የብሔራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሳ መግለጫ ፦
- መንግስት ከዚህ በኋላ ከትግራይ አጠቃላይ የቆዳ ስፋት ውስጥ በ14 በመቶው ብቻ ድጋፍ ያደርጋል ፤ ቀሪው 86 በመቶው የዓለም ምግብ ፕሮግራምን ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ እርዳታ ሰጭ ተቋማት ይሸፈናል። ከዚህ ቀደም 70% ሲሸፈን የነበረው በኢትዮጵያ መንግስት ብቻ ነበር።
- ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስ በ3 መንገድ እየተሰራ ነው።
ሶስቱ መንገዶች ፦
• ሰላም በተረጋገጠባቸው ቦታዎች ላይ ህዝቡን በማወያየት መመለስ፣
• ሙሉ ሰላም ያልተረጋገጠባቸው ቦታዎች ላይ ስነልቦናዊ ችግሮችን ለማቅለል ወደዘመድ እንዲሄዱ መርዳት
• ሰላም ካልተረጋገጠባቸው ቦታዎች ለተፈናቀሉት ደግሞ ጊዜያዊ መጠለያን ማዘጋጀት የሚሉ ናቸው።
- ለሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ተጨማሪ 4 ተቋማት ፈቃድ አግኝተዋል፡፡
- ሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረግ አልተቻለም በሚል የሚቀርቡ ክሶችና ወቀሳዎች ከአሁን በኋላ ተቀባይነት የላቸውም።
- እርዳታዎችን ለማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ተከፍተዋል።
- “በረሀብ የሞተ ሰው የለም”፤ ነገር ግን ዓለም አቀፍ ተቋማት “እርዳታ ለማግኘት ሲሉ ጉዳዩን እያስጮሁት” ነው። “ልክ እንደ የመን እና ሶሪያ እርዳታ ለማግኘት ጉዳዩን እየተደረገ ያለ ሩጫ ነው።
በሌላ በኩል ፦
በሀገሪቱ ያለው የተፈናቃይ ብዛት 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሲሆን 40 በመቶ ያህሉን ለመመለስ መታሰቡን ተጠቁሟል።
አጣየ በተመለከተ፦ አማራ ክልል ውስጥ ለ50ሺ ተረጂዎች ድጋፍ እንዲደረግ ችግሩ በተፈጠረበት ወቅት ወዲያውኑ መጠየቁን ተከትሎ ድጋፉ በማግስቱ (ቅዳሜ ተጠይቆ እሁድ) እንዲደርስ ተደርጓል።
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
- መንግስት ከዚህ በኋላ ከትግራይ አጠቃላይ የቆዳ ስፋት ውስጥ በ14 በመቶው ብቻ ድጋፍ ያደርጋል ፤ ቀሪው 86 በመቶው የዓለም ምግብ ፕሮግራምን ጨምሮ በሌሎች ዓለም አቀፍ እርዳታ ሰጭ ተቋማት ይሸፈናል። ከዚህ ቀደም 70% ሲሸፈን የነበረው በኢትዮጵያ መንግስት ብቻ ነበር።
- ተፈናቃዮችን ወደቀያቸው ለመመለስ በ3 መንገድ እየተሰራ ነው።
ሶስቱ መንገዶች ፦
• ሰላም በተረጋገጠባቸው ቦታዎች ላይ ህዝቡን በማወያየት መመለስ፣
• ሙሉ ሰላም ያልተረጋገጠባቸው ቦታዎች ላይ ስነልቦናዊ ችግሮችን ለማቅለል ወደዘመድ እንዲሄዱ መርዳት
• ሰላም ካልተረጋገጠባቸው ቦታዎች ለተፈናቀሉት ደግሞ ጊዜያዊ መጠለያን ማዘጋጀት የሚሉ ናቸው።
- ለሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት ተጨማሪ 4 ተቋማት ፈቃድ አግኝተዋል፡፡
- ሰብዓዊ ድጋፎችን ለማድረግ አልተቻለም በሚል የሚቀርቡ ክሶችና ወቀሳዎች ከአሁን በኋላ ተቀባይነት የላቸውም።
- እርዳታዎችን ለማድረግ የሚያስችሉ ሁኔታዎች ሙሉ በሙሉ ተከፍተዋል።
- “በረሀብ የሞተ ሰው የለም”፤ ነገር ግን ዓለም አቀፍ ተቋማት “እርዳታ ለማግኘት ሲሉ ጉዳዩን እያስጮሁት” ነው። “ልክ እንደ የመን እና ሶሪያ እርዳታ ለማግኘት ጉዳዩን እየተደረገ ያለ ሩጫ ነው።
በሌላ በኩል ፦
በሀገሪቱ ያለው የተፈናቃይ ብዛት 2 ነጥብ 1 ሚሊዮን ሲሆን 40 በመቶ ያህሉን ለመመለስ መታሰቡን ተጠቁሟል።
አጣየ በተመለከተ፦ አማራ ክልል ውስጥ ለ50ሺ ተረጂዎች ድጋፍ እንዲደረግ ችግሩ በተፈጠረበት ወቅት ወዲያውኑ መጠየቁን ተከትሎ ድጋፉ በማግስቱ (ቅዳሜ ተጠይቆ እሁድ) እንዲደርስ ተደርጓል።
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የUN ድጋፍ ለኢትዮጵያ !
UN በኢትዮጵያ ለሰብአዊ ድጋፍ የሚውል 65 ሚሊየን ዶላር ለቋል።
ድጋፉ በተለያዩ ምክንያቶች ሰብአዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ምግብ ፣ የመጠለያ ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችላል።
የUN ድጋፍ በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ ከ16 ሚሊየን በላይ ዜጎች ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስ ይውላል። ከነዚህ ውስጥ 4.5 ሚሊዮን ገደማ በትግራይ ክልል የሚገኙ ናቸው።
ከድጋፍ ውስጥ 40 ሚሊየን ዶላሩ በትግራይ ሰብአዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሚውል ሲሆን ቀሪው በሌሎች የሃገሪቱ አካባቢዎች ይውላል።
* የUN መግለጫ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
UN በኢትዮጵያ ለሰብአዊ ድጋፍ የሚውል 65 ሚሊየን ዶላር ለቋል።
ድጋፉ በተለያዩ ምክንያቶች ሰብአዊ ድጋፍ የሚያስፈልጋቸው ዜጎች ምግብ ፣ የመጠለያ ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እና የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ ያስችላል።
የUN ድጋፍ በመላው ኢትዮጵያ ለሚገኙ ከ16 ሚሊየን በላይ ዜጎች ሰብአዊ ድጋፍ ለማድረስ ይውላል። ከነዚህ ውስጥ 4.5 ሚሊዮን ገደማ በትግራይ ክልል የሚገኙ ናቸው።
ከድጋፍ ውስጥ 40 ሚሊየን ዶላሩ በትግራይ ሰብአዊ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሚውል ሲሆን ቀሪው በሌሎች የሃገሪቱ አካባቢዎች ይውላል።
* የUN መግለጫ ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
"ከ20 እስከ 30 ወንድሞቻችንን እና እህቶቻችን እናስመርቃለን"
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ወንድማማችነት እና እህትማማችንነትን ለማጎልበት በማሰብና አመርቂ ውጤት ያላቸውን ተማሪዎች ለማበረታት እገዛ ለማድረግ ስራዎችን ጀምሮ ነበር።
በፀጥታ ችግር እና በኮቪድ-19 ምክንያት ዩኒቨርሲቲዎች በመዘጋታቸው መስተጓጎል ተፈጥሮ የነበር ቢሆንም ከዚህ ቀደም እንዳሳወቅነው ለሁለት (የ2012) ተመራቂዎች ስጦታውን ማበርከት ተችሏል ።
ለደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ እና ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጥሩ ውጤት ካላቸው እና ቤተሰቦቻችን አቅም ካጠራቸው መካከል ለመመረቂያቸው እንዲሆን ለ2 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው 10 ሺህ ብር ልከናል።
እቅዱ የነበረው ላፕቶፕ ኮምፒዩተሮችን ገዞት ለመስጠት የነበር ቢሆንም አልተሳካም።
ምክንያት ?
የአቅም ውስንነት ተፈጥሮ ነበር።
በፀጥታ ችግር (በተለይ የትግራይ ቲክቫህ አባላት ባሉበት ትግራይ ክልል ጦርነት በመቀስቀሱ) ምክንያት እንዲሁም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መነሻ ጊዜ ሰዎች አንገብጋቢ መረጃ ለመለዋወጥ በሚፈልጉበት ወቅት ማስታወቂያ ስለማናሰራጭ / ሙሉ በሙሉ ማስታወቂያ ስለሚቆም ቃል የገባነውን ለማድረግ የአቅም ውስንነት ተፈጥሮ ነበር።
ቲክቫህ ቤተሰብ ከሚሰራጩት ውስን ማስታወቂያዎች ውጭ ምንም አይነት የተለየ ድጋፍ የሌለው መሆኑ ይታወቃል።
ዘንድሮ ?
ከ20 እስከ 30 የዩኒቨርሲቲ (2013) ተመራቂ ተማሪዎችን በተለይ ጥሩ ውጤት ያላቸውን የመመረቂያ አልባሳቶቻቸውን ሙሉ ወጪ ለመሸፈን እንሰራለን።
መነሻችን ደብረ ታቦር እና ወለጋ ያደረግን ሲሆን አሁን በሌሎች 4 ዩኒቨርሲቲዎች ይቀጥላል። የትኞቹን ዩኒቨርሲቲዎች የሚለውን በቀጣይ እንገልፃለን።
በዘንድሮው ቤተሰባዊ የስራ ለመሳተፍ @tikvahethiopiaBOT መልዕክት አስቀምጡ።
#TikvahFamily❤️
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ወንድማማችነት እና እህትማማችንነትን ለማጎልበት በማሰብና አመርቂ ውጤት ያላቸውን ተማሪዎች ለማበረታት እገዛ ለማድረግ ስራዎችን ጀምሮ ነበር።
በፀጥታ ችግር እና በኮቪድ-19 ምክንያት ዩኒቨርሲቲዎች በመዘጋታቸው መስተጓጎል ተፈጥሮ የነበር ቢሆንም ከዚህ ቀደም እንዳሳወቅነው ለሁለት (የ2012) ተመራቂዎች ስጦታውን ማበርከት ተችሏል ።
ለደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ እና ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ጥሩ ውጤት ካላቸው እና ቤተሰቦቻችን አቅም ካጠራቸው መካከል ለመመረቂያቸው እንዲሆን ለ2 ተማሪዎች ለእያንዳንዳቸው 10 ሺህ ብር ልከናል።
እቅዱ የነበረው ላፕቶፕ ኮምፒዩተሮችን ገዞት ለመስጠት የነበር ቢሆንም አልተሳካም።
ምክንያት ?
የአቅም ውስንነት ተፈጥሮ ነበር።
በፀጥታ ችግር (በተለይ የትግራይ ቲክቫህ አባላት ባሉበት ትግራይ ክልል ጦርነት በመቀስቀሱ) ምክንያት እንዲሁም በኮቪድ-19 ወረርሽኝ መነሻ ጊዜ ሰዎች አንገብጋቢ መረጃ ለመለዋወጥ በሚፈልጉበት ወቅት ማስታወቂያ ስለማናሰራጭ / ሙሉ በሙሉ ማስታወቂያ ስለሚቆም ቃል የገባነውን ለማድረግ የአቅም ውስንነት ተፈጥሮ ነበር።
ቲክቫህ ቤተሰብ ከሚሰራጩት ውስን ማስታወቂያዎች ውጭ ምንም አይነት የተለየ ድጋፍ የሌለው መሆኑ ይታወቃል።
ዘንድሮ ?
ከ20 እስከ 30 የዩኒቨርሲቲ (2013) ተመራቂ ተማሪዎችን በተለይ ጥሩ ውጤት ያላቸውን የመመረቂያ አልባሳቶቻቸውን ሙሉ ወጪ ለመሸፈን እንሰራለን።
መነሻችን ደብረ ታቦር እና ወለጋ ያደረግን ሲሆን አሁን በሌሎች 4 ዩኒቨርሲቲዎች ይቀጥላል። የትኞቹን ዩኒቨርሲቲዎች የሚለውን በቀጣይ እንገልፃለን።
በዘንድሮው ቤተሰባዊ የስራ ለመሳተፍ @tikvahethiopiaBOT መልዕክት አስቀምጡ።
#TikvahFamily❤️
"የዘንድሮው የፊቼ ጫምባላላ በዓል በኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት በአደባባይ አይከበርም" - አቶ ደስታ ሌዳሞ
የዘንድሮውን የፊቼ ጫምባላላ በዓል የኮሮና ወረርሽኝ መስፋፋትን ለመከላከል ሲባል በአደባባይ እንደማይከበር የሲዳማ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።
ህብረተሰቡ በዓሉን ሲያከብር ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመርዳትና እርስ በእርስ በመደጋገፍ ሊሆን እንደሚገባውም ርዕሰ መስተዳደሩ ዛሬ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ገልጸዋል።
የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ የሆነው“ ፊቼ ጫምባላላ ” ከጥንት ጀምሮ ሲከበር የቆየ መሆኑን አስታውሰው፤ በዓሉ የተጣሉትን በማስታረቅ ፣ የተቸገሩትን በመርዳትና ለሰው ልጆችና እንስሳት ክብር በመስጠት የሚከበር ታላቅ በዓል መሆኑን አስረድተዋል።
“ለበዓሉ ሲባል እንስሳት የማይታረዱበት በቀያቸው በእንክብካቤ የሚያሳልፉበት እንዲሁም ዛፍ የማይቆረጥበት በመሆኑም እለቱን ልዩ ያደርገዋል” ብለዋል።
በአሁን ወቅት በፍጥነት እየተዛመተና በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያሰከተለ ባለው የኮሮና ወረርሽኝ ተዕዕኖ ምክንያት በዓሉ እንደወትሮው በአደባባይ በመሰባሰብ እንደማይከበርም ገልጸዋል።
ሆኖም በዓሉ ባህላዊ ትውፊቱን ሳይለቅ ዘንድሮ ሁሉም የብሄሩ ተወላጅ በየቤቱ ሆኖ የሚያከብረው መሆኑን አመላክተዋል።
ህብረተሰቡ የዘንድሮውን ፊቼ ጫምባላላ በአልን ሲያከብር እራሱን ከኮሮና ወረርሽኝ በመከላከል ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።
በተለይ ከተጣላው ጋር ይቅር በመባባል እና ከመዋደድ ባሻገር እርስ በእርስ በመደጋገፍ እንዲሆንም አቶ ደስታ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የዘንድሮው የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ “ፊቼ ጫምባላላ” በዓል ከንክኪ በራቀ መልክ ሚያዝያ 29 እና 30 እንደሚከበርም ጨምረው ገልፀዋል። #ENA
@tikvahethiopiaBOT
የዘንድሮውን የፊቼ ጫምባላላ በዓል የኮሮና ወረርሽኝ መስፋፋትን ለመከላከል ሲባል በአደባባይ እንደማይከበር የሲዳማ ክልል ርዕሰ-መስተዳደር አቶ ደስታ ሌዳሞ አስታወቁ።
ህብረተሰቡ በዓሉን ሲያከብር ለችግር የተጋለጡ ወገኖችን በመርዳትና እርስ በእርስ በመደጋገፍ ሊሆን እንደሚገባውም ርዕሰ መስተዳደሩ ዛሬ ባስተላለፉት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ገልጸዋል።
የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ የሆነው“ ፊቼ ጫምባላላ ” ከጥንት ጀምሮ ሲከበር የቆየ መሆኑን አስታውሰው፤ በዓሉ የተጣሉትን በማስታረቅ ፣ የተቸገሩትን በመርዳትና ለሰው ልጆችና እንስሳት ክብር በመስጠት የሚከበር ታላቅ በዓል መሆኑን አስረድተዋል።
“ለበዓሉ ሲባል እንስሳት የማይታረዱበት በቀያቸው በእንክብካቤ የሚያሳልፉበት እንዲሁም ዛፍ የማይቆረጥበት በመሆኑም እለቱን ልዩ ያደርገዋል” ብለዋል።
በአሁን ወቅት በፍጥነት እየተዛመተና በህብረተሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያሰከተለ ባለው የኮሮና ወረርሽኝ ተዕዕኖ ምክንያት በዓሉ እንደወትሮው በአደባባይ በመሰባሰብ እንደማይከበርም ገልጸዋል።
ሆኖም በዓሉ ባህላዊ ትውፊቱን ሳይለቅ ዘንድሮ ሁሉም የብሄሩ ተወላጅ በየቤቱ ሆኖ የሚያከብረው መሆኑን አመላክተዋል።
ህብረተሰቡ የዘንድሮውን ፊቼ ጫምባላላ በአልን ሲያከብር እራሱን ከኮሮና ወረርሽኝ በመከላከል ሊሆን እንደሚገባም አሳስበዋል።
በተለይ ከተጣላው ጋር ይቅር በመባባል እና ከመዋደድ ባሻገር እርስ በእርስ በመደጋገፍ እንዲሆንም አቶ ደስታ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
የዘንድሮው የሲዳማ ህዝብ ዘመን መለወጫ “ፊቼ ጫምባላላ” በዓል ከንክኪ በራቀ መልክ ሚያዝያ 29 እና 30 እንደሚከበርም ጨምረው ገልፀዋል። #ENA
@tikvahethiopiaBOT
#Egypt
የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዑክ ከግብጹ ፕሬዝዳንት ጋር በታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ መነጋገራቸው ተሰምቷል።
ማክሰኞ ግብጽ የገቡት ልዑኩ ጄፍሪ ፌልትማን ትናንት ነው የግብጹን ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አልሲሲን ያነጋገሩት።
አብዱል ፈታህ አል ሲሲ አሜሪካ በግድቡ ምክንያት ለተነሳው ውዝግብ መፍትሄ ለማግኘት ውጤታማ ሚና እንድትጫወት ጠይቀዋል ተብሏል።
ግድቡ የሃገራቸው ህልውና ጉዳይ መሆኑን ተናግረው ግብጽ የውሃ ፍላጎቷን የሚጎዳን ማንንም እንደማትቀበል እንዳስታወቁ ተሰምቷል።
በተጨማሪ ፌልትማን የግብጹን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያነጋገሩ ሲሆን ፥ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ጥንቃቄ ለሚፈልገው ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ለመሻት ከልብ እንዳሰበበት ተናግረዋል።
ፌልትማን ኤርትራ ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳንን በቀጣይ እንደሚጎበኙ ዶቼ ቨለ አሶሼትድ ፕሬስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
@tikvahethiopiopia @tikvahethiopiaBOT
የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዑክ ከግብጹ ፕሬዝዳንት ጋር በታላቁ ህዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ መነጋገራቸው ተሰምቷል።
ማክሰኞ ግብጽ የገቡት ልዑኩ ጄፍሪ ፌልትማን ትናንት ነው የግብጹን ፕሬዝዳንት አብደል ፈታህ አልሲሲን ያነጋገሩት።
አብዱል ፈታህ አል ሲሲ አሜሪካ በግድቡ ምክንያት ለተነሳው ውዝግብ መፍትሄ ለማግኘት ውጤታማ ሚና እንድትጫወት ጠይቀዋል ተብሏል።
ግድቡ የሃገራቸው ህልውና ጉዳይ መሆኑን ተናግረው ግብጽ የውሃ ፍላጎቷን የሚጎዳን ማንንም እንደማትቀበል እንዳስታወቁ ተሰምቷል።
በተጨማሪ ፌልትማን የግብጹን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ያነጋገሩ ሲሆን ፥ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ጥንቃቄ ለሚፈልገው ለዚህ ጉዳይ መፍትሄ ለመሻት ከልብ እንዳሰበበት ተናግረዋል።
ፌልትማን ኤርትራ ፣ ኢትዮጵያ እና ሱዳንን በቀጣይ እንደሚጎበኙ ዶቼ ቨለ አሶሼትድ ፕሬስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
@tikvahethiopiopia @tikvahethiopiaBOT
#Ethiopia😷
ባለፉት 24 ሰዓት 27 ሰዎች በኮቪድ-19 ህይወታቸው አልፏል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 4,914 የላብራቶሪ ምርመራ 663 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 2,050 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 260,802 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,822 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 205,458 ሰዎች አገግመዋል።
አሁን ላይ 748 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
በሀገራችን እየተሰጠ ያለውን የኮቪድ-19 ክትባት የተከተቡ ዜጎች ቁጥር 1,237,826 ደርሷል።
#Purpose
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ባለፉት 24 ሰዓት 27 ሰዎች በኮቪድ-19 ህይወታቸው አልፏል።
በተመሳሳይ ከተደረገው 4,914 የላብራቶሪ ምርመራ 663 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ትላንት 2,050 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 260,802 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 3,822 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 205,458 ሰዎች አገግመዋል።
አሁን ላይ 748 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
በሀገራችን እየተሰጠ ያለውን የኮቪድ-19 ክትባት የተከተቡ ዜጎች ቁጥር 1,237,826 ደርሷል።
#Purpose
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ዛሬ ምሽት በetv ቀርበው ስለህዳሴው ግድብ ከተናገሩት ፦
- DRC ኮንጎ አመራርነቱን ከተረከበች በኃላ በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ እስካሁን አንድ ጊዜ ለሶስትዮሽ ድርድር ተቀምጠዋል።
- የሶስትዮሽ ድርድሩ በሁለቱ ሀገራት ምክንያት (ግብፅ እና ሱዳን) ፍላጎት ማነስ ተቋርጧል።
- ኢትዮጵያ ሁል ጊዜም ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ መቀጠል ነው።
- ኢትዮጵያ ሁሌም የምትለውን ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ አቋም ላይ እንድረስ የሚል ነው። በዋናነት በሙሌቱና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ እንስማማ እያለች ነው።
- የሙሌት ስምምነቱን በተመለከተ ግን ሱዳን እና ግብፅ አጠቃላይ ስምምነቱን ካልደረስን ካልተፈራረምን በሚል ፣ ሌሎች አደራዳሪዎችን በመፈለግ ሂደቱን እያፈረሱት ነው።
- ኢትዮጵያ አጠቃላይ ስምምነቱ በሂደት ይመጣል ብላለች። በአንዴ የሚሆን አይደለም ጊዜ ይወስዳል። በበርካታ ጉዳዮች ላይ መነጋጋረ አለብን ብላለች።
- አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ዝናብ ነው፣ ብዙ ውሃ አለ፣ ከሚመጣው ውሃ እንኳን አብዛኛውን እየተያዘ አይደለም ፤ ሙሌቱ ላይ እንስማማ የሚል አቋም ነው ያለው በኢትዮጵያ በኩል። እነሱ ግን አልተቀበሉትም።
- ግድቡ የሚሰራው ሊሞላ ነው ፤ አምና የመጀመሪያው ሙሌት ሄዷል ዘንድሮ ሁለተኛው ይሄዳል፤ ይሄ በ2015 የሶስትዮሽ ስምምነት ላይ ያለ ነው ፤ ነገር ግን ይሄንንም እየተቃወሙ ነው።
- ኢትዮጵያ ሙሌቱ እና አጠቃላይ ፕሮጀክቱ እንደማይጎዳቸው እየገለፀች ነው።
- አሁን በተለይ ሱዳኖቹ ጥያቄዎቻቸው የተመለሱላቸው ይመስላል ፤ ድብቅ ፍላጎታቸው ሌላ ቢሆንም፤አንዴ የአፍሪካ ህብረትን ሚና እያሳነሱ ሌላ አደራዳሪ እየፈለጉ፤ አንዴ ሚናዎችን እንዲበረዙ መሰናክሎች እየደረደሩ ነው።
- ኢትዮጵያ ወደሁለተኛው ሙሌቱ መሄዷ የማይቀር ነው።
@tikvahethiopia
- DRC ኮንጎ አመራርነቱን ከተረከበች በኃላ በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ እስካሁን አንድ ጊዜ ለሶስትዮሽ ድርድር ተቀምጠዋል።
- የሶስትዮሽ ድርድሩ በሁለቱ ሀገራት ምክንያት (ግብፅ እና ሱዳን) ፍላጎት ማነስ ተቋርጧል።
- ኢትዮጵያ ሁል ጊዜም ድርድሩ በአፍሪካ ህብረት ማዕቀፍ መቀጠል ነው።
- ኢትዮጵያ ሁሌም የምትለውን ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርግ አቋም ላይ እንድረስ የሚል ነው። በዋናነት በሙሌቱና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ እንስማማ እያለች ነው።
- የሙሌት ስምምነቱን በተመለከተ ግን ሱዳን እና ግብፅ አጠቃላይ ስምምነቱን ካልደረስን ካልተፈራረምን በሚል ፣ ሌሎች አደራዳሪዎችን በመፈለግ ሂደቱን እያፈረሱት ነው።
- ኢትዮጵያ አጠቃላይ ስምምነቱ በሂደት ይመጣል ብላለች። በአንዴ የሚሆን አይደለም ጊዜ ይወስዳል። በበርካታ ጉዳዮች ላይ መነጋጋረ አለብን ብላለች።
- አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ዝናብ ነው፣ ብዙ ውሃ አለ፣ ከሚመጣው ውሃ እንኳን አብዛኛውን እየተያዘ አይደለም ፤ ሙሌቱ ላይ እንስማማ የሚል አቋም ነው ያለው በኢትዮጵያ በኩል። እነሱ ግን አልተቀበሉትም።
- ግድቡ የሚሰራው ሊሞላ ነው ፤ አምና የመጀመሪያው ሙሌት ሄዷል ዘንድሮ ሁለተኛው ይሄዳል፤ ይሄ በ2015 የሶስትዮሽ ስምምነት ላይ ያለ ነው ፤ ነገር ግን ይሄንንም እየተቃወሙ ነው።
- ኢትዮጵያ ሙሌቱ እና አጠቃላይ ፕሮጀክቱ እንደማይጎዳቸው እየገለፀች ነው።
- አሁን በተለይ ሱዳኖቹ ጥያቄዎቻቸው የተመለሱላቸው ይመስላል ፤ ድብቅ ፍላጎታቸው ሌላ ቢሆንም፤አንዴ የአፍሪካ ህብረትን ሚና እያሳነሱ ሌላ አደራዳሪ እየፈለጉ፤ አንዴ ሚናዎችን እንዲበረዙ መሰናክሎች እየደረደሩ ነው።
- ኢትዮጵያ ወደሁለተኛው ሙሌቱ መሄዷ የማይቀር ነው።
@tikvahethiopia
#Update
ፌልትንማን ከኤርትራ ፕሬዜዳንት ጋር ተወያዩ።
በጁፍሪ ፌልትማን የሚመራው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዑክ ኤርትራ አስመራ ገብቷል።
የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈረወርቂ ልዑኩን በደንደን የእንግዳ መቀበያ ተቀብለው አነጋግረዋቸዋል።
ፕሬዜዳንት ኢሳያስ ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ከአሜሪካ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን እንዳስረዱ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።
አምባሳደር ፌልማን በበኩላቸው በአፍሪካ ቀንድ እየታዩ ባሉ ችግሮች ዙሪያ የአሜሪካ አስተዳደር ያለውን አመለካከትና እይታ ለፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እንዳብራሩላቸው የኤርትራው ኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ገልፀዋል።
የነበረው ውይይት 4:00 ሰዓት ገደማ የወሰደ እንደነበረ የተሰማ ሲሆን ከላይ ከተገለፀው መረጃ ውጭ ሌሎች ዝርዝር መረጃዎች እስካሁን ይፋ አልሆኑም።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ፌልትንማን ከኤርትራ ፕሬዜዳንት ጋር ተወያዩ።
በጁፍሪ ፌልትማን የሚመራው የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዑክ ኤርትራ አስመራ ገብቷል።
የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈረወርቂ ልዑኩን በደንደን የእንግዳ መቀበያ ተቀብለው አነጋግረዋቸዋል።
ፕሬዜዳንት ኢሳያስ ኤርትራ በአፍሪካ ቀንድ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት በሚደረገው ጥረት ከአሜሪካ ጋር በትብብር ለመስራት ዝግጁ መሆኗን እንዳስረዱ የኢንፎርሜሽን ሚኒስትሩ የማነ ገ/መስቀል በይፋዊ ትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።
አምባሳደር ፌልማን በበኩላቸው በአፍሪካ ቀንድ እየታዩ ባሉ ችግሮች ዙሪያ የአሜሪካ አስተዳደር ያለውን አመለካከትና እይታ ለፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ እንዳብራሩላቸው የኤርትራው ኢንፎርሜሽን ሚኒስትር ገልፀዋል።
የነበረው ውይይት 4:00 ሰዓት ገደማ የወሰደ እንደነበረ የተሰማ ሲሆን ከላይ ከተገለፀው መረጃ ውጭ ሌሎች ዝርዝር መረጃዎች እስካሁን ይፋ አልሆኑም።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
'በኮንሶ ዞን ካራት ከተማ ሰዓት እላፊ ታወጀ'
ምክንያት ?
የካራት ከተማ አስተዳደር እንደሚለው ከዚህ ቀደም በተናጥል ሆነ በቡድን በመደራጀት የመንግሥትና የግለሰቦች ንብረት የመስረቅና የመቀማት ድርጊቶች የዕለት ተዕለት የሌቦች እና የዘራፊዎች ተግባር ሆኖ ቆይቷል።
የጸጥታ ኃይል ይህንን "አስጸያፊ መጤ ድርጊት" ለመመከት የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ከእነዚያ ሌቦች፣ ዘራፊዎችና ቀማኞችን በብዙ ጥረት በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ አድርጓል፣ በማድረግም ላይም ይገኛል ብሏል አስተዳደሩ።
ነገር ግን ይላል ከተማው አብዛኛዎቹ እየተሰወሩና በድብቅ እየተደራጁ ጨለማን ተገን በማድረግ በሰፈር ውስጥ እና በቀበሌያት እንዲሁም በመንግሥት መ/ቤቶች ላይ በከፍተኛ ደረጃ የስርቆት ድርጊቶችን ቀጥለዋል ፤ ይህንን መንግስት ደርሶባቸዋል ሲል አስረድቷል።
በተጨማሪም "6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማወክ እና ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ለማጠልሸት ሌት ተቀን እየሰሩ ያሉ ፀረሠላም ግለሰቦች እና ቡድኖች እንዳሉ መንግስት ደርሶባቸዋል፤ ክትትል እያደረገም ይገኛል" ብሏል።
በዚህ ምክንያት ነው በካራት ደረጃ መንግሥት ሁኔታውን በማጤን ለህብረተሰቡ ደህንነት ሲባል የሰዓት እላፊ ቁጥጥር ገደብ እንዲበጅለት የተወሰነው ብሏል።
የተጣሉ ክልከላዎችን ምንድናቸው ?
- ማንኛውም ግለሰብ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማለዳ 11፡00 ሰዓት መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- ማንኛውም ባለ 2 እና 3 እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማለዳ 12፡00 ሰዓት ማሽከርከር ተከልክለዋል።
- ማንኛውም ሆቴል፣ ምግብ ቤት፣ መጠጥ ቤት ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት መስጠት ተከልክሏል።
ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/Konsso-Zone-Government-05-06
@tikvahethiopia
ምክንያት ?
የካራት ከተማ አስተዳደር እንደሚለው ከዚህ ቀደም በተናጥል ሆነ በቡድን በመደራጀት የመንግሥትና የግለሰቦች ንብረት የመስረቅና የመቀማት ድርጊቶች የዕለት ተዕለት የሌቦች እና የዘራፊዎች ተግባር ሆኖ ቆይቷል።
የጸጥታ ኃይል ይህንን "አስጸያፊ መጤ ድርጊት" ለመመከት የተለያዩ ስልቶችን በመጠቀም ከእነዚያ ሌቦች፣ ዘራፊዎችና ቀማኞችን በብዙ ጥረት በህግ ቁጥጥር ሥር እንዲውሉ አድርጓል፣ በማድረግም ላይም ይገኛል ብሏል አስተዳደሩ።
ነገር ግን ይላል ከተማው አብዛኛዎቹ እየተሰወሩና በድብቅ እየተደራጁ ጨለማን ተገን በማድረግ በሰፈር ውስጥ እና በቀበሌያት እንዲሁም በመንግሥት መ/ቤቶች ላይ በከፍተኛ ደረጃ የስርቆት ድርጊቶችን ቀጥለዋል ፤ ይህንን መንግስት ደርሶባቸዋል ሲል አስረድቷል።
በተጨማሪም "6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማወክ እና ህብረ ብሔራዊ አንድነታችንን ለማጠልሸት ሌት ተቀን እየሰሩ ያሉ ፀረሠላም ግለሰቦች እና ቡድኖች እንዳሉ መንግስት ደርሶባቸዋል፤ ክትትል እያደረገም ይገኛል" ብሏል።
በዚህ ምክንያት ነው በካራት ደረጃ መንግሥት ሁኔታውን በማጤን ለህብረተሰቡ ደህንነት ሲባል የሰዓት እላፊ ቁጥጥር ገደብ እንዲበጅለት የተወሰነው ብሏል።
የተጣሉ ክልከላዎችን ምንድናቸው ?
- ማንኛውም ግለሰብ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማለዳ 11፡00 ሰዓት መንቀሳቀስ ተከልክሏል።
- ማንኛውም ባለ 2 እና 3 እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ማለዳ 12፡00 ሰዓት ማሽከርከር ተከልክለዋል።
- ማንኛውም ሆቴል፣ ምግብ ቤት፣ መጠጥ ቤት ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት በኋላ አገልግሎት መስጠት ተከልክሏል።
ተጨማሪ ያንብቡ : https://telegra.ph/Konsso-Zone-Government-05-06
@tikvahethiopia
*Update
የኮቪድ-19 ስርጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተባብሷል።
ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የሚከተሉት ሪፖርቶችን ተመልከቷቸው፦
- ትላንት ህንድ ውስጥ 414,433 ሰዎች በኮቪድ-19 ሲያዙ 3,920 ሰዎች ሞተዋል። ህንድ በየዕለቱ አስገንጋጭ ቁጥሮችን ሪፖርት ማድረጓን ቀጥላለች።
- ብራዚል ትላንት 72,559 ዜጎቿ ለበሽታው ተጋላጭ መሆናቸውን እና 2,531 ሰዎች ደግሞ መሞታቸውን ሪፖርት አድርጋለች።
- ትላንት ከፍተኛ ሞት የተመዘገበባቸው ሀገራት ስንመለከተ፦
• አሜሪካ 860
• ቱርክ 304
• ፖላንድ 510
• ኮሎምቢያ 399
• አርጀንቲና 398
• ሩሲያ 351 ይገኙበታል።
- የአፍሪካ አቀፍ ስርጭትም ተባብሷል፤ ትላንት 12,434 ሰዎች ቫይረሱ ሲያዙ 383 ሰዎች ሞተዋል። አሁንም ደቡብ አፍሪካ 1,590,370፣ሞሮኮ 513,016፣ቱኒዝያ 317,010፣ ኢትዮጵያ 260,802 ታማሚዎችን በሪፖርት በማድረቅ የቀዳሚዎችን ቦታ ይዘዋል።
ክትባት በሚመለከት አንድ ከዛሬ የቢቢሲ መረጃ፦
የሪስያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን "ስፑትኒክ" የተሰኘው ሩሲያ ሠራሹ የኮቪድ-19 ክትባት ልክ እንደ 'ክላሽንኮቭ' የጦር መሳሪካ አስተማማኝ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
ፑቲን ይህን ያሉት ከአገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ጋር በነበራቸው የቪዲዮ ኮንፍረንስ ነው።
ትናንት የአገሪቱ ጤና ተመራማሪዎች በአንድ ዙር ብቻ የሚሰጠውን እና 'ስፑትኒክ ላይት' የሚል መጠሪያ ስላገኘው ክትባት ውጤታማነት መግለጫ ሰጥተዋል።
ፕሬዝደንት ፑቲን ከክትባቱ ጋር ያነጻጸሩት "ክላሽንኮቭ" የተሰኘው መሳሪያ ጋር ሲሆን መሳሪያው ፤ ይህ መሳሪያ የተፈበረከው በሩሲያ ሲሆን በመላው ዓለም ዝነኛ የጦር መሳሪያ ሆኖ ቀጥሏል።
የመረጃ ግብዓት የዎርልድሜትሮ ድረገፅ፣ቢቢሲ፣CDC አፍሪካ ናቸው።
#Purpose
@tikvahethiopia
የኮቪድ-19 ስርጭት በዓለም አቀፍ ደረጃ ተባብሷል።
ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የሚከተሉት ሪፖርቶችን ተመልከቷቸው፦
- ትላንት ህንድ ውስጥ 414,433 ሰዎች በኮቪድ-19 ሲያዙ 3,920 ሰዎች ሞተዋል። ህንድ በየዕለቱ አስገንጋጭ ቁጥሮችን ሪፖርት ማድረጓን ቀጥላለች።
- ብራዚል ትላንት 72,559 ዜጎቿ ለበሽታው ተጋላጭ መሆናቸውን እና 2,531 ሰዎች ደግሞ መሞታቸውን ሪፖርት አድርጋለች።
- ትላንት ከፍተኛ ሞት የተመዘገበባቸው ሀገራት ስንመለከተ፦
• አሜሪካ 860
• ቱርክ 304
• ፖላንድ 510
• ኮሎምቢያ 399
• አርጀንቲና 398
• ሩሲያ 351 ይገኙበታል።
- የአፍሪካ አቀፍ ስርጭትም ተባብሷል፤ ትላንት 12,434 ሰዎች ቫይረሱ ሲያዙ 383 ሰዎች ሞተዋል። አሁንም ደቡብ አፍሪካ 1,590,370፣ሞሮኮ 513,016፣ቱኒዝያ 317,010፣ ኢትዮጵያ 260,802 ታማሚዎችን በሪፖርት በማድረቅ የቀዳሚዎችን ቦታ ይዘዋል።
ክትባት በሚመለከት አንድ ከዛሬ የቢቢሲ መረጃ፦
የሪስያው ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን "ስፑትኒክ" የተሰኘው ሩሲያ ሠራሹ የኮቪድ-19 ክትባት ልክ እንደ 'ክላሽንኮቭ' የጦር መሳሪካ አስተማማኝ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።
ፑቲን ይህን ያሉት ከአገሪቱ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ጋር በነበራቸው የቪዲዮ ኮንፍረንስ ነው።
ትናንት የአገሪቱ ጤና ተመራማሪዎች በአንድ ዙር ብቻ የሚሰጠውን እና 'ስፑትኒክ ላይት' የሚል መጠሪያ ስላገኘው ክትባት ውጤታማነት መግለጫ ሰጥተዋል።
ፕሬዝደንት ፑቲን ከክትባቱ ጋር ያነጻጸሩት "ክላሽንኮቭ" የተሰኘው መሳሪያ ጋር ሲሆን መሳሪያው ፤ ይህ መሳሪያ የተፈበረከው በሩሲያ ሲሆን በመላው ዓለም ዝነኛ የጦር መሳሪያ ሆኖ ቀጥሏል።
የመረጃ ግብዓት የዎርልድሜትሮ ድረገፅ፣ቢቢሲ፣CDC አፍሪካ ናቸው።
#Purpose
@tikvahethiopia
አጭር መረጃ ስለኮቪድ-19 ኢትዮጵያ መተግበሪያ፦
የኮቪድ ኢትዮጵያ መተግበሪያ በውስጡ ስለኮቪድ ቁጥጥር ፣ ህክምና እና መከላከል ማወቅ ያለብንን በ7 ኮርሶች የያዘ ሲሆን ስልጠናው ፦
- የኮቪድ-19 ቫይረስ ተገኝቶቦት በቤት ውስጥ እራሳችንን ለይተን ለራሳችን ማድርግ ስለሚገባን እንክብካቤ እና ወደ ሌሎች እንዳይተላለፍ ማድረግ ስለሚገባን ጥንቃቄ ያሳውቃል።
- ስለኮቪድ-19 ክትባት ለማወቅ እና ስልጠና ለመውሰድ ይጠቅማል።
- ቤተሰቦች፣ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አስተዳደር ሰራተኞች ማድረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ለማውቅ ይረዳል።
- ሰልጣኞች ስልጠና እንዳጠናቀቁ በሚመዘገቡበት የስልክ ቁጥር ባላቸው የቴሌግራም አድራሻ ስልጠናውን በአግባቡ ላጠናቀቁ እና የስልጠና መመዝኛውን ከ80 በመቶ በላይ ላስመዘግቡ በጤና ሚኒስቴር የተረጋገጠ የተከታታይ ሙያ ማጎልብቻ ነጥብ ያለው ሰርተፍኬት የሚላክላቸው ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በየ3 አመት ለሚደረገው የሙያ ፍቃድ እድሳት ነጥብ ለመጠቀም ያስችላል።
- መተግበሪያውን በተንቀሳቃሽ ስልክዎ ከጫኑና ስልጠናዎች ካወረዱ በኋላ ኢንተርኔት የማይፍልግ ሲሆን ስልጠናውን የሚስብ እና ለመረዳት ቀላል ለማድረግ ቪድዮዎች ተካተውብታል።
- ኮቪድ-19 ኢትዮጵያ ለሁሉም የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ለመስጠት የተዘጋጀ ሲሆን በፍጥነት እየጨመረ ያለውን የኮቪድ ስርጭት ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እንዲሁም የተሻለ እንክብካቤ ለመስጠት ይረዳል።
መተግበሪያውን ከየት ላግኘው ?
መተግበሪያውን በስልክዎ ለመጫንና ስልጠናውን ለመከታተል ይህን ሊንክ ይጫኑ - https://bit.ly/3apv5J2
#MoH #EPHI
@tikvagethiopia @tikvagethiopiaBOT
የኮቪድ ኢትዮጵያ መተግበሪያ በውስጡ ስለኮቪድ ቁጥጥር ፣ ህክምና እና መከላከል ማወቅ ያለብንን በ7 ኮርሶች የያዘ ሲሆን ስልጠናው ፦
- የኮቪድ-19 ቫይረስ ተገኝቶቦት በቤት ውስጥ እራሳችንን ለይተን ለራሳችን ማድርግ ስለሚገባን እንክብካቤ እና ወደ ሌሎች እንዳይተላለፍ ማድረግ ስለሚገባን ጥንቃቄ ያሳውቃል።
- ስለኮቪድ-19 ክትባት ለማወቅ እና ስልጠና ለመውሰድ ይጠቅማል።
- ቤተሰቦች፣ ተማሪዎች፣ መምህራን እና የትምህርት ቤት አስተዳደር ሰራተኞች ማድረግ ስላለባቸው ጥንቃቄዎች ለማውቅ ይረዳል።
- ሰልጣኞች ስልጠና እንዳጠናቀቁ በሚመዘገቡበት የስልክ ቁጥር ባላቸው የቴሌግራም አድራሻ ስልጠናውን በአግባቡ ላጠናቀቁ እና የስልጠና መመዝኛውን ከ80 በመቶ በላይ ላስመዘግቡ በጤና ሚኒስቴር የተረጋገጠ የተከታታይ ሙያ ማጎልብቻ ነጥብ ያለው ሰርተፍኬት የሚላክላቸው ሲሆን በአሁኑ ጊዜ በየ3 አመት ለሚደረገው የሙያ ፍቃድ እድሳት ነጥብ ለመጠቀም ያስችላል።
- መተግበሪያውን በተንቀሳቃሽ ስልክዎ ከጫኑና ስልጠናዎች ካወረዱ በኋላ ኢንተርኔት የማይፍልግ ሲሆን ስልጠናውን የሚስብ እና ለመረዳት ቀላል ለማድረግ ቪድዮዎች ተካተውብታል።
- ኮቪድ-19 ኢትዮጵያ ለሁሉም የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ለመስጠት የተዘጋጀ ሲሆን በፍጥነት እየጨመረ ያለውን የኮቪድ ስርጭት ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እንዲሁም የተሻለ እንክብካቤ ለመስጠት ይረዳል።
መተግበሪያውን ከየት ላግኘው ?
መተግበሪያውን በስልክዎ ለመጫንና ስልጠናውን ለመከታተል ይህን ሊንክ ይጫኑ - https://bit.ly/3apv5J2
#MoH #EPHI
@tikvagethiopia @tikvagethiopiaBOT
TIKVAH-ETHIOPIA
እንኳን አደረሳችሁ! TIKVAH-ETHIOPIA እንኳን ለሲዳማ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ ለማለት ይወዳል። በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታ፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እንመኛለን! ይህን ዓለምን ያስጨነቀ ወረርሽኝን አሸንፈን የዓለም ቅርስ የሆነውን 'ፊቼ ጨምባላላ በዓል' በአደባባይ ተሰባስበን የምናከብርበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን #ተስፋ እናደርጋለን!! በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ!…
እንኳን አደረሰን !
እንኳን ለሲዳማ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የደስታ ፣ የመተሳሰብ ይሆንልን ዘንድ ከወዲሁ እንመኛለን።
ካለፈው ዓመት ጀምሮ በዓሉ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት በአደባባይ እየተከበረ አይደለም።
የተሻለ ጊዜ መጥቶ ፣ ይህ አስከፊ ወረርሽኝ መፍትሄ አግኝቶ ሁሉም በደስታ እንደቀድሞ አደባባይ ተሰብስቦ የሚያከብርበት ጊዜ እንዲመጣ እንመኛለን።
በዓሉን በየቤታችሁ የምታከብሩ አባላት አስፈላጊውን የኮቪድ-19 ጥንቃቄ እየተገበራችሁ እንዲሆን አደራ እንላለን።
መልካም በዓል !
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እንኳን ለሲዳማ የፊቼ ጨምበላላ በዓል በሰላም አደረሰን ፤ አደረሳችሁ። በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅር ፣ የደስታ ፣ የመተሳሰብ ይሆንልን ዘንድ ከወዲሁ እንመኛለን።
ካለፈው ዓመት ጀምሮ በዓሉ በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት በአደባባይ እየተከበረ አይደለም።
የተሻለ ጊዜ መጥቶ ፣ ይህ አስከፊ ወረርሽኝ መፍትሄ አግኝቶ ሁሉም በደስታ እንደቀድሞ አደባባይ ተሰብስቦ የሚያከብርበት ጊዜ እንዲመጣ እንመኛለን።
በዓሉን በየቤታችሁ የምታከብሩ አባላት አስፈላጊውን የኮቪድ-19 ጥንቃቄ እየተገበራችሁ እንዲሆን አደራ እንላለን።
መልካም በዓል !
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ስለፊቼ ጨምባላላ ምን ያህል አውቃለሁ ?
- የሲዳማ ሕዝብ የጨረቃና ከዋክብትን አቀማመጥ በማጥናት አዲስ ዓመት ያከብራል። በዓሉም ፊቼ ጨምበላላ ይባላል።
- ፊቼ ጫምባላላ መከበር ከጀመረ ከ1800 ዓመታት በላይ ማስቆጠሩን የአገር ሽማግሌዎች ይናገራል።
- በዓሉ የሲዳማ ሕዝብ ማንነቱን ከተረዳበት ጊዜ አንስቶ ሲከበር ቆይቷል።
- ፊቼ ጨምበላላ በዓል የሚከበርበት ቋሚ ቀን የለውም። በአያንቱዎች ጥቆማ መሰረት በዓሉ የሚከበርበት ቀን ይቆረጣል።
- 'የፊቼ ጨምበላላ ዋነኛ ትርጉም ሰላም ነው'፤ አንድነትና ፍቅር የበዓሉ መለያ ነው።
- የተጣሉ ሰዎች በፊቼ ጨምበላላ በዓል ላይ ይታረቃሉ። ሃዘን ላይ የነበሩ ሰዎችም የሃዘን ልብሳቸውን ይቀይራሉ።
- ከቀዬው ርቆ የነበረ ሰው ለፊቼ ጨምበላላ ወደቀዬው ይመለሳል።
- ለዚህ በዓል ተብሎ እርድ አይፈጸምም፤ ስጋም አይበላም። ክብቶችን መምታትም ክልክል ነው። ላሞች ሳር የበዛበት መስክ ላይ ይሰማራሉ።
- በሲዳማ ሕዝብ ዘንድ በፊቼ ጨምበላላ በዓል ወቅት ማረስ ነውር ነው። ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮም ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው።
- ፊቼ የአዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ ሲሆን፤ ጨምበላላ ደግሞ የአዲስ ዓመት መጀመሪያው ቀን ነው።
- ሲዳማ ከአንድ ዓመት ወደሌላው የሚሸጋገርበት ሂደት ሁሉቃ ይባላል። ሁሉቃ ማለት ከሸምበቆና ከአርጥብ ቅጠል ተሠርቶ የሚቆም ነገር ነው። ሁሉቃ በቤተሰብና በማኅበረሰብ ደረጃ የሚሠራ ሲሆን፤ አዲስ ዓመት ሲገባ ሰዎችና ከብቶች ይተላለፉበታል።
- የሲዳማ ሕዝብ አዲስ ዓመትን ሲቀበሉ፤ ዓመቱ የብልጽግና እንዲሆንላቸው 'ፊቼ ጄጂ' ይላሉ።
ይህ መረጃ የቀረበው ከ2019 የቢቢሲ ድረገፅ ላያ ከወጣው ፅሁፍ ነው።
@tikvahethiopiaaBot @tikvahethiopia
- የሲዳማ ሕዝብ የጨረቃና ከዋክብትን አቀማመጥ በማጥናት አዲስ ዓመት ያከብራል። በዓሉም ፊቼ ጨምበላላ ይባላል።
- ፊቼ ጫምባላላ መከበር ከጀመረ ከ1800 ዓመታት በላይ ማስቆጠሩን የአገር ሽማግሌዎች ይናገራል።
- በዓሉ የሲዳማ ሕዝብ ማንነቱን ከተረዳበት ጊዜ አንስቶ ሲከበር ቆይቷል።
- ፊቼ ጨምበላላ በዓል የሚከበርበት ቋሚ ቀን የለውም። በአያንቱዎች ጥቆማ መሰረት በዓሉ የሚከበርበት ቀን ይቆረጣል።
- 'የፊቼ ጨምበላላ ዋነኛ ትርጉም ሰላም ነው'፤ አንድነትና ፍቅር የበዓሉ መለያ ነው።
- የተጣሉ ሰዎች በፊቼ ጨምበላላ በዓል ላይ ይታረቃሉ። ሃዘን ላይ የነበሩ ሰዎችም የሃዘን ልብሳቸውን ይቀይራሉ።
- ከቀዬው ርቆ የነበረ ሰው ለፊቼ ጨምበላላ ወደቀዬው ይመለሳል።
- ለዚህ በዓል ተብሎ እርድ አይፈጸምም፤ ስጋም አይበላም። ክብቶችን መምታትም ክልክል ነው። ላሞች ሳር የበዛበት መስክ ላይ ይሰማራሉ።
- በሲዳማ ሕዝብ ዘንድ በፊቼ ጨምበላላ በዓል ወቅት ማረስ ነውር ነው። ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የፊቼ ጨምበላላ በዓል የሲዳማ ሕዝብ ብቻ ሳይሆን የተፈጥሮም ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው።
- ፊቼ የአዲስ ዓመት በዓል ዋዜማ ሲሆን፤ ጨምበላላ ደግሞ የአዲስ ዓመት መጀመሪያው ቀን ነው።
- ሲዳማ ከአንድ ዓመት ወደሌላው የሚሸጋገርበት ሂደት ሁሉቃ ይባላል። ሁሉቃ ማለት ከሸምበቆና ከአርጥብ ቅጠል ተሠርቶ የሚቆም ነገር ነው። ሁሉቃ በቤተሰብና በማኅበረሰብ ደረጃ የሚሠራ ሲሆን፤ አዲስ ዓመት ሲገባ ሰዎችና ከብቶች ይተላለፉበታል።
- የሲዳማ ሕዝብ አዲስ ዓመትን ሲቀበሉ፤ ዓመቱ የብልጽግና እንዲሆንላቸው 'ፊቼ ጄጂ' ይላሉ።
ይህ መረጃ የቀረበው ከ2019 የቢቢሲ ድረገፅ ላያ ከወጣው ፅሁፍ ነው።
@tikvahethiopiaaBot @tikvahethiopia
ችሎት !
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በእነ ስብሃት ነጋ መዝገብ የቅድመ ምርመራ የምስክሮች አሰማም ሂደት፤ በዝግ ችሎት እና የምስክሮች ስምና አድራሻቸው ሳይጠቀስ እንዲካሄድ ዛሬ አርብ ውሳኔ አስተላለፈ።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ዐቃቤ ህግ “ለምስክሮች ጥበቃ አድርጊያለሁ” ማለቱን ተከትሎ በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበውን መቃወሚያ ከመረመረ በኋላ ነው።
በዐቃቤ ህግ በኩል የተነሳው የምስክሮች ጥበቃ ህገ-መንግስታዊ መሆኑን የገለጸው ፍርድ ቤቱ፤ ከቀረቡለት ሶስት የምስክር አሰማም ሂደቶች ሁለቱን መቀበሉን በውሳኔው አመልክቷል።
ተቀባይነት ካገኙት የምስክር አሰማም ሂደቶች የመጀመሪያው ማንኛውም ሚዲያ እና ታዳሚ ሳይገባ በዝግ ችሎት የቅድመ ምርመራ ምስክሮች የሚሰሙበት ነው።
የምስክሮች ስም እና አድራሻ ለተጠርጣሪዎች ሳይጠቀስ የምስክሮች ቃል የሚሰማበት ሁለተኛው አካሄድም እንዲሁ በፍርድ ቤቱ ተቀባይነት አግኝቷል።
ፍርድ ቤቱ ውድቅ ያደረገው የምስክር አሰማም ሂደት፤ ምስክሮች በአካል ሳይታዩ ከመጋረጃ ጀርባ ሆነው እንዲመሰክሩ በሚል በዐቃቤ ህግ የቀረበውን ነው።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በእነ ስብሃት ነጋ መዝገብ የቅድመ ምርመራ የምስክሮች አሰማም ሂደት፤ በዝግ ችሎት እና የምስክሮች ስምና አድራሻቸው ሳይጠቀስ እንዲካሄድ ዛሬ አርብ ውሳኔ አስተላለፈ።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ዐቃቤ ህግ “ለምስክሮች ጥበቃ አድርጊያለሁ” ማለቱን ተከትሎ በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበውን መቃወሚያ ከመረመረ በኋላ ነው።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በእነ ስብሃት ነጋ መዝገብ የቅድመ ምርመራ የምስክሮች አሰማም ሂደት፤ በዝግ ችሎት እና የምስክሮች ስምና አድራሻቸው ሳይጠቀስ እንዲካሄድ ዛሬ አርብ ውሳኔ አስተላለፈ።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ዐቃቤ ህግ “ለምስክሮች ጥበቃ አድርጊያለሁ” ማለቱን ተከትሎ በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበውን መቃወሚያ ከመረመረ በኋላ ነው።
በዐቃቤ ህግ በኩል የተነሳው የምስክሮች ጥበቃ ህገ-መንግስታዊ መሆኑን የገለጸው ፍርድ ቤቱ፤ ከቀረቡለት ሶስት የምስክር አሰማም ሂደቶች ሁለቱን መቀበሉን በውሳኔው አመልክቷል።
ተቀባይነት ካገኙት የምስክር አሰማም ሂደቶች የመጀመሪያው ማንኛውም ሚዲያ እና ታዳሚ ሳይገባ በዝግ ችሎት የቅድመ ምርመራ ምስክሮች የሚሰሙበት ነው።
የምስክሮች ስም እና አድራሻ ለተጠርጣሪዎች ሳይጠቀስ የምስክሮች ቃል የሚሰማበት ሁለተኛው አካሄድም እንዲሁ በፍርድ ቤቱ ተቀባይነት አግኝቷል።
ፍርድ ቤቱ ውድቅ ያደረገው የምስክር አሰማም ሂደት፤ ምስክሮች በአካል ሳይታዩ ከመጋረጃ ጀርባ ሆነው እንዲመሰክሩ በሚል በዐቃቤ ህግ የቀረበውን ነው።
የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ የጊዜ ቀጠሮ ችሎት፤ በእነ ስብሃት ነጋ መዝገብ የቅድመ ምርመራ የምስክሮች አሰማም ሂደት፤ በዝግ ችሎት እና የምስክሮች ስምና አድራሻቸው ሳይጠቀስ እንዲካሄድ ዛሬ አርብ ውሳኔ አስተላለፈ።
ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን ያስተላለፈው ዐቃቤ ህግ “ለምስክሮች ጥበቃ አድርጊያለሁ” ማለቱን ተከትሎ በተከሳሽ ጠበቆች የቀረበውን መቃወሚያ ከመረመረ በኋላ ነው።
ምንጭ፦ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በህገወጥ መንገድ ሲዘዋወር ነበር የተባለ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር ተያዘ !
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር አረኩት ባለው ክትትል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መያዙን አስታውቋል።
ፖሊስ ገንዘቡን ከነተጠርጣሪዎቹ ነው በቁጥጥር ስር መዋሉን ያሳወቀው።
መቼ እና የት ?
በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረው ዶላር የተያዘው ሚያዚያ 28 ለ29 አጥቢያ 2013 ዓ/ም የካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ "ላምበረት" ተብሎ በሚጠራው መናኸሪያ ግቢ ውስጥ በግምት ከለሊቱ 10 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ገደማ ነው፡፡
ገንዘቡ እንዴት ሊገኝ ቻለ ?
የአ/አ ፖሊስ እንዳለው ገንዘቡ የተገኘው ከህዝብ በተገኘ ጥቆማ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በቅንጅት በተደረገው ክትትል ነው።
110 ሺህ ዶላሩ ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ሊጓዙ የተዘጋጁ 2 ተጠርጣሪዎች በያዙት ሻንጣ ላይ በተደረገ ፍተሻ በጥቁር ላስቲክ ተጠቅልሎ ነው የተገኘው።
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
@tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና በብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር አረኩት ባለው ክትትል በህገ ወጥ መንገድ ሲዘዋወር የነበረ 110 ሺህ የአሜሪካ ዶላር መያዙን አስታውቋል።
ፖሊስ ገንዘቡን ከነተጠርጣሪዎቹ ነው በቁጥጥር ስር መዋሉን ያሳወቀው።
መቼ እና የት ?
በህገ ወጥ መንገድ ሲጓጓዝ የነበረው ዶላር የተያዘው ሚያዚያ 28 ለ29 አጥቢያ 2013 ዓ/ም የካ ክፍለ ከተማ በተለምዶ "ላምበረት" ተብሎ በሚጠራው መናኸሪያ ግቢ ውስጥ በግምት ከለሊቱ 10 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ገደማ ነው፡፡
ገንዘቡ እንዴት ሊገኝ ቻለ ?
የአ/አ ፖሊስ እንዳለው ገንዘቡ የተገኘው ከህዝብ በተገኘ ጥቆማ የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በቅንጅት በተደረገው ክትትል ነው።
110 ሺህ ዶላሩ ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ሊጓዙ የተዘጋጁ 2 ተጠርጣሪዎች በያዙት ሻንጣ ላይ በተደረገ ፍተሻ በጥቁር ላስቲክ ተጠቅልሎ ነው የተገኘው።
ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው እንደሚገኝ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
@tikvahethiopia
የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቅባቸዋል በተባሉ ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች እስከ ግንቦት 06 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ !
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ዋና ተግባር የሆነው የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ አስታውሷል።
በአሁኑ ወቅት በጊዜያዊነት በተሰበሰበው መረጃ (ያለፉት 3 ቀናትን ሳይጨምር) 28,731,935 ያህል መራጮች የተመዘገቡ መሆኑን ገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ በ41,798 ያህል ምርጫ ጣቢያዎች እየተከናወነ ይገኛልም ብሏል።
የመራጮች ምዝገባ ከተያዘለት የጊዜ ገደብ በተጨማሪ ለ15 ቀን ተጨምሮ ከአፋርና ከሶማሌ ክልሎች ውጪ የማጠናቀቂያ ጊዜው በዛሬ ሚያዝያ 29 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሆን ማሳወቁ አስታውሷል።
በዚህ ወቅት ፦
1. የመራጮች ምዝገባ በተራዘመበት ወቅት ተደራራቢ የበአላት ቀናት መኖራቸው እና በዚያም የተነሳ በህጉ መሰረት ብሔራዊ በአላት ዝግ በመሆናቸው የመራጮች ምዝገባ ሊከናወን አለመቻሉን
2. የመራጮች ምዝገባ በተራዘመበት ወቅት 1500 መራጮች የመዘገቡ ጣቢያዎቸን ለይቶ ንኡስ ጣቢያዎችን የማደራጀት ሂደት ጊዜ መውሰዱን በዚህም ምክንያት ከፍተኛ የመራጮች መጨናነቅ ምርጫ ጣቢያ ላይ መፈጠሩን
ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የመራጮች ካርድ በመውሰድ መምረጥ የሚችሉ ቀላል የማይባሉ ዜጎች በዚህ የተነሳ የመራጮች ካርድ አለመውሰዳቸውን ቦርዱ ተገንዝቢያለሁ ብሏል።
ቦርዱ ባደረገው ስብሰባ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቅባቸው በነበሩ፦
- አዲስ አበባ ከተማ
- ድሬዳዋ ከተማ
- አማራ
- ቤኒሻንጉል ጉሙዝ
- ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል
- ጋምቤላ
- ሃረሪ
- ኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች የመራጮች ምዝገባ እስከ አርብ ግንቦት 6/2013 ድረስ ለተጨማሪ 7 ቀናት እንዲከናወን ወስኗል።
@tikvahethiopia
ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ዋና ተግባር የሆነው የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ አስታውሷል።
በአሁኑ ወቅት በጊዜያዊነት በተሰበሰበው መረጃ (ያለፉት 3 ቀናትን ሳይጨምር) 28,731,935 ያህል መራጮች የተመዘገቡ መሆኑን ገልጿል።
የመራጮች ምዝገባ በ41,798 ያህል ምርጫ ጣቢያዎች እየተከናወነ ይገኛልም ብሏል።
የመራጮች ምዝገባ ከተያዘለት የጊዜ ገደብ በተጨማሪ ለ15 ቀን ተጨምሮ ከአፋርና ከሶማሌ ክልሎች ውጪ የማጠናቀቂያ ጊዜው በዛሬ ሚያዝያ 29 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሆን ማሳወቁ አስታውሷል።
በዚህ ወቅት ፦
1. የመራጮች ምዝገባ በተራዘመበት ወቅት ተደራራቢ የበአላት ቀናት መኖራቸው እና በዚያም የተነሳ በህጉ መሰረት ብሔራዊ በአላት ዝግ በመሆናቸው የመራጮች ምዝገባ ሊከናወን አለመቻሉን
2. የመራጮች ምዝገባ በተራዘመበት ወቅት 1500 መራጮች የመዘገቡ ጣቢያዎቸን ለይቶ ንኡስ ጣቢያዎችን የማደራጀት ሂደት ጊዜ መውሰዱን በዚህም ምክንያት ከፍተኛ የመራጮች መጨናነቅ ምርጫ ጣቢያ ላይ መፈጠሩን
ይህንን ከግምት ውስጥ በማስገባት የመራጮች ካርድ በመውሰድ መምረጥ የሚችሉ ቀላል የማይባሉ ዜጎች በዚህ የተነሳ የመራጮች ካርድ አለመውሰዳቸውን ቦርዱ ተገንዝቢያለሁ ብሏል።
ቦርዱ ባደረገው ስብሰባ የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቅባቸው በነበሩ፦
- አዲስ አበባ ከተማ
- ድሬዳዋ ከተማ
- አማራ
- ቤኒሻንጉል ጉሙዝ
- ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ክልል
- ጋምቤላ
- ሃረሪ
- ኦሮሚያና ሲዳማ ክልሎች የመራጮች ምዝገባ እስከ አርብ ግንቦት 6/2013 ድረስ ለተጨማሪ 7 ቀናት እንዲከናወን ወስኗል።
@tikvahethiopia