ነገ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች !
የመስቀል አደባባይና እስከ ማዘጋጃ ቤት ድረስ የተከናወነው የመንገድ ግንባታ ምረቃ ምክንያት በማድረግ ሰኔ 6/2013 የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
የምረቃ ስነ ስርዓቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ፦
- ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን የላይኛው አደባባይ
- ፒያሳ ጣሊያን ሰፈር መግቢያ
- ሱማሌ ተራ አካባቢ የሚገኘው አደባባይ
- አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ
- ጎላ ሚካኤል
- ጥቁር አንበሳ ሼል
- ሜትሮሎጂ
- ጎማ ቁጠባ
- ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ
- ለገሃር ጉምሩክ መብራት
- ቡናና ሻይ
- ገነት መብራት
- 4ኛ ክፍለ ጦር (ጥላሁን አደባባይ)
- ቂርቆስ መታጠፊያ
- አጎና ሲኒማ
- ኦሎምፒያ
- ኡራኤል አደባባይ
- ባምቢስ መታጠፊያ
- ካዛንቺስ ሼል
- ፍልውሃ ሸራተን አካባቢ መስጊድ
- ኦርማ ጋራዥ
- ንግድ ማተሚ ቤት
- ራስ መኮንን ድልድይ
- አፍንጮ በር ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ብሏል የከተማው ፖሊስ።
አሽከርካሪዎች ይህን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀሙ ተብሏል።
@tikvahethiopia
የመስቀል አደባባይና እስከ ማዘጋጃ ቤት ድረስ የተከናወነው የመንገድ ግንባታ ምረቃ ምክንያት በማድረግ ሰኔ 6/2013 የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
የምረቃ ስነ ስርዓቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ፦
- ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን የላይኛው አደባባይ
- ፒያሳ ጣሊያን ሰፈር መግቢያ
- ሱማሌ ተራ አካባቢ የሚገኘው አደባባይ
- አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ
- ጎላ ሚካኤል
- ጥቁር አንበሳ ሼል
- ሜትሮሎጂ
- ጎማ ቁጠባ
- ሜክሲኮ ሰንጋ ተራ
- ለገሃር ጉምሩክ መብራት
- ቡናና ሻይ
- ገነት መብራት
- 4ኛ ክፍለ ጦር (ጥላሁን አደባባይ)
- ቂርቆስ መታጠፊያ
- አጎና ሲኒማ
- ኦሎምፒያ
- ኡራኤል አደባባይ
- ባምቢስ መታጠፊያ
- ካዛንቺስ ሼል
- ፍልውሃ ሸራተን አካባቢ መስጊድ
- ኦርማ ጋራዥ
- ንግድ ማተሚ ቤት
- ራስ መኮንን ድልድይ
- አፍንጮ በር ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ ብሏል የከተማው ፖሊስ።
አሽከርካሪዎች ይህን ተገንዝበው አማራጭ መንገዶች እንዲጠቀሙ ተብሏል።
@tikvahethiopia
#Tigray
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ድጋፍ ጉዳዮች ኃላፊ ማርክ ሎውኮክ ትግራይ ክልል ውስጥ የኤርትራ ኃይሎች የትግራይ ህዝብ ለረሃብ እንዲጋለጥ እያደረጉ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ሎውኮክ ይህን ያሉት ከሮይተርስ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ ወቅት ነው።
ኃላፊው ፥ የኤርትራ ወታደሮች እና የአከባቢው ተዋጊዎች ሆን ብለው ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ ባሉ አካባቢዎች ለሚገኙ ከ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሰብዓዊ አቅርቦት እንዳይደርስ እያገዱ ነው ብለዋል።
"በእርግጠኝነት ምግብ እንደ ጦር መሳሪያነት እያገለገለ ነው" ሲሉም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ፣ የተባበሩት መንግስታት እና የእርዳታ ድርጅቶች ከመጋቢት ወር ጀምሮ ለ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ለሚጠጉ የትግራይ ነዋሪዎች ምግብና ሌሎች ድጋፎችን ማድረሳቸውን OCHA ገልጿል፤ ነገር ግን አብዛኛው እርዳታ በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች የሚከናወን ነው ሲሉ ሎኮክ ተናግረዋል።
የተመድ ሰብዓዊ ጉዳዮች ኃላፊ በሆኑት ማርክ ሎውኮክ ለቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት አሁናዊ ምላሽ ባይሰጥም ከዚህ ቀደም የኤርትራ ጦር ትግራይ ውስጥ ሰብዓዊ ድጋፎችን ይዘርፋል፤ ያግዳል መባሉን በተመለከተ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል "የፈጠራ ወሬ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተው ነበር።
የሮይተርስ ሙሉ ዘገባ👇
https://www.reuters.com/world/africa/exclusive-un-official-accuses-eritrean-forces-deliberately-starving-tigray-2021-06-11/
@tikvahethiopia
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ ድጋፍ ጉዳዮች ኃላፊ ማርክ ሎውኮክ ትግራይ ክልል ውስጥ የኤርትራ ኃይሎች የትግራይ ህዝብ ለረሃብ እንዲጋለጥ እያደረጉ ነው ሲሉ ከሰዋል።
ሎውኮክ ይህን ያሉት ከሮይተርስ ጋር በነበራቸው ቃለምልልስ ወቅት ነው።
ኃላፊው ፥ የኤርትራ ወታደሮች እና የአከባቢው ተዋጊዎች ሆን ብለው ከመንግስት ቁጥጥር ውጭ ባሉ አካባቢዎች ለሚገኙ ከ 1 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ሰብዓዊ አቅርቦት እንዳይደርስ እያገዱ ነው ብለዋል።
"በእርግጠኝነት ምግብ እንደ ጦር መሳሪያነት እያገለገለ ነው" ሲሉም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ፣ የተባበሩት መንግስታት እና የእርዳታ ድርጅቶች ከመጋቢት ወር ጀምሮ ለ3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ለሚጠጉ የትግራይ ነዋሪዎች ምግብና ሌሎች ድጋፎችን ማድረሳቸውን OCHA ገልጿል፤ ነገር ግን አብዛኛው እርዳታ በመንግስት ቁጥጥር ስር ባሉ አካባቢዎች የሚከናወን ነው ሲሉ ሎኮክ ተናግረዋል።
የተመድ ሰብዓዊ ጉዳዮች ኃላፊ በሆኑት ማርክ ሎውኮክ ለቀረበው ክስ የኤርትራ መንግስት አሁናዊ ምላሽ ባይሰጥም ከዚህ ቀደም የኤርትራ ጦር ትግራይ ውስጥ ሰብዓዊ ድጋፎችን ይዘርፋል፤ ያግዳል መባሉን በተመለከተ የማስታወቂያ ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል "የፈጠራ ወሬ ነው" ሲሉ ምላሽ ሰጥተው ነበር።
የሮይተርስ ሙሉ ዘገባ👇
https://www.reuters.com/world/africa/exclusive-un-official-accuses-eritrean-forces-deliberately-starving-tigray-2021-06-11/
@tikvahethiopia
#Tigray
የኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ጉዳይ የዛሬው የG7 ስብሰባ ትልቁ አጀንዳ እንደነበር ተሰምቷል።
ከG7 ስብሰባ ጋር በተገናኘ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዜዳንት ቻርልስ ሚሼል በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
የ7 ወራቱ ግጭት ፣ ጭካኔ ፣ ብሔርን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች ፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ዜጎችን ከመቼውም ጊዜ ወደ ከፋ ሰው ሰራሽ ረሃብ እየወሰደ ነው ብለዋል።
መላው የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ችግሩን ለማስወገድ እንዲንቀሳቀስ ጥሪ እናቀርባለን ሲሉ ፅፈዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ጉዳይ የዛሬው የG7 ስብሰባ ትልቁ አጀንዳ እንደነበር ተሰምቷል።
ከG7 ስብሰባ ጋር በተገናኘ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዜዳንት ቻርልስ ሚሼል በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።
የ7 ወራቱ ግጭት ፣ ጭካኔ ፣ ብሔርን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶች ፣ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሃን ዜጎችን ከመቼውም ጊዜ ወደ ከፋ ሰው ሰራሽ ረሃብ እየወሰደ ነው ብለዋል።
መላው የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ችግሩን ለማስወገድ እንዲንቀሳቀስ ጥሪ እናቀርባለን ሲሉ ፅፈዋል።
@tikvahethiopia
#Tigray
ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዛሬ በቪድዮ መልዕክት አሰራጭተዋል።
በመልዕክታቸውም በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በመጠቀም የተለያዩ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ኢትዮጵያን አሳዝኗል ብለዋል።
ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሚያስፈልጋት ጠንክራ ድጋፍ መሆኑን በመግለፅ፥ የኢትዮጵያን ህዝቦችና የግዛት አንድነት አንዲሁም ትስስርን በሰብዓዊነት ሽፋን ዝቅ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተቀባይነት የለውም ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍን ከፍ ለማድረግ፣ ማህበራዊ ትስስርን መልሶ ለመገንባት እና መሰረታዊ የሆኑ አገልግሎቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ከሁሉም አጋሮቿ ጋር ለመስራት ዝግጁ ናት ሲሉም ተደምጠዋል።
በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ወገኖች በሰብዓዊነት ሽፋን የኢትዮጵያን ህዝቦች እና የግዛት አንድነት እና ትስስር ለማዳከም ተልእኮ ይዘው ሲሰሩ ማየት 'የሚያሳዝን ተግባር ነው' እነዚህ ግለሰቦች እና አጋሮቻቸው ከዚህ ተግራቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል።
አቶ ደመቀ፥ "ኢትዮጵያ በራሷ ዜጎች ላይ ረሃብን እንደ ጦር መሣሪያነት እየተጠቀመች ነው" በሚል በሀገሪቱ ላይ የተለጠፉ ክሶች መሰረተ ቢስ ናቸው ብለዋል፤ እንደዚህ አይነት ክሶች በምንምን ስሌት ሰላምንና መረጋጋትን ለመፍጠር አይረዱም።
የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጪ አካላት በትግራይ ውስጥ በነጻነት እንዲሰሩ የሚያስችሉ አሰራሮች መዘርጋቱን ገልፀው፥ “አንዳንድ ተዋንያን ግን በሰብዓዊ ዕርዳታ ሽፋን የሽብርተኞችን ቡድን ለማስታጠቅ መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስገባት መሞከራቸውን የሚያመለክቱ ተዓማኒ #ማስረጃዎች እንዳሉ ተናግረዋል፤ይህ አይነቱ ድርጊትት ተቀባይነት የለውም ብለዋል።
#AlAIN
@tikvahethiopia
ምክትል ጠ/ሚና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ለዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ዛሬ በቪድዮ መልዕክት አሰራጭተዋል።
በመልዕክታቸውም በትግራይ ክልል ያለውን ሁኔታ በመጠቀም የተለያዩ አካላት በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለመፍጠር የሚያደርጉት ጥረት ኢትዮጵያን አሳዝኗል ብለዋል።
ኢትዮጵያ አሁን ላይ የሚያስፈልጋት ጠንክራ ድጋፍ መሆኑን በመግለፅ፥ የኢትዮጵያን ህዝቦችና የግዛት አንድነት አንዲሁም ትስስርን በሰብዓዊነት ሽፋን ዝቅ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት ተቀባይነት የለውም ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍን ከፍ ለማድረግ፣ ማህበራዊ ትስስርን መልሶ ለመገንባት እና መሰረታዊ የሆኑ አገልግሎቶችን ወደ ነበሩበት ለመመለስ ከሁሉም አጋሮቿ ጋር ለመስራት ዝግጁ ናት ሲሉም ተደምጠዋል።
በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ውስጥ ያሉ አንዳንድ ወገኖች በሰብዓዊነት ሽፋን የኢትዮጵያን ህዝቦች እና የግዛት አንድነት እና ትስስር ለማዳከም ተልእኮ ይዘው ሲሰሩ ማየት 'የሚያሳዝን ተግባር ነው' እነዚህ ግለሰቦች እና አጋሮቻቸው ከዚህ ተግራቸው እንዲታቀቡ አሳስበዋል።
አቶ ደመቀ፥ "ኢትዮጵያ በራሷ ዜጎች ላይ ረሃብን እንደ ጦር መሣሪያነት እየተጠቀመች ነው" በሚል በሀገሪቱ ላይ የተለጠፉ ክሶች መሰረተ ቢስ ናቸው ብለዋል፤ እንደዚህ አይነት ክሶች በምንምን ስሌት ሰላምንና መረጋጋትን ለመፍጠር አይረዱም።
የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ ድጋፍ ሰጪ አካላት በትግራይ ውስጥ በነጻነት እንዲሰሩ የሚያስችሉ አሰራሮች መዘርጋቱን ገልፀው፥ “አንዳንድ ተዋንያን ግን በሰብዓዊ ዕርዳታ ሽፋን የሽብርተኞችን ቡድን ለማስታጠቅ መሣሪያዎችን በድብቅ ለማስገባት መሞከራቸውን የሚያመለክቱ ተዓማኒ #ማስረጃዎች እንዳሉ ተናግረዋል፤ይህ አይነቱ ድርጊትት ተቀባይነት የለውም ብለዋል።
#AlAIN
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዛሬ ጥዋት የፌዴሬሽን ም/ቤት አፈጉባኤ አደም ፋራህ የጠ/ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን መልዕክት ለአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ቻርለስ ሚሼል እና ለአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ዩርሱላ ቮን ደር ላየን ማድረሳቸው መገለፁ ይታወሳል። የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስም ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩቴ የተላከ ደብዳቤን ስለማድረሳቸው ተሰምቷል። ደብዳቤውን…
#Update
ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን መልዕክትን ለተለያዩ ሀገራት /ተቋማት እያደረሱ መሆኑን በተለያዩ መረጃዎች ተለዋውጠናል።
ለማስታወስ ያህል ፦
- የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ከጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ለኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩቴ የተላከ ደብዳቤን አድረሳዋል።
- የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ከጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድን የተላከ መልዕክት ለአውሮፓ ህብረት የስራ ሃላፊዎች አድርሰዋል።
- የውሀ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ የተላከ መልዕክት ለኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አድርሰዋል።
በዛሬው ዕለት ደግሞ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የተመራ ልዑክ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን መልእክት ለፈረንሳይ ፕሬዚደንት አድርሷል።
መልእክቱን የተቀበሉት የፈረንሳይ ፕሬዚደንት የአፍሪካ ጉዳዮች ልዩ አማካሪ ሚንስትር ፍራንክ ፓሪስ ናቸው።
ሚኒስትሯ መልዕክቱን ባስተላለፉበት ወቅት በሀገሪቱ ውሥጥ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ ከእሳቤው ጀምሮ ሂደቱና ውጤቶቹ ላይ ያተኮረ ገለጻ አድርገዋል።
በትግራይ ስላሉ የሰብዓዊ ድጋፍ እና የመልሶ ማቋቋም ተግባራት ላይ ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸው ታውቋል።
መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
ከሰሞኑ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ባለስልጣናት የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድን መልዕክትን ለተለያዩ ሀገራት /ተቋማት እያደረሱ መሆኑን በተለያዩ መረጃዎች ተለዋውጠናል።
ለማስታወስ ያህል ፦
- የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ከጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ ለኔዘርላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ማርክ ሩቴ የተላከ ደብዳቤን አድረሳዋል።
- የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ከጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድን የተላከ መልዕክት ለአውሮፓ ህብረት የስራ ሃላፊዎች አድርሰዋል።
- የውሀ መስኖ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ዶ/ር ኢ/ር ስለሺ በቀለ ከጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ የተላከ መልዕክት ለኡጋንዳው ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አድርሰዋል።
በዛሬው ዕለት ደግሞ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል የተመራ ልዑክ የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድን መልእክት ለፈረንሳይ ፕሬዚደንት አድርሷል።
መልእክቱን የተቀበሉት የፈረንሳይ ፕሬዚደንት የአፍሪካ ጉዳዮች ልዩ አማካሪ ሚንስትር ፍራንክ ፓሪስ ናቸው።
ሚኒስትሯ መልዕክቱን ባስተላለፉበት ወቅት በሀገሪቱ ውሥጥ እየተካሄደ ስላለው ለውጥ ከእሳቤው ጀምሮ ሂደቱና ውጤቶቹ ላይ ያተኮረ ገለጻ አድርገዋል።
በትግራይ ስላሉ የሰብዓዊ ድጋፍ እና የመልሶ ማቋቋም ተግባራት ላይ ሰፊ ማብራሪያ መስጠታቸው ታውቋል።
መረጃው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
#Ethiopia #COVID19
ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ካደረገችው 5,405 የኮቪድ19 የላብራቶሪ ምርመራ 136 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል፤ ይህም አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 274,028 አድርሶታል።
በ24 ሰዓት 2 ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 4,237 ደርሷል።
የኮቪድ-19 ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,936,566 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ካደረገችው 5,405 የኮቪድ19 የላብራቶሪ ምርመራ 136 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል፤ ይህም አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር 274,028 አድርሶታል።
በ24 ሰዓት 2 ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን በአጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 4,237 ደርሷል።
የኮቪድ-19 ክትባት የተከተቡ ዜጎች 1,936,566 ደርሰዋል።
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ነገ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ! የመስቀል አደባባይና እስከ ማዘጋጃ ቤት ድረስ የተከናወነው የመንገድ ግንባታ ምረቃ ምክንያት በማድረግ ሰኔ 6/2013 የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል። የምረቃ ስነ ስርዓቱ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ድረስ ፦ - ጊዮርጊስ ቤ/ክርስቲያን የላይኛው አደባባይ - ፒያሳ ጣሊያን ሰፈር መግቢያ - ሱማሌ ተራ አካባቢ የሚገኘው አደባባይ -…
የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ነገ ይመረቃል።
2.6 ቢሊዮን ብር ወጥቶበት የተገነባው የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ነገ እንደሚመረቅ ይጠበቃል።
ፕሮጀክቱ እስከ ማዘጋጃ ቤት የሚዘልቅ የመንገድ ግንባታን ያካተተ ነው።
በተለይ የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት በተጀመረበት ወቅት በአንዳንድ አካላት ከፍተኛ የሆነ ቅራኔ እና ተቃውሞ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርቦ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።
ከሰሞኑ በተሰራጨው የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ "ቃልን በተግባር" በተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ላይ ጠ/ሚስትሩ ይህንን ጉዳይ አንስተውት ነበር።
ጠ/ሚኒስትሩ ፥ ስራው ሲጀመር ቅራኔዎች እና ተቃውሞዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። አሁን ላይ ስራው ተሰርቶ መጠናቀቁን በመግለፅ ሁሉም ዜጋ ቦታውን የመጠበቅ ፣የማሳመር፣ የማስዋብ፣ ከዚህም የተሻለ ቦታ የመስራት ኃላፊነት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
መስቀል አደባባይ ፥ የህዝብ በዓላት ፣ የሙዚቃ ኮንሰርት ፣ ሃይማኖታዊ በዓላት፣ የመንግስት ፕሮግራሞች፣ የተለያዩ አይነት ትርዒቶች ሊታዩበት በሚያስችል መልኩ የተሰራ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።
እስከ 1 ሚሊዮን ሰዎችን ማስተናገድ የሚችልበት አቅም እንዲኖረው መደረጉን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የመስቀል አደባባይ ፓርኪንግ እጅግ ሰፊ እና ለአይንም ማራኪ ሆኖ የተሰራ እስከ 1450 ገደማ መኪና መያዝ የሚችል መሆኑን ገልፀዋል።
Photo Credit : Tikvah Family
@tikvahethiopia
2.6 ቢሊዮን ብር ወጥቶበት የተገነባው የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት ነገ እንደሚመረቅ ይጠበቃል።
ፕሮጀክቱ እስከ ማዘጋጃ ቤት የሚዘልቅ የመንገድ ግንባታን ያካተተ ነው።
በተለይ የመስቀል አደባባይ ፕሮጀክት በተጀመረበት ወቅት በአንዳንድ አካላት ከፍተኛ የሆነ ቅራኔ እና ተቃውሞ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቀርቦ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም።
ከሰሞኑ በተሰራጨው የጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ "ቃልን በተግባር" በተሰኘ ዘጋቢ ፊልም ላይ ጠ/ሚስትሩ ይህንን ጉዳይ አንስተውት ነበር።
ጠ/ሚኒስትሩ ፥ ስራው ሲጀመር ቅራኔዎች እና ተቃውሞዎች እንደነበሩ አስታውሰዋል። አሁን ላይ ስራው ተሰርቶ መጠናቀቁን በመግለፅ ሁሉም ዜጋ ቦታውን የመጠበቅ ፣የማሳመር፣ የማስዋብ፣ ከዚህም የተሻለ ቦታ የመስራት ኃላፊነት እንዳለበት አስገንዝበዋል።
መስቀል አደባባይ ፥ የህዝብ በዓላት ፣ የሙዚቃ ኮንሰርት ፣ ሃይማኖታዊ በዓላት፣ የመንግስት ፕሮግራሞች፣ የተለያዩ አይነት ትርዒቶች ሊታዩበት በሚያስችል መልኩ የተሰራ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።
እስከ 1 ሚሊዮን ሰዎችን ማስተናገድ የሚችልበት አቅም እንዲኖረው መደረጉን ተናግረዋል።
በተጨማሪም የመስቀል አደባባይ ፓርኪንግ እጅግ ሰፊ እና ለአይንም ማራኪ ሆኖ የተሰራ እስከ 1450 ገደማ መኪና መያዝ የሚችል መሆኑን ገልፀዋል።
Photo Credit : Tikvah Family
@tikvahethiopia
ለምርጫ ቅስቀሳው የቀረችው የመጨረሻዋ እሁድ!
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከየካቲት 8 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅቶች ነበሩ።
ግንቦት 28 ይደረጋል በተባለው ምርጫ የምርጫ ቅስቀሳው የሚያበቃው በግንቦት 23 ነበር። ሆኖም ምርጫው ወደ ሰኔ 14 መዛወሩን ተከትሎ የመርጫ ቅስቀሳውም አብሮ መራዘሙ ይታወሳል።
ብዙዎች የምርጫ ቅስቀሳዎቹ በተለይ በጅምሩ ጊዜያት ተቀዛቅዞ እንደነበር ይጠቅሳሉ።
አንዳንድ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ያላቸውን አማራጭ ኃሳብ ባገኙት አጋጣሚ በአግባቡ አለማድረሳቸው ይገለፃል።
በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት በአንዳንድ አከባቢዎች የምርጫ ቅስቀሳ የተከለከለባቸው፤ አባሎቻቸውም የታሰሩባቸው ስለመኖሩ ከፖርቲዎች የሚቀርብ ክስ ነው።
በአንጻሩ በዚህ ወቅት ምርጫው በበርካቶች ዘንድ ትኩረት ማግኘቱ እሙን ነው። ከአላስፈላጊ ቃላት ልውውጥ ውጪ ዜጎች አማራጭ ኃሳቦችን እንዲመለከቱ፤ እንዲያወዳድሩና እንንዲመርጡ ቀላል የማይባሉ ሥራዎች ተሰርተዋል።
የምርጫ ቅስቀሳው ከመጭው አርብ በፊት ተጠናቆ ምንም ቅስቀሳ ወደማይካሄድበት ወደ የጥሞና ጊዜ ለመግባት የዛሬዋ እሁድና ጥቂት ቀናት ቀርተዋል።
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከየካቲት 8 ቀን 2013 ዓ/ም ጀምሮ የምርጫ ቅስቀሳ ወቅቶች ነበሩ።
ግንቦት 28 ይደረጋል በተባለው ምርጫ የምርጫ ቅስቀሳው የሚያበቃው በግንቦት 23 ነበር። ሆኖም ምርጫው ወደ ሰኔ 14 መዛወሩን ተከትሎ የመርጫ ቅስቀሳውም አብሮ መራዘሙ ይታወሳል።
ብዙዎች የምርጫ ቅስቀሳዎቹ በተለይ በጅምሩ ጊዜያት ተቀዛቅዞ እንደነበር ይጠቅሳሉ።
አንዳንድ የተፎካካሪ ፓርቲዎች ያላቸውን አማራጭ ኃሳብ ባገኙት አጋጣሚ በአግባቡ አለማድረሳቸው ይገለፃል።
በምርጫ ቅስቀሳው ወቅት በአንዳንድ አከባቢዎች የምርጫ ቅስቀሳ የተከለከለባቸው፤ አባሎቻቸውም የታሰሩባቸው ስለመኖሩ ከፖርቲዎች የሚቀርብ ክስ ነው።
በአንጻሩ በዚህ ወቅት ምርጫው በበርካቶች ዘንድ ትኩረት ማግኘቱ እሙን ነው። ከአላስፈላጊ ቃላት ልውውጥ ውጪ ዜጎች አማራጭ ኃሳቦችን እንዲመለከቱ፤ እንዲያወዳድሩና እንንዲመርጡ ቀላል የማይባሉ ሥራዎች ተሰርተዋል።
የምርጫ ቅስቀሳው ከመጭው አርብ በፊት ተጠናቆ ምንም ቅስቀሳ ወደማይካሄድበት ወደ የጥሞና ጊዜ ለመግባት የዛሬዋ እሁድና ጥቂት ቀናት ቀርተዋል።
@tikvahethiopia
#Afar
በአፋር ክልል በአሳይታ ከተማ በሼይኽ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲን አማካኝነት ግንባታው ተጀምሮ በመሃል ግንባታው ለረጅም አመታት እንዲቋረጥ ተደርጎ የቆየው ግዙፉ የኢስላማዊ ማእከል የተቋረጠውን ግንባታ ዳግም ለማስጀምር እና ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እንዲቻል በዛሬው ዕለት በአሳይታ ከተማ የገቢ ማሰባሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል።
በአሳይታ ከተማ ለሱልጣን አሊ ሚራህ መድረሳ ማስቀጠያ ዝግጅት ፦
- የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ፣
- የፌዴራልና የክልል መጅሊስ አመራሮች ፣
- የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
መረጃው ከሀሩን ሚድያ እና ከኡስታዝ አቡበክር አህመድ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia
በአፋር ክልል በአሳይታ ከተማ በሼይኽ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲን አማካኝነት ግንባታው ተጀምሮ በመሃል ግንባታው ለረጅም አመታት እንዲቋረጥ ተደርጎ የቆየው ግዙፉ የኢስላማዊ ማእከል የተቋረጠውን ግንባታ ዳግም ለማስጀምር እና ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እንዲቻል በዛሬው ዕለት በአሳይታ ከተማ የገቢ ማሰባሰቢያ እየተካሄደ ይገኛል።
በአሳይታ ከተማ ለሱልጣን አሊ ሚራህ መድረሳ ማስቀጠያ ዝግጅት ፦
- የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ አወል አርባ፣
- የፌዴራልና የክልል መጅሊስ አመራሮች ፣
- የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ነው እየተካሄደ የሚገኘው።
መረጃው ከሀሩን ሚድያ እና ከኡስታዝ አቡበክር አህመድ የተገኘ ነው።
@tikvahethiopia