በሀዋሳ ከተማ አስተዳደር የመሀል ክ/ከተማ የኮቪድ 19 የህክምና ማዕከል በህክምና ላይ ሴት ልጅ የተገላገለች እናት ዛሬ ከማዕከሉ ሙሉ ለሙሉ አገግማ መውጣቷን የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ይርዳቸው አኒቶ አስታውቀዋል።
እንደ ስራ አስኪያጁ ገለፃ ከሆነ በማዕከሉ ክትትል ሲደረግላት የነበረች እናት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር ከቫይረሱ ነፃ የሆነች ሴት ልጅ የተገላገለችው።
እናቲቱ በቆይታዋም ከማዕከሉ የህክምና ባለሙያዎች ተገቢው ክትትል ሲደረግላት ቆይቶ በዛሬ ዕለት ሙሉ ለሙሉ ማገገሟ በመረጋገጡ ወደ ቤቷ መመለስ እንደቻለች ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
በዚህም የማዕከሉ የህክምና ባለሙያዎችና አመራሩ ለእናቲቱ እና ለጨቅላዋ አሸኛኘት እንዳደረጉላቸው አቶ ይርዳቸው ገልፀዋል።
ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ፣📸ዶ/ር ሀኒባል አበራ (Tikvah Family)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እንደ ስራ አስኪያጁ ገለፃ ከሆነ በማዕከሉ ክትትል ሲደረግላት የነበረች እናት ባሳለፍነው ሳምንት ነበር ከቫይረሱ ነፃ የሆነች ሴት ልጅ የተገላገለችው።
እናቲቱ በቆይታዋም ከማዕከሉ የህክምና ባለሙያዎች ተገቢው ክትትል ሲደረግላት ቆይቶ በዛሬ ዕለት ሙሉ ለሙሉ ማገገሟ በመረጋገጡ ወደ ቤቷ መመለስ እንደቻለች ስራ አስኪያጁ ተናግረዋል።
በዚህም የማዕከሉ የህክምና ባለሙያዎችና አመራሩ ለእናቲቱ እና ለጨቅላዋ አሸኛኘት እንዳደረጉላቸው አቶ ይርዳቸው ገልፀዋል።
ምንጭ፦ የሀዋሳ ከተማ ኮሚኒኬሽን ቢሮ፣📸ዶ/ር ሀኒባል አበራ (Tikvah Family)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር የኮሮና ክትባት ተከተቡ!
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑት ሰርጌይ ሾይጉ ሃገራቸው በማዘጋጀት ላይ ያለችውን 'ስፑትኒክ ቪ' የኮሮና ቫይረስ ክትባት መከተባቸውን አል አይን RuNews24 ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ 'ስፑትኒክ ቪ'ን የተከተቡት የክትባቱ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ የሙከራ ሂደቶች አበረታች ውጤቶችን አስገኝተዋል በተባለበት በትላንትናው ዕለት ነው፡፡
ሙከራውን የተመለከቱ የጥናት ውጤቶች ትናንት “ላንሴት” በተሰኘው ዓለም አቀፍ የህክምና ጉዳዮች መጽሄት ላይ ወጥተዋል፡፡
'ስፑትኒክ ቪ' ክትባት እምብዛም የጎንዮሽ ጉዳትን ሳያስከትል ሰውነት ቫይረሱን ለመከላከል የሚያስችልበትን ጸረ እንግዳ አካል (አንቲቦዲ) ለማዘጋጀት ስለማስቻሉም ነው ጥናታዊ ጽሁፎቹ ያመለከቱት፡፡
በመጀመሪያ ፍላጎቱ ያላቸው የሃገሪቱ ጦር የህክምና አባላትና የጦር መኮንኖች ክትባቱን በሙሉ ፍቃደኝነት እንደሚወስዱ የተናገሩት ሚኒስትሩ በቀጣይ ሁሉም የጦሩ አባላት እንደሚከተቡ መግለፃቸውን ከአል አይን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሩሲያ መከላከያ ሚኒስትር የሆኑት ሰርጌይ ሾይጉ ሃገራቸው በማዘጋጀት ላይ ያለችውን 'ስፑትኒክ ቪ' የኮሮና ቫይረስ ክትባት መከተባቸውን አል አይን RuNews24 ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
ሚኒስትሩ 'ስፑትኒክ ቪ'ን የተከተቡት የክትባቱ የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ደረጃ የሙከራ ሂደቶች አበረታች ውጤቶችን አስገኝተዋል በተባለበት በትላንትናው ዕለት ነው፡፡
ሙከራውን የተመለከቱ የጥናት ውጤቶች ትናንት “ላንሴት” በተሰኘው ዓለም አቀፍ የህክምና ጉዳዮች መጽሄት ላይ ወጥተዋል፡፡
'ስፑትኒክ ቪ' ክትባት እምብዛም የጎንዮሽ ጉዳትን ሳያስከትል ሰውነት ቫይረሱን ለመከላከል የሚያስችልበትን ጸረ እንግዳ አካል (አንቲቦዲ) ለማዘጋጀት ስለማስቻሉም ነው ጥናታዊ ጽሁፎቹ ያመለከቱት፡፡
በመጀመሪያ ፍላጎቱ ያላቸው የሃገሪቱ ጦር የህክምና አባላትና የጦር መኮንኖች ክትባቱን በሙሉ ፍቃደኝነት እንደሚወስዱ የተናገሩት ሚኒስትሩ በቀጣይ ሁሉም የጦሩ አባላት እንደሚከተቡ መግለፃቸውን ከአል አይን ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse
በሀገራችን የተደረገው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ምርመራ ከ1 ሚልዮን በላይ ሆኗል፤ ይህን ተከትሎም የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሚሰሩትን ሁሉንም የጤና ባለሙያዎች እና ሰራተኞች በተለይም የናሙና ሰብሳቢዎች ፣ የላብራቶሪ ቴክኒሻኖች ፣ ፈጣን የምላሽ ቡድኖች ፣ የሎጂስቲክስ ቡድኖች ፣ ሾፌሮች ፣ አስተባባሪዎችና በሁሉም ላቦራቶሪና አገልግሎት መስጫ የሚገኙትን ሀላፊዎችን አመስግነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ህብረተሰቡም ለዚህ ውጤት ላደረገው አስተዋጽዎና ስርጭቱን ለማስቆም የአፍና አፍንጫ ጭምብል በማድረግ ማህበራዊ ርቀትን እና የእጅ ንፅህናን በመጠበቅ በሂደቱ እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ አመስግነዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሀገራችን የተደረገው የኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ምርመራ ከ1 ሚልዮን በላይ ሆኗል፤ ይህን ተከትሎም የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል።
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሚሰሩትን ሁሉንም የጤና ባለሙያዎች እና ሰራተኞች በተለይም የናሙና ሰብሳቢዎች ፣ የላብራቶሪ ቴክኒሻኖች ፣ ፈጣን የምላሽ ቡድኖች ፣ የሎጂስቲክስ ቡድኖች ፣ ሾፌሮች ፣ አስተባባሪዎችና በሁሉም ላቦራቶሪና አገልግሎት መስጫ የሚገኙትን ሀላፊዎችን አመስግነዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ህብረተሰቡም ለዚህ ውጤት ላደረገው አስተዋጽዎና ስርጭቱን ለማስቆም የአፍና አፍንጫ ጭምብል በማድረግ ማህበራዊ ርቀትን እና የእጅ ንፅህናን በመጠበቅ በሂደቱ እያደረገ ለሚገኘው ድጋፍ አመስግነዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን መከሰትን ተከትሎ ተጥሎ የነበረው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ በድጋሜ ሳይታደስ ግዜው አብቅቷል!
አዋጁ እንዳይራዘምና በዚህ ምትክም ነባር አዋጆችን እና እነሱን መሠረት አድርገው የሚወጡ አዳዲስ መመርያዎችን በመጠቀም የቫይረሱ ሥርጭትን ለመቆጣጠር መታቀዱን ሪፖርተር ጋዜጣ ከዚህ በፊት ጠቁሞ ነበር።
መጋቢት 30 ታውጆ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተወሰነለት የአምስት ወራት ዕድሜ ነሐሴ 30 እኩለ ለሊት ተጠናቋል።
Via Elias Meseret (Associated Press)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዋጁ እንዳይራዘምና በዚህ ምትክም ነባር አዋጆችን እና እነሱን መሠረት አድርገው የሚወጡ አዳዲስ መመርያዎችን በመጠቀም የቫይረሱ ሥርጭትን ለመቆጣጠር መታቀዱን ሪፖርተር ጋዜጣ ከዚህ በፊት ጠቁሞ ነበር።
መጋቢት 30 ታውጆ ተግባራዊ ሲደረግ የቆየው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የተወሰነለት የአምስት ወራት ዕድሜ ነሐሴ 30 እኩለ ለሊት ተጠናቋል።
Via Elias Meseret (Associated Press)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ልፋታችንን ከንቱ አታድርጉብን!!
(በዶ/ር ኃይለልዑል መኮንን - የጤና ባለሞያ)
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ዛሬ በትራንስፖርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተዘጋጀ "ከጳጉሜ እስከ ጳጉሜ እንደርሳለን!" ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሰዎችን ነው።
በአንድ በኩል ጤና ሚንስቴር አካላዊ እርቀታችንን እንጠብቅ፣ አስፈላጊ ካልሆነ ከቤት አንውጣ እያለ በዚህ በኩል ደግሞ ትራንስፖርት ሚንስቴር እንደዚህ ያለውን መርሃግብር በአደባባይ ያከናውናል።
የእኛን ልፋት ከንቱ አታድርጉብን ፤ እናንተ ካልተጠነቀቃችሁ የኛ መድከም በከንቱ ይሆናል። የዛሬው ድርጊት ነገ ዋጋ እንዳያስከፍለን እባካችሁ እንጠንቀቅ ፣ ምክራችንን ተግባራዊ አድርጉ።
ዛሬም ኮሮና ቫይረስ ገዳይ ነው!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(በዶ/ር ኃይለልዑል መኮንን - የጤና ባለሞያ)
በምስሉ ላይ የምትመለከቱት ዛሬ በትራንስፖርት ሚኒስቴር አማካኝነት የተዘጋጀ "ከጳጉሜ እስከ ጳጉሜ እንደርሳለን!" ሀገር አቀፍ የመንገድ ትራፊክ ደህንነት ንቅናቄ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሰዎችን ነው።
በአንድ በኩል ጤና ሚንስቴር አካላዊ እርቀታችንን እንጠብቅ፣ አስፈላጊ ካልሆነ ከቤት አንውጣ እያለ በዚህ በኩል ደግሞ ትራንስፖርት ሚንስቴር እንደዚህ ያለውን መርሃግብር በአደባባይ ያከናውናል።
የእኛን ልፋት ከንቱ አታድርጉብን ፤ እናንተ ካልተጠነቀቃችሁ የኛ መድከም በከንቱ ይሆናል። የዛሬው ድርጊት ነገ ዋጋ እንዳያስከፍለን እባካችሁ እንጠንቀቅ ፣ ምክራችንን ተግባራዊ አድርጉ።
ዛሬም ኮሮና ቫይረስ ገዳይ ነው!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrDerejeDuguma
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር #ለኢዜአ አስታውቀዋል።
ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።
'የመመርመሪያ ኪቱን ሀገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል' ያሉት ዶክተር ደረጀ ፣ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እንደሚዳረስ ተናግረዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጤና ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር #ለኢዜአ አስታውቀዋል።
ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።
ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።
'የመመርመሪያ ኪቱን ሀገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል' ያሉት ዶክተር ደረጀ ፣ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት እንደሚዳረስ ተናግረዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Hawassa
በሐዋሳ ከተማ ከ30 ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥር አዲስ ኢንደስትሪ ፓርክ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሀግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
ይህ ፓርክ በዓለም ገበያ ከፍተኛ ተፈላጊነት ያለውን የጨርቃ ጨርቅ ምርት የሚያመርት ሲሆን ይህንንም ከሠላሳ ዓመታት በላይ እድሜ ባስቆጠረው ከሀዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ተቋም ጋር በመሆን 3 የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ሼር ሆልደር ሆነው ነው የሚያሠሩት፡፡
ከ2 ቢልየን ብር ወጪ የሚደረግበት ፓርኩ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፖርክ ያለውን የሥራ ጫና በመካፈል ከፍተኛ ምርት አምርቶ 90 በመቶ የሚሆን ምርት ለዉጭ ገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል ተብሏል፡፡
ከ3 ወር በኃላ ሥራው የሚጀመረው ይህ ፖርክ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የፌዴራል ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ምስጋና በተገኙበት የግንባታ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል።
"ሲኖማ ኢንጀነሪንግ" የተሠኘ የቻይና ካምፓኒ ሲሆን ግንባታውን የሚያከናውነው ወደ 14 የሚጠጉ ሼዶችን ገንብቶ ለጠናቅቅ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚጠይቅ ተገልጿል፡፡
ምንጭ፦ ሲዳማ ሚዲያ ኔትዎርክ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሐዋሳ ከተማ ከ30 ሺ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የስራ እድል የሚፈጥር አዲስ ኢንደስትሪ ፓርክ ግንባታ ማስጀመሪያ መርሀግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
ይህ ፓርክ በዓለም ገበያ ከፍተኛ ተፈላጊነት ያለውን የጨርቃ ጨርቅ ምርት የሚያመርት ሲሆን ይህንንም ከሠላሳ ዓመታት በላይ እድሜ ባስቆጠረው ከሀዋሳ ጨርቃ ጨርቅ ተቋም ጋር በመሆን 3 የሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ሼር ሆልደር ሆነው ነው የሚያሠሩት፡፡
ከ2 ቢልየን ብር ወጪ የሚደረግበት ፓርኩ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፖርክ ያለውን የሥራ ጫና በመካፈል ከፍተኛ ምርት አምርቶ 90 በመቶ የሚሆን ምርት ለዉጭ ገበያ በማቅረብ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ያስገኛል ተብሏል፡፡
ከ3 ወር በኃላ ሥራው የሚጀመረው ይህ ፖርክ የሲዳማ ብሔራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ እና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የፌዴራል ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ምስጋና በተገኙበት የግንባታ ማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሂዷል።
"ሲኖማ ኢንጀነሪንግ" የተሠኘ የቻይና ካምፓኒ ሲሆን ግንባታውን የሚያከናውነው ወደ 14 የሚጠጉ ሼዶችን ገንብቶ ለጠናቅቅ ከ400 ሚሊየን ብር በላይ እንደሚጠይቅ ተገልጿል፡፡
ምንጭ፦ ሲዳማ ሚዲያ ኔትዎርክ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#መሸፈን
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የፖርቹጋልና ክሮሺያን ጨዋታ ሲመለከት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ (ማስክ) እንዲያደርግ ሲታዘዝ 😷
ማስክ ለጤናችን!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ክርስቲያኖ ሮናልዶ የፖርቹጋልና ክሮሺያን ጨዋታ ሲመለከት የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ (ማስክ) እንዲያደርግ ሲታዘዝ 😷
ማስክ ለጤናችን!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መጠናቀቅ #1
በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ሲባል በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው በከፊል የመጫን ዕገዳ ከዛሬ ጀምሮ መነሳቱ ተገልጿል።
የፌደራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን የአዋጁ ጊዜ መጠናቀቁን በማስመልከት ዕገዳው የተነሳ መሆኑን ዛሬ ለአማራ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።
ከዛሬ ጀምሮ ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ ተሽከርካሪዎች በከፊል የመጫን ዕገዳው በመነሳቱ በወንበራቸው ልክ በመጫን ተጠቃሚዎችን 'በመደበኛው ታሪፍ' የሚያስከፍሉ ይሆናል።
አሽከርካሪዎች ፣ ረዳቶች እና ተገልጋዮች የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አስገዳጅ መሆኑን በመገንዘብ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአማራ ክልል የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ሲባል በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ላይ የተጣለው በከፊል የመጫን ዕገዳ ከዛሬ ጀምሮ መነሳቱ ተገልጿል።
የፌደራል ትራንስፖርት ባለሥልጣን የአዋጁ ጊዜ መጠናቀቁን በማስመልከት ዕገዳው የተነሳ መሆኑን ዛሬ ለአማራ ክልል መንገድና ትራንስፖርት ቢሮው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል።
ከዛሬ ጀምሮ ማንኛውም የሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጭ ተሽከርካሪዎች በከፊል የመጫን ዕገዳው በመነሳቱ በወንበራቸው ልክ በመጫን ተጠቃሚዎችን 'በመደበኛው ታሪፍ' የሚያስከፍሉ ይሆናል።
አሽከርካሪዎች ፣ ረዳቶች እና ተገልጋዮች የአፍ እና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ አስገዳጅ መሆኑን በመገንዘብ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጳጉሜ 1/2012 ዓ/ም
የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መረጃዎች #1፦
#Somali
በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 769 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 7 ሰዎች በኮቪድ-19 መያቸው ተረጋግጧል።
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 542 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 22 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በቫይረሱ የተያዙት፦
- 5 ከአሶሳ ከተማ መናኸሪያ
- 7 ከጾሬ ስደተኛ መጠለያ
- 1 ከማኦ ኮሞ ጉራስምቦላ ስደተኛ መጠለያ
- 6 ከደቡስ ኬላ
- 3 ከሸርቆሌ ስድተኛ መጠለያ
#Amhara
በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 7,802 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 84 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል (ከባህር ዳር)
በቫይረሱ ከተያዙት መካከል፦
- 23 ከሰ/ሸዋ ዞን
- 21 ከሰ/ወሎ ዞን
- 13 ከጎንደር ከተማ
- 9 ከባህር ዳር ከተማ
- 6 ከምዕ/ጎንደር ዞን
- 6 ከደ/ጎንደር ዞን ይገኙበታል።
#Tigray
በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1,957 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 41 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 31 ሰዎች ከማህበረሰቡ የተገኙ ናቸው።
#Oromia
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 4,022 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 506 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በቫይረሱ ከተያዙት መካከል ፦
- 269 ከምስራቅ ሸዋ
- 51 ከዱከም ከተማ
- 46 ደ/ምዕ/ሸዋ
- 28 ከፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን
- 25 ከሰሜን ሸዋ
- 20 ከሰበታ ከተማ
- 13 ከሞጆ ከተማ
- 10 ከምስራቅ ሀረርጌ
- 8 ከአምቦ ከተማ
- 8 ከቢሾፍቱ ከተማ ይገኙበታል።
@tikvahethiopiaBOT
የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መረጃዎች #1፦
#Somali
በሱማሌ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 769 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 7 ሰዎች በኮቪድ-19 መያቸው ተረጋግጧል።
#BenishangulGumuz
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 542 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 22 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በቫይረሱ የተያዙት፦
- 5 ከአሶሳ ከተማ መናኸሪያ
- 7 ከጾሬ ስደተኛ መጠለያ
- 1 ከማኦ ኮሞ ጉራስምቦላ ስደተኛ መጠለያ
- 6 ከደቡስ ኬላ
- 3 ከሸርቆሌ ስድተኛ መጠለያ
#Amhara
በአማራ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት 7,802 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 84 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። የአንድ ሰው ህይወት አልፏል (ከባህር ዳር)
በቫይረሱ ከተያዙት መካከል፦
- 23 ከሰ/ሸዋ ዞን
- 21 ከሰ/ወሎ ዞን
- 13 ከጎንደር ከተማ
- 9 ከባህር ዳር ከተማ
- 6 ከምዕ/ጎንደር ዞን
- 6 ከደ/ጎንደር ዞን ይገኙበታል።
#Tigray
በትግራይ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 1,957 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 41 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ ከተያዙት መካከል 31 ሰዎች ከማህበረሰቡ የተገኙ ናቸው።
#Oromia
በኦሮሚያ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 4,022 የላብራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን 506 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በቫይረሱ ከተያዙት መካከል ፦
- 269 ከምስራቅ ሸዋ
- 51 ከዱከም ከተማ
- 46 ደ/ምዕ/ሸዋ
- 28 ከፊንፊኔ ዙሪያ ልዩ ዞን
- 25 ከሰሜን ሸዋ
- 20 ከሰበታ ከተማ
- 13 ከሞጆ ከተማ
- 10 ከምስራቅ ሀረርጌ
- 8 ከአምቦ ከተማ
- 8 ከቢሾፍቱ ከተማ ይገኙበታል።
@tikvahethiopiaBOT
በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ሟቾች ቁጥር ከ900 አለፈ!
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 25,158 የላብራቶሪ ምርመራ 1,206 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ21 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 531 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 58,672 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 918 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 21,307 ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገው 25,158 የላብራቶሪ ምርመራ 1,206 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ሲረጋገጥ የ21 ሰዎች ህይወት አልፏል። በተጨማሪ በትላንትናው ዕለት 531 ሰዎች አገግመዋል።
በአጠቃላይ በሀገራችን በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 58,672 የደረሱ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 918 ደርሷል ፤ ከበሽታው ያገገሙ አጠቃላይ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 21,307 ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጳጉሜ 1/2012 ዓ/ም
የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መረጃዎች #2፦
#SNNPRS
በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2,401 የላብራቶሪ ምርመራ ሰላሳ ሰባት (37) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል (ከወላይታ ዞን - በህክምና ማዕከል የነበሩ የ80 ዓመት ወንድ)
በቫይረሱ የተያዙት፡-
- ከጋሞ ዞን 9 (6 ከጋጮባባ ፣2 ከምዕራብ አባያ እና 1 ከቁጫ)፣
- ከዳውሮ ዞን 7 (6 ከማረቃ እና 1 ከተርጫ ከተማ)፣
- ከወላይታ ዞን 7 (2 ከሶዶ ዙሪያ፣ 2 ከአረካ ከተማ፣ 1 ከሶዶ ከተማ ፣ 1 ከገሱባ እና 1 ከኪንዶ ኮይሻ )፣
- ከጌዴኦ ዞን 5 ( 3 ከጨሉቅቱ፣ 1 ከዲላ ከተማ እና 1 ከኮቾሬ)፣
- ከሃዲያ ዞን 3 ( 3ቱም ከሾኔ ከተማ)፣
- ከከምባታ ጠምባሮ ዞን 3 ( 3ቱም ከዱራሜ ከተማ)፣
- ከቤንች ሸኮ ዞን 2 ( 2ቱም ከሸኮ ወረዳ) ፣
- ከኮንሶ ዞን 1 ( ከካራት ዙሪያ) ናቸው።
#DireDawa
ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 375 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 38 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሁሉም ሰዎች ናሙናቸው ከማህበረሰቡ ውስጥ የተሰበሰበ ነው።
@tikvahethiopiaBOT
የኢትዮጵያ የኮቪድ-19 መረጃዎች #2፦
#SNNPRS
በደቡብ ክልል ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2,401 የላብራቶሪ ምርመራ ሰላሳ ሰባት (37) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል፤ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል (ከወላይታ ዞን - በህክምና ማዕከል የነበሩ የ80 ዓመት ወንድ)
በቫይረሱ የተያዙት፡-
- ከጋሞ ዞን 9 (6 ከጋጮባባ ፣2 ከምዕራብ አባያ እና 1 ከቁጫ)፣
- ከዳውሮ ዞን 7 (6 ከማረቃ እና 1 ከተርጫ ከተማ)፣
- ከወላይታ ዞን 7 (2 ከሶዶ ዙሪያ፣ 2 ከአረካ ከተማ፣ 1 ከሶዶ ከተማ ፣ 1 ከገሱባ እና 1 ከኪንዶ ኮይሻ )፣
- ከጌዴኦ ዞን 5 ( 3 ከጨሉቅቱ፣ 1 ከዲላ ከተማ እና 1 ከኮቾሬ)፣
- ከሃዲያ ዞን 3 ( 3ቱም ከሾኔ ከተማ)፣
- ከከምባታ ጠምባሮ ዞን 3 ( 3ቱም ከዱራሜ ከተማ)፣
- ከቤንች ሸኮ ዞን 2 ( 2ቱም ከሸኮ ወረዳ) ፣
- ከኮንሶ ዞን 1 ( ከካራት ዙሪያ) ናቸው።
#DireDawa
ድሬዳዋ ከተማ ባለፉት 24 ሰዓት 375 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 38 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል። በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠ ሁሉም ሰዎች ናሙናቸው ከማህበረሰቡ ውስጥ የተሰበሰበ ነው።
@tikvahethiopiaBOT
WHO ስለኮሮና ቫይረስ ክትባት!
ለኮቪድ-19 መከላከያ የሚሆን ደህንነቱ የተረጋገጠና ውጤታማ የሆነ ክትባት በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል እስከ መጭው የአውሮፓውያን አመት አጋማሽ ላይደርስ እንደሚችል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
ሰዎች ክትባቱ ፈጥኖ ሊደርስልን ነው የሚለውን ጉጉትና ተስፋ በልክ እንዲያደርጉ የጤና ባለስልጣናት እየመከሩ ይገኛሉ።
በጤና ላይ አደጋ የማያስከትልና በደንብ ውጤት የሚያመጣ ክትባት እንደዚሁ በይድረስ ይድረስ ተቻኩሎ መስራት የሚሆን አይደለም፤ጊዜ ይጠይቃልም ብለዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ክትባት ፍለጋው በተገቢው መንገድ የማከናወኑ ሂደት በደንብ እየተካሄደ እንደሆነ እየገለፀ ነው።
ከስድስት እስከ ዘጠኝ የሚደርሱ ክትባቶች በአሁኑ ጊዜ በሶስተኛ ምዕራፍ የሰው ሙከራ ደረጃ ላይ እንደሚገኙም አመልክቷል።
በእነዚህ በጥንቃቄ በተዘጋጁት ሙከራዎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እየተሳተፉ መሆናቸው የWHO ቃል አቀባይ ማርጋሬት ሃሪስ ገልፀዋል።
የኮሮና ቫይረስ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ከመፈቀዱ በፊት የጤና ስጋት የማያስከትልና ቢያንስ በሙከራው ከሚሳተፉት 50 በመቶውን ከቫይረሱ መከላከል መቻሉ መረጋገጥ አለበት ሲሉ አሳስበዋል።
አያይዘው በተጨባጭ ያለውን ሁኔታ ካየን ከመጭው የአውሮፓውያን 2020/2021 አጋማሽ በፊት ክትባት ለህዝብ መስጠት ይጀመራል ብለን አንጠብቅም ብለዋል።
ከዚህ ባለፈም ቃል አቀባይ ማርጋሬት ሃሪስ ለቬኦኤ እንደተናገሩት መንግስታት ክትባት መቼ በአጣዳፊ ሁኔታ ወይም ለአጠቃላይ ጥቅም እንደሚያውሉ WHO አይነግራቸውም የየራሳቸውን ውሳኔ መውሰድ አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል። ነገር ግን ይህን ወረርሽኝ ድራሹን የሚያጠፋ ክትባት እየደረሰ ነው ብሎ ለህዝብ ያልሆነ ተስፋ መስጠት እንደማይገባ እናስጠነቅቃለን ማለታቸውን #ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
ለኮቪድ-19 መከላከያ የሚሆን ደህንነቱ የተረጋገጠና ውጤታማ የሆነ ክትባት በስፋት ጥቅም ላይ ለማዋል እስከ መጭው የአውሮፓውያን አመት አጋማሽ ላይደርስ እንደሚችል የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቋል።
ሰዎች ክትባቱ ፈጥኖ ሊደርስልን ነው የሚለውን ጉጉትና ተስፋ በልክ እንዲያደርጉ የጤና ባለስልጣናት እየመከሩ ይገኛሉ።
በጤና ላይ አደጋ የማያስከትልና በደንብ ውጤት የሚያመጣ ክትባት እንደዚሁ በይድረስ ይድረስ ተቻኩሎ መስራት የሚሆን አይደለም፤ጊዜ ይጠይቃልም ብለዋል።
የዓለም ጤና ድርጅት ክትባት ፍለጋው በተገቢው መንገድ የማከናወኑ ሂደት በደንብ እየተካሄደ እንደሆነ እየገለፀ ነው።
ከስድስት እስከ ዘጠኝ የሚደርሱ ክትባቶች በአሁኑ ጊዜ በሶስተኛ ምዕራፍ የሰው ሙከራ ደረጃ ላይ እንደሚገኙም አመልክቷል።
በእነዚህ በጥንቃቄ በተዘጋጁት ሙከራዎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች እየተሳተፉ መሆናቸው የWHO ቃል አቀባይ ማርጋሬት ሃሪስ ገልፀዋል።
የኮሮና ቫይረስ ክትባት ጥቅም ላይ እንዲውል ከመፈቀዱ በፊት የጤና ስጋት የማያስከትልና ቢያንስ በሙከራው ከሚሳተፉት 50 በመቶውን ከቫይረሱ መከላከል መቻሉ መረጋገጥ አለበት ሲሉ አሳስበዋል።
አያይዘው በተጨባጭ ያለውን ሁኔታ ካየን ከመጭው የአውሮፓውያን 2020/2021 አጋማሽ በፊት ክትባት ለህዝብ መስጠት ይጀመራል ብለን አንጠብቅም ብለዋል።
ከዚህ ባለፈም ቃል አቀባይ ማርጋሬት ሃሪስ ለቬኦኤ እንደተናገሩት መንግስታት ክትባት መቼ በአጣዳፊ ሁኔታ ወይም ለአጠቃላይ ጥቅም እንደሚያውሉ WHO አይነግራቸውም የየራሳቸውን ውሳኔ መውሰድ አለባቸው ሲሉ ተናግረዋል። ነገር ግን ይህን ወረርሽኝ ድራሹን የሚያጠፋ ክትባት እየደረሰ ነው ብሎ ለህዝብ ያልሆነ ተስፋ መስጠት እንደማይገባ እናስጠነቅቃለን ማለታቸውን #ቪኦኤ ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የዓለም ጤና ድርጅት ቃል አቀባይ ዶ/ር ማርጋሬት ሀሪስ ፦
"ደግመን ደጋግመን እንደምንናገረው ማንም ቢሆን ክትባት ይህን ሁሉ ችግር ይፈታል ወይም የሆነ ተአምረኛ መድሃኒት ይገኛል በሚል ቁጭ ብሎ አንዳች የአስማት መፍትሄ ሊጠብቅ አይገባውም።
አሁን ማድረግ የሚገባን የቫይረሱን መዛመት ሊገቱ የሚችሉ ተግባራት ቋሚ ልማድ አድርገን ያለማቋረጥ መፈፀም ነው፤ እነዚህም እጆችን መታጠብ፣ በአካል አለመቀራረብና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛዎችን ማድረግ ነው።"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ደግመን ደጋግመን እንደምንናገረው ማንም ቢሆን ክትባት ይህን ሁሉ ችግር ይፈታል ወይም የሆነ ተአምረኛ መድሃኒት ይገኛል በሚል ቁጭ ብሎ አንዳች የአስማት መፍትሄ ሊጠብቅ አይገባውም።
አሁን ማድረግ የሚገባን የቫይረሱን መዛመት ሊገቱ የሚችሉ ተግባራት ቋሚ ልማድ አድርገን ያለማቋረጥ መፈፀም ነው፤ እነዚህም እጆችን መታጠብ፣ በአካል አለመቀራረብና የአፍና የአፍንጫ መሸፈኛዎችን ማድረግ ነው።"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአሥራት ጋዜጠኞች በዋስትና እንዲፈቱ ተወሰነ!
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ አስተላልፏል።
ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ ፣ ሙሉጌታ አንበርብር ፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።
ምንጭ፦ አስራት ቴሌቪዥን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አራዳ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሥራት ጋዜጠኞች እያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ አስተላልፏል።
ፖሊስ በተደጋጋሚ መረጃ አቀርባለሁ በሚል ቀጠሮ እንዲሰጠው ቢጠይቅም በተሰጠው ቆጠሮ አለኝ ያለውን መረጃ ማቅረብ አልቻለም።
በመሆኑም ፍርድ ቤቱ በላይ ማናዬ ፣ ሙሉጌታ አንበርብር ፣ ምስጋናው ከፈለኝ እና ዮናታን ሙሉጌታ በእያንዳንዳቸው በ10 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲለቀቁ ወስኗል።
ምንጭ፦ አስራት ቴሌቪዥን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እናመሰግናለን!
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በዓለም ላይ ከተከሰተበት ጊዜ በኃላ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ሆነው የሰዎችን ሕይወት ለመታደግ የራሳቸውን ሕይወት አደጋ ላይ የጣሉት የጤና ባለሞያዎችን እናመሰግናለን።
በዓለማችን ይህ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ 7,000 የሚሆኑ የጤና ባለሞያዎች ሕይወታቸው እንዳለፈ አሚነስቲ ኢንተርናሽናል በቅርቡ ይፋ ያደረገው መረጃ ያሳያል፡፡ በአፍሪካም ከ400 ያላነሱ የጤና ባለሞያዎች በዚህ ወቅት ሌሎችን ለመጠበቅ ሲሉ መስዋዕት ሆነዋል፡፡
ወደ ሀገራችን ስንመጣም ወቅታዊ የአሀዝ መረጃ ባይኖርም በመቶዎች የሚቆጠሩ የጤና ባለሞያዎች በኮቪድ 19 ተይዘዋል፡፡ መያዝ ብቻም አይደለም በሞያቸው ህዝባቸውን ሲያገለግሉ ህይወታቸው ያለፈም የጤና ባለሞያዎች ጭምር አሉ፡፡
በትግራይ ክልል ጤና ቢሮ በኮሮና ቫይረስ መረጃ ትንተናና ትንበያ ክፍል በመስራት ላይ እያሉ በቫይረሱ ተይዘው ህይወታቸው ያለፈው ዶ/ር ፍሳሃየ አለምሰገድ እንዲሁም በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባልደረባ የነበሩት ነርስ አምበሳአውድም ዮሃንስ በቅርቡ በወረርሽኙ ምክንያት ያጣናቸው የህክምና ባለሞያዎች ናቸው፡፡
የህክምና ባለሞያዎችን ስናመሰግናቸው ግን በቃላት ወይም ከወራት አንዱን ቀን መርጠን ብቻ ሳይሆን ዕለት ዕለት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረግን ራሳችንን እያዳንን ለእነርሱም ምክንያት ባለመሆን ጭምር መሆን ይገባዋል፡፡
እየተጠነቀቅን እናመሰግናችኀለን!
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ጳጉሜ 2/2012 ዓ/ም
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮቪድ 19 ወረርሽኝ በዓለም ላይ ከተከሰተበት ጊዜ በኃላ ግንባር ቀደም ተሰላፊ ሆነው የሰዎችን ሕይወት ለመታደግ የራሳቸውን ሕይወት አደጋ ላይ የጣሉት የጤና ባለሞያዎችን እናመሰግናለን።
በዓለማችን ይህ ወረርሽኝ ከተከሰተ ጀምሮ 7,000 የሚሆኑ የጤና ባለሞያዎች ሕይወታቸው እንዳለፈ አሚነስቲ ኢንተርናሽናል በቅርቡ ይፋ ያደረገው መረጃ ያሳያል፡፡ በአፍሪካም ከ400 ያላነሱ የጤና ባለሞያዎች በዚህ ወቅት ሌሎችን ለመጠበቅ ሲሉ መስዋዕት ሆነዋል፡፡
ወደ ሀገራችን ስንመጣም ወቅታዊ የአሀዝ መረጃ ባይኖርም በመቶዎች የሚቆጠሩ የጤና ባለሞያዎች በኮቪድ 19 ተይዘዋል፡፡ መያዝ ብቻም አይደለም በሞያቸው ህዝባቸውን ሲያገለግሉ ህይወታቸው ያለፈም የጤና ባለሞያዎች ጭምር አሉ፡፡
በትግራይ ክልል ጤና ቢሮ በኮሮና ቫይረስ መረጃ ትንተናና ትንበያ ክፍል በመስራት ላይ እያሉ በቫይረሱ ተይዘው ህይወታቸው ያለፈው ዶ/ር ፍሳሃየ አለምሰገድ እንዲሁም በቅዱስ ጴጥሮስ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባልደረባ የነበሩት ነርስ አምበሳአውድም ዮሃንስ በቅርቡ በወረርሽኙ ምክንያት ያጣናቸው የህክምና ባለሞያዎች ናቸው፡፡
የህክምና ባለሞያዎችን ስናመሰግናቸው ግን በቃላት ወይም ከወራት አንዱን ቀን መርጠን ብቻ ሳይሆን ዕለት ዕለት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እያደረግን ራሳችንን እያዳንን ለእነርሱም ምክንያት ባለመሆን ጭምር መሆን ይገባዋል፡፡
እየተጠነቀቅን እናመሰግናችኀለን!
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ጳጉሜ 2/2012 ዓ/ም
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia