የደንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች!
በዚህ ፈታኝ ወቅት በከፍተኛ ደረጃ ለኮቪድ-19 ተጋላጭ ሆነው በተለያዩ ሀገራት ህዝብና ወገንን እያገለገሉ የሚገኙ የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች እንዲሁም ረዳቶቻቸው ናቸው።
በምስራቅ አፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በየዕለቱ የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች በኮቪድ-19 መያዛቸውን እየሰማን ነው።
ዛሬ እንኳን ሀገራችን ሪፖርት ካደረገቻቸው ኬዞች መካከል 2 የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች ይገኙበታል።
የኬንያ ጤና ሚኒስቴር በሰጠው መረጃ ደግሞ በታንዛኒያ ድንበር 53 (51 የታንዛኒያና 2 የቡሩንዲ ዜጎች) የድንበር ተሻጋሪ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጦ ሁሉም ወደየመጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል።
ባለፉት 24 ሰዓት በዩጋንዳ 1,071 የላብራቶሪ ምርመራ (በድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች) ላይ ተደርጎ ሃያ አንዱ (21) ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።
የደንበር ተሻጋሪ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ ክትትል ማድረግ ካልተቻለ ፤ የጤናቸውን ሁኔታ መከታተል ካልተቻል፣ እራሳቸውን ከቫይረሱ የሚጠብቁበትን መንገድ ማመቻቸት ካልተቻለ ፤ በሁሉም ሀገራት ከፍተኛ የሆነ አደጋ መፈጠሩ የማይቀር ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በዚህ ፈታኝ ወቅት በከፍተኛ ደረጃ ለኮቪድ-19 ተጋላጭ ሆነው በተለያዩ ሀገራት ህዝብና ወገንን እያገለገሉ የሚገኙ የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች እንዲሁም ረዳቶቻቸው ናቸው።
በምስራቅ አፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በየዕለቱ የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች በኮቪድ-19 መያዛቸውን እየሰማን ነው።
ዛሬ እንኳን ሀገራችን ሪፖርት ካደረገቻቸው ኬዞች መካከል 2 የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች ይገኙበታል።
የኬንያ ጤና ሚኒስቴር በሰጠው መረጃ ደግሞ በታንዛኒያ ድንበር 53 (51 የታንዛኒያና 2 የቡሩንዲ ዜጎች) የድንበር ተሻጋሪ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጦ ሁሉም ወደየመጡበት እንዲመለሱ ተደርጓል።
ባለፉት 24 ሰዓት በዩጋንዳ 1,071 የላብራቶሪ ምርመራ (በድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪዎች) ላይ ተደርጎ ሃያ አንዱ (21) ቫይረሱ ተገኝቶባቸዋል።
የደንበር ተሻጋሪ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ላይ ከፍተኛ ክትትል ማድረግ ካልተቻለ ፤ የጤናቸውን ሁኔታ መከታተል ካልተቻል፣ እራሳቸውን ከቫይረሱ የሚጠብቁበትን መንገድ ማመቻቸት ካልተቻለ ፤ በሁሉም ሀገራት ከፍተኛ የሆነ አደጋ መፈጠሩ የማይቀር ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሱማሊያ ተጨማሪ 34 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ!
ባለፉት 24 ሰዓት በሱማሊያ ተጨማሪ 34 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 1,455 ደርሷል።
በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት አስራ አንድ (11) ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 163 ደርሷል።
በተጨማሪ የ1 ሰው ህይወት ማለፉን ተከትሎ አጠቃላይ በሀገሪቱ በኮቪድ-19 ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሃምሳ ሰባት (57) ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት በሱማሊያ ተጨማሪ 34 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 1,455 ደርሷል።
በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት አስራ አንድ (11) ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 163 ደርሷል።
በተጨማሪ የ1 ሰው ህይወት ማለፉን ተከትሎ አጠቃላይ በሀገሪቱ በኮቪድ-19 ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ሃምሳ ሰባት (57) ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጅቡቲ በአንድ ቀን 117 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ!
በጅቡቲ ባለፉት 24 ሰዓት 813 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 117 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 1,518 ደርሰዋል።
በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት አርባ ስድስት (46) ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1,018 መድረሳቸው ገልጿል።
በተጨማሪ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር ሰባት (7) ደርሷል ፤ ባለፉት 24 ሰዓት የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የጅቡቲ ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጅቡቲ ባለፉት 24 ሰዓት 813 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 117 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 1,518 ደርሰዋል።
በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት አርባ ስድስት (46) ሰዎች ከበሽታው ማገገማቸውን ተከትሎ አጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 1,018 መድረሳቸው ገልጿል።
በተጨማሪ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር ሰባት (7) ደርሷል ፤ ባለፉት 24 ሰዓት የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉን የጅቡቲ ጤና ሚኒስቴር አሳውቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጣልያን የሟቾች ቁጥር ከ100 በታች ሆኖ ተመዘገበ!
ባለፉት 24 ሰዓት በጣልያን የዘጠና ዘጠኝ (99) ሰዎች ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደርጓል ፤ ከየካቲት 30/2012 ዓ/ም በኃላ የተመዘገበ #ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ነው።
በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት 451 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል ፤ ይህ ደግሞ ከየካቲት 23/2012 ዓ/ም በኃላ የተመዘገበ #ዝቅተኛው ኬዝ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት በጣልያን የዘጠና ዘጠኝ (99) ሰዎች ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደርጓል ፤ ከየካቲት 30/2012 ዓ/ም በኃላ የተመዘገበ #ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ነው።
በሌላ በኩል በትላንትናው ዕለት 451 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋግጧል ፤ ይህ ደግሞ ከየካቲት 23/2012 ዓ/ም በኃላ የተመዘገበ #ዝቅተኛው ኬዝ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የቡሩንዲ ምርጫ ከፊታችን ረቡዕ ይካሄዳል!
(በጋዜጠኛ እሸት በቀለ)
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ላይ ይሰሩ የነበሩ የዓለም ጤና ድርጅት ባለሙያዎችን ባለፈው ሳምንት ያባረረችው ቡሩንዲ ረቡዕ አዲስ ፕሬዝዳንት ትመርጣለች።
አገሪቱ እስካሁን አርባ ሁለት (42) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አረጋግጣለች።
ቡሩንዲን እንደ ብረት ቀጥቅጠው ላለፉት 15 አመታት የገዙትን ፕሬዝዳንት ፒየር ንኩሩንዚዛን ለመተካት 7 እጩዎች ቀርበዋል።
የገዢው CNDD-FDD ፓርቲ እጩ 'እግዜር ቡሩንዲን ስለሚያፈቅር የአገሪቱ ዜጎች ኮሮናን መፍራት የለባቸውም' ብለዋል።
የፕሬዝዳንቱ ቃል አቀባይ ባለፈው ወር ቡሩንዲ "ከፈጣሪ ልዩ ቃል ኪዳን ተፈራርማለች" ሲሉ የኮሮና ሥጋትን አጣጥለው ነበር።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(በጋዜጠኛ እሸት በቀለ)
በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ላይ ይሰሩ የነበሩ የዓለም ጤና ድርጅት ባለሙያዎችን ባለፈው ሳምንት ያባረረችው ቡሩንዲ ረቡዕ አዲስ ፕሬዝዳንት ትመርጣለች።
አገሪቱ እስካሁን አርባ ሁለት (42) ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውን አረጋግጣለች።
ቡሩንዲን እንደ ብረት ቀጥቅጠው ላለፉት 15 አመታት የገዙትን ፕሬዝዳንት ፒየር ንኩሩንዚዛን ለመተካት 7 እጩዎች ቀርበዋል።
የገዢው CNDD-FDD ፓርቲ እጩ 'እግዜር ቡሩንዲን ስለሚያፈቅር የአገሪቱ ዜጎች ኮሮናን መፍራት የለባቸውም' ብለዋል።
የፕሬዝዳንቱ ቃል አቀባይ ባለፈው ወር ቡሩንዲ "ከፈጣሪ ልዩ ቃል ኪዳን ተፈራርማለች" ሲሉ የኮሮና ሥጋትን አጣጥለው ነበር።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse
የኮሮና ቫይረስ ወረረሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የተዘጋጀ በተንቀሳቃሽ ሰልክ የሚሰጥ ስልጠናን አስመልክቶ የተዘጋጀ መግለጫ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ ወረረሽኝን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ለጤና ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች የተዘጋጀ በተንቀሳቃሽ ሰልክ የሚሰጥ ስልጠናን አስመልክቶ የተዘጋጀ መግለጫ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በደቡብ ሱዳን ተጨማሪ 57 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ!
የደቡብ ሱዳን ጤና ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ተጨማሪ ሃምሳ ሰባት (57) ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸውን ሪፖርት አድርጓል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 347 ደርሰዋል።
በአጠቃላይ በሀገሪቱ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች አራት (4) ሲሆኑ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ደግሞ ስድስት (6) ደርሰዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የደቡብ ሱዳን ጤና ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ተጨማሪ ሃምሳ ሰባት (57) ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸውን ሪፖርት አድርጓል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 347 ደርሰዋል።
በአጠቃላይ በሀገሪቱ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች አራት (4) ሲሆኑ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ደግሞ ስድስት (6) ደርሰዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በስፔን ለሁለተኛ ቀን የሟቾች ቁጥር ከ100 በታች ሆኖ ተመዝግቧል!
በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ሃምሳ ዘጠኝ (59) ሰዎች ህይወታቸው አልፏል ፤ ከመጋቢት 7/2012 ዓ/ም በኃላ የተመዘገበ #ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ነው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በስፔን ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ሃምሳ ዘጠኝ (59) ሰዎች ህይወታቸው አልፏል ፤ ከመጋቢት 7/2012 ዓ/ም በኃላ የተመዘገበ #ዝቅተኛው የሟቾች ቁጥር ነው።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ሰበር ዜና!
የደቡብ ሱዳን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሬክ ማቻር እና ባለቤታቸው አንጀሊና ቴኒ (የመከላከያ ሚኒስትር) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በተጨማሪም የተቀዳሚ ም/ፕሬዘዳንቱ የቢሮ ሰራተኞች እና ጠባቂዎች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው ተገልጿል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የደቡብ ሱዳን ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንት ዶ/ር ሬክ ማቻር እና ባለቤታቸው አንጀሊና ቴኒ (የመከላከያ ሚኒስትር) በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
በተጨማሪም የተቀዳሚ ም/ፕሬዘዳንቱ የቢሮ ሰራተኞች እና ጠባቂዎች በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) መያዛቸው ተገልጿል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ተጨማሪ መረጃ ፦
- ዶክተር ሬክ ማቻርን ጨምሮ ሌሎች 'የኮቪድ-19 ታስክ ፎርስ' አባላት ምርመራ የተደረገላቸው ግንቦት 5/2012 ዓ/ም ነው።
- ከተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንቱና ከባለቤታቸው (አንጀሊና ቴኒ) ፣ ከቢሮ ሰራተኞች እንዲሁም ከጠባቂዎቻቸው በተጨማሪ ቁጥራቸው ያልተገለፀ የቀድሞ ታስክ ፎርስ አባላት በቫይረሱ ተይዘዋል።
- ከዚህ ቀደም ዶክተር ሬክ ማቻር ሚያዚያ 19/2012 ዓ/ም ምርመራ ተደርጎላቸው ከቫይረሱ #ነፃ መሆናቸው ተረጋግጦ ነበር። ሌላኛው ምርመራ የተደረገው ከታስክ ፎርሱ አባላት በአንዱ ላይ ቫይረሱ ስለተገኘ ነው።
- ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሬክ ማቻር እና ሌሎች በቫይረሱ የተያዙ ከፍተኛ አመራሮች ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ 14 ቀናት ራሳቸውን አግልለው ክትትል ይደረግላቸዋል።
- ዶክተር ሬክ ማቻር እስካሁን ምንም ምልክት የለባቸውም።
#JamesGatdetDak #FVPDrRiekMachar
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- ዶክተር ሬክ ማቻርን ጨምሮ ሌሎች 'የኮቪድ-19 ታስክ ፎርስ' አባላት ምርመራ የተደረገላቸው ግንቦት 5/2012 ዓ/ም ነው።
- ከተቀዳሚ ምክትል ፕሬዘዳንቱና ከባለቤታቸው (አንጀሊና ቴኒ) ፣ ከቢሮ ሰራተኞች እንዲሁም ከጠባቂዎቻቸው በተጨማሪ ቁጥራቸው ያልተገለፀ የቀድሞ ታስክ ፎርስ አባላት በቫይረሱ ተይዘዋል።
- ከዚህ ቀደም ዶክተር ሬክ ማቻር ሚያዚያ 19/2012 ዓ/ም ምርመራ ተደርጎላቸው ከቫይረሱ #ነፃ መሆናቸው ተረጋግጦ ነበር። ሌላኛው ምርመራ የተደረገው ከታስክ ፎርሱ አባላት በአንዱ ላይ ቫይረሱ ስለተገኘ ነው።
- ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሬክ ማቻር እና ሌሎች በቫይረሱ የተያዙ ከፍተኛ አመራሮች ከዛሬ ጀምሮ ለቀጣይ 14 ቀናት ራሳቸውን አግልለው ክትትል ይደረግላቸዋል።
- ዶክተር ሬክ ማቻር እስካሁን ምንም ምልክት የለባቸውም።
#JamesGatdetDak #FVPDrRiekMachar
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሱዳን ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን!
(በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ)
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል በሱዳን ካርቱም ግዛት ከዛሬ ግንቦት 11/2012 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሁለት (2) ሣምንታት ከዚህ በፊት የታወጀዉ የእንቅስቃሴ ዕገዳና ከቤት ያለ መዉጣት ገደብ መቀጠሉን የሱዳን መንግስት አስታዉቋል።
ስለዚህ ሱዳን ካርቱም ግዛት የምትኖሩ ዜጎቻችን ይህን ዉሳኔ በማክበር እራሳችሁንና ቤተሰቦቻችሁን ከቫይረሱ እንድትጠብቁ በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ኤምባሲ አሳስቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ)
የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል በሱዳን ካርቱም ግዛት ከዛሬ ግንቦት 11/2012 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣይ ሁለት (2) ሣምንታት ከዚህ በፊት የታወጀዉ የእንቅስቃሴ ዕገዳና ከቤት ያለ መዉጣት ገደብ መቀጠሉን የሱዳን መንግስት አስታዉቋል።
ስለዚህ ሱዳን ካርቱም ግዛት የምትኖሩ ዜጎቻችን ይህን ዉሳኔ በማክበር እራሳችሁንና ቤተሰቦቻችሁን ከቫይረሱ እንድትጠብቁ በሱዳን የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ኤምባሲ አሳስቧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኳታር ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን!
(የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ዶሃ)
የኳታር የሚኒስትሮች ም/ቤት የኮሮና ቫይረስ መስፋፋትን ለመግታት ያስችላሉ ያላቸውን ተጨማሪ ውሳኔዎች አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦
- ሁሉም የአገሪቱ ዜጎች እና ሁሉም ነዋሪዎች ከግንቦት 14 ቀን 2012 ዓ.ም (22 May 2020) ጀምሮ ከቤታቸው ሲወጡ የቫይረስ ተጋላጭነት ደረጃን የሚያሳየውን EHTERAZ የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ በስልኮቻቸው ማውረድ ይጠበቅባቸዋል።
- በግል መኪናዎች ውስጥ ከ2 ሰው በላይ ሆኖ መጓዝ አይፈቀድም። በታክሲዎች፣ በሊሞዚኖች እና በቤተሰብ ሹፌሮች በሚሽከረከሩ መኪናዎች ውስጥ ከ3 ሰው በላይ ሆኖ መጓዝ አይቻልም። አምቡላንሶችና የጤና ሚኒስቴር መስሪያ ቤት መኪኖች፣ የመከላከያ፣ የፖሊስ እና የደህንነት ተቋማት ተሽከርካሪዎች ውሳኔው አይመለከታቸውም።
- ከግንቦት 11 - 22 ቀን 2012 ዓ.ም (19 -30 May 2020) ሁሉም ሱቆች ዝግ ሆነው ይቆያሉ፤ የንግድ እንቅስቃሴዎች ይቆማሉ። ምግብ ቤቶች፣ የምግብ አቅራቢ ድርጅቶች እና ፋርማሲዎች ውሳኔው አይመለከታቸውም።
- ከግንቦት 11 ቀን 2012 ዓ.ም (19 May 2020) ጀምሮ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በመኖሪያ ቤቶች አቅራቢያ እና አስፈላጊውን ጥንቃቄ (የፊት መሸፈኛ በመጠቀም፣ ርቀትን በመጠበቅ) በማድረግ መከናወን ይኖርባቸዋል።
- ውሳኔዎቹን ተላልፎ የተገኘ ግለሰብ እስከ ሶስት ዓመት እስር እና እስከ 200,000 የኳታር ሪያል የሚቀጣ ይሆናል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(የኢትዮጵያ ኤምባሲ - ዶሃ)
የኳታር የሚኒስትሮች ም/ቤት የኮሮና ቫይረስ መስፋፋትን ለመግታት ያስችላሉ ያላቸውን ተጨማሪ ውሳኔዎች አሳልፏል። በዚህም መሰረት፦
- ሁሉም የአገሪቱ ዜጎች እና ሁሉም ነዋሪዎች ከግንቦት 14 ቀን 2012 ዓ.ም (22 May 2020) ጀምሮ ከቤታቸው ሲወጡ የቫይረስ ተጋላጭነት ደረጃን የሚያሳየውን EHTERAZ የተሰኘ የሞባይል መተግበሪያ በስልኮቻቸው ማውረድ ይጠበቅባቸዋል።
- በግል መኪናዎች ውስጥ ከ2 ሰው በላይ ሆኖ መጓዝ አይፈቀድም። በታክሲዎች፣ በሊሞዚኖች እና በቤተሰብ ሹፌሮች በሚሽከረከሩ መኪናዎች ውስጥ ከ3 ሰው በላይ ሆኖ መጓዝ አይቻልም። አምቡላንሶችና የጤና ሚኒስቴር መስሪያ ቤት መኪኖች፣ የመከላከያ፣ የፖሊስ እና የደህንነት ተቋማት ተሽከርካሪዎች ውሳኔው አይመለከታቸውም።
- ከግንቦት 11 - 22 ቀን 2012 ዓ.ም (19 -30 May 2020) ሁሉም ሱቆች ዝግ ሆነው ይቆያሉ፤ የንግድ እንቅስቃሴዎች ይቆማሉ። ምግብ ቤቶች፣ የምግብ አቅራቢ ድርጅቶች እና ፋርማሲዎች ውሳኔው አይመለከታቸውም።
- ከግንቦት 11 ቀን 2012 ዓ.ም (19 May 2020) ጀምሮ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች በመኖሪያ ቤቶች አቅራቢያ እና አስፈላጊውን ጥንቃቄ (የፊት መሸፈኛ በመጠቀም፣ ርቀትን በመጠበቅ) በማድረግ መከናወን ይኖርባቸዋል።
- ውሳኔዎቹን ተላልፎ የተገኘ ግለሰብ እስከ ሶስት ዓመት እስር እና እስከ 200,000 የኳታር ሪያል የሚቀጣ ይሆናል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#WHA73 የዓለም የጤና ድርጅት አመታዊ ጉባኤ በቪዲዮ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው። ጉባዔው በዋናነት አባል ሀገራቱ ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ በኮሮና ቫይረስ ዙሪያ የሚያተኩር ነው ተብሏል። በጉባዔው መክፈቻ ላይ የቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ ሃገራቸው ቫይረሱን ለመቆጣጠር አበረታች ስራ መስራቷን ጠቅሰው፥ አስፈላጊው ግምገማ ቫይረሱን መቆጣጠር ከተቻለ በኋላ ይደረጋል ብለዋል። አያይዘውም ሃገራቸው ቫይረሱን…
#WHA73 #DrTedrosAdhanom
በትንሹ 320 ነርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሞተዋል!
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የሚሞቱ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር ከፍተኛ አደጋን ደቅኗል ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ተናገረዋል።
ዓለም አቀፉ የነርሶች ምክርቤት በስሩ ካሉት ማህበራት ባሰባሰበድ መረጃ መሰረት በአንዳንድ ሃገራት የሚስተዋለው የነርሶቹ የተጠቂነት ቁጥር በ20 በመቶ አሻቅቧል፤ በዓለም አቀፍ ደረጃም በትንሹ 320 ነርሶች ሞተዋል፡፡
ዶ/ር ቴድሮስ መረጃዎች በወጉ ሊሰበሰቡ ቢችሉ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የድርጅቱ አባል ሃገራት የጤና ባለሙያዎቻቸውን ከወረርሽኙ #ሊጠብቁ ፣ አስፈላጊውን የህክምና ግብዓቶች ሊያሟሉላቸው እና መረጃዎችን ስርዓት ባለው መልኩ ሊሰበስቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በትንሹ 320 ነርሶች በዓለም አቀፍ ደረጃ ሞተዋል!
በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት የሚሞቱ የጤና ባለሙያዎች ቁጥር ከፍተኛ አደጋን ደቅኗል ሲሉ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ተናገረዋል።
ዓለም አቀፉ የነርሶች ምክርቤት በስሩ ካሉት ማህበራት ባሰባሰበድ መረጃ መሰረት በአንዳንድ ሃገራት የሚስተዋለው የነርሶቹ የተጠቂነት ቁጥር በ20 በመቶ አሻቅቧል፤ በዓለም አቀፍ ደረጃም በትንሹ 320 ነርሶች ሞተዋል፡፡
ዶ/ር ቴድሮስ መረጃዎች በወጉ ሊሰበሰቡ ቢችሉ ቁጥሩ ከዚህም በላይ ሊሆን እንደሚችልም ገልጸዋል፡፡
በመሆኑም የድርጅቱ አባል ሃገራት የጤና ባለሙያዎቻቸውን ከወረርሽኙ #ሊጠብቁ ፣ አስፈላጊውን የህክምና ግብዓቶች ሊያሟሉላቸው እና መረጃዎችን ስርዓት ባለው መልኩ ሊሰበስቡ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ምንጭ፦ አል ዓይን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዶናልድ ትራምፕ ማስጠንቀቂያ!
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዳይሬክተር ጀነራል ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ቴድሮስን በ30 ቀናት በድርጅታቸው ውስጥ "መሰረታዊ ለውጥ" እንዲያመጡ ያሳሰቡ ሲሆን አለበለዚያ ግን አሜሪካ ሙሉ በሙሉ ለድርጅቱ የምታደርገውን ድጋፍ ታቋርጣለች ሲሉ ለዶ/ር ቴድሮስ በጻፉት ደብዳቤ አስጠንቅዋል - #BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ዳይሬክተር ጀነራል ኃላፊ ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም የ30 ቀን ማስጠንቀቂያ ሰጥተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ቴድሮስን በ30 ቀናት በድርጅታቸው ውስጥ "መሰረታዊ ለውጥ" እንዲያመጡ ያሳሰቡ ሲሆን አለበለዚያ ግን አሜሪካ ሙሉ በሙሉ ለድርጅቱ የምታደርገውን ድጋፍ ታቋርጣለች ሲሉ ለዶ/ር ቴድሮስ በጻፉት ደብዳቤ አስጠንቅዋል - #BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 14 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3,271 የላብራቶሪ ምርመራ አስራ አራት (14) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 365 ደርሷል፡፡
ቫይረሱ የተገኘባቸው 11 ወንድ እና 3 ሴት ናቸው። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ከ9 እስከ 68 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 9 ሰዎች ከአዲስ አበባ (1 የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ ፣ 7 በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው ፣ 1 ሰው የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #የሌለው) ፣ 1 ሰው ከትግራይ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ ፣ መቐለ ለይቶ ማቆያ ያለ) ፣ 1 ሰው ከኦሮሚያ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ) ፣ እንዲሁም 3 ሰዎች ከሶማሌ ክልል (ጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ) ናቸው።
የዕለቱ ታማሚዎች የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት ፦
• የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው - 6
• በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው - 7
• የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው - 1
ተጨማሪ መረጃ ፦
በትላትናው ዕለት 4 ሰዎች (3 ከሶማሌ ክልል 1 ከአፋር ክልል) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ ሃያ (120) ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ተጨማሪ 14 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል!
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 3,271 የላብራቶሪ ምርመራ አስራ አራት (14) ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል። በአጠቃላይ በሀገራችን ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 365 ደርሷል፡፡
ቫይረሱ የተገኘባቸው 11 ወንድ እና 3 ሴት ናቸው። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ከ9 እስከ 68 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው።
ቫይረሱ የተገኘባቸው 9 ሰዎች ከአዲስ አበባ (1 የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ ፣ 7 በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው ፣ 1 ሰው የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት #የሌለው) ፣ 1 ሰው ከትግራይ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ ፣ መቐለ ለይቶ ማቆያ ያለ) ፣ 1 ሰው ከኦሮሚያ ክልል (የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ) ፣ እንዲሁም 3 ሰዎች ከሶማሌ ክልል (ጅግጅጋ ለይቶ ማቆያ) ናቸው።
የዕለቱ ታማሚዎች የጉዞ ታሪክና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ያላቸው ግንኙነት ፦
• የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያላቸው - 6
• በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው - 7
• የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት የሌላቸው - 1
ተጨማሪ መረጃ ፦
በትላትናው ዕለት 4 ሰዎች (3 ከሶማሌ ክልል 1 ከአፋር ክልል) ከበሽታው ያገገሙ ሲሆን አጠቃላይ በሀገራችን ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር አንድ መቶ ሃያ (120) ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#DrLiaTadesse ዛሬ ቫይረሱ የተገኘባቸው 17 ወንድ እና 18 ሴት ናቸው። በዜግነት ሁሉም ኢትዮጵያውያን ሲሆኑ ከ15 እስከ 80 ዓመት የእድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ቫይረሱ የተገኘባቸው 29 ሰዎች ከአዲስ አበባ (አንድ የውጭ ሀገር የጉዞ ታሪክ ያለው የድንበር ተሻጋሪ አሽከርካሪ፣ 23 በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያለቸው ፣ 5 ሰዎች የውጭ ሀገር ጉዞ ታሪክ እና በበሽታው ከተያዘ…
#DrLiaTadesse
"በትላንትናው ዕለት (ግንቦት 10/2012 ዓ/ም) በወጣው መግለጫ ላይ ከአማራ ክልል (ሰሜን ሸዋ ዞን ፣ አጣየ ከተማ ለይቶ ማቆያ) ቫይረሱ በምርመራ የተገኘበት ተብሎ የተገለፀው በግንቦት 9 ቀን በወጣው መግለጫ ላይ ተጠቅሶ የነበረ መሆኑንና በትላትናው ዕለት በድጋሚ ሪፖርት የተደረገ ነው። በመሆኑም በትላንትናው ዕለት ቫይረሱ በምርመራው የተገኝባቸው ሰዎች ቁጥር 34 መሆኑን ከይቅርታ ጋር እንገልፃለን።" - ዶክተር ሊያ ታደሰ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"በትላንትናው ዕለት (ግንቦት 10/2012 ዓ/ም) በወጣው መግለጫ ላይ ከአማራ ክልል (ሰሜን ሸዋ ዞን ፣ አጣየ ከተማ ለይቶ ማቆያ) ቫይረሱ በምርመራ የተገኘበት ተብሎ የተገለፀው በግንቦት 9 ቀን በወጣው መግለጫ ላይ ተጠቅሶ የነበረ መሆኑንና በትላትናው ዕለት በድጋሚ ሪፖርት የተደረገ ነው። በመሆኑም በትላንትናው ዕለት ቫይረሱ በምርመራው የተገኝባቸው ሰዎች ቁጥር 34 መሆኑን ከይቅርታ ጋር እንገልፃለን።" - ዶክተር ሊያ ታደሰ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia