ኢትዮጵያ ዜጎቿን ከሳዑዲ አረቢያ ማስወጣቷን ቀጥላለች።
ኢትዮጵያ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በችግር ላይ የወደቁ ዜጎችን በተከታታይ እያስወጣች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ እያደረገች እንደሆነ ይታወቃል።
በዛሬው ዕለት 292 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረብያ ጂዳ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ሳዑዲ አረቢያ ውስጥ በችግር ላይ የወደቁ ዜጎችን በተከታታይ እያስወጣች ወደሀገራቸው እንዲመለሱ እያደረገች እንደሆነ ይታወቃል።
በዛሬው ዕለት 292 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ አረብያ ጂዳ ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
“የትግራይ ጉዳይ ያሳስበናል” - IMF
By : https://am.al-ain.com/ (አል ዓይን)
በትግራይ ያጋጠመውን ሰብአዊ ቀውስ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በትኩረት እየተከታተለው መሆኑን የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጅዮርጅየቫ ተናገሩ፡፡
ዳይሬክተርዋ ከToday News Africa’s የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዘጋቢ ሳይሞን አቴባ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ እንዳሉት ከሆነ፤ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የተከሰተው ቀውስ ከሰብኣዊ እርዳታ በተጨማሪ የኢኮኖሚ ምላሽ የሚያስፈልገው ነው ብለዋል፡፡
“የትግራይ ጉዳይ ያሳስበናል” ያለው ሁኔታ በቅርበት እየተከታተልነው ነው ፤ በእንደዚህ አይነት ሰብአዊ ቀውስ ዜጎች ያልተገባ ዋጋ ሊከፍሉ አይገባም ሲሉ ተናገረዋል የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጅዮርጅየቫ፡፡
ክሪስታሊና ጅዮርጅየቫ አሁን በሀገሪቱ ያለው አጠቃላይ የኢኮኖሚ ሁኔታና የሚፈጥረው ተፅእኖ ድርጅታቸው IMF በትኩረት እየተከታተለው መሆኑ በመናገር፤ ሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጫናውን ተቋቁማ መቀጠል እንድትችል አስፈላጊውን ምክረ ሀሳብ ለመስጠት ድርጅታቸው ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ማኔጂንግ ዳይሬክተርዋ የኢትዮጵያ ጥሩ መሆን ለተቀረው አህጉረ አፍሪካ ወሳኝ ነው ብለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
By : https://am.al-ain.com/ (አል ዓይን)
በትግራይ ያጋጠመውን ሰብአዊ ቀውስ የዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) በትኩረት እየተከታተለው መሆኑን የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጅዮርጅየቫ ተናገሩ፡፡
ዳይሬክተርዋ ከToday News Africa’s የአለም አቀፍ ጉዳዮች ዘጋቢ ሳይሞን አቴባ ጋር በነበራቸው ቃለ ምልልስ እንዳሉት ከሆነ፤ በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የተከሰተው ቀውስ ከሰብኣዊ እርዳታ በተጨማሪ የኢኮኖሚ ምላሽ የሚያስፈልገው ነው ብለዋል፡፡
“የትግራይ ጉዳይ ያሳስበናል” ያለው ሁኔታ በቅርበት እየተከታተልነው ነው ፤ በእንደዚህ አይነት ሰብአዊ ቀውስ ዜጎች ያልተገባ ዋጋ ሊከፍሉ አይገባም ሲሉ ተናገረዋል የአለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ማኔጂንግ ዳይሬክተር ክሪስታሊና ጅዮርጅየቫ፡፡
ክሪስታሊና ጅዮርጅየቫ አሁን በሀገሪቱ ያለው አጠቃላይ የኢኮኖሚ ሁኔታና የሚፈጥረው ተፅእኖ ድርጅታቸው IMF በትኩረት እየተከታተለው መሆኑ በመናገር፤ ሀገሪቱ የኢኮኖሚ ጫናውን ተቋቁማ መቀጠል እንድትችል አስፈላጊውን ምክረ ሀሳብ ለመስጠት ድርጅታቸው ዝግጁ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡
ማኔጂንግ ዳይሬክተርዋ የኢትዮጵያ ጥሩ መሆን ለተቀረው አህጉረ አፍሪካ ወሳኝ ነው ብለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ወንድ ህፃናትን የደፈሩ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ ፦
#አርባ_ምንጭ :
በ10 ዓመት ህጻን ላይ የግብረ-ሰዶም ወንጀል የፈጸመ ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አሳወቀ፡፡
ተከሳሽ አቶ ተመኘሁ ጣሰው የተባለ በከተማው የድልፋና ቀበሌ ነዋሪ የሆነ የ39 ዓመት ግለሰብ በቀበሌው ነዋሪ የሆነውን የ10 ዓመት ህጻን ላይ የግብረ - ሰዶም ወንጀል መፈጸሙን ፍርድ ቤቱ በሰነድና በሰው ማስረጃ አረጋግጧል።
ወንጀሉን ለየት የሚያደርገው በአከባቢው ያልተለመደ እና የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ በማስፈራራት ተከሳሽ ወንጀሉን እየፈጸመ መቆየቱና በመጨረሻ በአርባ ምንጭ ከተማ ሼቻ ቀበሌ "ገሮ መኝታ ቤት" ወንጀሉን እየፈጸመ እያለ በአከባቢው ህብረተሰብ ጥቆማ ሊያዝ መቻሉ ነው።
በወንጀል ህግ ቁጥር 631 ንዑስ 1 ሀ መሠረት በአቃቤ ህግ ክስ ቀርቦ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ወንጀሉን ስለመፈጸሙ የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማጣራት በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።
#ማዕከላዊ_ጎንደር ፡
በአማራ ክልል በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዐቃቤ ሕግ መምርያ የግብረ ሰዶም ወንጀል የፈፀመውን ግለሰብ በእስራት ቀጥቷል።
ተከሳሽ አቶ የምስራች ዓባይ ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቀኑ 5:00 ላይ ታች አርማጭሆ ወረዳ ሙሴ ባንብ ቀበሌ የ8 ዓመት ሕፃን ወንድ ልጅ አስገድዶ ደፍሯል፡፡
የሙሴ ባንብ ንዑስ ወረዳ ፍርድ ቤት የተከሳሽን የወንጀል ድርጊት በሰው እና በሕክምና ማስረጃ ማረጋገጥ ችሏል፡፡
ተከሳሽ የወንጀል ሕግ ቁ631/1/ለ/ ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡
መልዕክት ፦
ወላጆችና አሳዳጊዎች ህጻናት ለወንጀል ተጋላጭ እና ራሳቸውን ለመከላከል ስለማይችሉ የጥቃት ሰለባዎች እንዳይሆኑ የልጆቻቸሁን አዋዋል ልትከታተሉና ልትቆጣጠሩ ይገባል።
በህጻናት ላይ የተለየና አጣራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥም ለሚመለከተው አካል ጥቆማ ስጡ።
[ይህ መረጃ የተሰባጠረው ከአርባ ምንጭ ኮሚኒኬሽን ፣ የአርባ ምርጭ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት አቶ አለማየሁ አልታዬ እና ከአዲስ ዘይቤ /Addis Zeybe/ ደረገፅ ነው]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#አርባ_ምንጭ :
በ10 ዓመት ህጻን ላይ የግብረ-ሰዶም ወንጀል የፈጸመ ግለሰብ በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የአርባ ምንጭ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አሳወቀ፡፡
ተከሳሽ አቶ ተመኘሁ ጣሰው የተባለ በከተማው የድልፋና ቀበሌ ነዋሪ የሆነ የ39 ዓመት ግለሰብ በቀበሌው ነዋሪ የሆነውን የ10 ዓመት ህጻን ላይ የግብረ - ሰዶም ወንጀል መፈጸሙን ፍርድ ቤቱ በሰነድና በሰው ማስረጃ አረጋግጧል።
ወንጀሉን ለየት የሚያደርገው በአከባቢው ያልተለመደ እና የግል ተበዳይን በተደጋጋሚ በማስፈራራት ተከሳሽ ወንጀሉን እየፈጸመ መቆየቱና በመጨረሻ በአርባ ምንጭ ከተማ ሼቻ ቀበሌ "ገሮ መኝታ ቤት" ወንጀሉን እየፈጸመ እያለ በአከባቢው ህብረተሰብ ጥቆማ ሊያዝ መቻሉ ነው።
በወንጀል ህግ ቁጥር 631 ንዑስ 1 ሀ መሠረት በአቃቤ ህግ ክስ ቀርቦ ፍርድ ቤቱ ተከሳሽ ወንጀሉን ስለመፈጸሙ የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማጣራት በ18 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ ተወስኗል።
#ማዕከላዊ_ጎንደር ፡
በአማራ ክልል በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዐቃቤ ሕግ መምርያ የግብረ ሰዶም ወንጀል የፈፀመውን ግለሰብ በእስራት ቀጥቷል።
ተከሳሽ አቶ የምስራች ዓባይ ጥር 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ከቀኑ 5:00 ላይ ታች አርማጭሆ ወረዳ ሙሴ ባንብ ቀበሌ የ8 ዓመት ሕፃን ወንድ ልጅ አስገድዶ ደፍሯል፡፡
የሙሴ ባንብ ንዑስ ወረዳ ፍርድ ቤት የተከሳሽን የወንጀል ድርጊት በሰው እና በሕክምና ማስረጃ ማረጋገጥ ችሏል፡፡
ተከሳሽ የወንጀል ሕግ ቁ631/1/ለ/ ላይ የተደነገገውን በመተላለፉ በ10 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኗል፡፡
መልዕክት ፦
ወላጆችና አሳዳጊዎች ህጻናት ለወንጀል ተጋላጭ እና ራሳቸውን ለመከላከል ስለማይችሉ የጥቃት ሰለባዎች እንዳይሆኑ የልጆቻቸሁን አዋዋል ልትከታተሉና ልትቆጣጠሩ ይገባል።
በህጻናት ላይ የተለየና አጣራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥም ለሚመለከተው አካል ጥቆማ ስጡ።
[ይህ መረጃ የተሰባጠረው ከአርባ ምንጭ ኮሚኒኬሽን ፣ የአርባ ምርጭ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ፕሬዜዳንት አቶ አለማየሁ አልታዬ እና ከአዲስ ዘይቤ /Addis Zeybe/ ደረገፅ ነው]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ሃዋሳ ገብተዋል።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ሀዋሳ ከተማ የገቡ ሲሆን በሲዳማ ክልል አመራሮች እና በሲዳማ አባቶች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በሚመረቀው የይርጋለም ከተማ አግሮ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ምረቃ ስነ ስርኣት ላይ ይገኛሉ፥ ፓርኩንም ያስመርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ ሌሎች የፌዴራል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችም ሀዋሳ ገብተዋል።
PHOTO : Sidama Media Network & Dr. Abiy Ahmed
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ሀዋሳ ከተማ የገቡ ሲሆን በሲዳማ ክልል አመራሮች እና በሲዳማ አባቶች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ነገ በሚመረቀው የይርጋለም ከተማ አግሮ ኢንዱስትሪያል ፓርክ ምረቃ ስነ ስርኣት ላይ ይገኛሉ፥ ፓርኩንም ያስመርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ከጠቅላይ ሚኒስትሩ በተጨማሪ ሌሎች የፌዴራል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችም ሀዋሳ ገብተዋል።
PHOTO : Sidama Media Network & Dr. Abiy Ahmed
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Attention😷
በ24 ሰዓታት ውስጥ የ27 ሰዎች ህይወት አለፈ።
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 6,985 የላብራቶሪ ምርመራ 1,361 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ በተመሳሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 27 ሰዎች ሞተዋል።
ትላንት 355 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 172,571 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 2,510 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 141,195 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 454 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose #Tikvah
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በ24 ሰዓታት ውስጥ የ27 ሰዎች ህይወት አለፈ።
በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ከተደረገው 6,985 የላብራቶሪ ምርመራ 1,361 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ በተመሳሳይ በ24 ሰዓታት ውስጥ 27 ሰዎች ሞተዋል።
ትላንት 355 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
በአጠቃላይ 172,571 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ሲረጋገጥ ከእነዚህ መካከል 2,510 ሰዎች ህይወታቸው አልፏል፤ 141,195 ሰዎች አገግመዋል።
በአሁን ሰዓት 454 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።
#Purpose #Tikvah
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የኢትዮጵያ እና የሱዳን ድንበር ውጥረት ጦሱ ሱዳን ውስጥ ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እየተረፈ ነው!
By : Almneh Mekonnen(ዶቼ ቨለ)
ሱዳን ገዳሪፍ ግዛት ውስጥ ሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሱዳን ታጣቂዎች እንደሚዘርፏቸው፣ እንደሚደበድቧቸው፣ ከመኖሪያቸው አካባቢ እያባረሯቸውን እንደሆነ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያኑ እየተደበደቡ፣እየተዘረፉ፣ እየተባረሩ ያሉት የድንበር ውዝግቡ ከተባባሰ በኃላ መሆኑን ገልፀዋል።
እንደ ምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር መረጃ ባለፉት ወራት ከሱዳን በታጣቂዎች የተባረሩ 230 ኢትዮጵያውያን ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ተገደዋል።
አሁንም ሱዳን ውስጥ የሚኖሩን ኢትዮጵያውያን ችግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
ከሱዳን ከተባረሩት ኢትዮጵያውያን መካከል አንዳንዶቹ እስከ 30 ዓመት ሱዳን ውስጥ የኖሩ ናቸው።
ተባረው ወደ ኢትዮጵያ ከገቡት መካከል አንዳዶቹ የሱዳን ታጣቂዎች ማንነት/ዘርን መሰረት አድረግው የአማራ ተወላጆችን ተከታትለው ያጠቀሉ ሲሉ ከሰዋል።
ሱዳን ውስጥ ከዚህ ቀደም ዘር እና ሃይማኖትን ሳንለይ አብረን እንኖር ነበር አሁን ላይ ግን ሱዳን መሬት ላይ የአማራ ተወላጅ ሆኖ መኖር ፈተና ሆኗል ሲሉ ያለውን ሁኔታ አስረድተዋል።
መተማ ዮሐንስ አካባቢ የሰፈሩት ተባራሪዎች የመጠለያ እና የመሰረታዊ አገልግሎት ችግር እንዳለባቸው እያሳወቁ ነው።
የምዕራብ ጎንደር ዞን በበኩሉ ከሱዳን ለመጡት ዜጎች የተወሰነ ድጋፍ ቢደረግም የተደራጀ ባለመሆኑ የተሟላ አይደለም፤ ነገር ግን ትኩረት እንዲደረግ ከበላይ አመራር ጋር እየሰራን ነው ብለዋል።
እንደ ዞኑ አስተዳደር ፥ በድንበር አካባቢ ባለው ችግር በየዕለቱ ከሱዳን ከ8 እስከ 10 ሰዎች ወደሀገር እየገቡ ነው፤ በሀገር ውስጥም በድንበር አካባቢ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተዘርፈዋል፣ ንብረታቸው ወድሟል ተገናቅለዋል።
@tikvahethiopia
By : Almneh Mekonnen(ዶቼ ቨለ)
ሱዳን ገዳሪፍ ግዛት ውስጥ ሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሱዳን ታጣቂዎች እንደሚዘርፏቸው፣ እንደሚደበድቧቸው፣ ከመኖሪያቸው አካባቢ እያባረሯቸውን እንደሆነ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያውያኑ እየተደበደቡ፣እየተዘረፉ፣ እየተባረሩ ያሉት የድንበር ውዝግቡ ከተባባሰ በኃላ መሆኑን ገልፀዋል።
እንደ ምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር መረጃ ባለፉት ወራት ከሱዳን በታጣቂዎች የተባረሩ 230 ኢትዮጵያውያን ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት ተገደዋል።
አሁንም ሱዳን ውስጥ የሚኖሩን ኢትዮጵያውያን ችግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
ከሱዳን ከተባረሩት ኢትዮጵያውያን መካከል አንዳንዶቹ እስከ 30 ዓመት ሱዳን ውስጥ የኖሩ ናቸው።
ተባረው ወደ ኢትዮጵያ ከገቡት መካከል አንዳዶቹ የሱዳን ታጣቂዎች ማንነት/ዘርን መሰረት አድረግው የአማራ ተወላጆችን ተከታትለው ያጠቀሉ ሲሉ ከሰዋል።
ሱዳን ውስጥ ከዚህ ቀደም ዘር እና ሃይማኖትን ሳንለይ አብረን እንኖር ነበር አሁን ላይ ግን ሱዳን መሬት ላይ የአማራ ተወላጅ ሆኖ መኖር ፈተና ሆኗል ሲሉ ያለውን ሁኔታ አስረድተዋል።
መተማ ዮሐንስ አካባቢ የሰፈሩት ተባራሪዎች የመጠለያ እና የመሰረታዊ አገልግሎት ችግር እንዳለባቸው እያሳወቁ ነው።
የምዕራብ ጎንደር ዞን በበኩሉ ከሱዳን ለመጡት ዜጎች የተወሰነ ድጋፍ ቢደረግም የተደራጀ ባለመሆኑ የተሟላ አይደለም፤ ነገር ግን ትኩረት እንዲደረግ ከበላይ አመራር ጋር እየሰራን ነው ብለዋል።
እንደ ዞኑ አስተዳደር ፥ በድንበር አካባቢ ባለው ችግር በየዕለቱ ከሱዳን ከ8 እስከ 10 ሰዎች ወደሀገር እየገቡ ነው፤ በሀገር ውስጥም በድንበር አካባቢ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ተዘርፈዋል፣ ንብረታቸው ወድሟል ተገናቅለዋል።
@tikvahethiopia
አሜሪካ ስለህዳሴው ግድብ ፦
ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን የታላቁ የኅዳሴ ግድብን (GERD) በተመለከተ ያላቸውን አለመግባባት በትብብር እና ገንቢ በሆነ ጥረት እንዲፈቱ አሜሪካ ድጋፍ መስጠቷን እንደምትቀጥል ማስታወቋን #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።
ሦስቱ ሃገሮች ውጤታማ ወደሆነ ውይይት እንዲመለሱ እናበረታታለን ሲል የዋይት ሃውስ የብሄራዊ ጸጥታ ምክር ቤት ቃል አቀባይ ቢሮ አስታውቋል።
ውዝግቡ ገንቢ መፍትሄ እንዲያገኝ እና በክልሉ ያለው ውጥረት እንዲረግብ ለመርዳት በምንሰጠው ድጋፍ ከግድቡ ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ሚዛናዊ በሆነ መንገድ መያዛቸውን በማረጋገጥ መስራታችንን እንቀጥላለን ብሏል መግለጫው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ ፣ ግብጽ እና ሱዳን የታላቁ የኅዳሴ ግድብን (GERD) በተመለከተ ያላቸውን አለመግባባት በትብብር እና ገንቢ በሆነ ጥረት እንዲፈቱ አሜሪካ ድጋፍ መስጠቷን እንደምትቀጥል ማስታወቋን #ቪኦኤ በድረገፁ አስነብቧል።
ሦስቱ ሃገሮች ውጤታማ ወደሆነ ውይይት እንዲመለሱ እናበረታታለን ሲል የዋይት ሃውስ የብሄራዊ ጸጥታ ምክር ቤት ቃል አቀባይ ቢሮ አስታውቋል።
ውዝግቡ ገንቢ መፍትሄ እንዲያገኝ እና በክልሉ ያለው ውጥረት እንዲረግብ ለመርዳት በምንሰጠው ድጋፍ ከግድቡ ጋር የተገናኙ ጉዳዮች ሚዛናዊ በሆነ መንገድ መያዛቸውን በማረጋገጥ መስራታችንን እንቀጥላለን ብሏል መግለጫው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ በአየርላንድ የሚገኙትን አምባሳደሯን ጠራች !
By : Selam Mulgeta
የኢትዮጵያ መንግስት በአየርላንድ የሚገኙትን አምባሳደር እሸቱ ደሴን ወደ ሃገር ቤት መጥራቱን ከዲኘሎማቲክ ምንጮች ለማወቅ ተችሏል።
ኢትዮጵያ አምባሳደሯን የጠራችው ለምክክር እንደሆነ ነው የተገልፀው።
አየርላንድ ተመድ እና የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ግንባር ቀደሙን እንቅስቃሴ እያደረገች እንደሆነ ይነገርላታል።
አየርላንድ በጀመረችውን ተግባር የምትቀጥል ከሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ኤምባሲውን ሙሉ ለሙሉ እስከመዝጋት የሚደርስ ውሳኔን ሊያሳልፍ ይችላል ተብሏል።
አየርላድ የሁለቱን ሃገራት ነባር ወዳጅነት በማይመጥን እንቅስቃሴ ውሰጥ ናት ያሉት ዲኘሎማቲክ ምንጮች ወቅታዊ ተግባሯ በወደፊቱ የሃገራቱ ግንኙነት ላይም ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ብለዋል።
* አየርላንድ ከሰሞኑን የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በትግራይ ክልል ጉዳይ እንዲመክር ጥሪ እንዳቀረበች መነገሩ በኃላም ስብሰባው ያለምንም ስምምነት መበተኑ አይዘነጋም።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
By : Selam Mulgeta
የኢትዮጵያ መንግስት በአየርላንድ የሚገኙትን አምባሳደር እሸቱ ደሴን ወደ ሃገር ቤት መጥራቱን ከዲኘሎማቲክ ምንጮች ለማወቅ ተችሏል።
ኢትዮጵያ አምባሳደሯን የጠራችው ለምክክር እንደሆነ ነው የተገልፀው።
አየርላንድ ተመድ እና የአውሮፓ ህብረት በኢትዮጵያ ላይ ማዕቀብ እንዲጥሉ ግንባር ቀደሙን እንቅስቃሴ እያደረገች እንደሆነ ይነገርላታል።
አየርላንድ በጀመረችውን ተግባር የምትቀጥል ከሆነ የኢትዮጵያ መንግስት ኤምባሲውን ሙሉ ለሙሉ እስከመዝጋት የሚደርስ ውሳኔን ሊያሳልፍ ይችላል ተብሏል።
አየርላድ የሁለቱን ሃገራት ነባር ወዳጅነት በማይመጥን እንቅስቃሴ ውሰጥ ናት ያሉት ዲኘሎማቲክ ምንጮች ወቅታዊ ተግባሯ በወደፊቱ የሃገራቱ ግንኙነት ላይም ቀላል የማይባል አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል ብለዋል።
* አየርላንድ ከሰሞኑን የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት በትግራይ ክልል ጉዳይ እንዲመክር ጥሪ እንዳቀረበች መነገሩ በኃላም ስብሰባው ያለምንም ስምምነት መበተኑ አይዘነጋም።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#NewsAlert
አቶ አገኘሁ የመጀመሪያውን የኮቪድ-19 ክትባት ወሰዱ!
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት ወሰዱ፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ ክትባቱን የወሰዱት ዛሬ በክልሉ በተጀመረው የኮሮና ቫይረስ ክትባት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ነው፡፡
ም/ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ፋንታ ማንደፍሮን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም ክትባቱን ወስደዋል፡፡ (AMMA)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
አቶ አገኘሁ የመጀመሪያውን የኮቪድ-19 ክትባት ወሰዱ!
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አገኘሁ ተሻገር የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት ወሰዱ፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ ክትባቱን የወሰዱት ዛሬ በክልሉ በተጀመረው የኮሮና ቫይረስ ክትባት ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ነው፡፡
ም/ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ፋንታ ማንደፍሮን ጨምሮ ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችም ክትባቱን ወስደዋል፡፡ (AMMA)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#WHO #DrTedrosAdhanom
የአስትራዜኔካ ክትባት የደም መርጋትን ስለማስከተሉ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ ባለመኖሩ በዚህ ስጋት አገሮች ክትባቱን ከመስጠት መቆጠብ የለባቸውም ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
በትንሹ 5 የአውሮፓ ሀገራት አይስላንድ፣ ቡልጋሪያ፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ክትባቱን መስጠት አቁመዋል ፤ ይህ የሆነ አንዲት የዳኒሽ ሴት ከደም መርጋት ጋር በተገናኘ እንደሞተች ከተነገረ በኃላ ነው።
ይህንን በተመለከተ የዓለም ጤና ድርጅት በክትባቱ እና በደም መርጋት መካከል ምንም አይነት ግንኙነት የለም ብሏል።
እስካሁን ወደ 5 ሚሊዮን የሚጠጉ አውሮፓውያን የአስትራዜኔካ ክትባትን ወስደዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም በበኩላቸው ፥ እስካሁን በመላው ዓለም 335 ሚሊዮን በላይ የኮቪድ-19 ክትባት መሰራጨቱን የገለፁ ሲሆን እስካሁን ከክትባቱ ጋር በተገናኘ ምንም ሞት አለመመዝገቡን አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የአስትራዜኔካ ክትባት የደም መርጋትን ስለማስከተሉ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ ባለመኖሩ በዚህ ስጋት አገሮች ክትባቱን ከመስጠት መቆጠብ የለባቸውም ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
በትንሹ 5 የአውሮፓ ሀገራት አይስላንድ፣ ቡልጋሪያ፣ ዴንማርክ እና ኖርዌይ ክትባቱን መስጠት አቁመዋል ፤ ይህ የሆነ አንዲት የዳኒሽ ሴት ከደም መርጋት ጋር በተገናኘ እንደሞተች ከተነገረ በኃላ ነው።
ይህንን በተመለከተ የዓለም ጤና ድርጅት በክትባቱ እና በደም መርጋት መካከል ምንም አይነት ግንኙነት የለም ብሏል።
እስካሁን ወደ 5 ሚሊዮን የሚጠጉ አውሮፓውያን የአስትራዜኔካ ክትባትን ወስደዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ ኣድሃኖም በበኩላቸው ፥ እስካሁን በመላው ዓለም 335 ሚሊዮን በላይ የኮቪድ-19 ክትባት መሰራጨቱን የገለፁ ሲሆን እስካሁን ከክትባቱ ጋር በተገናኘ ምንም ሞት አለመመዝገቡን አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የኮቪድ-19 ክትባት በአማራ ክልል፦
- ባህርዳር ከተማ ፈለገህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ክትባት መሰጠት ተጀምሯል፡፡
- የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ ፣ የጤና ቢሮ ሀላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ እና ሌሎች አመራሮች እና የጤና ባለሙያዎች ክትባቱን ወስደዋል፡፡
- በሀገር አቀፍ በተሰጠው ኮታ መሰረት 108 ሺህ ዶዝ ክትባት ለአማራ ክልል ተሰጥቷል።
- በአማራ ክልል 251 ሺህ 597 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተመረምረው 7 ሺህ 392 ቫይረሱ ሲገኝባቸው 6 ሺህ 826 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡ 140 ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል። (ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopia
- ባህርዳር ከተማ ፈለገህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ክትባት መሰጠት ተጀምሯል፡፡
- የአማራ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ አገኘሁ ተሻገር ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳደር ዶክተር ፋንታ ማንደፍሮ ፣ የጤና ቢሮ ሀላፊ ዶክተር መልካሙ አብቴ እና ሌሎች አመራሮች እና የጤና ባለሙያዎች ክትባቱን ወስደዋል፡፡
- በሀገር አቀፍ በተሰጠው ኮታ መሰረት 108 ሺህ ዶዝ ክትባት ለአማራ ክልል ተሰጥቷል።
- በአማራ ክልል 251 ሺህ 597 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተመረምረው 7 ሺህ 392 ቫይረሱ ሲገኝባቸው 6 ሺህ 826 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል፡፡ 140 ሰዎች በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል። (ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopia
የኮቪድ-19 ክትባት በአዲስ አበባ ፦
- በአ/አ የኮቪድ-19 ክትባት መሰጠት ተጀምሯል።
- በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 እፎይታ ጤና ጣቢያ ነው የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር የተጀመረው።
- ክትባቱን በይፋ ያስጀመሩት ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ናቸው።
- የኮቪድ -19 ክትባት በቅድሚያ ለጤና ባለሙያዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል፤ ሌላው ህብረተሰብ ክትባቱ እስኪደርሰው ድርስ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
- እንደ አዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ ፥ የኮቪድ-19 ክትባት በዛሬው ዕለት በከተማዋ በሁሉም ጤና ተቋማት ለሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች ፣ በእድሜና ለበሽታው ተጋላጭ ጤና ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሠብ ክፍሎች ይሰጣል።
- በአ/አ የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ላይ የኮቪድ -19 ወረርሽኝን ከገባ ጀምሮ በሽታውን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ግንባር ቀደም ለሆኑ የጤና ባለሙያዎች ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
Via Addis Ababa Press secretary
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
- በአ/አ የኮቪድ-19 ክትባት መሰጠት ተጀምሯል።
- በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 እፎይታ ጤና ጣቢያ ነው የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር የተጀመረው።
- ክትባቱን በይፋ ያስጀመሩት ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ ናቸው።
- የኮቪድ -19 ክትባት በቅድሚያ ለጤና ባለሙያዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል፤ ሌላው ህብረተሰብ ክትባቱ እስኪደርሰው ድርስ አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል።
- እንደ አዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሃንስ ጫላ ፥ የኮቪድ-19 ክትባት በዛሬው ዕለት በከተማዋ በሁሉም ጤና ተቋማት ለሚገኙ የህክምና ባለሙያዎች ፣ በእድሜና ለበሽታው ተጋላጭ ጤና ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ የህብረተሠብ ክፍሎች ይሰጣል።
- በአ/አ የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር ማስጀመሪያ ላይ የኮቪድ -19 ወረርሽኝን ከገባ ጀምሮ በሽታውን ፊት ለፊት በመጋፈጥ ግንባር ቀደም ለሆኑ የጤና ባለሙያዎች ምስጋና ቀርቦላቸዋል።
Via Addis Ababa Press secretary
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ዶ/ር ዮሀንስ ጫላ የኮቪድ-19 ክትባት ወሰዱ።
By : EPA
የአ/አ ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ዛሬ በአ/አ በተጀመረው የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር ክትባቱን ወስደዋል።
ዶክተር ዮሀንስ ፥ በክትባቱ ዙርያ የሚናፈሱት አሉባልታዎች ሁሉ ከእውነታ የራቁ ናቸው ብለዋል። ለዚህም ምስክርና ማሳያ ይሆን ዘንድ ራሳቸው የመጀመሪያውን ክትባት ወስደዋል።
ክትባቱ በሁለት ዙር የሚሰጥ ሲሆን ሁለተኛው ዙር ክትባት የመጀሪያዉ ክትባት በተሰጠ ከ 8-12 ሳምንት ድረስ እንደሚሰጥ ነው ዶክተር ዮሀንስ ያስታወቁት።
ክትባቱ ቅድሚያ ለጤና ባለሞያዎች ይሰጣል ፤ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸውንና እድሜያቸው የገፉ ሰዎች ደግሞ ከጤና ባለሞያዎች ቀጥሎ ክትባቱ እነደሚሰጣቸው ተገልጿል።
@tikvahethiopia
By : EPA
የአ/አ ከተማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሀንስ ጫላ ዛሬ በአ/አ በተጀመረው የኮቪድ-19 ክትባት መርሃ ግብር ክትባቱን ወስደዋል።
ዶክተር ዮሀንስ ፥ በክትባቱ ዙርያ የሚናፈሱት አሉባልታዎች ሁሉ ከእውነታ የራቁ ናቸው ብለዋል። ለዚህም ምስክርና ማሳያ ይሆን ዘንድ ራሳቸው የመጀመሪያውን ክትባት ወስደዋል።
ክትባቱ በሁለት ዙር የሚሰጥ ሲሆን ሁለተኛው ዙር ክትባት የመጀሪያዉ ክትባት በተሰጠ ከ 8-12 ሳምንት ድረስ እንደሚሰጥ ነው ዶክተር ዮሀንስ ያስታወቁት።
ክትባቱ ቅድሚያ ለጤና ባለሞያዎች ይሰጣል ፤ ተጓዳኝ ህመም ያለባቸውንና እድሜያቸው የገፉ ሰዎች ደግሞ ከጤና ባለሞያዎች ቀጥሎ ክትባቱ እነደሚሰጣቸው ተገልጿል።
@tikvahethiopia
የኮቪድ-19 ክትባት በትግራይ ፦
የኮቪድ-19 ክትባት በአገር አቀፍ ደረጃ በመቐለ መሰጠት ተጀምሯል።
መርሐ ግብሩን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በመቐለ አጠቃላይ ሆስፒታል አስጀምረውታል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋና የአስተዳደሩ ካቢኔ አባላት ተከትበዋል።
ክትባቱ ለጤና ባለሙያዎች እና ለቫይረሱ ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ ወገኖች ቅድሚያ እንደሚሰጥ ተገልጿል። - ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
የኮቪድ-19 ክትባት በአገር አቀፍ ደረጃ በመቐለ መሰጠት ተጀምሯል።
መርሐ ግብሩን የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በመቐለ አጠቃላይ ሆስፒታል አስጀምረውታል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ሙሉ ነጋና የአስተዳደሩ ካቢኔ አባላት ተከትበዋል።
ክትባቱ ለጤና ባለሙያዎች እና ለቫይረሱ ይበልጥ ተጋላጭ ለሆኑ ወገኖች ቅድሚያ እንደሚሰጥ ተገልጿል። - ENA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#NewsAlert
የአማራ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ለመቀየር የቀረበውን አዋጅ አፀደቀ።
በቀጣይ 6 ወራት በጥናት ላይ ተመስርቶ የአማራ ህዝብን ታሪክና ስነ ልቦና የሚያንፀባርቅ ሰንደቅ ዓላማ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እንዲውልም ምክር ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል ነው የተባለው።
ነባሩ ሰንደቅ ዓላማ አንድን ፓርቲ የሚወክል እንጂ የአማራ ህዝብን ስነ ልቦና የማያንፀባርቅ በመሆኑ በህዝቡ ተቀባይነት ማጣቱም በምክር ቤቱ ተገልጿል። (AMMA)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የአማራ ክልል ምክር ቤት የክልሉን ሰንደቅ ዓላማ ለመቀየር የቀረበውን አዋጅ አፀደቀ።
በቀጣይ 6 ወራት በጥናት ላይ ተመስርቶ የአማራ ህዝብን ታሪክና ስነ ልቦና የሚያንፀባርቅ ሰንደቅ ዓላማ ተዘጋጅቶ ጥቅም ላይ እንዲውልም ምክር ቤቱ ውሳኔ አስተላልፏል ነው የተባለው።
ነባሩ ሰንደቅ ዓላማ አንድን ፓርቲ የሚወክል እንጂ የአማራ ህዝብን ስነ ልቦና የማያንፀባርቅ በመሆኑ በህዝቡ ተቀባይነት ማጣቱም በምክር ቤቱ ተገልጿል። (AMMA)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኮቪድ-19 ክትባት የወሰዱት የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ መሪ ፦
ፖል ካጋሜ የኮቪድ-19 ክትባት የወሰዱ የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ መሪ ሆነዋል።
የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ እና ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ጃኔት ክትባቱን ሲወስዱ የሚያሳይ ፎቶግራፍም በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ይፋዊ ትዊተር ገጽ ላይ ተለቋል።
ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ የኮሮና ክትባት የወሰዱ የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ መሪ ሆነዋል፡፡
እስካሁንም በሩዋንዳ ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች የኮቪድ 19 ክትባን መውሰዳቸው ተገልጿል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ፖል ካጋሜ የኮቪድ-19 ክትባት የወሰዱ የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ መሪ ሆነዋል።
የሩዋንዳው ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ እና ባለቤታቸው ቀዳማዊት እመቤት ጃኔት ክትባቱን ሲወስዱ የሚያሳይ ፎቶግራፍም በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ይፋዊ ትዊተር ገጽ ላይ ተለቋል።
ፕሬዚዳንት ፖል ካጋሜ የኮሮና ክትባት የወሰዱ የመጀመሪያው የምስራቅ አፍሪካ መሪ ሆነዋል፡፡
እስካሁንም በሩዋንዳ ከ200 ሺህ በላይ ሰዎች የኮቪድ 19 ክትባን መውሰዳቸው ተገልጿል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia