል።
በሌላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ ፦ ወደ ኤርትራ #አስመራ ተቋርጦ የነበረው የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት ከዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2013 ጀምሮ የሚቀጥል መሆኑን አሳውቋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ' ሙሉ በሙሉ ' የኮቪድ-19 ክትባት በወሰዱ ሰራተኞች በረራ ማድረግ መጀመሩን ዛሬ አሳውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት አቶ ተወልደ ገብረማርያም ፥ በረራዎችን ሙሉ በሙሉ ክትባት በወሰዱ ሠራተኞች በማድረጋችን ተደስተናል ብለዋል።
አክለውም ፥ "ይህንን ማድረጋችን የሰራተኞቻችንን እና የደንበኞቻችንን የጤና ደህንነት በመጠበቅ ረገድ ትልቅ እርምጃ ነው" ሲሉ ገልፀዋል።
አቶ ተወልደ፥ በመላው ዓለም በኮቪድ-19 ክትባት በመተማመን ለንግድ ፣ ለቪኤፍአር እና ለቱሪዝም የሚጓዙ መንገደኞች ቁጥር እየጨመረ በመሄዱ ተበረታተናል ብለዋል።
አየር መንገዱ ለሰራተኞቹ እንዲሁም ለባለድርሻ አካላቱ ከ37,000 በላይ የክትባቶችን ገዝቶ ማስገባቱን አቶ ተወልደ አሳውቀዋል።
በሌላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ መረጃ ፦ ወደ ኤርትራ #አስመራ ተቋርጦ የነበረው የመንገደኞች የበረራ አገልግሎት ከዛሬ ሰኔ 16 ቀን 2013 ጀምሮ የሚቀጥል መሆኑን አሳውቋል።
@tikvahethiopia
#ምርጫ2013
በዘንድሮ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ተሳትፎ ምን ይመስላል ?
በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ተሳትፎና የሚዲያዎች ሚና ምን እንደሚመስል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በቀጥታ በVoice Chat አጭር ገለፃ ያደርጋሉ።
ገለፃ የሚያደርጉት ፡
- ጋዜጠኛ ሲሳይ ሳህሉ
- ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ
- ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ናቸው።
(ከምሽት 2:10 - 2:40 ድረስ)
@tikvahethiopia
በዘንድሮ ምርጫ የመገናኛ ብዙሃን ባለሞያዎች ተሳትፎ ምን ይመስላል ?
በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ተሳትፎና የሚዲያዎች ሚና ምን እንደሚመስል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት በቀጥታ በVoice Chat አጭር ገለፃ ያደርጋሉ።
ገለፃ የሚያደርጉት ፡
- ጋዜጠኛ ሲሳይ ሳህሉ
- ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ
- ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ናቸው።
(ከምሽት 2:10 - 2:40 ድረስ)
@tikvahethiopia
Audio
AudioLab
#ምርጫ2013
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች በ #ምርጫ2013 የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ተሳትፎና የሚዲያዎች ሚና ላይ ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሰጡት ገለፃ።
- ጋዜጠኛ ሲሳይ ሳህሉ
- ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ
- ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች በ #ምርጫ2013 የመገናኛ ብዙኃን ባለሞያዎች ተሳትፎና የሚዲያዎች ሚና ላይ ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የሰጡት ገለፃ።
- ጋዜጠኛ ሲሳይ ሳህሉ
- ጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ
- ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢትዮጵያ ፣ ትግራይ ክልል የተነሳው ግጭት እንሆ 8 ወር አስቆጥሯል። ግጭቱ የሺዎችን ህይወት እንደቀጠፈ፣ ሺዎችንም እንዳሰደደ ቤት ፣ በርካቶች አካል እንዳጎደለ፣ በርካታ ሴቶችን ለፆታዊ ጥቃት እንደዳረገ፣ በርካታ ህፃናትን በአካልም በስነልቦናም እንደጎዳ፣ እንደተመድ ሪፖርት መቶ ሺዎችን ለረሃብ እንዳጋለጠ ይታመናል። የፌዴራል መንግስቱ የትግራይ ሁሉንም ከተሞች በቁጥጥሩ ስር ካደረገ በኃላ በተለያዩ…
ፎቶ፦ በመቐለ አይደር ሆስፒታል ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 16/2013 ዓ/ም ጉዳት ስለደረሰባቸው የቶጎጋ ነዋሪዎች ቤተሰቦቻቸው መረጃ ሲጠባበቁ።
ዛሬ ጥዋት በተለዋወጥነው መረጃ ትላንት ከመቐለ ከተማ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ቶጎጋ በነበረ ጥቃት የሰዎች ህይወት አልፏል፣ የአካል ጉዳት ደርሷል (እስካሁን ትክክለኛ የተጎጂ ዜጎች ቁጥር አይታወቅም) ።
የአየር ድብደባ የተፈፀመው እና ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰው በገበያ ቀን በተፈፀመ ጥቃት መሆኑን የአይን እማኞች ይገልፃሉ። ከጥቃቱ በኃላ አምቡላሶች ሌሎች ተሽከርካሪዎች ወደቦታው እንዳይሄዱ ተከልክለው እንደነበር ከአካባቢው የወጡት ሪፖርቶች ያመላክታሉ።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቃል አቀባይ ኮሎኔል ጌትነት "በገበያ ቦታ ላይ ፈጽሞ የአየር ጥቃት አልፈጸምንም። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ? ሠራዊቱ ኢላማውን በትክክል የመምታት አቅም አለው" ጥቃቱን ሀሰት ብለውታል።
ኮሎኔሉ ፥ "... የአየር ጥቃቶችን ፈጽመናል ነገር ግን በተመረጡ ውስን ኢላማዎች ላይ ያነጣጠሩ ናቸው። ስለዚህ በገበያ ስፍራ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል የተባለው ሙሉ ለሙሉ ውሸት ነው" ሲሉ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ክሱን ውድቅ አድርገውታል።
(ከሰሞኑ በትግራይ ስላሉት ሁኔታዎች ሙሉ መረጃው ከላይ በReply ተያይዟል)
Photo Credit : AFP
@tikvahethiopia
ዛሬ ጥዋት በተለዋወጥነው መረጃ ትላንት ከመቐለ ከተማ በቅርብ ርቀት በምትገኘው ቶጎጋ በነበረ ጥቃት የሰዎች ህይወት አልፏል፣ የአካል ጉዳት ደርሷል (እስካሁን ትክክለኛ የተጎጂ ዜጎች ቁጥር አይታወቅም) ።
የአየር ድብደባ የተፈፀመው እና ሰዎች ላይ ጉዳት የደረሰው በገበያ ቀን በተፈፀመ ጥቃት መሆኑን የአይን እማኞች ይገልፃሉ። ከጥቃቱ በኃላ አምቡላሶች ሌሎች ተሽከርካሪዎች ወደቦታው እንዳይሄዱ ተከልክለው እንደነበር ከአካባቢው የወጡት ሪፖርቶች ያመላክታሉ።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ቃል አቀባይ ኮሎኔል ጌትነት "በገበያ ቦታ ላይ ፈጽሞ የአየር ጥቃት አልፈጸምንም። ይህ እንዴት ሊሆን ይችላል ? ሠራዊቱ ኢላማውን በትክክል የመምታት አቅም አለው" ጥቃቱን ሀሰት ብለውታል።
ኮሎኔሉ ፥ "... የአየር ጥቃቶችን ፈጽመናል ነገር ግን በተመረጡ ውስን ኢላማዎች ላይ ያነጣጠሩ ናቸው። ስለዚህ በገበያ ስፍራ ላይ ጥቃት ተፈጽሟል የተባለው ሙሉ ለሙሉ ውሸት ነው" ሲሉ ለቢቢሲ በሰጡት ቃል ክሱን ውድቅ አድርገውታል።
(ከሰሞኑ በትግራይ ስላሉት ሁኔታዎች ሙሉ መረጃው ከላይ በReply ተያይዟል)
Photo Credit : AFP
@tikvahethiopia
#Ethiopia
የ24 ሰዓት የኮቪድ ሪፖርት :
• የላብራቶሪ ምርመራ - 4,406
• ቫይረሱ የተገኘባቸው - 111
• ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ከበሽታው ያገገሙ 825
አጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 275,502 የደረሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 4,292 ህይወታቸው ሲያልፍ 256,787 ሰዎች አገግመዋል። ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,987,301 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
የ24 ሰዓት የኮቪድ ሪፖርት :
• የላብራቶሪ ምርመራ - 4,406
• ቫይረሱ የተገኘባቸው - 111
• ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ከበሽታው ያገገሙ 825
አጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 275,502 የደረሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 4,292 ህይወታቸው ሲያልፍ 256,787 ሰዎች አገግመዋል። ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,987,301 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የታገደው የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶክተር ዐቢይ አህመድ ቃለምልልስ ዛሬ ይሰራጫል ተብሏል። የ "ጥሞና ወቅት" ላይ እንዳይተላለፍ የተባለው የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዜዳንት እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ቃለ ምልልስ ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ላይ ነው በተለያዩ ሚዲያዎች ይተላለፋል የተባለው። ቃለምልልሱ ዛሬ እንደሚተላለፍ የሰማነው ከጠ/ሚር ፅ/ቤት ይፋዊ ከሆነው…
የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ጉዳይ ፡
ከሱዳን ድንበር ጋር ያለው ችግር በንግግር እና ውይይት ይፈታል ብለው እንደሚያምኑ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተናግሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ሲናገሩ የተደመጡት የምርጫ 2013 የጥሞና ወቅት መተላለፍ የለበትም ተብሎ የታደውና ዛሬ በተላለፈው ቃለምልልስ ላይ ነው።
ከኢትዮ - ሱዳን ድንበር ጋር በተያያዘ ስላውን ችግር ተጠይቀው ምላሽ የሰጡት ዶ/ር ዐቢይ ፥ ችግሩን በዴፕሎማቲክ መንገድ ማየት ቅድሚያ እንደሚሰጠው ፣ ችግሩን ለመፍታት ከውይይት እና ንግግር ውጭ ያለው መንገድ ለሱዳንም ለኢትዮጵያም የሚበጅ እንዳልሆነ ገልፀዋል።
የድንበርን ጉዳይ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ሞክረዋለች ሲሉ ያስታወሱት ዶ/ር ዐቢይ ፥ "በጦርነት አሸንፋ ወደፍርድ ቤት ከሄደች በኃላ የተፈጠረውን ውጤት የምናውቀው ነው ፤ አሁንም ሰው ገድለን ሰው ሞቶብን ፣ መሬት ከያዝን በኃላ ሄዶ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ህግጋቶች የሚታይ ከሆነ ቀድሞ ለውጊያ መሽቀዳደም ጠቃሚ ነው የሚል ሃሳብ የለንም" ብለዋል።
ችግሩን በሰከነ መንፈስ በውይይት፣ ንግግር ፣ በሰጥቶ መቀበል መርህ የሚፈታበትን መንገድ ማየት ይበጃል ከዚህ ውጭ ግን ያለው መንገድ ጉዳቱ ለኢትዮጵያም ለሱዳንም እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ ተናግረዋል።
ከሱዳን ጋር ያለው ችግር በንግግር፣ በውይይት፣ በህግ አግባብ ይፈታል ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት ዶ/ር ዐቢይ፥ "ነገር ግን ሁሉም መንገድ ፣ በሁሉም ሙከራ ዝግ ከሆኑ ፣ ሁሉም ትዕግስት የማይመልሳቸው ከሆነ ሱዳን ብቻ ሳይትሆን ማንም ሀገር ከህግ አግባብ ውጪ የኢትዮጵያን አንድ ስንዝር መሬት ወስዶ መቀመጥ አይችልም ፤ ይህንን ሱዳኖችም ያውቁታል እኛም እናውቀዋለን" ሲሉ ተደምጠዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/Ethio-Sudan-06-23
@tikvahethiopia
ከሱዳን ድንበር ጋር ያለው ችግር በንግግር እና ውይይት ይፈታል ብለው እንደሚያምኑ የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተናግሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ሲናገሩ የተደመጡት የምርጫ 2013 የጥሞና ወቅት መተላለፍ የለበትም ተብሎ የታደውና ዛሬ በተላለፈው ቃለምልልስ ላይ ነው።
ከኢትዮ - ሱዳን ድንበር ጋር በተያያዘ ስላውን ችግር ተጠይቀው ምላሽ የሰጡት ዶ/ር ዐቢይ ፥ ችግሩን በዴፕሎማቲክ መንገድ ማየት ቅድሚያ እንደሚሰጠው ፣ ችግሩን ለመፍታት ከውይይት እና ንግግር ውጭ ያለው መንገድ ለሱዳንም ለኢትዮጵያም የሚበጅ እንዳልሆነ ገልፀዋል።
የድንበርን ጉዳይ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ሞክረዋለች ሲሉ ያስታወሱት ዶ/ር ዐቢይ ፥ "በጦርነት አሸንፋ ወደፍርድ ቤት ከሄደች በኃላ የተፈጠረውን ውጤት የምናውቀው ነው ፤ አሁንም ሰው ገድለን ሰው ሞቶብን ፣ መሬት ከያዝን በኃላ ሄዶ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ህግጋቶች የሚታይ ከሆነ ቀድሞ ለውጊያ መሽቀዳደም ጠቃሚ ነው የሚል ሃሳብ የለንም" ብለዋል።
ችግሩን በሰከነ መንፈስ በውይይት፣ ንግግር ፣ በሰጥቶ መቀበል መርህ የሚፈታበትን መንገድ ማየት ይበጃል ከዚህ ውጭ ግን ያለው መንገድ ጉዳቱ ለኢትዮጵያም ለሱዳንም እንደሚሆን ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ ተናግረዋል።
ከሱዳን ጋር ያለው ችግር በንግግር፣ በውይይት፣ በህግ አግባብ ይፈታል ብለው እንደሚያምኑ የተናገሩት ዶ/ር ዐቢይ፥ "ነገር ግን ሁሉም መንገድ ፣ በሁሉም ሙከራ ዝግ ከሆኑ ፣ ሁሉም ትዕግስት የማይመልሳቸው ከሆነ ሱዳን ብቻ ሳይትሆን ማንም ሀገር ከህግ አግባብ ውጪ የኢትዮጵያን አንድ ስንዝር መሬት ወስዶ መቀመጥ አይችልም ፤ ይህንን ሱዳኖችም ያውቁታል እኛም እናውቀዋለን" ሲሉ ተደምጠዋል።
ያንብቡ : telegra.ph/Ethio-Sudan-06-23
@tikvahethiopia