#ባህርዳር
የባህር ዳር ቲክቫህ አባላት ከለሊት 7:40 አካባቢ ሶስት ጊዜ የፍንዳታ ድምፅ እንደሰሙ ገልፀዋል።
አባላቶቻችን ከዚህ ቀደም የሰሙት አይነት ተመሳሳይ ፍንዳታ እንደሆነም ነው የገለፁት።
ፍንዳታውን ተከትሎ የተኩስ ድምፅ እንደነበርም ገልፀዋል።
ዝርዝር መረጃ በሚመለከታቸው አካላት ሲገለፅ ተከታትለን እናሳውቃለን።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የባህር ዳር ቲክቫህ አባላት ከለሊት 7:40 አካባቢ ሶስት ጊዜ የፍንዳታ ድምፅ እንደሰሙ ገልፀዋል።
አባላቶቻችን ከዚህ ቀደም የሰሙት አይነት ተመሳሳይ ፍንዳታ እንደሆነም ነው የገለፁት።
ፍንዳታውን ተከትሎ የተኩስ ድምፅ እንደነበርም ገልፀዋል።
ዝርዝር መረጃ በሚመለከታቸው አካላት ሲገለፅ ተከታትለን እናሳውቃለን።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#UPDATE
የአማራ ክልል መንግስት የህወሓት ቡድን 7፡40 አካባቢ ወደ ባህር ዳር የሮኬት ጥቃት መፈፀሙን ለአብመድ አሳውቋል።
በተፈፀመው ጥቃት የደረሰ ጉዳት መኖር አለመኖሩ እየተጣራ መሆኑን የክልሉ መንግስት ገልጿል።
የሮኬት ጥቃቱ የት ቦታ ላይ ኢላማ እንዳደረግ አልተገለፀም።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የአማራ ክልል መንግስት የህወሓት ቡድን 7፡40 አካባቢ ወደ ባህር ዳር የሮኬት ጥቃት መፈፀሙን ለአብመድ አሳውቋል።
በተፈፀመው ጥቃት የደረሰ ጉዳት መኖር አለመኖሩ እየተጣራ መሆኑን የክልሉ መንግስት ገልጿል።
የሮኬት ጥቃቱ የት ቦታ ላይ ኢላማ እንዳደረግ አልተገለፀም።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#UPDATE
ትላንት ለሊት በባህር ዳር ከተማ የተፈፀመው የሮኬት ጥቃት ምንም አይነት ጉዳታ እንዳላደረሰ የክልሉ መንግስት ገልጿል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ትላንት ለሊት በባህር ዳር ከተማ የተፈፀመው የሮኬት ጥቃት ምንም አይነት ጉዳታ እንዳላደረሰ የክልሉ መንግስት ገልጿል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
'የሮይተርስ የኢትዮጵያ ዘጋቢ ታገደች'
የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ተሰማ።
እርምጃ እየተወሰደባቸው የሚገኙት ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ዓለም በተሳሳተ መንገድ እንዲያውቀውና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በማድረጋቸው ነው ተብሏል።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 እንደተናገረው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ወቅታዊውን ሁኔታ በጥንቃቄ እንዲሁም በሞያዊ ስነ ምግባር እንዲዘግቡ ማሳሰቢያ ቢሰጣቸውም በእንቢተኝነት በቀጠሉት ላይ እርምጃ መወሰዱን አሳውቋል።
ዶቼ ቨለ (DW) ፣ BBC ፣ ሮይተርስ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ከተሰጣቻው መካከል ይገኙበታል።
"ሮይተርስ" ከትላንትና ወዲህ በሀገር ውስጥ ያላቸው ዘጋቢ በኢትዮጵያ ጉዳይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳታደርግ ፣ ዘገባዎችን ፣ ዜናዎችን እንዳትሰራ ሙሉ በሙሉ እንደታገደች የብሮድካስት ባለስልጣን ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ተሰማ።
እርምጃ እየተወሰደባቸው የሚገኙት ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ዓለም በተሳሳተ መንገድ እንዲያውቀውና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በማድረጋቸው ነው ተብሏል።
የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 እንደተናገረው መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ወቅታዊውን ሁኔታ በጥንቃቄ እንዲሁም በሞያዊ ስነ ምግባር እንዲዘግቡ ማሳሰቢያ ቢሰጣቸውም በእንቢተኝነት በቀጠሉት ላይ እርምጃ መወሰዱን አሳውቋል።
ዶቼ ቨለ (DW) ፣ BBC ፣ ሮይተርስ የማስጠንቀቂያ ደብዳቤ ከተሰጣቻው መካከል ይገኙበታል።
"ሮይተርስ" ከትላንትና ወዲህ በሀገር ውስጥ ያላቸው ዘጋቢ በኢትዮጵያ ጉዳይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳታደርግ ፣ ዘገባዎችን ፣ ዜናዎችን እንዳትሰራ ሙሉ በሙሉ እንደታገደች የብሮድካስት ባለስልጣን ለሬድዮ ጣቢያው ገልጿል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#TiborNagy
አሜሪካ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳዮች ጣልቃ እንደማትገባ በይፋ አሳውቃለች።
በኢትዮጵያ መንግሥት እና በሕወሓት አመራር መካከል ትግራይ ውስጥ ያለው ግጭት የሚያበቃውም በሁለቱ ኃይላት መሆኑን አሜሪካ ገልፃለች።
ትናንት ማምሻውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዥ እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ስላለው ሁኔታ በስልክ ኮንፈረንስ ለጋዜጠኞች ልዩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ቲቦር ናዥ ፥ «የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ግጭቱ ፍጻሜ እንዲያገኝ፤ ሰላም እንዲሰፍን፤ ሰላማዊ ሰዎች መጠበቃቸውን ለማሳሰብ የተቻለውን ጥረት ያደርጋል» ብለዋል።
«ግጭቱን ማስቆም ያለበት ግን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አይደለም» ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል።
* ዝርዝር መረጃው ከላይ ተያይዟል (በጀርመን ድምፅ ሬድዮ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አሜሪካ በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳዮች ጣልቃ እንደማትገባ በይፋ አሳውቃለች።
በኢትዮጵያ መንግሥት እና በሕወሓት አመራር መካከል ትግራይ ውስጥ ያለው ግጭት የሚያበቃውም በሁለቱ ኃይላት መሆኑን አሜሪካ ገልፃለች።
ትናንት ማምሻውን የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪቃ ጉዳዮች ረዳት ሚንስትር ቲቦር ናዥ እና በኢትዮጵያ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሚካኤል ራይኖር ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ ስላለው ሁኔታ በስልክ ኮንፈረንስ ለጋዜጠኞች ልዩ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ቲቦር ናዥ ፥ «የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት ግጭቱ ፍጻሜ እንዲያገኝ፤ ሰላም እንዲሰፍን፤ ሰላማዊ ሰዎች መጠበቃቸውን ለማሳሰብ የተቻለውን ጥረት ያደርጋል» ብለዋል።
«ግጭቱን ማስቆም ያለበት ግን የዩናይትድ ስቴትስ መንግሥት አይደለም» ሲሉ አጽንዖት ሰጥተዋል።
* ዝርዝር መረጃው ከላይ ተያይዟል (በጀርመን ድምፅ ሬድዮ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ዛሬ በ10,000 ብር ዋስ ፍርድ ቤት ከእስር እንዲለቀቅ ቢወሰንለትም ፣ ፖሊስ ይግባኝ በመጠየቁ ሊለቀቅ እንዳልቻለ "አውሎ ሚዲያ" ገለፀ። "የመዝገብ ክፍል ሰዎች ባለመኖራቸው" ምክንያት ክሊራንስ ጨርሶ ከእስር የሚወጣው ነገ ነው ተብሎ ነበር። ማምሻውን ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀበት በእስር ይቆያል። @tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ጋዜጠኛ በቃሉ ከእስር ተፈታ !
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በ10 ሺ ብር ዋስ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ተለቋል።
ባለፈው ማክሰኞ በዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኖ የነበረ ቢሆንም ፤ ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀበት በእስር እንዲቆይ እንደተደረገ ይታወሳል።
ዛሬ በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ በዋስ እንዲለቀቅ ተወስኖ የነበረውን ውሳኔ በማፅደቅ ከእስር መፈታቱን አውሎ ሚዲያ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው በ10 ሺ ብር ዋስ ዛሬ ማምሻውን ከእስር ተለቋል።
ባለፈው ማክሰኞ በዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኖ የነበረ ቢሆንም ፤ ፖሊስ ይግባኝ ስለጠየቀበት በእስር እንዲቆይ እንደተደረገ ይታወሳል።
ዛሬ በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ በዋስ እንዲለቀቅ ተወስኖ የነበረውን ውሳኔ በማፅደቅ ከእስር መፈታቱን አውሎ ሚዲያ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል 'አክሱም ከተማ' በእጃችን ላይ ትገኛለች ሲሉ ለሮይተርስ በፅሁፍ በላኩት መልዕክት ገልፀዋል። 'ሽረ ከተማ' በፌዴራል ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሆነችም አረጋግጠዋል። ዶክተር ደብረፅዮን ፥ ሽረ ከ3 ቀን በፊት በፌዴራል ወታደሮች ቁጥጥር ስር እንደሆነች የገለፁ ሲሆን 'አክሱም ከተማ' ግን በቁጥጥራችን ስር ናት ብለዋል። ዶ/ር ደብረፅዮን አክለውም የፌዴራል…
#FDREDefenseForce
ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2013 ዓ/ም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አክሱምን ፣ አድዋን እና የአዲግራትን ዙሪያ እንደተቆጣጠረ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
* ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2013 ዓ/ም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አክሱምን ፣ አድዋን እና የአዲግራትን ዙሪያ እንደተቆጣጠረ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
* ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የአውሮፓ ኮሚሽን ድጋፍ አደረገ።
በትግራይ ክልል በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ወደ ሱዳን እየተሰደዱ ላሉ ዜጎች የአስቸኳይ እርዳታ አራት ሚሊዮን ዩሮ ለግሷል።
የአስቸካይ እርዳታው በጦርነቱ ምክንያት ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደ ሱዳን ለተሰደዱ ኢትዮጵያውያን የሚውል ነው ብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በትግራይ ክልል በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ወደ ሱዳን እየተሰደዱ ላሉ ዜጎች የአስቸኳይ እርዳታ አራት ሚሊዮን ዩሮ ለግሷል።
የአስቸካይ እርዳታው በጦርነቱ ምክንያት ቤት ንብረታቸውን ጥለው ወደ ሱዳን ለተሰደዱ ኢትዮጵያውያን የሚውል ነው ብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 5,488
• በበሽታው የተያዙ - 452
• ህይወታቸው ያለፈ - 13
• ከበሽታው ያገገሙ - 342
አጠቃላይ 104,879 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,620 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ፤ 65,325 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
315 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የባለፉት 24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት :
• የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 5,488
• በበሽታው የተያዙ - 452
• ህይወታቸው ያለፈ - 13
• ከበሽታው ያገገሙ - 342
አጠቃላይ 104,879 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው ሲረጋገጥ ፤ የ1,620 ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ፤ 65,325 ሰዎች ደግሞ ከበሽታው አገግመዋል።
315 ሰዎች በፅኑ ታመው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#FDREDefenseForce ዛሬ ህዳር 11 ቀን 2013 ዓ/ም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አክሱምን ፣ አድዋን እና የአዲግራትን ዙሪያ እንደተቆጣጠረ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ ገልጿል። * ዝርዝር መግለጫው ከላይ ተያይዟል። @tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
* ማብራሪያ
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ በሰጠው ማብራሪያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት አክሱም እና አድዋን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል።
በተጨማሪም ሰራዊቱ የአዲግራትን ዙሪያ እንደተቆጣጠረ የተገለፀ ሲሆን ወደ "አዲግራት ከተማ" አየገሰገሰ ይገኛል ብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መረጃ ማጣሪያ በሰጠው ማብራሪያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት አክሱም እና አድዋን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል።
በተጨማሪም ሰራዊቱ የአዲግራትን ዙሪያ እንደተቆጣጠረ የተገለፀ ሲሆን ወደ "አዲግራት ከተማ" አየገሰገሰ ይገኛል ብሏል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ATTENTION በደቡብ ክልል የኮንሶ ዞን ፣ የአሌ ልዩ ወረዳ ፣ የቡርጂ እና የደራሼ ልዩ ወረዳ አዋሳኝ አከባቢዎች ከፍተኛ የጸጥታ ስጋት መኖሩን የቲክቫህ ቤተሰቦች ጠቁመዋል። ያንብቡ : https://telegra.ph/TIKVAH-11-19-2 @TIKVAHETHIOPIA @TIKVAHETHIOPIABOT
'94,586 ሰዎች ተፈናቅለዋል'
በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን "በታጣቂዎች የተፈፀመውን ጥቃት" ተከትሎ 94,586 ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።
የኮንሶ ዞን ባለስልጣናት ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ እንደገለፁት ነዋሪዎች የተፈናቀሉት ኮልሜ ክልስተር፣ ካራትና በሰገን ዙሪያ ወረዳዎች ከሚገኙ መንደሮች ነው።
ከኮልሜ ክላስተር ቦርቆራ ቀበሌ የተፈናቀሉ አንድ አርሶ አደር ፥ ስለሆኔታው ምንም እንደማያውቁ ተናግረዋል። አርሶ አደሩ ፥ "ንብረታቸው ወድሟል፣ ቤታችን ተቃጥሏል፣ ንብረታቸው ተዘርፏል፣ ብዙ ሰውም ሞቷል፣ ቆስሏል በአጠቃላይ በስቃይ ውስጥ ነን ሲሉ" ገልፀዋል።
የኮንሶ ዞን ባለስልጣናት አሁንም የታጠቁ አካላት በአካባቢው እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ትላንትም በሰው እና በተሽከርካሪ ላይ ጥቃት አድርሰዋል።
ለተፈናቀሉ ዜጎች 'የሰብዓዊ እርዳታ' እንዲያገኙ ዞኑ ለደቡብ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የድጋፍ ጥያቄ ማቅረቡን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ቢቢሲ በዚህ ጉዳይ ያዘጋጀውን ሰፊ ዘገባ ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-11-20
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በደቡብ ክልል ኮንሶ ዞን "በታጣቂዎች የተፈፀመውን ጥቃት" ተከትሎ 94,586 ሰዎች ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለዋል።
የኮንሶ ዞን ባለስልጣናት ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ እንደገለፁት ነዋሪዎች የተፈናቀሉት ኮልሜ ክልስተር፣ ካራትና በሰገን ዙሪያ ወረዳዎች ከሚገኙ መንደሮች ነው።
ከኮልሜ ክላስተር ቦርቆራ ቀበሌ የተፈናቀሉ አንድ አርሶ አደር ፥ ስለሆኔታው ምንም እንደማያውቁ ተናግረዋል። አርሶ አደሩ ፥ "ንብረታቸው ወድሟል፣ ቤታችን ተቃጥሏል፣ ንብረታቸው ተዘርፏል፣ ብዙ ሰውም ሞቷል፣ ቆስሏል በአጠቃላይ በስቃይ ውስጥ ነን ሲሉ" ገልፀዋል።
የኮንሶ ዞን ባለስልጣናት አሁንም የታጠቁ አካላት በአካባቢው እየተንቀሳቀሱ እንደሚገኙ ገልፀዋል።
ትላንትም በሰው እና በተሽከርካሪ ላይ ጥቃት አድርሰዋል።
ለተፈናቀሉ ዜጎች 'የሰብዓዊ እርዳታ' እንዲያገኙ ዞኑ ለደቡብ ክልል የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የድጋፍ ጥያቄ ማቅረቡን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ገልጿል።
ከዚህ በተጨማሪ ቢቢሲ በዚህ ጉዳይ ያዘጋጀውን ሰፊ ዘገባ ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-11-20
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የኢሰመጉ አስቸኳይ ጋዜጣዊ መግለጫ !
(አስከፊ ደረጃ ላይ ያለው የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ በኢትዮጵያ)
- የኮንሶ ዞን እና አዋሳኝ አካባቢዎች
- የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
- የምዕራብ ወለጋና የቄለም ወለጋ አካባቢዎች
- የጋዜጠኞች እስር
ህዳር 11 ቀን 2013 ዓ.ም
* ይህ መግለጫ የወጣው ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ከእስር ከመፈታቱ ቀደም ብሎ ነው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
(አስከፊ ደረጃ ላይ ያለው የሰብዓዊ መብቶች ሁኔታ በኢትዮጵያ)
- የኮንሶ ዞን እና አዋሳኝ አካባቢዎች
- የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል
- የምዕራብ ወለጋና የቄለም ወለጋ አካባቢዎች
- የጋዜጠኞች እስር
ህዳር 11 ቀን 2013 ዓ.ም
* ይህ መግለጫ የወጣው ጋዜጠኛ በቃሉ አላምረው ከእስር ከመፈታቱ ቀደም ብሎ ነው።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Ethiopia
በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እንዲያበቃ እና ችግሩ በድርድር እንዲፈታ በርካቶች ሲጠይቁ ቆይተዋል።
ህወሓትም ጦርነቱ ቆሞ ችግሩ በውይይት ይፈታ ዘንድ ለAU እና ለሌሎችም ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።
ድርድርን በሚመለከት የፌዴራል መንግስቱ በፍፁም ህወሓት ውስጥ ካሉት 'ወንጀለኛ' ቡድን ጋር ቁጭ ብዬ #አልደራደርም ብሎ አሳውቋል።
ይህ 'ህወሓት' ውስጥ ያለው ቡድን ታሪክ ይቅር የማይለውን ጥፋት አጥፍቷል፣ የሀገር መከታ የሆነውን መከላከያ ሰራዊት አጥቅቷል ፣ ይህን ጉዳይ አምኗል ፤ አሁን እየተካሄደ ያለው የህግ ማስከበር እና የሀገርን ህልውና እና ክብር የማስጠበቅ ዘመቻ የሚጠናቀቀው ወንጀለኞቹ ህግ ፊት ሲቀርቡ ብቻ ነው ሲል ከዚህ ቀደም አቋሙን ገልጿል።
ትላንት ምሽት ድርድርን በሚመለከት በተለያዩ መገናኛ ብዙን አንድ መረጃ ሲሰራጭ ነበር። ይህ የተሰራጨው መረጃው ግን ሀሰተኛ ነው ተብሏል።
ጉዳዩን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የተሰጠው አጭር ምላሽ ይኸው ነው ፦
"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኀብረት ሊቀ መንበር የሆኑትን የሲሪል ራማፎሳን ልዑካን ተቀብለው በግል ይወያያሉ።
ሆኖም ግን ፣ የፌደራል መንግሥትን እና በህወሓት የሚገኙ ወንጀለኞችን ለማሸማገል ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው ዜና #ሀሰት መሆኑን እናረጋግጣለን።
#ድርድርን አስመልክቶ የፌደራል መንግሥት ያለው አቋም ፈጽሞ ያልተለወጠ ነው።"
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ውስጥ እየተካሄደ ያለው ጦርነት እንዲያበቃ እና ችግሩ በድርድር እንዲፈታ በርካቶች ሲጠይቁ ቆይተዋል።
ህወሓትም ጦርነቱ ቆሞ ችግሩ በውይይት ይፈታ ዘንድ ለAU እና ለሌሎችም ጥሪ ሲያቀርብ ነበር።
ድርድርን በሚመለከት የፌዴራል መንግስቱ በፍፁም ህወሓት ውስጥ ካሉት 'ወንጀለኛ' ቡድን ጋር ቁጭ ብዬ #አልደራደርም ብሎ አሳውቋል።
ይህ 'ህወሓት' ውስጥ ያለው ቡድን ታሪክ ይቅር የማይለውን ጥፋት አጥፍቷል፣ የሀገር መከታ የሆነውን መከላከያ ሰራዊት አጥቅቷል ፣ ይህን ጉዳይ አምኗል ፤ አሁን እየተካሄደ ያለው የህግ ማስከበር እና የሀገርን ህልውና እና ክብር የማስጠበቅ ዘመቻ የሚጠናቀቀው ወንጀለኞቹ ህግ ፊት ሲቀርቡ ብቻ ነው ሲል ከዚህ ቀደም አቋሙን ገልጿል።
ትላንት ምሽት ድርድርን በሚመለከት በተለያዩ መገናኛ ብዙን አንድ መረጃ ሲሰራጭ ነበር። ይህ የተሰራጨው መረጃው ግን ሀሰተኛ ነው ተብሏል።
ጉዳዩን በሚመለከት ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት የተሰጠው አጭር ምላሽ ይኸው ነው ፦
"ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የአፍሪካ ኀብረት ሊቀ መንበር የሆኑትን የሲሪል ራማፎሳን ልዑካን ተቀብለው በግል ይወያያሉ።
ሆኖም ግን ፣ የፌደራል መንግሥትን እና በህወሓት የሚገኙ ወንጀለኞችን ለማሸማገል ልዑካን ወደ ኢትዮጵያ ይመጣሉ ተብሎ በመሰራጨት ላይ የሚገኘው ዜና #ሀሰት መሆኑን እናረጋግጣለን።
#ድርድርን አስመልክቶ የፌደራል መንግሥት ያለው አቋም ፈጽሞ ያልተለወጠ ነው።"
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
'የሮይተርስ የኢትዮጵያ ዘጋቢ ታገደች' የኢትዮጵያ መንግስት በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እየወሰደ መሆኑ ተሰማ። እርምጃ እየተወሰደባቸው የሚገኙት ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን ሁኔታ ዓለም በተሳሳተ መንገድ እንዲያውቀውና በኢትዮጵያ መንግስት ላይ ጫና እንዲበረታ በማድረጋቸው ነው ተብሏል። የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 እንደተናገረው መቀመጫቸውን…
'የብሮድካስት ባለስልጣን ማስተባበያ'
ትላንትና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ም/ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ወንድወሰን አንዱአለም ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ፦
- ለዶቼ ቨለ (DW) ፣ BBC ፣ ሮይተርስ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደተሰጣቸው፤
- የሮይተርስ የኢትዮጵያ ዘጋቢ ሙሉ በሙሉ እንደታገደች፤
በራሳቸው አንደበት ተናግረው ነበር።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ደግሞ ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ተከታዩን ሲሉ ተደምጠዋል (በቅድሚያ ያነሱት ታገደች ስለተባለችው የ "ሮይተርስ" ዘጋቢ ነው) ፦
"..የሀገሩን ህግ አክብረሽ በትህትና መረጃዎችሽን ለማግኘት ጥረት የማታደርጊ ከሆነ ፤ እዚህ እንድትሰሪ የምንፈቅደው በሀገሪቱ ህግ ስለሆነ ናይሮቢ ከሚገኘው የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ ጋር ተነጋግረን አንቺ እንድትተኪ እናደርጋለን ፤ ይሄንን ደግሞ ላንቺ በግልፅ እንነግርሻለን፣ ምክንያቱ ደግሞ ይሄ ይሄ ነው ብለን አስረድተናት ፤ ተቀብላ ነው የወጣችው።
ምንም ያገድነው ነገር የለም። እኛ ለሮይተርስ ነው ውሳኔውን የተውነው ፤ ሮይተርስ እኛ ባቀረብነው ቅሬታ ላይ ተመስርቶ አቤቱታችንን ተቀብሎ ካነሳት ሴትዮዋን #የሮይተርስ ነው ውሰኔው የሚሆነው እንጂ አሁንም የፕሬስ ፍቃዷ በእጇ ነው እኛ ያገድናት ነገር የለም።
ለሌሎቹም ሚዲያዎች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ የሚባለው ነገር ማስጠንቀቂያ ሳይሆን በሪፖርቶቻቸው ላይ ውይይትና ምክክር ነው። ለምን ማድረግ የሚገባቸውን ነገር ሳያደርጉ እንደቀሩ አንድም ለማገዝ ፤ አለበለዛም ሞያዊ ግዴታቸውን በአግባቢ እንዲወጡ ለመሞገት የተደረገ ጥረት ነው ፤ እንጂ ሌላ ነገር የለውም።"
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ትላንትና የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን ም/ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ወንድወሰን አንዱአለም ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ፦
- ለዶቼ ቨለ (DW) ፣ BBC ፣ ሮይተርስ ማስጠንቀቂያ ደብዳቤ እንደተሰጣቸው፤
- የሮይተርስ የኢትዮጵያ ዘጋቢ ሙሉ በሙሉ እንደታገደች፤
በራሳቸው አንደበት ተናግረው ነበር።
የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር ጌታቸው ድንቁ ደግሞ ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ተከታዩን ሲሉ ተደምጠዋል (በቅድሚያ ያነሱት ታገደች ስለተባለችው የ "ሮይተርስ" ዘጋቢ ነው) ፦
"..የሀገሩን ህግ አክብረሽ በትህትና መረጃዎችሽን ለማግኘት ጥረት የማታደርጊ ከሆነ ፤ እዚህ እንድትሰሪ የምንፈቅደው በሀገሪቱ ህግ ስለሆነ ናይሮቢ ከሚገኘው የምስራቅ አፍሪካ ቢሮ ጋር ተነጋግረን አንቺ እንድትተኪ እናደርጋለን ፤ ይሄንን ደግሞ ላንቺ በግልፅ እንነግርሻለን፣ ምክንያቱ ደግሞ ይሄ ይሄ ነው ብለን አስረድተናት ፤ ተቀብላ ነው የወጣችው።
ምንም ያገድነው ነገር የለም። እኛ ለሮይተርስ ነው ውሳኔውን የተውነው ፤ ሮይተርስ እኛ ባቀረብነው ቅሬታ ላይ ተመስርቶ አቤቱታችንን ተቀብሎ ካነሳት ሴትዮዋን #የሮይተርስ ነው ውሰኔው የሚሆነው እንጂ አሁንም የፕሬስ ፍቃዷ በእጇ ነው እኛ ያገድናት ነገር የለም።
ለሌሎቹም ሚዲያዎች ላይ ማስጠንቀቂያ ተሰጠ የሚባለው ነገር ማስጠንቀቂያ ሳይሆን በሪፖርቶቻቸው ላይ ውይይትና ምክክር ነው። ለምን ማድረግ የሚገባቸውን ነገር ሳያደርጉ እንደቀሩ አንድም ለማገዝ ፤ አለበለዛም ሞያዊ ግዴታቸውን በአግባቢ እንዲወጡ ለመሞገት የተደረገ ጥረት ነው ፤ እንጂ ሌላ ነገር የለውም።"
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#FDREDefenseForce
ሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ጥዋት አዲግራት ከተማን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩ ተገልጿል።
ሰራዊቱ በአሁኑ ጊዜ ወደ መቐለ እያመራ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ አሳውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ጥዋት አዲግራት ከተማን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠሩ ተገልጿል።
ሰራዊቱ በአሁኑ ጊዜ ወደ መቐለ እያመራ መሆኑን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ አሳውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Youtube
ዩቲዩብ (YouTube) ብዙ ቪዲዮዎች ላይ ማስታወቂያዎች ማሳየት እንደሚጀምር እና ለሁሉም ማስታወቂያ ግን ክፍያ ላይፈጽም እንደሚችል አስታውቋል።
ኩባንያው በአሁኑ ወቅት የማስታወቂያ ገቢውን በሽርክና መርሃ ግብሩ ላይ ከተመዘገቡ ቪዲዮ ሠሪዎች ጋር ይጋራል።
ከዚህ በኋላ ግን ዩቲዩብ የሽርክና መርሃ ግብሩ አካል ያልሆኑ በአንዳንድ ቪዲዮዎች ላይም ማስታወቂያዎችን ማስገባት እጀምራለሁ ብሏል።
በአገልግሎት ውሉ ላይ በተደረጉ ለውጦች ምክንያት ዩቲዩብ ከማስታወቂያዎቹ የሚገኘውን ገቢ ለቪዲዮ ሠሪዎች ላያጋራ ይችላል።
ከዚህ በተጨማሪ ተመልካቾች ከፍተኛ የሆነ ቁጥር ያላቸውን ማስታወቂያዎችን እንዲያዩ ሊገደዱ ይችላሉ መባሉን BBC አስነብቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
ዩቲዩብ (YouTube) ብዙ ቪዲዮዎች ላይ ማስታወቂያዎች ማሳየት እንደሚጀምር እና ለሁሉም ማስታወቂያ ግን ክፍያ ላይፈጽም እንደሚችል አስታውቋል።
ኩባንያው በአሁኑ ወቅት የማስታወቂያ ገቢውን በሽርክና መርሃ ግብሩ ላይ ከተመዘገቡ ቪዲዮ ሠሪዎች ጋር ይጋራል።
ከዚህ በኋላ ግን ዩቲዩብ የሽርክና መርሃ ግብሩ አካል ያልሆኑ በአንዳንድ ቪዲዮዎች ላይም ማስታወቂያዎችን ማስገባት እጀምራለሁ ብሏል።
በአገልግሎት ውሉ ላይ በተደረጉ ለውጦች ምክንያት ዩቲዩብ ከማስታወቂያዎቹ የሚገኘውን ገቢ ለቪዲዮ ሠሪዎች ላያጋራ ይችላል።
ከዚህ በተጨማሪ ተመልካቾች ከፍተኛ የሆነ ቁጥር ያላቸውን ማስታወቂያዎችን እንዲያዩ ሊገደዱ ይችላሉ መባሉን BBC አስነብቧል።
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia