በድሬዳዋ በህገ-ወጥ መንገድ ሲቀሳቀሱ የነበሩ የብር ኖቶች ተያዙ!
በድሬደዋ የፀጥታ አካላት በጋራ ባካሄዱት የክትትልና ቁጥጥር ስራ በህገ -ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የሀገርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች መያዛቸው ተገለፀ።
ገንዘቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ትላንት መስከረም 6/2013 ዓ/ም ሲሆን ከህበረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ባደረገ ክትልል መሆኑን ድሬ ፖሊስ አስታውቋል።
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ መታየት መጀመሩም ተገልፃል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የብር ኖቶች ውስጥ በዋነኝነት፦
-ዘጠኝ መቶ አርባ አርት ሺ አንድ መቶ አስር (944,110) የኢትዮጽያ ብር
-አንድ ሺ ሁለት መቶ ሀምሳ (1250) የአሜሪካን ዶላር
-አንድ መቶ ስልሳ አምስት (165)የሳውዲ ሪያል
-ሰባት መቶ አርባ አምስት (745) ዩሮ ሲሆኑ ከእነዚህ ጋር አብሮም ከዘጠኝ በላይ የሚሆኑ ሀገራት የተለያየ መጠን ያላቸው የብር ኖቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በድሬደዋ የፀጥታ አካላት በጋራ ባካሄዱት የክትትልና ቁጥጥር ስራ በህገ -ወጥ መንገድ የሚንቀሳቀሱ የሀገርን ጨምሮ የተለያዩ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች መያዛቸው ተገለፀ።
ገንዘቡ በቁጥጥር ስር የዋለው ትላንት መስከረም 6/2013 ዓ/ም ሲሆን ከህበረተሰቡ በተሰጠ ጥቆማ መሰረት ባደረገ ክትልል መሆኑን ድሬ ፖሊስ አስታውቋል።
ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 4 ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው በህግ መታየት መጀመሩም ተገልፃል።
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የብር ኖቶች ውስጥ በዋነኝነት፦
-ዘጠኝ መቶ አርባ አርት ሺ አንድ መቶ አስር (944,110) የኢትዮጽያ ብር
-አንድ ሺ ሁለት መቶ ሀምሳ (1250) የአሜሪካን ዶላር
-አንድ መቶ ስልሳ አምስት (165)የሳውዲ ሪያል
-ሰባት መቶ አርባ አምስት (745) ዩሮ ሲሆኑ ከእነዚህ ጋር አብሮም ከዘጠኝ በላይ የሚሆኑ ሀገራት የተለያየ መጠን ያላቸው የብር ኖቶች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የፕ/ር ክንደያ ገ/ሂወት ከሃላፊነት መነሳት አፈፃፀም ዙርያ በመቐለ ዩኒቨርሲቲ ሰራተኞችና ማህበረሰብ የተነሱ ለቲቫህ ኢትዮጵያ የተላኩ ጥያቄዎች!
ሰሞኑ መቐለ ዩኒቨርሲቲን ላለፉት ሰባት (7) ዓመታት ፕሬዚዳንት ሆነው ያገለገሉት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሂወት የስልጣን ጊዜያቸው በመጠናቀቁ ኃላፊነቱ እንደተነሳላቸው የሚገልፅ ደብዳቤ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ደርሷቸው ነበር።
የአንድ የዩኒቨርሲቲ መሪ የስልጣን ዘመን ሲጠናቀቅ ህግን የተከተለ መንገድ የመቀየር/የማስቀጠል አካሄድ እንዳለ ይታወቃል።
የፕሮፌሰር ክንደያ መነሳት በዚህ ረገድ ሲጠበቅ የነበረ እና እራሳቸውም ለቦርድ አሳውቀው ውሳኔ ሲጠብቁ የነበረ ጉዳይ ቢሆንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን ከሰሞኑ የፈፀመበት አካሄድ ግን ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና የተለያዩ ወገኖች የሚከተሉት ሃሳቦችን አስነስቷል ፦
- ተቋሙን የሚመራው ቦርድ ያልተወያየበት እና ውሳኔ ያልሰጠበት በመሆኑ የከፍተኛ ትምህርት መመርያ ይጥሳል፣
- በቅርብ አመታት በወጣው እና በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች በተተገበረው የዩነቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች አመራረጥ መመርያ ጋር ተያይዞ የፕሬዚዳንቱ የአግልግሎት ዘመን ማለቅ አስመልክት የወጣ የውድድር ማስታወቅያና የተካሄደ ውድድር አለመኖሩ፣
- የስንብት ደብዳቤውን የፃፉት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ሚኒስቴር እና ስልጣናቸው በምክር ቤት ያልፀደቀ በመሆኑ ውሳኔውን ማስተላለፍ የማይችሉ ናቸው።
ሁኔታው ለነዚህ ጥያቄዎች የጠራ ምላሽ በማይሰጥ ሂደት በመፈፀሙ በርካቶች ድርጊቱ ከመዋቅራዊ አሰራር ይልቅ የትግራይ ክልል መንግስት ካካሄደው ምርጫ እና በምርጫው በታዛቢነት ከተሳተፉ የተቋሙ አጋር ተመራማሪዎች ጋር የተያያዘ በማእከላይ መንግስት የተሰጠ ፖለቲካዊ ውሳኔ ነው ብለውታል።
@tikvahethiopiaBot
ሰሞኑ መቐለ ዩኒቨርሲቲን ላለፉት ሰባት (7) ዓመታት ፕሬዚዳንት ሆነው ያገለገሉት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሂወት የስልጣን ጊዜያቸው በመጠናቀቁ ኃላፊነቱ እንደተነሳላቸው የሚገልፅ ደብዳቤ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ደርሷቸው ነበር።
የአንድ የዩኒቨርሲቲ መሪ የስልጣን ዘመን ሲጠናቀቅ ህግን የተከተለ መንገድ የመቀየር/የማስቀጠል አካሄድ እንዳለ ይታወቃል።
የፕሮፌሰር ክንደያ መነሳት በዚህ ረገድ ሲጠበቅ የነበረ እና እራሳቸውም ለቦርድ አሳውቀው ውሳኔ ሲጠብቁ የነበረ ጉዳይ ቢሆንም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጉዳዩን ከሰሞኑ የፈፀመበት አካሄድ ግን ከዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና የተለያዩ ወገኖች የሚከተሉት ሃሳቦችን አስነስቷል ፦
- ተቋሙን የሚመራው ቦርድ ያልተወያየበት እና ውሳኔ ያልሰጠበት በመሆኑ የከፍተኛ ትምህርት መመርያ ይጥሳል፣
- በቅርብ አመታት በወጣው እና በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች በተተገበረው የዩነቨርሲቲ ፕሬዚዳንቶች አመራረጥ መመርያ ጋር ተያይዞ የፕሬዚዳንቱ የአግልግሎት ዘመን ማለቅ አስመልክት የወጣ የውድድር ማስታወቅያና የተካሄደ ውድድር አለመኖሩ፣
- የስንብት ደብዳቤውን የፃፉት የሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ሚኒስቴር እና ስልጣናቸው በምክር ቤት ያልፀደቀ በመሆኑ ውሳኔውን ማስተላለፍ የማይችሉ ናቸው።
ሁኔታው ለነዚህ ጥያቄዎች የጠራ ምላሽ በማይሰጥ ሂደት በመፈፀሙ በርካቶች ድርጊቱ ከመዋቅራዊ አሰራር ይልቅ የትግራይ ክልል መንግስት ካካሄደው ምርጫ እና በምርጫው በታዛቢነት ከተሳተፉ የተቋሙ አጋር ተመራማሪዎች ጋር የተያያዘ በማእከላይ መንግስት የተሰጠ ፖለቲካዊ ውሳኔ ነው ብለውታል።
@tikvahethiopiaBot
በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልል የተከሰተውን ግድያ እና መፈናቀል አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ !
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመከላከያ ሚኒስቴር ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል!
በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈጠሩ ችግሮችን ለማረጋጋት የመከላከያ ሰራዊት በወሰደው ሁሉን አቀፍ ዘመቻ በግጭት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ከ25 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ማድረጉን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል መሀመድ ተሰማ ሰሞነኛ ጉዳዮችን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ተከታዩን ብለዋል ፦
- በክልሉ የተፈጠረው የፀጥታ ችግር ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎች አቅም በላይ አልነበረም ሊከሰትም አይገባው ነበር።
- ችግሩ በተፈጠረበት ሰዓት መከላከያ የራሱ ተልዕኮ ላይ ነበር ሠራዊቱ ወደ ስፍራው በማቅናት የአከባቢውን ሰላምና ደህንነት የማስከበር ስራ በጀግንነት ተሰርቷል።
- መከላከያ ከገባ በኋላ በአጥፊዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ በመውሰዱ አሁን በክልሉ ያለው ሁኔታ ወደ ቀድሞ ሰላማዊና መረጋጋት እንቅስቃሴ ተመልሷል።
- በማህበራዊ ሚዲያዎች “መካላከያ ቀድሞ ወደ ስፍራው አልደረሰም” በሚል እየተናፈሰ ያለው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው።
- በክልሎች የፀጥታ ችግሮች ሲከሰቱ የማረጋጋት ግዴታ በዋናነት የክልልና የወረዳ የጸጥታ ኃይል ነው መከላከያ የራሱ ግዳጆች ቢኖሩትም ከክልሎቹ አቅም በላይ የሆነ የፀጥታ ችግር ሲያጋጥም አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
- በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መከላከያ ግዳጅ እንደተሰጠው ከ150 ኪሎ ሜትር ውስጥ 50 ኪሎ ሜትሩን በእግሩ በመጓዝ በታጣቂዎች ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ወስዷል። (ኢቲቪ)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል የተፈጠሩ ችግሮችን ለማረጋጋት የመከላከያ ሰራዊት በወሰደው ሁሉን አቀፍ ዘመቻ በግጭት ምክንያት ከቀያቸው የተፈናቀሉ ከ25 ሺህ በላይ ዜጎች ወደ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ማድረጉን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የመከላከያ ኢንዶክትሪኔሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሜጀር ጀኔራል መሀመድ ተሰማ ሰሞነኛ ጉዳዮችን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ተከታዩን ብለዋል ፦
- በክልሉ የተፈጠረው የፀጥታ ችግር ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎች አቅም በላይ አልነበረም ሊከሰትም አይገባው ነበር።
- ችግሩ በተፈጠረበት ሰዓት መከላከያ የራሱ ተልዕኮ ላይ ነበር ሠራዊቱ ወደ ስፍራው በማቅናት የአከባቢውን ሰላምና ደህንነት የማስከበር ስራ በጀግንነት ተሰርቷል።
- መከላከያ ከገባ በኋላ በአጥፊዎች ላይ ህጋዊ እርምጃ በመውሰዱ አሁን በክልሉ ያለው ሁኔታ ወደ ቀድሞ ሰላማዊና መረጋጋት እንቅስቃሴ ተመልሷል።
- በማህበራዊ ሚዲያዎች “መካላከያ ቀድሞ ወደ ስፍራው አልደረሰም” በሚል እየተናፈሰ ያለው መረጃ ከእውነት የራቀ ነው።
- በክልሎች የፀጥታ ችግሮች ሲከሰቱ የማረጋጋት ግዴታ በዋናነት የክልልና የወረዳ የጸጥታ ኃይል ነው መከላከያ የራሱ ግዳጆች ቢኖሩትም ከክልሎቹ አቅም በላይ የሆነ የፀጥታ ችግር ሲያጋጥም አስፈላጊውን እርምጃ እየወሰደ ይገኛል።
- በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መከላከያ ግዳጅ እንደተሰጠው ከ150 ኪሎ ሜትር ውስጥ 50 ኪሎ ሜትሩን በእግሩ በመጓዝ በታጣቂዎች ላይ አስፈላጊውን እርምጃ ወስዷል። (ኢቲቪ)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TikvahFamilyBulen
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን ወረዳ ቲክቫህ አባላት ሚዲያዎች በወቅቱ መረጃ ይፋ ባለማድረጋቸው ቅር እንደተሰኙ ገልፀውልናል።
ሚዲያዎች ጳጉሜ ወር ውስጥ የነበረውን ጥቃት ከሳምንት በኃላ ይቆይተው ትላንት እየተቀባበሉት መመልከታቸውንም ተናግረዋል።
መረጃዎች በወቅቱ ህዝቡ ጋር መድረስ አለባቸው ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ሳይሆን ሁሉም ሚዲያ ዜጎችን በእኩል አይን አይተው በዜጎች ላይ የተፈጠረውን ማሳወቅ ፣ መንግስትም ችግሩን ለመፍታት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በቶሎ ማሳወቅ አለባቸው ብለዋል።
በአሁን ሰዓት ያሉበት አካባቢ ወደ ሰላም እየተመለሰ እንደሆነ ገልፀዋል።
ጳጉሜ ወር ውስጥ በአካባቢው ጥቃት እየተፈፀመ መሆኑን የገለፁልን አባላቶቻችን ወደ መደበኛ ስራቸው መመለሳቸው አሳውቀውናል።
PHOTO : FDRE DEFENSE FORCE
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን ወረዳ ቲክቫህ አባላት ሚዲያዎች በወቅቱ መረጃ ይፋ ባለማድረጋቸው ቅር እንደተሰኙ ገልፀውልናል።
ሚዲያዎች ጳጉሜ ወር ውስጥ የነበረውን ጥቃት ከሳምንት በኃላ ይቆይተው ትላንት እየተቀባበሉት መመልከታቸውንም ተናግረዋል።
መረጃዎች በወቅቱ ህዝቡ ጋር መድረስ አለባቸው ፣ በማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ ሳይሆን ሁሉም ሚዲያ ዜጎችን በእኩል አይን አይተው በዜጎች ላይ የተፈጠረውን ማሳወቅ ፣ መንግስትም ችግሩን ለመፍታት እየወሰደ ያለውን እርምጃ በቶሎ ማሳወቅ አለባቸው ብለዋል።
በአሁን ሰዓት ያሉበት አካባቢ ወደ ሰላም እየተመለሰ እንደሆነ ገልፀዋል።
ጳጉሜ ወር ውስጥ በአካባቢው ጥቃት እየተፈፀመ መሆኑን የገለፁልን አባላቶቻችን ወደ መደበኛ ስራቸው መመለሳቸው አሳውቀውናል።
PHOTO : FDRE DEFENSE FORCE
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአሶሳ ከተማ 243 ህገ-ወጥ የሽጉጥ ጥይት በቁጥጥር ስር ዋለ!
በክልሉ አሶሳ ከተማ 243 ህገ-ወጥ የሽጉጥ ጥይት የያዘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገለጸ።
ዛሬ መስከረም 7 የሸርቆሌ ወረዳ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ በአሶሳ ከተማ ወረዳ 1 ቀጠና 3 ከመነሀሪያ በስተጀርባ በሚገኝ አንድ መኝታ ቤት ከያዘው ክፍል ውስጥ 243 ፍሬ ህገ-ወጥ የሽጉጥ ጥይት ይዞ በመገኘቱ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።
የከተማ ፖሊስ ተጠርጣሪው ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈፀመው ለግል ጥቅም ለማዋል በማሰብ እንደሆነ ገልጾ ፣ በአሁኑ ሰዓት በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት እንደሆነ ተናግሯል፡፡
ምንጭ፦ የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በክልሉ አሶሳ ከተማ 243 ህገ-ወጥ የሽጉጥ ጥይት የያዘ ግለሰብ በቁጥጥር ስር መዋሉን ፖሊስ ገለጸ።
ዛሬ መስከረም 7 የሸርቆሌ ወረዳ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ በአሶሳ ከተማ ወረዳ 1 ቀጠና 3 ከመነሀሪያ በስተጀርባ በሚገኝ አንድ መኝታ ቤት ከያዘው ክፍል ውስጥ 243 ፍሬ ህገ-ወጥ የሽጉጥ ጥይት ይዞ በመገኘቱ በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጿል።
የከተማ ፖሊስ ተጠርጣሪው ህገ-ወጥ ድርጊቱን የፈፀመው ለግል ጥቅም ለማዋል በማሰብ እንደሆነ ገልጾ ፣ በአሁኑ ሰዓት በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተካሄደበት እንደሆነ ተናግሯል፡፡
ምንጭ፦ የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የመስከረም 7 የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦
የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 10,605
በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ - 689
ከበሽታው ያገገሙ - 420
ህይወታቸው ያለፈ - 15
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ - 10,605
በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ - 689
ከበሽታው ያገገሙ - 420
ህይወታቸው ያለፈ - 15
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
አቶ እስክንድር እና አቶ ስንታየሁ ወደቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተዘዋወሩ!
የባልደራስ ሊቀመንበር አቶ እስክንድር ነጋ እንዲሁም የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከዚህ ቀደም ታስረውበት ወደ ነበረው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት መዛወራቸውን ጠበቃቸው ሔኖክ አክሊሉ ለቢቢሲ (BBC) ገልፀዋል።
ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ ለBBC ከተናገሩት ፦
- ሁለቱ ተጠርጣሪዎች (አቶ እስክንድርና አቶ ስንታየሁ) ብቻ ሳይሆኑ ሌላ አንድ ግለሰብም ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተወስደዋል።
- ጳጉሜ 5/2012 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ላይ አቶ እስክንድር ላይ ክስ ተመስርቶ ነበር ፤ ፍርድ ቤት ክስ የቀረበባቸው በመሆኑ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ አዟል።
- በትናንትናው ዕለት መስከረም 06/2013 ዓ/ም ከነበሩበት የፌደራል ፖሊስ ጊዜያዊ ማቆያ ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት በተለምዶ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ሚባለው ተዘዋውረዋል።
- አቶ እስክንድር ከዚህ ቀደም ከስድስት ዓመታት በላይ በታሰሩበት ስፍራ እና ክፍል ዳግም መታሰራቸውን ተናግረዋል።
- አቶ አስክንድር ከሁለት ወራት በላይ ከቆዩበት ሌላ እስር ቤት ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከተዘዋወሩ በኋላ በተለምዶ ዋይት ሐውስ ወደ ሚባለው ክፍል አስገብተዋቸዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የባልደራስ ሊቀመንበር አቶ እስክንድር ነጋ እንዲሁም የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት አቶ ስንታየሁ ቸኮል ከዚህ ቀደም ታስረውበት ወደ ነበረው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት መዛወራቸውን ጠበቃቸው ሔኖክ አክሊሉ ለቢቢሲ (BBC) ገልፀዋል።
ጠበቃ ሔኖክ አክሊሉ ለBBC ከተናገሩት ፦
- ሁለቱ ተጠርጣሪዎች (አቶ እስክንድርና አቶ ስንታየሁ) ብቻ ሳይሆኑ ሌላ አንድ ግለሰብም ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተወስደዋል።
- ጳጉሜ 5/2012 ዓ.ም በነበረው የፍርድ ቤት ውሎ ላይ አቶ እስክንድር ላይ ክስ ተመስርቶ ነበር ፤ ፍርድ ቤት ክስ የቀረበባቸው በመሆኑ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ አዟል።
- በትናንትናው ዕለት መስከረም 06/2013 ዓ/ም ከነበሩበት የፌደራል ፖሊስ ጊዜያዊ ማቆያ ወደ አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት በተለምዶ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ወደ ሚባለው ተዘዋውረዋል።
- አቶ እስክንድር ከዚህ ቀደም ከስድስት ዓመታት በላይ በታሰሩበት ስፍራ እና ክፍል ዳግም መታሰራቸውን ተናግረዋል።
- አቶ አስክንድር ከሁለት ወራት በላይ ከቆዩበት ሌላ እስር ቤት ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከተዘዋወሩ በኋላ በተለምዶ ዋይት ሐውስ ወደ ሚባለው ክፍል አስገብተዋቸዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ ጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ እንደሚጀመር አስታወቁ! በዛሬው እለት ከሶማሌ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ጋር ቆይታ ያደረጉት ፣ የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል ዋና አዛዥ ረ/ኮሚሽነር መሀመድ አህመድ በሁሉም የሶማሌ ክልል አከባቢዎች ጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ዘመቻ እንደሚጀመር እና ከአሁን በኋላ ለአንድም የሲቪል ማህበረሰብ ትጥቅ እንደማይፈቀድላቸው አስታወቀዋል። በተጨማሪ…
በሶማሌ ክልል የጦር መሳሪያዎችን የመሰብሰብ ስራ ተጀመረ!
የሶማሌ ክልል መንግሥት ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎችና የሚመለከታቸው አካላት በስተቀር በሌሎች የክልሉ ነዋሪዎች እጅ የሚገኙ የጦር መሳሪያዎችን መሰብሰብ ጀምሯል።
አሁን በተመረጠ ሁኔታ ተግባራዊ መሆን የጀመረው ይህ የጦር መሳሪያ ስብሰባ ወደፊት በሁሉም የክልሉ ዞኖች ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል።
የሱማሌ ክልል ፍትህና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱላሂ መሃመድ አብዲ ለቪኦኤ (ጋዜጠኛ አዲስ ቸኮል) ተከታዩን መረጃ ሰጥተዋል ፦
- የክልሉ መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው በጎሳ ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ በመሆኑ ነው።
- ባለፈው ሳምንት በጎሳ ግጭት የተነሳ የታጠቁ ሰዎች በቱሉ ጉሌድ ወረዳ 7 ሰዎች ላይ ግድያ ፈፅመዋል።
- አሁን ላይ በቱሉ ጉሌድ ወረዳና እና ኦሮሚያ ክልል ስር በሚገኘው አጎራባች የጭናክሰን ወረዳ ላይ ትጥቅ የማስፈታቱ ስራ በሁለቱ ክልሎች ትብብር እየተሰራ ነው።
- እስካሁን ከምን ያህል ሰዎች ትጥቅ ማስፈታት እንደተቻለ ባይገለፅም አብዛኞቹ AK 47 (በተለምዶ ክላሽንኮቭ) የጦር መሳሪያ ናቸው። ነገር ግን መትረየስን ጨምሮ በግለሰቦች እጅ መኖር የሌለባቸው ከባድ መሳሪያዎች በማህበረሰቡ ውስጥ ይገኛሉ።
- አሁን በቱሉ ጉሌድ ወረዳ በ4 ቀበሌዎች የተጀመረው ትጥቅ የማስፈታት ስራ ወደፊትም ህዝቡን የማሳመን ስራ እየተሰራ በሁሉም የክልሉ ዞኖች ይተገበራል።
- ድንበር አካባቢ የሚካሄዱ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ንግድ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሶማሌ ክልል መንግሥት ከክልሉ የፀጥታ ኃይሎችና የሚመለከታቸው አካላት በስተቀር በሌሎች የክልሉ ነዋሪዎች እጅ የሚገኙ የጦር መሳሪያዎችን መሰብሰብ ጀምሯል።
አሁን በተመረጠ ሁኔታ ተግባራዊ መሆን የጀመረው ይህ የጦር መሳሪያ ስብሰባ ወደፊት በሁሉም የክልሉ ዞኖች ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልጿል።
የሱማሌ ክልል ፍትህና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱላሂ መሃመድ አብዲ ለቪኦኤ (ጋዜጠኛ አዲስ ቸኮል) ተከታዩን መረጃ ሰጥተዋል ፦
- የክልሉ መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው በጎሳ ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ በመሆኑ ነው።
- ባለፈው ሳምንት በጎሳ ግጭት የተነሳ የታጠቁ ሰዎች በቱሉ ጉሌድ ወረዳ 7 ሰዎች ላይ ግድያ ፈፅመዋል።
- አሁን ላይ በቱሉ ጉሌድ ወረዳና እና ኦሮሚያ ክልል ስር በሚገኘው አጎራባች የጭናክሰን ወረዳ ላይ ትጥቅ የማስፈታቱ ስራ በሁለቱ ክልሎች ትብብር እየተሰራ ነው።
- እስካሁን ከምን ያህል ሰዎች ትጥቅ ማስፈታት እንደተቻለ ባይገለፅም አብዛኞቹ AK 47 (በተለምዶ ክላሽንኮቭ) የጦር መሳሪያ ናቸው። ነገር ግን መትረየስን ጨምሮ በግለሰቦች እጅ መኖር የሌለባቸው ከባድ መሳሪያዎች በማህበረሰቡ ውስጥ ይገኛሉ።
- አሁን በቱሉ ጉሌድ ወረዳ በ4 ቀበሌዎች የተጀመረው ትጥቅ የማስፈታት ስራ ወደፊትም ህዝቡን የማሳመን ስራ እየተሰራ በሁሉም የክልሉ ዞኖች ይተገበራል።
- ድንበር አካባቢ የሚካሄዱ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ንግድ ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገ ይገኛል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአስሩ ክልሎች እና የሁለቱ ከተማ አስተዳደሮች ወቅታዊ የኮሮና ቫይረስ (COVID-19) ስርጭት ቁጥራዊ መረጃ ፦
#Afar
በቫይረሱ የተያዙ - 1,408
ያገገሙ - 231
#Amhara
በቫይረሱ የተያዙ - 3,388
ህይወታቸው ያለፈ - 34
ያገገሙ - 2,224
#BenishangulGumuz
በቫይረሱ የተያዙ - 1138
ያገገሙ - 382
#Harari
በቫይረሱ የተያዙ - 1,505
ህይወታቸው ያለፈ - 27
ያገገሙ - 693
#Oromia
በቫይረሱ የተያዙ - 9,415
ህይወታቸው ያለፈ - 63
ያገገሙ - 4,415
#SNNPRS
በቫይረሱ የተያዙ - 2,211
ህይወታቸው ያለፈ - 16
ያገገሙ - 1,656
#AddisAbaba
በቫይረሱ የተያዙ - 36,939
ህይወታቸው ያለፈ ድምር - አልተገለፀም
ያገገሙ ሰዎች ድምር - አልተገለፀም
#Tigray
በቫይረሱ የተያዙ - 5,403
ህይወታቸው ያለፈ - 27
ያገገሙ - 4,275
#Somali
በቫይረሱ የተያዙ - 1,375
ህይወታቸው ያለፈ - 26
ያገገሙ - 1,076
#Sidama
በቫይረሱ የተያዙ - 1,897
ህይወታቸው ያለፈ - 22
ያገገሙ - 1,449
#DireDawa
በቫይረሱ የተያዙ - 1,246
ህይወታቸው ያለፈ - 21
ያገገሙ - 1,041
#Gambela
በቫይረሱ የተያዙ - 954
ያገገሙ - 506
ህይወታቸው ያለፈ - አራት በኮሮና ተቋም፣ አምስት ከአስክሬን፣ አስራ አንድ ላብራቶሪ ውጤት በመጠበቅ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#Afar
በቫይረሱ የተያዙ - 1,408
ያገገሙ - 231
#Amhara
በቫይረሱ የተያዙ - 3,388
ህይወታቸው ያለፈ - 34
ያገገሙ - 2,224
#BenishangulGumuz
በቫይረሱ የተያዙ - 1138
ያገገሙ - 382
#Harari
በቫይረሱ የተያዙ - 1,505
ህይወታቸው ያለፈ - 27
ያገገሙ - 693
#Oromia
በቫይረሱ የተያዙ - 9,415
ህይወታቸው ያለፈ - 63
ያገገሙ - 4,415
#SNNPRS
በቫይረሱ የተያዙ - 2,211
ህይወታቸው ያለፈ - 16
ያገገሙ - 1,656
#AddisAbaba
በቫይረሱ የተያዙ - 36,939
ህይወታቸው ያለፈ ድምር - አልተገለፀም
ያገገሙ ሰዎች ድምር - አልተገለፀም
#Tigray
በቫይረሱ የተያዙ - 5,403
ህይወታቸው ያለፈ - 27
ያገገሙ - 4,275
#Somali
በቫይረሱ የተያዙ - 1,375
ህይወታቸው ያለፈ - 26
ያገገሙ - 1,076
#Sidama
በቫይረሱ የተያዙ - 1,897
ህይወታቸው ያለፈ - 22
ያገገሙ - 1,449
#DireDawa
በቫይረሱ የተያዙ - 1,246
ህይወታቸው ያለፈ - 21
ያገገሙ - 1,041
#Gambela
በቫይረሱ የተያዙ - 954
ያገገሙ - 506
ህይወታቸው ያለፈ - አራት በኮሮና ተቋም፣ አምስት ከአስክሬን፣ አስራ አንድ ላብራቶሪ ውጤት በመጠበቅ
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስቸኳይ ስብሰባ እየተካሄደ ነው!
የኢፌዴሪ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባ እየተካሄደ ይገኛል። የመወያያ አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው ፦
1. የም/ቤቱን 5ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣
2. የጤና ሚኒስቴር አገራዊ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምላሽና ቀጣይ እርምጃዎች በተመለከተ በሚያቀርበው ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፍ፣
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢፌዴሪ 5ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 3ኛ አስቸኳይ ስብሰባ እየተካሄደ ይገኛል። የመወያያ አጀንዳዎች የሚከተሉት ናቸው ፦
1. የም/ቤቱን 5ኛ አመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ስብሰባ ቃለ ጉባኤ መርምሮ ማጽደቅ፣
2. የጤና ሚኒስቴር አገራዊ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምላሽና ቀጣይ እርምጃዎች በተመለከተ በሚያቀርበው ሪፖርት ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ማሳለፍ፣
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮሮና ቫይረስ ምክንያት ተራዝሞ የነበረው 'የ2012 ሀገራዊ ምርጫ' አሁን ላይ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቶ ማካሄድ እንደሚቻል የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክረ ሀሳብ አቅርቧል።
በጤና ሚኒስቴር በቀረበው መክረ ሀሳብ ላይ የምክር ቤቱ አባላት አስተያየት እየሰጡ ሲሆን ፥ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጤና ሚኒስቴር በቀረበው መክረ ሀሳብ ላይ የምክር ቤቱ አባላት አስተያየት እየሰጡ ሲሆን ፥ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ውሳኔ ያሳልፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጤና ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶችን መክፈት ይቻላል የሚል ምክረ ሀሳብ አቀረበ!
የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች በመተግበር እንደየአከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ትምህርት ቤቶችን መክፈት እንደሚቻል የጤና ሚኒስቴር ምክረ ሀሳብ ማቅረቡን ኢቲቪ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች በመተግበር እንደየአከባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ትምህርት ቤቶችን መክፈት እንደሚቻል የጤና ሚኒስቴር ምክረ ሀሳብ ማቅረቡን ኢቲቪ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ተጨማሪ መረጃ ፦
- ትምህርት ከመጀመሩ በፊት የዓለም ጤና ድርጅት ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች በአግባቡ መከናወናቸው የሚያረጋግጥ ግብረ ኃይል በየትምህርት ቤቶቹ ሊቋቋም እንደሚገባ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።
- የሰዎችን ቁጥር በመመጠን እና የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መስፈርቶችን በመተግበር ስብሰባ ፣ ሲኒማ ፣ ቲያትር ፣ የስፖርት ዝግጅቶች ፣ ማህበራዊና ሐይማኖታዊ በዓላት፣ የአደባባይ በዓላት፣ ሊፈቀዱ እንደሚገባ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
- ጤና ሚኒስቴር በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ በመላ ሀገሪቱ አስገዳጅ ሊሆን ይገባል ብሏል።
- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በጤና ሚኒስቴር በቀረበው ምክረ ሃሳብ ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ በዋነት ለሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ቋሚ ኮሚቴ እና ለህግ ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የውሳኔ ሃሳብ እንዲያቀርቡ መርቷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- ትምህርት ከመጀመሩ በፊት የዓለም ጤና ድርጅት ያስቀመጣቸውን መስፈርቶች በአግባቡ መከናወናቸው የሚያረጋግጥ ግብረ ኃይል በየትምህርት ቤቶቹ ሊቋቋም እንደሚገባ ዶ/ር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል።
- የሰዎችን ቁጥር በመመጠን እና የኮሮና ቫይረስ መከላከያ መስፈርቶችን በመተግበር ስብሰባ ፣ ሲኒማ ፣ ቲያትር ፣ የስፖርት ዝግጅቶች ፣ ማህበራዊና ሐይማኖታዊ በዓላት፣ የአደባባይ በዓላት፣ ሊፈቀዱ እንደሚገባ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል።
- ጤና ሚኒስቴር በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የአፍ እና የአፍንጫ መሸፈኛ ማድረግ በመላ ሀገሪቱ አስገዳጅ ሊሆን ይገባል ብሏል።
- የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ በጤና ሚኒስቴር በቀረበው ምክረ ሃሳብ ላይ ውይይት ካደረገ በኋላ በዋነት ለሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ቋሚ ኮሚቴ እና ለህግ ፣ ፍትህና ዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የውሳኔ ሃሳብ እንዲያቀርቡ መርቷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia