TIKVAH-ETHIOPIA
#SecurityAlert www.tikvahethiopia.net በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በኩጅ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት የፀጥታ እና የደህንነት ችግር መኖሩን እያሳወቁን ይገኛሉ። ታጣቂዎች በሰውና በንብረት ላይ ጥቃት እያደረሱ እንደሆነም ገልፀውልናል። ጉዳዩ የሚመለከተው አካል አስቸኳይ መፍትሄ እንዲፈልግም አባላቶቻችን ጥሪ አቅርበዋል። በየአካባቢው ያሉ የፀጥታ…
#Metekel
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል "መተከል ዞን" ቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ በተፈፀመው ጥቃት የሰዎች ህይወት ማለፉ ፣ ሰዎች መቁሰላቸውን ፣ ንብረት መውደሙን የቲክቫህ አባላት በፎቶ አስደግፈው አሳውቀዋል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን የምንለዋወጥ ይሆናል።
በ www.tikvahethiopia.net ላይ በየአካባቢያቹ ያለውን ማንኛውም የፀጥታና የደህንነት ስጋት ማሳወቅ ትችላላችሁ።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል "መተከል ዞን" ቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ በተፈፀመው ጥቃት የሰዎች ህይወት ማለፉ ፣ ሰዎች መቁሰላቸውን ፣ ንብረት መውደሙን የቲክቫህ አባላት በፎቶ አስደግፈው አሳውቀዋል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን የምንለዋወጥ ይሆናል።
በ www.tikvahethiopia.net ላይ በየአካባቢያቹ ያለውን ማንኛውም የፀጥታና የደህንነት ስጋት ማሳወቅ ትችላላችሁ።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#KulubiGabriel
የም/ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ሰኞ በሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ንግሥ በዓል ላይ የሚገኙ ምእመናንን ደህንነት ለመጠበቅ እና በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል።
በበዓሉ የሚታደሙ ምእመናን የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል (ማስክ) ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ከድሬዳዋ አስተዳደር ፣ ከሐረሪ ክልል ፣ ከፌዴራል ፖሊስ እና ከመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም ከሚሊሺያ እና የመረጃ ደህንነት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተደርጎ የሰላም ማስከበሩን ሥራ በቅንጅት ለመሥራት ዝግጅት መደረጉም ተነግሯል።
በሜታ ወረዳ ሰላማ ቀበሌ ፖሊስ ዘረፋ እና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ዝግጅት መደረጉን ፖሊስ አሳውቋል።
የፀጥታ አካላት ከወዲሁ ወደ ስፍራው ተልከዋል።
በዘንድሮ በዓል የጥበቃ ሥራው ከምሥራቅ ሸዋ ሞጆ ከተማ ፣ ጅግጅጋ እና ድሬዳዋ ጀምሮ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያዎች ፣ ዐቃቤ ሕግ እና ጊዜያዊ ፍርድ ቤት ተቋቁሟል። (ENA)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የም/ሐረርጌ ዞን ፖሊስ ሰኞ በሚከበረው የቁልቢ ገብርኤል ንግሥ በዓል ላይ የሚገኙ ምእመናንን ደህንነት ለመጠበቅ እና በዓሉ በሰላም እንዲጠናቀቅ ለማድረግ ዝግጅት መደረጉን አስታውቋል።
በበዓሉ የሚታደሙ ምእመናን የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ጭንብል (ማስክ) ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።
ከድሬዳዋ አስተዳደር ፣ ከሐረሪ ክልል ፣ ከፌዴራል ፖሊስ እና ከመከላከያ ሠራዊት እንዲሁም ከሚሊሺያ እና የመረጃ ደህንነት ኃላፊዎች ጋር ውይይት ተደርጎ የሰላም ማስከበሩን ሥራ በቅንጅት ለመሥራት ዝግጅት መደረጉም ተነግሯል።
በሜታ ወረዳ ሰላማ ቀበሌ ፖሊስ ዘረፋ እና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ዝግጅት መደረጉን ፖሊስ አሳውቋል።
የፀጥታ አካላት ከወዲሁ ወደ ስፍራው ተልከዋል።
በዘንድሮ በዓል የጥበቃ ሥራው ከምሥራቅ ሸዋ ሞጆ ከተማ ፣ ጅግጅጋ እና ድሬዳዋ ጀምሮ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን በዓሉ በሚከበርበት ስፍራ ጊዜያዊ ፖሊስ ጣቢያዎች ፣ ዐቃቤ ሕግ እና ጊዜያዊ ፍርድ ቤት ተቋቁሟል። (ENA)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ATTENTION
#ቁልቢ_ገብርኤል_ንግስ_በዓል
የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከነገ ታኅሣሥ 15/2013 ጀምሮ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ድረስ ባለው ዋናው መንገድ ላይ ከባድ ተሽከርካሪዎች አቁሞ መሄድ እና መተላለፍ አይቻልም ተብሏል።
መልዕክት ለምእመናን ፦
ማንኛውም ዓይነት ወንጀል ሲፈጸም እንዲሁም ወድቆ የተገኘ ንብረትና ገንዘብ ሲገኝ ቁልቢ ገብርኤል ገዳም ለሚገኘው ጊዜያዊ የፖሊስ ጣቢያ በስልክ ቁጥር 0253390335 ደውለው ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብር እንድታደርጉ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ቁልቢ_ገብርኤል_ንግስ_በዓል
የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር ከነገ ታኅሣሥ 15/2013 ጀምሮ ከጨለንቆ ከተማ እስከ ቀርሳ ከተማ ድረስ ባለው ዋናው መንገድ ላይ ከባድ ተሽከርካሪዎች አቁሞ መሄድ እና መተላለፍ አይቻልም ተብሏል።
መልዕክት ለምእመናን ፦
ማንኛውም ዓይነት ወንጀል ሲፈጸም እንዲሁም ወድቆ የተገኘ ንብረትና ገንዘብ ሲገኝ ቁልቢ ገብርኤል ገዳም ለሚገኘው ጊዜያዊ የፖሊስ ጣቢያ በስልክ ቁጥር 0253390335 ደውለው ጥቆማ በመስጠት የተለመደ ትብብር እንድታደርጉ ከወዲሁ መልዕክት ተላልፏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ኢብራሂም ሀጂ አሊ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ጋዜጠኛ ፣ አርቲስት እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ዕድገት ውስጥ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱት ኢብራሂም ሀጂ አሊ ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ኤፍ ቢ ሲ አሳወቀ። ኢብራሂም ሀጂ አሊ ካለፈው ክረምት ጀምሮ ባጋጠማቸው የጤና እክል ሳቢያ የህክምና ክትትል ሲደረግላቸው ቆይተው ትናንት ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። የቀብር ስነስርዓታቸው ዛሬ 9 ሰዓት ላይ…
የኢብራሂም ሃጂ አሊ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ።
የጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ዕድገት ውስጥ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱት ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርአተ ቀብር ተፈፅሟል፡፡
ስርዓተ ቀብራቸው ቤተሰቦቻቸው ፣ ባልደረቦቻቸው ፣ የሙያ አጋሮቻቸው እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት ነው በኮልፌ የሙስሊም መቃብር መፈፀሙን ኤፍ ቢ ሲ የገለፀው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የጋዜጠኛ፣ አርቲስት እና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋ ዕድገት ውስጥ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከቱት ኢብራሂም ሀጂ አሊ ስርአተ ቀብር ተፈፅሟል፡፡
ስርዓተ ቀብራቸው ቤተሰቦቻቸው ፣ ባልደረቦቻቸው ፣ የሙያ አጋሮቻቸው እና አድናቂዎቻቸው በተገኙበት ነው በኮልፌ የሙስሊም መቃብር መፈፀሙን ኤፍ ቢ ሲ የገለፀው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#ETHIOPIA #SUDAN
ሱደን አሁን ላይ በድንበር ስላለው ሁኔታ ውይይት እንዲደረግ ትናንት ከኢትዮጵያ በኩል የቀረበውን ጥያቄ ሱዳን መቀበል እንዳልፈለገች የሱዳን ሚዲያዎች እንደዘገቡ አል ዓይን በድረገፁ አስነብቧል።
ሱዳን አሁን ከድንበር ማካለል ጉዳይ ውጭ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ ባለፉት ቀናት በተፈጠረው ጉዳይ ላይ መወያየት እንደማትፈልግ ገልጻለች ነው የተባለው፡፡
More : https://telegra.ph/AlAin-12-23
@tikvahethiopiaBOt @tikvahethiopia
ሱደን አሁን ላይ በድንበር ስላለው ሁኔታ ውይይት እንዲደረግ ትናንት ከኢትዮጵያ በኩል የቀረበውን ጥያቄ ሱዳን መቀበል እንዳልፈለገች የሱዳን ሚዲያዎች እንደዘገቡ አል ዓይን በድረገፁ አስነብቧል።
ሱዳን አሁን ከድንበር ማካለል ጉዳይ ውጭ በሁለቱ ሀገራት ድንበር ላይ ባለፉት ቀናት በተፈጠረው ጉዳይ ላይ መወያየት እንደማትፈልግ ገልጻለች ነው የተባለው፡፡
More : https://telegra.ph/AlAin-12-23
@tikvahethiopiaBOt @tikvahethiopia
#የኢትዮጵያ_ማሳሰቢያ
በካርቱም ሲካሄድ የነበረው 2ተኛው የኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳዮች ከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት መጠናቀቁን ፋና ዘግቧል።
ሁለቱም ወገኖች በጋራ የድንበር አካባቢ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።
ከጥቅምት መጨረሻ ጀምሮ "በጋራ ድንበር" አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለውጦችና እንቅስቃሴዎች የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ መሆናቸው ተነስቷል፡፡
ከዚህ ባለፍ መሬት ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጥ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆሙ እና ወደቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ ኢትዮጵያ አሳስባለች፡፡
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በካርቱም ሲካሄድ የነበረው 2ተኛው የኢትዮ ሱዳን የድንበር ጉዳዮች ከፍተኛ ደረጃ የፖለቲካ ውይይት መጠናቀቁን ፋና ዘግቧል።
ሁለቱም ወገኖች በጋራ የድንበር አካባቢ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሃሳብ ተለዋውጠዋል።
ከጥቅምት መጨረሻ ጀምሮ "በጋራ ድንበር" አካባቢ በሱዳን በኩል የተደረጉ አዳዲስ ለውጦችና እንቅስቃሴዎች የቀደሙ ስምምነቶችን የሚጥሱ መሆናቸው ተነስቷል፡፡
ከዚህ ባለፍ መሬት ላይ ያለውን እውነታ የሚለውጥ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆሙ እና ወደቀደመ ቦታቸው እንዲመለሱ ኢትዮጵያ አሳስባለች፡፡
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#TikvahFamilyBulenWoreda
ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ከትላንት ሌሊት ጀምሮ እስከ ጠዋት በዘለቀው ጥቃት ከ 96 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ አባላት ገልጸዋል።
እስካሁን ድረስ በግልጽ ስለተፈጸመውም ጥቃት ይህ ነው የሚባል መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት የተሰማ ነገር የለም።
የምን ያህል ሰው ህይወት እንዳለፈም በውል ማረጋገጥ አልቻልንም።
ጉዳቱ ግን "እጅግ በጣም ከባድ" እንደሆነ በበኩጂ ቀበሌ የተፈጸመውን ድርጊት ተመልክተው የፎቶ ማስረጃም የላኩ ቤተሰቦቻችን ገልጸዋል።
በቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልም ከ20 በላይ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች እርዳታ እየተደረገላቸው ነው ብለዋል።
www.tikvahethiopia.net
@tikvahethiopia @tikvahethmagazine
ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ከትላንት ሌሊት ጀምሮ እስከ ጠዋት በዘለቀው ጥቃት ከ 96 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ አባላት ገልጸዋል።
እስካሁን ድረስ በግልጽ ስለተፈጸመውም ጥቃት ይህ ነው የሚባል መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት የተሰማ ነገር የለም።
የምን ያህል ሰው ህይወት እንዳለፈም በውል ማረጋገጥ አልቻልንም።
ጉዳቱ ግን "እጅግ በጣም ከባድ" እንደሆነ በበኩጂ ቀበሌ የተፈጸመውን ድርጊት ተመልክተው የፎቶ ማስረጃም የላኩ ቤተሰቦቻችን ገልጸዋል።
በቡለን የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታልም ከ20 በላይ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች እርዳታ እየተደረገላቸው ነው ብለዋል።
www.tikvahethiopia.net
@tikvahethiopia @tikvahethmagazine
#GondarUniversity
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ ታኅሳስ 14 ቀን 2013 ባደረገው ስብሰባ ለዶ/ር በላይ ተሰማን እና ዶ/ር ውዱ ተመስገንን የሙሉ ኘሮፌሰርነት ማዕረግ እንዲሰጣቸው ወስኗል።
ዩኒቨርሲቲው ኘሮፌሰር በላይ ተሰማ እና ኘሮፌሰር ውዱ ተመስገን ለዚህ ስኬት በመብቃታቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስራ አመራር ቦርድ ታኅሳስ 14 ቀን 2013 ባደረገው ስብሰባ ለዶ/ር በላይ ተሰማን እና ዶ/ር ውዱ ተመስገንን የሙሉ ኘሮፌሰርነት ማዕረግ እንዲሰጣቸው ወስኗል።
ዩኒቨርሲቲው ኘሮፌሰር በላይ ተሰማ እና ኘሮፌሰር ውዱ ተመስገን ለዚህ ስኬት በመብቃታቸው የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
TIKVAH-ETHIOPIA
#TikvahFamilyBulenWoreda ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ቡለን ወረዳ ከትላንት ሌሊት ጀምሮ እስከ ጠዋት በዘለቀው ጥቃት ከ 96 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ የቲክቫህ አባላት ገልጸዋል። እስካሁን ድረስ በግልጽ ስለተፈጸመውም ጥቃት ይህ ነው የሚባል መረጃ ከሚመለከታቸው አካላት የተሰማ ነገር የለም። የምን ያህል ሰው ህይወት እንዳለፈም በውል…
#UPDATE
በመተከል ዞን የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ቃል አቀባይ ኮ/ል አያሌው በየነ ዛሬ በቡለን ወረዳ ንጹሃን መገደላቸውን እንዳረጋገጡ አል ዓይን በድረገፁ አስነብቧል።
ቃል አቀባዩ የሟቾቹ ቁጥር ከ100 ሊበልጥም ሊያንስም ይችላል ብለዋል፡፡
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ በቡለን ወረዳ ኩጂ ቀበሌ በንፁሃን ላይ አሳዛኝ ጥቃት መፈፀሙን አሳውቋል።
ምን ያህል ንፁሃን እንደተገደሉ አልገለፀም።
የክልሉ መንግስት በጥቃቱ በሰዎች እና ንብረት ላይ ጎዳት መድረሱንም ገልጿል።
መከላከያ ሰራዊት ፣ እና የክልሉ ፀጥታ አካላት በጥቃት አድራሾቹ ላይ እርምጃ እየወሰዱና አካባቢውን እያረጋጉ ነው ብሏል።
በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አሁንም በ www.tikvahethiopia.net ላይ የደህንነት እና የፀጥታ ስጋት እንዳለባቸው እያሳወቁን ይገኛሉ።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በመተከል ዞን የተቋቋመው ኮማንድ ፖስት ቃል አቀባይ ኮ/ል አያሌው በየነ ዛሬ በቡለን ወረዳ ንጹሃን መገደላቸውን እንዳረጋገጡ አል ዓይን በድረገፁ አስነብቧል።
ቃል አቀባዩ የሟቾቹ ቁጥር ከ100 ሊበልጥም ሊያንስም ይችላል ብለዋል፡፡
የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ማምሻውን ባወጣው መግለጫ በቡለን ወረዳ ኩጂ ቀበሌ በንፁሃን ላይ አሳዛኝ ጥቃት መፈፀሙን አሳውቋል።
ምን ያህል ንፁሃን እንደተገደሉ አልገለፀም።
የክልሉ መንግስት በጥቃቱ በሰዎች እና ንብረት ላይ ጎዳት መድረሱንም ገልጿል።
መከላከያ ሰራዊት ፣ እና የክልሉ ፀጥታ አካላት በጥቃት አድራሾቹ ላይ እርምጃ እየወሰዱና አካባቢውን እያረጋጉ ነው ብሏል።
በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ቲክቫህ ኢትዮጵያ አባላት አሁንም በ www.tikvahethiopia.net ላይ የደህንነት እና የፀጥታ ስጋት እንዳለባቸው እያሳወቁን ይገኛሉ።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#COVID19Ethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 5,096
• በበሽታው የተያዙ - 351
• ህይወታቸው ያለፈ - 6
• ከበሽታው ያገገሙ - 1,006
አጠቃላይ 120,989 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,870 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 105,824 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
253 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 5,096
• በበሽታው የተያዙ - 351
• ህይወታቸው ያለፈ - 6
• ከበሽታው ያገገሙ - 1,006
አጠቃላይ 120,989 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,870 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 105,824 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
253 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Metekel
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን "የጸጥታ ችግር" ጋር በተያያዘ እጃቸው እንዳለበት የተረጋገጠ ከፍተኛና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋል እንደጀመሩ የክልሉ መንግስት ዛሬ ምሽት ገልጿል።
እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ፦
• አቶ ቶማስ ኩዊ ፡- የኢፌዴሪ ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ
• አቶ አድጎ አምሳያ፡- የቀድሞው የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር
• አቶ ሽፈራው ጨሊቦ፡-የቀድሞ የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር
• አቶ ባንዲንግ ማራ፡- የመተከል ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
• አረጋ ባልቢድ፡- የመተከል ዞን የቀድሞ አመራር የነበሩ
#BenishangulGumuz #MetekelZone
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን "የጸጥታ ችግር" ጋር በተያያዘ እጃቸው እንዳለበት የተረጋገጠ ከፍተኛና በየደረጃው ያሉ አመራሮች በቁጥጥር ስር መዋል እንደጀመሩ የክልሉ መንግስት ዛሬ ምሽት ገልጿል።
እስካሁን ድረስ በቁጥጥር ስር የዋሉ ፦
• አቶ ቶማስ ኩዊ ፡- የኢፌዴሪ ሠራተኛ እና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የማኅበራዊ ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ
• አቶ አድጎ አምሳያ፡- የቀድሞው የክልሉ ምክትል ርዕሰ-መስተዳድር
• አቶ ሽፈራው ጨሊቦ፡-የቀድሞ የክልሉ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ ዳይሬክተር
• አቶ ባንዲንግ ማራ፡- የመተከል ዞን ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ
• አረጋ ባልቢድ፡- የመተከል ዞን የቀድሞ አመራር የነበሩ
#BenishangulGumuz #MetekelZone
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#Eritrea
ጎረቤታችን ኤርትራ ትላንት የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ሞት አስተናግዳለች።
ሟቹ የ50 ዓመት እድሜ ያለው ወንድ #ደቀምሓረ ሆስፒተል ውስጥ የኮቪድ-19 ህክምና ሲደረግለት የነበረ ነው።
የዛሬ ሪፖርትን ጨምሮ በአጠቃላይ በኤርትራ ውስጥ 877 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ሲረጋገጥ የ1 ሰው ህይወት አልፏል፤ 599 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
ጎረቤታችን ኤርትራ ትላንት የመጀመሪያውን የኮሮና ቫይረስ ሞት አስተናግዳለች።
ሟቹ የ50 ዓመት እድሜ ያለው ወንድ #ደቀምሓረ ሆስፒተል ውስጥ የኮቪድ-19 ህክምና ሲደረግለት የነበረ ነው።
የዛሬ ሪፖርትን ጨምሮ በአጠቃላይ በኤርትራ ውስጥ 877 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ሲረጋገጥ የ1 ሰው ህይወት አልፏል፤ 599 ሰዎች ከበሽታው አገግመዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
#BenishangulGumuz
የኢትዮጵያ መንግሥት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ያለውን ችግር ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ዛሬ ጥዋት አሳወቁ።
በክልሉ መተከል ዞን ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
በተፈጸመው ኢሰብአዊ የሆነ ተግባርም በእጅጉ ማዘናቸውን ገልፀዋል።
ጠ/ሚሩ ችግሩን በተለያዩ መንገዶች ለመፍታት የተደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት አላመጣም ብለዋል። መንግስት አሁን ላይ የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ ማድረጉን በፌስቡክ ገፃቸው አሳውቀዋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግሥት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ያለውን ችግር ከመሠረቱ ለመፍታት አስፈላጊውን የተቀናጀ ኃይል እንዲሠማራ ማድረጉን ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ ዛሬ ጥዋት አሳወቁ።
በክልሉ መተከል ዞን ውስጥ በዜጎች ላይ እየተፈጸመ ያለው ጭፍጨፋ እጅግ አሳዛኝ ሆኗል ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ።
በተፈጸመው ኢሰብአዊ የሆነ ተግባርም በእጅጉ ማዘናቸውን ገልፀዋል።
ጠ/ሚሩ ችግሩን በተለያዩ መንገዶች ለመፍታት የተደረገው ጥረት የሚፈለገውን ውጤት አላመጣም ብለዋል። መንግስት አሁን ላይ የተቀናጀ ኃይል እንዲሰማራ ማድረጉን በፌስቡክ ገፃቸው አሳውቀዋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ሀገር መከላከያ ሰራዊት በወሰደው እርምጃ 42 ታጣቂዎች ተደመሰሱ !
በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ በትናንትናው ዕለት በንጹኃን ዜጎች ላይ #ጥቃት ያደረሱ የታጠቁ ኃይሎች ላይ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ተከታትሎ በወሰደው እርምጃ 42ቱ መደምሰሳቸውን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት አሰውቋል።
የመከላከያ ሠራዊት በወሰደው እርምጃ ታጣቂዎቹ ለጥፋት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እና ቀስቶችን በቁጥጥር ስር አዉሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ በኩጂ ቀበሌ በትናንትናው ዕለት በንጹኃን ዜጎች ላይ #ጥቃት ያደረሱ የታጠቁ ኃይሎች ላይ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ተከታትሎ በወሰደው እርምጃ 42ቱ መደምሰሳቸውን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ከደቂቃዎች በፊት አሰውቋል።
የመከላከያ ሠራዊት በወሰደው እርምጃ ታጣቂዎቹ ለጥፋት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ በርካታ የጦር መሳሪያዎችን እና ቀስቶችን በቁጥጥር ስር አዉሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#SecurityAlert
በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤማንጂ፣በኖሽ፣ ዶቢ ቀበሌዎች አሁንም ከፍተኛ የደህንነት ችግር እንዳለባቸውን የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።
ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ እንደነበረ ጠቁመዋል። ስለደረሰው ጉዳት አጣርተው እንደሚያሳውቁን ገልፀዋል።
በተጠቀሱት አካባቢዎች ነዋሪው ቤት ንብረቱን ጥሎ እየሸሸ መሆኑንም አባላቶቻችን መልዕክት አድርሰዋል።
በ www.tikvahethiopia.net ላይ በየአካባቢው ያለውን የፀጥታ እንዲሁም ደህንነት ስጋት ልታሳውቁን ትችላላችሁ።
#TikvahFamilyBulenWoreda
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በመተከል ዞን ቡለን ወረዳ ኤማንጂ፣በኖሽ፣ ዶቢ ቀበሌዎች አሁንም ከፍተኛ የደህንነት ችግር እንዳለባቸውን የቲክቫህ አባላት አሳውቀዋል።
ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ እንደነበረ ጠቁመዋል። ስለደረሰው ጉዳት አጣርተው እንደሚያሳውቁን ገልፀዋል።
በተጠቀሱት አካባቢዎች ነዋሪው ቤት ንብረቱን ጥሎ እየሸሸ መሆኑንም አባላቶቻችን መልዕክት አድርሰዋል።
በ www.tikvahethiopia.net ላይ በየአካባቢው ያለውን የፀጥታ እንዲሁም ደህንነት ስጋት ልታሳውቁን ትችላላችሁ።
#TikvahFamilyBulenWoreda
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#TikvahFamilyBulenWoreda
ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ ነበር።
በቀበሌው በተፈፀመው ጥቃት የአምስት ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ በቡለን ወረዳ የቲክቫህ ኢትጵያ አባላት አሳውቀዋል።
አሁን በስልክ ያገኘናቸው የዶቢ ቲክቫህ አባላት የሟቾችን ስርዓተ ቀብር በስጋት ውስጥ ሆነው እያከናወኑ እንደሆነ ተናግረዋል።
ጥቃት አድራሾቹ ከበኩጂ ቀበሌ የተበተኑ የታጠቁ ኃይሎች እንደሆኑ የቲክቫህ አባላት በ www.tikvahethiopia.net ላይ ገልፀዋል።
አንድ አባላችን እንደገለፁልን ወደ #ዶቢ የገቡት ታጣቂዎች እስከ 300 የሚደርሱ ናቸው።
የመከላከያ ሰራዊት መረጃው ደርሶት በመግባት ምሽግ ይዞ ጥቃቱን ባይከላከል የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችል ነበር ብለውናል።
አንድ የመከላከያ አባልም መጠነኛ ጉዳት ደርሶበታል።
የመተከል ዞን የቲክቫህ አባላት ለአካባቢው እንዲህ መሆን አመራሮችን ተጠያቂ ያደርጋሉ።
መንግስት ውስጡን እንዲፈትሽም በተደጋጋሚ አሳውቀዋል።
ነዋሪው ተስፋ ቆርጧል ፥ ግፍ እና መከራ አድክሞታል እጅግ በጣም አስቸኳይ መፍትሄ ይፈልጋል ብለዋል።
አሁንም ቢሆን በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ከፍተኛ የደህንነት ስጋት በመኖሩ የሚመመለከተው አካል ንፁሃንን እንዲታደግ አባላቶቻችን እየተማፀኑ ነው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ትላንት ለሊቱን በዶቢ ቀበሌ ከፍተኛ የተኩስ ድምፅ ሲሰማ ነበር።
በቀበሌው በተፈፀመው ጥቃት የአምስት ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ በቡለን ወረዳ የቲክቫህ ኢትጵያ አባላት አሳውቀዋል።
አሁን በስልክ ያገኘናቸው የዶቢ ቲክቫህ አባላት የሟቾችን ስርዓተ ቀብር በስጋት ውስጥ ሆነው እያከናወኑ እንደሆነ ተናግረዋል።
ጥቃት አድራሾቹ ከበኩጂ ቀበሌ የተበተኑ የታጠቁ ኃይሎች እንደሆኑ የቲክቫህ አባላት በ www.tikvahethiopia.net ላይ ገልፀዋል።
አንድ አባላችን እንደገለፁልን ወደ #ዶቢ የገቡት ታጣቂዎች እስከ 300 የሚደርሱ ናቸው።
የመከላከያ ሰራዊት መረጃው ደርሶት በመግባት ምሽግ ይዞ ጥቃቱን ባይከላከል የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችል ነበር ብለውናል።
አንድ የመከላከያ አባልም መጠነኛ ጉዳት ደርሶበታል።
የመተከል ዞን የቲክቫህ አባላት ለአካባቢው እንዲህ መሆን አመራሮችን ተጠያቂ ያደርጋሉ።
መንግስት ውስጡን እንዲፈትሽም በተደጋጋሚ አሳውቀዋል።
ነዋሪው ተስፋ ቆርጧል ፥ ግፍ እና መከራ አድክሞታል እጅግ በጣም አስቸኳይ መፍትሄ ይፈልጋል ብለዋል።
አሁንም ቢሆን በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ከፍተኛ የደህንነት ስጋት በመኖሩ የሚመመለከተው አካል ንፁሃንን እንዲታደግ አባላቶቻችን እየተማፀኑ ነው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#የእሳት_አደጋ_በጅግጅጋ ፦
በጅግጅጋ ከተማ በ ቀበሌ 02 በልዩ ስሙ ድብኡራሾ ሱቅ ተብሎ በሚታወቀው ቦታ ትላንት ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።
መነሻ መንስዔው ያልታወቀው እሳቱ የተነሳው ከአንድ ሱቅ መሆኑ ተገልጿል።
በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰ የተገለፀ ሲሆን እሳቱ በፍጥነት በመዛመቱ 7 የንግድ ቦታዎች ላይ ከፍተኛ አደጋ አድረሷል።
ድምሩ ወደ 1.2 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት ነው።
#እሳት_አደጋ_በመቅደላ_ወረዳ ፦
ትላንት ምሽት በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።
የእሳት አደጋው መነሀሪያ ሸድ ላይ የተከሰተ ነበር።
በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የሌለ ሲሆን በንብረት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን እና ተያያዥ ጉዳዮች እየተጣራ ነው።
ምንጭ፦ አዲስ ዘይቤ ድረገፅ፣ የመቅደላ ወረዳ ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በጅግጅጋ ከተማ በ ቀበሌ 02 በልዩ ስሙ ድብኡራሾ ሱቅ ተብሎ በሚታወቀው ቦታ ትላንት ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።
መነሻ መንስዔው ያልታወቀው እሳቱ የተነሳው ከአንድ ሱቅ መሆኑ ተገልጿል።
በሰው ህይወት ላይ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰ የተገለፀ ሲሆን እሳቱ በፍጥነት በመዛመቱ 7 የንግድ ቦታዎች ላይ ከፍተኛ አደጋ አድረሷል።
ድምሩ ወደ 1.2 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት ነው።
#እሳት_አደጋ_በመቅደላ_ወረዳ ፦
ትላንት ምሽት በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የእሳት አደጋ ተከስቶ ነበር።
የእሳት አደጋው መነሀሪያ ሸድ ላይ የተከሰተ ነበር።
በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት የሌለ ሲሆን በንብረት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን እና ተያያዥ ጉዳዮች እየተጣራ ነው።
ምንጭ፦ አዲስ ዘይቤ ድረገፅ፣ የመቅደላ ወረዳ ኮሚኒኬሽን
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia