ዛሬ አ/አ መርካቶ "ሚሊቴሪ ተራ" አካባቢ በደረሰ የእሣት አደጋ ንብረት ወደመ።
የአዲስ አበባ የእሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን እንዳሳወቀው ሚሊቴሪ ተራ አካባቢ በደረሰው የእሣት አደጋ ከ50,000 ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።
በእሣት አደጋው ምክንያት በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
አደጋው በንግድ ሱቆች ላይ የደረሰ ሲሆን ቃጠሎ መንስኤ የኤሌክትሪክ ኮንታክት መሆኑ ተገልጿል።
በተደረገው ርብርብ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት ማትረፍ ተችሏል።
እሳቱን ለመቆጣጠር 39 የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች መሳተፋቸውንና 30 ሺህ ሊትር ውሃ ጥቅም ላይ መዋሉን የአዲስ አበባ የእሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢዜአ ገልጿል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ የእሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን እንዳሳወቀው ሚሊቴሪ ተራ አካባቢ በደረሰው የእሣት አደጋ ከ50,000 ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።
በእሣት አደጋው ምክንያት በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።
አደጋው በንግድ ሱቆች ላይ የደረሰ ሲሆን ቃጠሎ መንስኤ የኤሌክትሪክ ኮንታክት መሆኑ ተገልጿል።
በተደረገው ርብርብ ከ50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ ንብረት ማትረፍ ተችሏል።
እሳቱን ለመቆጣጠር 39 የአደጋ ጊዜ ሠራተኞች መሳተፋቸውንና 30 ሺህ ሊትር ውሃ ጥቅም ላይ መዋሉን የአዲስ አበባ የእሳት አደጋና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ለኢዜአ ገልጿል።
@tikvahethiopia
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በካፋ ዞን የውሽውሽ ሻይ ልማት የስራ እንቅስቃሴን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራል፣ የክልል እንዲሁም የዞን የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ና ሌሎች እንግዶች ወደ ሚዛን በሚሄዱበት ጊዜ የዞኑ ህዝብ ደማቅ አሸኛኘት እንዳደረገላቸው የካፋ ዞን መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አሳውቆናል።
@tikvahethiopia
በጉብኝቱ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራል፣ የክልል እንዲሁም የዞን የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ና ሌሎች እንግዶች ወደ ሚዛን በሚሄዱበት ጊዜ የዞኑ ህዝብ ደማቅ አሸኛኘት እንዳደረገላቸው የካፋ ዞን መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ አሳውቆናል።
@tikvahethiopia
#Mekelle
በመቐለ 400 ኩንታል የእርዳታ እህል ወደ ግለሰብ መጋዘን ሲራገፍ ተያዘ።
የእርዳታ እህሉ መነሻውን ከጅቡቲ አድርጎ በቀጥታ መቐለ አዋሽ ተብሎ ከሚጠራው መጋዘን መራገፍ ሲኖርበት በ2 ግለሰብ መጋዘኖች ሲራገፍ በህብረተሰቡ ጥቆማ ተይዟል፡፡
ከእርዳታ እህሉ ጋር የተሽከርካሪው ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ የመጋዘኑ ባለቤቶች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል።
በመቐለ ሰሜን ክፍለ ከተማ ላጨ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሁለት መጋዘኖች ሲራገፍ የተያዘው የእርዳታ እህል ትናንት ማምሻውን የገባ ነው፡፡
በትግራይ ክልል ከሳምንት በፊት በወጣ አንድ ሪፖርት ባለፉት ጥቂት ወራት ከ4 ሺ 400 በላይ የእርዳታ ስንዴ ለመሸጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ መገለፁን ኤፍ ቢ ሲ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
በመቐለ 400 ኩንታል የእርዳታ እህል ወደ ግለሰብ መጋዘን ሲራገፍ ተያዘ።
የእርዳታ እህሉ መነሻውን ከጅቡቲ አድርጎ በቀጥታ መቐለ አዋሽ ተብሎ ከሚጠራው መጋዘን መራገፍ ሲኖርበት በ2 ግለሰብ መጋዘኖች ሲራገፍ በህብረተሰቡ ጥቆማ ተይዟል፡፡
ከእርዳታ እህሉ ጋር የተሽከርካሪው ሹፌርና ረዳቱን ጨምሮ የመጋዘኑ ባለቤቶች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተደረገባቸው ነው ተብሏል።
በመቐለ ሰሜን ክፍለ ከተማ ላጨ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሁለት መጋዘኖች ሲራገፍ የተያዘው የእርዳታ እህል ትናንት ማምሻውን የገባ ነው፡፡
በትግራይ ክልል ከሳምንት በፊት በወጣ አንድ ሪፖርት ባለፉት ጥቂት ወራት ከ4 ሺ 400 በላይ የእርዳታ ስንዴ ለመሸጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር እንደዋሉ መገለፁን ኤፍ ቢ ሲ አስነብቧል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia - የፀጥት ችግር እና ግጭት - አንበጣ መንጋ ጉዳት - የኮሮና ቫይረስ ተፅእኖ - የትግራይ ክልል ችግር ተደማምረው ኢትዮጵያ ውስጥ ከ12.5 ሚሊዮን በላይ ታዳጊዎች እና ህፃናት የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ ፈላጊዎች እንዳደረጋቸው ተገለፀ። ይህን የገለፁት UNICEF የኢትዮጵያ ቢሮ እና የስውዲን ኤምባሲ ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ ነው። መግለጫው ትኩረቱን ያደረገው በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው…
ቁጥራዊ መረጃ #ኢትዮጵያ ፦
ከUNICEF እና ከስውዲን ኤምባሲ መግለጫ :
- 23.5 ሚሊዮን በተያዘው ዩፈረንጆች ዓመት #ሰብዓዊ_እርዳታ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር (በረብሻ እና ግጭት፣ አንበጣ መንጋ፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የትግራይ ጦርነት ተዳምሮ)
- ከ23.5 ሚሊዮን መካከል 12.5 ታዳጊዎች እና ህፃናት እርዳታ ፈላጊ ናቸው።
- ከ700 ሺህ በላይ ህፃናት እና ታዳጊዎች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ።
- 6 ሺህ ህፃናት በትግራይ ጦርነት ምክንያት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተለያዩ እና መገናኘት ያልቻሉ (እስካሁን ባለው ብቻ)
- 192.7 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እስከ አመቱ መጨረሻ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ችግር ለመደገፍ UNICEF የሚያስፈልገው ተጨማሪ ገንዘብ።
- 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ፥ ከእአአ 2011 አንስቶ ስውዲን በUNICEF በኩል በኢትዮጵያ ለሚሰራው ስራ ያደረገችው ድጋፍ።
- 350 ሺህ ትግራይ ውስጥ ለረሃብ ፣ የከፋ ችግር ተጋልጠዋል የተባሉ ሰዎች ቁጥር።
@tikvahethiopia
ከUNICEF እና ከስውዲን ኤምባሲ መግለጫ :
- 23.5 ሚሊዮን በተያዘው ዩፈረንጆች ዓመት #ሰብዓዊ_እርዳታ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያን ቁጥር (በረብሻ እና ግጭት፣ አንበጣ መንጋ፣ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የትግራይ ጦርነት ተዳምሮ)
- ከ23.5 ሚሊዮን መካከል 12.5 ታዳጊዎች እና ህፃናት እርዳታ ፈላጊ ናቸው።
- ከ700 ሺህ በላይ ህፃናት እና ታዳጊዎች በሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከመኖሪያ ቀያቸው የተፈናቀሉ።
- 6 ሺህ ህፃናት በትግራይ ጦርነት ምክንያት ከቤተሰቦቻቸው ጋር የተለያዩ እና መገናኘት ያልቻሉ (እስካሁን ባለው ብቻ)
- 192.7 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር እስከ አመቱ መጨረሻ በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ችግር ለመደገፍ UNICEF የሚያስፈልገው ተጨማሪ ገንዘብ።
- 70 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ፥ ከእአአ 2011 አንስቶ ስውዲን በUNICEF በኩል በኢትዮጵያ ለሚሰራው ስራ ያደረገችው ድጋፍ።
- 350 ሺህ ትግራይ ውስጥ ለረሃብ ፣ የከፋ ችግር ተጋልጠዋል የተባሉ ሰዎች ቁጥር።
@tikvahethiopia
"... ታላቁ የግብፅ ኢማም የታላቁ ህዳሴ ግድብን በሚመለከት የሰጡት መግለጫ የኢትዮጵያን ሀቅ ያልተመለከተ እና እውነት የጐደለው ነው"- ቀዳማዊ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እድሪስ
የግብፁ አለማቀፋዊ እስልምና ተቋም ታላቅ ኢማም የሆኑት ሼክ አልሃዛር - አህመድ ጦይብ የህዳሴ ግድብን በሚመለከት ኢትዮጵያ ወንዙን በብቸኝነት በመጠቀም ሌሎች ሀገራት ላይ ጉዳት ለማድረስ እየሰራች መሆኑን መናገራቸው ከእውነት የራቀና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እድሪስ ተናገሩ።
ከሰሞኑን አልአዝሀር ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የህዳሴ ግድብ ትክክል አይደለም፤ ወንዙ የሁላችንም በመሆኑ ሁሉም ሰው ሊቃወመው ይገባል ፤ ግድቡ ግብጽ እና ሱዳን ታሪካዊ የውሃ ድርሻ የሚጎዳ በመሆኑ አረቦች እና ሙስሊሞች ሁሉ እንዲቃወሙት ሲል ጥሪ አቅርቦ ነበር።
ዛሬ መግለጫ የሰጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት መግለጫውን "የኢትዮጵያን ሀቅ ያልተመለከተ ነው" ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
ኢትዮጵያ ሁሌም ቢሆን ውሃውን በፍትሃዊነት እንጠቀም የሚል አቋምን ስትገልፅ ከርማለች ያሉት የጠቅላይ ም/ቤቱ ፕሬዚዳንት፣ ግብፅ እና ሱዳንም ይሄንን እውነት ይዘው ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የጠቅላይ ም/ቤቱ ፕሬዚዳንት ፥ የአባይ ውሃ ምንጩም ሆነ ተፈሳሱም አፍሪካ ምድር በመሆኑም መፍትሄውም እዚሁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና አል ዓይን ነው።
@tikvagethiopia
የግብፁ አለማቀፋዊ እስልምና ተቋም ታላቅ ኢማም የሆኑት ሼክ አልሃዛር - አህመድ ጦይብ የህዳሴ ግድብን በሚመለከት ኢትዮጵያ ወንዙን በብቸኝነት በመጠቀም ሌሎች ሀገራት ላይ ጉዳት ለማድረስ እየሰራች መሆኑን መናገራቸው ከእውነት የራቀና ተቀባይነት የሌለው ነው ሲሉ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጂ ኡመር እድሪስ ተናገሩ።
ከሰሞኑን አልአዝሀር ኢንስቲትዩት ኢትዮጵያ እየገነባችው ያለው የህዳሴ ግድብ ትክክል አይደለም፤ ወንዙ የሁላችንም በመሆኑ ሁሉም ሰው ሊቃወመው ይገባል ፤ ግድቡ ግብጽ እና ሱዳን ታሪካዊ የውሃ ድርሻ የሚጎዳ በመሆኑ አረቦች እና ሙስሊሞች ሁሉ እንዲቃወሙት ሲል ጥሪ አቅርቦ ነበር።
ዛሬ መግለጫ የሰጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት መግለጫውን "የኢትዮጵያን ሀቅ ያልተመለከተ ነው" ሲሉ ውድቅ አድርገውታል።
ኢትዮጵያ ሁሌም ቢሆን ውሃውን በፍትሃዊነት እንጠቀም የሚል አቋምን ስትገልፅ ከርማለች ያሉት የጠቅላይ ም/ቤቱ ፕሬዚዳንት፣ ግብፅ እና ሱዳንም ይሄንን እውነት ይዘው ወደ ሰላማዊ ድርድር እንዲመጡም ጥሪ አቅርበዋል።
የጠቅላይ ም/ቤቱ ፕሬዚዳንት ፥ የአባይ ውሃ ምንጩም ሆነ ተፈሳሱም አፍሪካ ምድር በመሆኑም መፍትሄውም እዚሁ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና አል ዓይን ነው።
@tikvagethiopia
#ምርጫ2013
ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከደቂቃዎች በኃላ ዕለታዊ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫውን የሚከታተሉ የቤተሰባችን አባላትም በቦታው ተገኝተዋል።
ውድ አባላት በመግለጫው ላይ የሚነሱትን ዋና ዋና ጉዳዮችን የምንልክላችሁ ይሆናል።
www.tikvahethiopia.net
@tikvahethiopia
ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከደቂቃዎች በኃላ ዕለታዊ መግለጫ ይሰጣል።
መግለጫውን የሚከታተሉ የቤተሰባችን አባላትም በቦታው ተገኝተዋል።
ውድ አባላት በመግለጫው ላይ የሚነሱትን ዋና ዋና ጉዳዮችን የምንልክላችሁ ይሆናል።
www.tikvahethiopia.net
@tikvahethiopia
#EMA
የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለሚዲያዎች የሰጡት ቃለምልልስ ከምርጫ በፊት እንዳይሰራጭ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አሳሰበ።
ቃለምልልሱ በዚህ በጥሞና ወቅት መተላለፍ የለበትም ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፥ ምንም እንኳን ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ ቢታወቅም በዚህ ጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም ብለዋል።
የቃለ መጠይቁ መተላለፍ ብዥታ እንዳይፈጥር ሲባል ከምርጫው በፊት መተላለፍ እንደሌለበት አቶ መሀመድ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም ቃለ መጠይቁ እንዳይተላለፍ የተፈለገው መንግስት በዚህ ዓመት የተሻለ ምርጫ እንዲካሄድና ፍትሀዊ እንዲሆን ፍላጎት ስላለው መሆኑን ተናግረዋል።
ስለዚህ ቃለ መጠይቁን ለማስተላለፍ ማስታወቂያ እየሰሩ ያሉ መገናኛ ብዙሃንም ሆኑ ለማስተላለፍ የተዘጋጁ ከወዲሁ #እንዲያቆሙ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የማሕበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ያሉ አካላትም ከድርጊታቸው መታቀብ አለባቸው ብለዋል።
መገናኛ ብዙሃንም ቢሆኑ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በመጠናቀቁ ቅስቀሳ መሰል ዘገባዎችን ከማስተላለፍ ሊጠነቀቁ ይገባል ሲሉ ማሳሰባቸውን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ይገልፃል።
@tikvahethiopia
የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንትና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለሚዲያዎች የሰጡት ቃለምልልስ ከምርጫ በፊት እንዳይሰራጭ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን አሳሰበ።
ቃለምልልሱ በዚህ በጥሞና ወቅት መተላለፍ የለበትም ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሀመድ እድሪስ ለኢዜአ በሰጡት ቃል ፥ ምንም እንኳን ቃለ መጠይቁ የመንግስት የስራ ክንውኖች ላይ ያተኮረና የምርጫ ቅስቀሳ እንዳልሆነ ቢታወቅም በዚህ ጥሞና ወቅት ሊተላለፍ አይገባም ብለዋል።
የቃለ መጠይቁ መተላለፍ ብዥታ እንዳይፈጥር ሲባል ከምርጫው በፊት መተላለፍ እንደሌለበት አቶ መሀመድ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም ቃለ መጠይቁ እንዳይተላለፍ የተፈለገው መንግስት በዚህ ዓመት የተሻለ ምርጫ እንዲካሄድና ፍትሀዊ እንዲሆን ፍላጎት ስላለው መሆኑን ተናግረዋል።
ስለዚህ ቃለ መጠይቁን ለማስተላለፍ ማስታወቂያ እየሰሩ ያሉ መገናኛ ብዙሃንም ሆኑ ለማስተላለፍ የተዘጋጁ ከወዲሁ #እንዲያቆሙ አሳስበዋል።
በተመሳሳይ የማሕበራዊ ሚዲያዎችን በመጠቀም የምርጫ ቅስቀሳ የሚመስሉ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ያሉ አካላትም ከድርጊታቸው መታቀብ አለባቸው ብለዋል።
መገናኛ ብዙሃንም ቢሆኑ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅት በመጠናቀቁ ቅስቀሳ መሰል ዘገባዎችን ከማስተላለፍ ሊጠነቀቁ ይገባል ሲሉ ማሳሰባቸውን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ይገልፃል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ምርጫ2013 ውድ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከደቂቃዎች በኃላ ዕለታዊ መግለጫ ይሰጣል። መግለጫውን የሚከታተሉ የቤተሰባችን አባላትም በቦታው ተገኝተዋል። ውድ አባላት በመግለጫው ላይ የሚነሱትን ዋና ዋና ጉዳዮችን የምንልክላችሁ ይሆናል። www.tikvahethiopia.net @tikvahethiopia
#ምርጫ2013
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መጪውን ምርጫ እንዳይታዘብ ተከልክሏል ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር የተጻጻፉትን ደብዳቤ መሰረት ተደረጎ ''የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መጪውን ምርጫ እንዳይታዘብ መከልከሉን'' የሚጠቅሱ ዘገባዎች ወጥተዋል።
ዛሬ በተሰጠው መግለጫ ይህ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ የኮሚውኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ ''ሁለቱም በመንግስት ገለልተኛ ተቋም ናቸው ተብለው የተቋቋሙ ናቸው እኛ ባጅ የምንሰጣቸው የምንቆጣጠራቸውን ነው'' ሲሉ ገልጸዋል።
በምርጫ ጣቢያዎች እንዲገቡ በቦርዱ የ "ይለፍ ካርድ" እንደሚሰጣቸው በአዋጅ 1162/2011 መጠቀሳቸውን ያነሱት ወ/ሪት ሶሊያና ኮሚሽኑ ከእነዚህ መካከል ባለመሆኑ በምርጫ ጣቢያዎች እንዲገቡ በቦርዱ የይለፍ ካርድ መስጠት እንደማይችል አንስተዋል።
ባጅ ከመስጠትና የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ እንዲገቡ ፈቃድ የሚሰጣቸው በአዋጁ የተጠቀሱ እንዲሁም ቦርዱ ፈቃድ ሊሰጣቸው አስፈላጊ ሲሆንም ይህንን ፈቃዳቸውን ሊሰርዝ የሚችልባቸውን እንጂ ከቦርዱ ጋር ትይዩ ሥልጣን ላላቸው የመንግስት ተቋማት አይደለም ብለዋል።
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መጪውን ምርጫ እንዳይታዘብ ተከልክሏል ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ጋር የተጻጻፉትን ደብዳቤ መሰረት ተደረጎ ''የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን መጪውን ምርጫ እንዳይታዘብ መከልከሉን'' የሚጠቅሱ ዘገባዎች ወጥተዋል።
ዛሬ በተሰጠው መግለጫ ይህ ጥያቄ የቀረበላቸው የቦርዱ የኮሚውኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ ''ሁለቱም በመንግስት ገለልተኛ ተቋም ናቸው ተብለው የተቋቋሙ ናቸው እኛ ባጅ የምንሰጣቸው የምንቆጣጠራቸውን ነው'' ሲሉ ገልጸዋል።
በምርጫ ጣቢያዎች እንዲገቡ በቦርዱ የ "ይለፍ ካርድ" እንደሚሰጣቸው በአዋጅ 1162/2011 መጠቀሳቸውን ያነሱት ወ/ሪት ሶሊያና ኮሚሽኑ ከእነዚህ መካከል ባለመሆኑ በምርጫ ጣቢያዎች እንዲገቡ በቦርዱ የይለፍ ካርድ መስጠት እንደማይችል አንስተዋል።
ባጅ ከመስጠትና የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ እንዲገቡ ፈቃድ የሚሰጣቸው በአዋጁ የተጠቀሱ እንዲሁም ቦርዱ ፈቃድ ሊሰጣቸው አስፈላጊ ሲሆንም ይህንን ፈቃዳቸውን ሊሰርዝ የሚችልባቸውን እንጂ ከቦርዱ ጋር ትይዩ ሥልጣን ላላቸው የመንግስት ተቋማት አይደለም ብለዋል።
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
#ምርጫ2013
የድምጽ መስጫ ቁሳቁሶችን ቦርዱ ከማዕከል ማንቀሳቀስ መጀመሩን አስታወቀ።
ዛሬ የ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ የድምጽ መስጫ ቁሳቁሶች እሸጋና ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የማንቀሳቀስ ሥራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ዛሬ ቦርዱ በገለጸው መሰረት ፦
- ለኦሮሚያ ክልል 118 (ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ) የምርጫ ክልሎች፤ የምርጫ ቁሳቁሶች ከማዕከል ተልከዋል።
- ለአማራ ክልል በሬሾ 1/3 በሚሆን መልኩ፤
- ለድሬደዋ ከተማ አስተዳደር 47 የምርጫ ክልሎች፤
- ለአፋር ክልል 25 የምርጫ ክልሎች፤
- ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል 7 የምርጫ ክልሎች፤
- ለጋምቤላ ክልል 14 የምርጫ ክልሎች የምርጫ ቁሳቁሶች ለምርጫ ክልሎች ተልከዋል።
ለቀሪ ክልሎች በቀጣይ ቀናት የእሸጋና የስርጭት ሥራዎች የሚሰራ ሲሆን ከምርጫ ክልል ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የሚደረጉ ሥርጭቶች የክልል መንግሥታት እና የከተማ አስተዳድሮች አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርጉ በጹሑፍ ጭምር እንደገለፁ ተጠቅሷል።
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
የድምጽ መስጫ ቁሳቁሶችን ቦርዱ ከማዕከል ማንቀሳቀስ መጀመሩን አስታወቀ።
ዛሬ የ ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው ዕለታዊ መግለጫ የድምጽ መስጫ ቁሳቁሶች እሸጋና ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የማንቀሳቀስ ሥራ እየሰራ መሆኑን አስታውቋል።
ዛሬ ቦርዱ በገለጸው መሰረት ፦
- ለኦሮሚያ ክልል 118 (ሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ) የምርጫ ክልሎች፤ የምርጫ ቁሳቁሶች ከማዕከል ተልከዋል።
- ለአማራ ክልል በሬሾ 1/3 በሚሆን መልኩ፤
- ለድሬደዋ ከተማ አስተዳደር 47 የምርጫ ክልሎች፤
- ለአፋር ክልል 25 የምርጫ ክልሎች፤
- ለቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል 7 የምርጫ ክልሎች፤
- ለጋምቤላ ክልል 14 የምርጫ ክልሎች የምርጫ ቁሳቁሶች ለምርጫ ክልሎች ተልከዋል።
ለቀሪ ክልሎች በቀጣይ ቀናት የእሸጋና የስርጭት ሥራዎች የሚሰራ ሲሆን ከምርጫ ክልል ወደ ምርጫ ጣቢያዎች የሚደረጉ ሥርጭቶች የክልል መንግሥታት እና የከተማ አስተዳድሮች አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርጉ በጹሑፍ ጭምር እንደገለፁ ተጠቅሷል።
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
የ24 ሰዓት የኮቪድ ሪፖርት :
• የላብራቶሪ ምርመራ - 5,764
• ቫይረሱ የተገኘባቸው - 174
• ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ከበሽታው ያገገሙ 744
አጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 274,775 የደረሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 4,262 ህይወታቸው ሲያልፍ 253,195 ሰዎች አገግመዋል። ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,964,005 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
• የላብራቶሪ ምርመራ - 5,764
• ቫይረሱ የተገኘባቸው - 174
• ህይወታቸው ያለፈ - 2
• ከበሽታው ያገገሙ 744
አጠቃላይ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች 274,775 የደረሱ ሲሆን ከእነዚህም መካከል 4,262 ህይወታቸው ሲያልፍ 253,195 ሰዎች አገግመዋል። ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,964,005 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
በሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቻችን ጉዳይ ፦
ኢትዮጵያ ሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ እና በችግር ላይ ያሉ ዜጎቿን በተለያየ ጊዜ ስትመልስ መቆየቷ ይታወቃል።
ነገር ግን አሁንም በርካታ ዜጎች በሳዑዲ እርስ ቤቶች ውስጥ ታጉረው እንደሚገኙ፣ በርካቶችም በችግር ውስጥ ሆነው ወደሀገራችን መልሱን እያሉ ድምፃቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።
በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎች የተለያዩ የመገናኛ ዜዴዎች በመጠቅም ስላሉበት የከፋ ሁኔታ እየገለፁ ነው።
ከሰሞኑን ደግሞ የሳዑዲ አረቢያ ፀጥታ ኃይል የሚሰራው ስራ በርካታ ዜጎቻችን የሰቀቅን ኑሮን እንዲገፉ ፣ በርካቶችንም ለስቃይ ፣ ለዘረፋ ፣ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳጋለጣቸው ሰምተናል።
አሁን አመሻሹን በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባሰራጨው መልዕክት ፥ በሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ወደ አገር የመመለስ ጉዳይ መንግስትን ሲያሳስብ የነበረና መንግስት የዜጎች ችግር መፍትሄ እንዲያገኝ ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር በጉዳዩ ላይ ሲመክር መቆየቱን ገልጿል።
ኤምባሲው የዜጎች ጥያቄ እልባት እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ አረቢያ መንግስት እና የኢፌዲሪ መንግስት መስሪያ ቤቶች ጋር ጉዳዪ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠው የበኩሉን ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሷል።
በዚህም መሰረት ፦
(1)--በእስር ቤት ያሉ እና
(2)--የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸው ወደ አገር መመለስ ፈልገው በተለያዩ ምክንያቶች ወደ አገር መመለስ ያልቻሉ ዜጎቻችን በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ወደ አገር የመመለስ ስራ ይጀመራል ብሏል።
በሳዑዲያ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቻችንም ኤምባሲው ቃሉን አክብሮ ወደእናት ሀገራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርጋቸው ባገኙት መገናኛ ዘዴ ጥሪ እያቀረቡ ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ሳዑዲ አረቢያ የሚገኙ እና በችግር ላይ ያሉ ዜጎቿን በተለያየ ጊዜ ስትመልስ መቆየቷ ይታወቃል።
ነገር ግን አሁንም በርካታ ዜጎች በሳዑዲ እርስ ቤቶች ውስጥ ታጉረው እንደሚገኙ፣ በርካቶችም በችግር ውስጥ ሆነው ወደሀገራችን መልሱን እያሉ ድምፃቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።
በችግር ውስጥ የሚገኙ ዜጎች የተለያዩ የመገናኛ ዜዴዎች በመጠቅም ስላሉበት የከፋ ሁኔታ እየገለፁ ነው።
ከሰሞኑን ደግሞ የሳዑዲ አረቢያ ፀጥታ ኃይል የሚሰራው ስራ በርካታ ዜጎቻችን የሰቀቅን ኑሮን እንዲገፉ ፣ በርካቶችንም ለስቃይ ፣ ለዘረፋ ፣ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳጋለጣቸው ሰምተናል።
አሁን አመሻሹን በሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባሰራጨው መልዕክት ፥ በሳዑዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ወደ አገር የመመለስ ጉዳይ መንግስትን ሲያሳስብ የነበረና መንግስት የዜጎች ችግር መፍትሄ እንዲያገኝ ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር በጉዳዩ ላይ ሲመክር መቆየቱን ገልጿል።
ኤምባሲው የዜጎች ጥያቄ እልባት እንዲያገኝ ከሚመለከታቸው የሳዑዲ አረቢያ መንግስት እና የኢፌዲሪ መንግስት መስሪያ ቤቶች ጋር ጉዳዪ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጠው የበኩሉን ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሷል።
በዚህም መሰረት ፦
(1)--በእስር ቤት ያሉ እና
(2)--የመኖሪያ ፍቃድ የሌላቸው ወደ አገር መመለስ ፈልገው በተለያዩ ምክንያቶች ወደ አገር መመለስ ያልቻሉ ዜጎቻችን በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ወደ አገር የመመለስ ስራ ይጀመራል ብሏል።
በሳዑዲያ አረቢያ የሚገኙ ዜጎቻችንም ኤምባሲው ቃሉን አክብሮ ወደእናት ሀገራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርጋቸው ባገኙት መገናኛ ዘዴ ጥሪ እያቀረቡ ነው።
@tikvahethiopia
#ምርጫ2013 #በምርጫብቻ
ውድ የቲክቫህ አባላት የፊታችን ሰኞ ከሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ ጥያቄዎች፣ ማብራሪያ የምትፈልጉበት ጉዳይ ይኖር ይሆን ?
የምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ በቀጥታ ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ።
ወ/ሪት ሶሊያና ምላሽ የሚሰጡት #በቀጥታ በ Voice Chat ላይ ነው።
ጥያቄዎቻችሁን ከታች በአስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጡ ፤ አንድ አባል ለሚያቀርበው ጥያቄ ሌላ አባል #Reply መስጠት የማችል ሲሆን Reply የሚሰጣጡ አባላትን ከአስተያየት መስጫው ተሳትፏቸውን የምንገድበው ይሆናል።
(ይህ ጥያቄ መቀበያ ነገ ጥዋት 3:00 ይዘጋል)
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
ውድ የቲክቫህ አባላት የፊታችን ሰኞ ከሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ ጥያቄዎች፣ ማብራሪያ የምትፈልጉበት ጉዳይ ይኖር ይሆን ?
የምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ በቀጥታ ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ።
ወ/ሪት ሶሊያና ምላሽ የሚሰጡት #በቀጥታ በ Voice Chat ላይ ነው።
ጥያቄዎቻችሁን ከታች በአስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጡ ፤ አንድ አባል ለሚያቀርበው ጥያቄ ሌላ አባል #Reply መስጠት የማችል ሲሆን Reply የሚሰጣጡ አባላትን ከአስተያየት መስጫው ተሳትፏቸውን የምንገድበው ይሆናል።
(ይህ ጥያቄ መቀበያ ነገ ጥዋት 3:00 ይዘጋል)
#TikvahFamily
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ምርጫ2013 #በምርጫብቻ ውድ የቲክቫህ አባላት የፊታችን ሰኞ ከሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ጋር በተያያዘ ጥያቄዎች፣ ማብራሪያ የምትፈልጉበት ጉዳይ ይኖር ይሆን ? የምርጫ ቦርድ የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወ/ሪት ሶሊያና ሽመልስ በቀጥታ ለቲክቫህ ቤተሰብ አባላት ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣሉ። ወ/ሪት ሶሊያና ምላሽ የሚሰጡት #በቀጥታ በ Voice Chat ላይ ነው። ጥያቄዎቻችሁን ከታች በአስተያየት መስጫው ላይ አስቀምጡ…
#ምርጫ2013 #በምርጫብቻ
ውድ የቲክቫህ አባላት ከትላንት ለሊት 6 ሰዓት አንስቶ በምርጫ ዙሪያ ግልፅ ያልሆነላችሁ፣ ማብራሪያ የምትፈልጉበት ጉዳይ ካለ በሚል ጥያቄዎችን ሰብስበባል።
እጅግ በርካታ ጥያቄዎች ከተለያየ የሀገሪቱ አቅጣጫ ከሚገኙ አባላቶቻችን ተሰብስቧል።
ተመሳስይነት ያላቸውን ጥያቄዎች አንድ ላይ በማድረግ እና የኢትጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የሚመለከተውን ብቻ ለኮሚኒኬሽን ኃላፊዋ ወ/ሪት ሶሊያና አቅርበን ምላሽ እንዲሁም ማብራሪያ እንዲሰጥበት፤ እናተም ጋር ብዥታ ካለ የሚጠራበት መንገድን እናመቻቻለን።
መቼ ነው ምላሽ የሚሰጠው ? ቀኑን ሰዓቱን እናሳውቃለን።
ከዚህ ቀደም ምላሽ ያገኙ ጥያቄዎችን ደግሞ ከ #ምርጫው ጋር የተያያዙ የተለዋወጥናቸውን መረጃዎችን መለስ ብላችሁ እንድትመለከቱት በትህትና እንጠይቃለን። ጠቃሚ የሚባሉ ወሳኝ መልዕክቶችን በድጋሚ እንልክላችኃለን።
@tikvahethiopia
ውድ የቲክቫህ አባላት ከትላንት ለሊት 6 ሰዓት አንስቶ በምርጫ ዙሪያ ግልፅ ያልሆነላችሁ፣ ማብራሪያ የምትፈልጉበት ጉዳይ ካለ በሚል ጥያቄዎችን ሰብስበባል።
እጅግ በርካታ ጥያቄዎች ከተለያየ የሀገሪቱ አቅጣጫ ከሚገኙ አባላቶቻችን ተሰብስቧል።
ተመሳስይነት ያላቸውን ጥያቄዎች አንድ ላይ በማድረግ እና የኢትጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የሚመለከተውን ብቻ ለኮሚኒኬሽን ኃላፊዋ ወ/ሪት ሶሊያና አቅርበን ምላሽ እንዲሁም ማብራሪያ እንዲሰጥበት፤ እናተም ጋር ብዥታ ካለ የሚጠራበት መንገድን እናመቻቻለን።
መቼ ነው ምላሽ የሚሰጠው ? ቀኑን ሰዓቱን እናሳውቃለን።
ከዚህ ቀደም ምላሽ ያገኙ ጥያቄዎችን ደግሞ ከ #ምርጫው ጋር የተያያዙ የተለዋወጥናቸውን መረጃዎችን መለስ ብላችሁ እንድትመለከቱት በትህትና እንጠይቃለን። ጠቃሚ የሚባሉ ወሳኝ መልዕክቶችን በድጋሚ እንልክላችኃለን።
@tikvahethiopia
የታጣቂዎች ጥቃት የ10 ሰዎችን ህይወት ቀጠፈ።
• 10 ሰዎች ተገድለዋል።
• የሟቾች አስክሬን ዛሬ አርብ ለቤተሰቦቻቸው ይሰጣል።
ከቀናት በፊት በደቡብ 'አማሮ ልዩ ወረዳ' አካባቢ ታጣቂዎች የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ህይወት በግፍ ማጥፋታቸውን ከሰማን በኃላ ዛሬ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት በመንገድ ግንባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 10 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን ሰምተናል።
ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው ቢቢሲ የአማርኛው ክፍል ነው።
ጥቃት ተፈፅም የሰዎች ህይወት መጥፋቱን የምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዲሪርሳ ዋቁማ ያረጋገጡ ሲሆን ጥቃቱ በዞኑ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ "ሎያ ጎዳኔ" ቀበሌ ውስጥ ረቡዕ ሰኔ 09/2013 ዓ.ም አመሻሽ 12 ሰዓት አካባቢ መፈፁም ገልፀዋል።
በታጣቂዎች የተገደሉት የፌደራል እና የኦሮሚያ መንገዶች ባለስልጣን ባለሙያ የሆኑ 9 ሰዎች እና የቀበሌው ነዋሪ የሆነች አንዲት ሴት ናቸው ብለዋል።
ጥቃቱ በተፈጸመበት መኪና ውስጥ ከነበሩ 11 የመንገድ ሥራ ባለሙያዎች በሕይወት የተረፉ መኖራቸውንም አክለዋል።
በጥቃቱ የተገደሉት ሰዎች አስከሬን አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል መላኩን እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ መነገሩን ጠቅሰው አስከሬናቸው ዛሬ አርብ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
አቶ ዲሪርሳ ፥ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አስራ አንድ የመንገድ ግንባታ ባለሙያዎች መካከል ከግድያው ያመለጡት ሁለቱ "በአካላቸው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም፤ ደህና ናቸው" ብለዋል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ ጥቃቱን የፈጸመው "ኦነግ-ሸኔ" የተባለው ቡድን እንደሆነ ገልፀዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-06-18
@tikvahethiopia
• 10 ሰዎች ተገድለዋል።
• የሟቾች አስክሬን ዛሬ አርብ ለቤተሰቦቻቸው ይሰጣል።
ከቀናት በፊት በደቡብ 'አማሮ ልዩ ወረዳ' አካባቢ ታጣቂዎች የሁለት ወጣት ኢንጂነሮችን ህይወት በግፍ ማጥፋታቸውን ከሰማን በኃላ ዛሬ ደግሞ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት በመንገድ ግንባታ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 10 ሰዎች በአሰቃቂ ሁኔታ መግደላቸውን ሰምተናል።
ይህን መረጃ ይፋ ያደረገው ቢቢሲ የአማርኛው ክፍል ነው።
ጥቃት ተፈፅም የሰዎች ህይወት መጥፋቱን የምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ዲሪርሳ ዋቁማ ያረጋገጡ ሲሆን ጥቃቱ በዞኑ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ "ሎያ ጎዳኔ" ቀበሌ ውስጥ ረቡዕ ሰኔ 09/2013 ዓ.ም አመሻሽ 12 ሰዓት አካባቢ መፈፁም ገልፀዋል።
በታጣቂዎች የተገደሉት የፌደራል እና የኦሮሚያ መንገዶች ባለስልጣን ባለሙያ የሆኑ 9 ሰዎች እና የቀበሌው ነዋሪ የሆነች አንዲት ሴት ናቸው ብለዋል።
ጥቃቱ በተፈጸመበት መኪና ውስጥ ከነበሩ 11 የመንገድ ሥራ ባለሙያዎች በሕይወት የተረፉ መኖራቸውንም አክለዋል።
በጥቃቱ የተገደሉት ሰዎች አስከሬን አዲስ አበባ ወደሚገኘው ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል መላኩን እና ለቤተሰቦቻቸው መርዶ መነገሩን ጠቅሰው አስከሬናቸው ዛሬ አርብ እንደሚሰጥ ተናግረዋል።
አቶ ዲሪርሳ ፥ ጥቃቱ ከተፈጸመባቸው አስራ አንድ የመንገድ ግንባታ ባለሙያዎች መካከል ከግድያው ያመለጡት ሁለቱ "በአካላቸው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም፤ ደህና ናቸው" ብለዋል።
በምዕራብ ሸዋ ዞን አስተዳዳሪ ጥቃቱን የፈጸመው "ኦነግ-ሸኔ" የተባለው ቡድን እንደሆነ ገልፀዋል።
ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-06-18
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጦር መሳሪያ እያጓጓዘ ነው ?
ከሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የአፍሪካ ግዙፉ እና ግንባር ቀደሙ አየር መንገድ ወትግራይ እንዲሁም ወደሌሎች ቦታዎች መሳሪያ እያዘዋወረ ነው በሚል ስሙ ተነስቷል።
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (OLF) ይፋዊ የፌስቡክ ገፅም አየር መንገዱ ወደ መቐለ፣ ሃዋሳ፣ ኮምቦልቻ የጦር መሳሪያ እያዘዋወረ ነው ሲል በይፋ ፅፏል፤አየር መንገዱን ሎጅስቲክስ በማመላለስ የጦርነት ተሳታፊ እየሆነ ነው ሲል ከሷል።
ትላንት ምሽት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ ምላሽ ሰጥቷል።
ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጦር መሳሪያ እያጓጓዘ እንደሆነ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ እና ከእውነት የራቀ መሆኑን አስረድቷል።
በየትኛውም የሀገር ውስጥ ሆነ የውጪ በረራዎቹ ማንኛውንም አይነት የጦር መሳሪያ እንዳላጓጓዘ ገልጿል።
አየር መንገድ፥ "ምንም አይነት የጦር መሳሪያ ወደ የትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል አላጓጓዝኩም፤ እንዳጓጉዝም አልተጠየኩም" ብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገዱ አንጋፋና ፓን አፍሪካዊ አየር መንገድ መሆኑን ፣ ለአፍሪካውያን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት በግንባር ቀደምነት ላለፉት 75 ዓመታት አህጉሩን ሲያገለግል መቆየቱን በዚህም አየር መንገዱ በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በተቀረው ዓለምም እጅግ የሚያኮራ ስም ማፍራቱን አንስቷል።
በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት በሰራው ስራም ከተለያዩ ሀገራት እና መሪዎች እውቅና ለማግኘት መብቃቱን አስታውሷል።
ነገር ግን "አንዳንድ ሀላፊነት የማይሰማቸው ግለስቦች" ሀሰተኛ እና በፎቶ ሾፕ የተቀናበሩ ምስሎችን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች በማሰራጨት የአየር መንገዱን ስም እና ዝና ለማጠልሸት የሚያደርጉት ጥረት መኖሩን ደምበኞቹ እንዲገነዘቡ አሳውቋል።
@tikvahethiopia
ከሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የአፍሪካ ግዙፉ እና ግንባር ቀደሙ አየር መንገድ ወትግራይ እንዲሁም ወደሌሎች ቦታዎች መሳሪያ እያዘዋወረ ነው በሚል ስሙ ተነስቷል።
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (OLF) ይፋዊ የፌስቡክ ገፅም አየር መንገዱ ወደ መቐለ፣ ሃዋሳ፣ ኮምቦልቻ የጦር መሳሪያ እያዘዋወረ ነው ሲል በይፋ ፅፏል፤አየር መንገዱን ሎጅስቲክስ በማመላለስ የጦርነት ተሳታፊ እየሆነ ነው ሲል ከሷል።
ትላንት ምሽት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ ምላሽ ሰጥቷል።
ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጦር መሳሪያ እያጓጓዘ እንደሆነ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ የተሳሳተ እና ከእውነት የራቀ መሆኑን አስረድቷል።
በየትኛውም የሀገር ውስጥ ሆነ የውጪ በረራዎቹ ማንኛውንም አይነት የጦር መሳሪያ እንዳላጓጓዘ ገልጿል።
አየር መንገድ፥ "ምንም አይነት የጦር መሳሪያ ወደ የትኛውም የኢትዮጵያ ክፍል አላጓጓዝኩም፤ እንዳጓጉዝም አልተጠየኩም" ብሏል።
የኢትዮጵያ አየር መንገዱ አንጋፋና ፓን አፍሪካዊ አየር መንገድ መሆኑን ፣ ለአፍሪካውያን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት በግንባር ቀደምነት ላለፉት 75 ዓመታት አህጉሩን ሲያገለግል መቆየቱን በዚህም አየር መንገዱ በአፍሪካ ብቻ ሳይሆን በተቀረው ዓለምም እጅግ የሚያኮራ ስም ማፍራቱን አንስቷል።
በኮቪድ ወረርሽኝ ወቅት በሰራው ስራም ከተለያዩ ሀገራት እና መሪዎች እውቅና ለማግኘት መብቃቱን አስታውሷል።
ነገር ግን "አንዳንድ ሀላፊነት የማይሰማቸው ግለስቦች" ሀሰተኛ እና በፎቶ ሾፕ የተቀናበሩ ምስሎችን በተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች በማሰራጨት የአየር መንገዱን ስም እና ዝና ለማጠልሸት የሚያደርጉት ጥረት መኖሩን ደምበኞቹ እንዲገነዘቡ አሳውቋል።
@tikvahethiopia