TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.5K photos
1.59K videos
216 files
4.34K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ያለፈቃዳችን ከደመወዛችን ተቆርጦብናል፤ ይመለስልን ” - መምህራን  ➡️ “ 'በእጃችን ይዘን በምንገባው ገንዘብ ራሳችንን ለማኖር እየተቸገርን ነው' እያሉ ባሉበት ወቅት ወርደው ሳያወያዩ ከደመወዛቸው መቆረጡ መምህራኑን አስቆጥቷል ” - የባስኬቶ ዞን መምህራን ማኀበር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባስኬቶ ዞን የላስካ ዙሪያ ወረዳ መምህራን፣ “ለህዳሴ ግድብ የቦንድ ግዥ” በሚል በአመራሮች ያለፈቃዳቸው እና…
#Update

" መንግስትን ጠይቀው ‘መምህራን በሀገራዊ ልማት መሳተፍ የለባቸውም’ ካለ ገንዘባቸው ሊመልስ ይችላል "  - የወረዳው ትምህርት ጽሕፈት ቤት

" እጅ በእጅ እስከ 380 ሺሕ ብር በዙሪያ ወረዳ ተሰብስቧል ! "

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ባስኬቶ ዞን ላስካ ዙሪያ ወረዳ ያሉ መምህራን ደመወዝ “ውይይት ሳይደረግ፤ ያለፈቃድ" መቆረጡ እንዳስቆጣቸው መምህራኑ፣ የክልሉና የዞኑ መምህራን ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

የባስኬቶ ዞን መምህራን ማኅበር ፤ " ' በእጃችን ይዘን በምንገባው ገንዘብ ራሳችንን ለማኖር እየተቸገርን ነው' እያሉ ባሉበት ወቅት ወርደው ሳያወያዩ ከደመወዛቸው መቆረጡ መምህራኑን አስቆጥቷል " ብሎ ነበር።

ቅሬታ የተነሳበት የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አለ ?

የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አብርሃም ሽብልቶ፣ " ያላግባብ የሚባል ነገር የለም፤ ደመወዝ እንደሚቆረጥ ሀገራዊ አጀንዳ ነው " ብለዋል።

ለቦንድ መግዣ በተቀመጠው ስኬል መሠረት ከ750 እስከ 1500 ብር እንደሚቆረጥ ገልጸዋል።

በጉዳዩ ዙሪያ መምህራን ማህበሩ፣ የየትምህርት ቤቱ ርዕሳነ መምህራን እንደተወያዩ ገልጸው፣ " ዛሬ የተፈጠረ አጀንዳም አይደለም፤ ከክልል የወረደ ነው፤ ተልኮ ከተሰጠ በኋላም በዙሪያ ወረዳ ምክትል አስተዳደርና በፋይናንስ ኃላፊው አማካኝነት በባንክ ነው የተሰበሰበው " ሲሉ አብራርተዋል።

"እጅ በእጅ እስከ 380 ሺሕ ብር በዙሪያ ወረዳ ተሰብስቧል ቀሪውን ግን በፋይናንስ ቆርጣችሁ ውሰዱ ጠዋት ማታ ብር አምጡ እያልን ሌላ አጀንዳ አንፈጥርም በሚል ተስማምተን እንጂ ዝም ብለን ያደረነው ነገር አይደለም " ነው ያሉት።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የመምህራኑ ደመወዝ የሚቆረጠው በአስገዳጅተነት ካልሆነ ታዲያ " ያለፈቃዳችን ተቆረጠብን ይመለስልን " ለሚሉት ገንዘቡን ለመመለስ ፈቃደኞች ናችሁ? የሚል ጥያቄ ለኃላፊው አቅርቧል።

ኃላፊው "
እኔ እንደ ዙሪያ ወረዳ ትምህርት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ይህን መወሰን አልችልም፤ ሆኖም አጀንዳው የመንግስት ስለሆነ ለመንግስት ማቅረብ ይችላሉ " ብለዋል።

" ለምሳሌ ሁለት ዙር ከፍሎ የትቆረጠበት ሰው አለ፤ ተጨማሪ የተቆረጠባቸው ሰዎች ገንዘባቸውን እንዲወስዱ መልዕክት አስተላልፈናል። ስለዚህ መንግስትን ጠይቀው 'መምህራን በሀገራዊ ልማት መሳተፍ የለባቸውም' ካለ ሊመልስ ይችላል " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

የዙሪያ ወረዳ እንጂ የከተማው መምህራን ደመወዛቸው አልተቆረጠም፤ ይህስ ለምን ሆነ ? ለምን ተመሳሳይ ተግባር አልተከተላችሁም ? ስንል ኃላፊውን ጠይቀናል።

ኃላፊው፣ " እኛም ጥያቄ አቅርበን (የከተማውም) ‘እጅ በእጅ ከፍለዋል’ ነው የተባልነው። በዚህ አግባብ ያልከፈሉ ደግሞ ከደመወቸው እንዲቆረጥ ደብዳቤ አስገብተናል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭212😡12972💔14😢11🕊11🙏8👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
“ ምን ያህል ተቃጥሎ ምን ያህል እንደቀረ አላወቅንም። እሳቱ ከባድ ነበር። ኮሚቴ ተልኳል ” - የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት በኦሮሚያ ክልል ቡኖ በደሌ ዞን በበደሌ ከተማ የሚገኝ ከተሰራ አመት የሆነው መስጂድ ምክንያቱ እስካሁን ባልታወቀ ሁኔታ በእሳት መቃጠሉ ተሰምቷል። “ ቡልቲ አዳ” የተሰኘው መስጂድ “ሙሉ ለሙሉ በእሳት” መቃጠሉን የተመለከተ መረጃም በማህበራዊ ሚዲያ ተሰራጭቷል። …
#Update

“ መስጂዱ ሙሉ ለሙሉ ነው የተቃጠለው። ተጠርጣሪዎች ተይዘው ምርመራ እየተደረገ ነው ” - ኮሚቴው

በቡኖ በደሌ ዞን የበደሌ ከተማ “ቡልቲ አዳ” መስጂድ የእሳት ቃጠሎ እንደደረሰበት፣ የቃጠሎውን ምክንያትና መጠኑን ለማረጋገጥ ወደ ስፍራው ኮሚቴ ተልኮ እንደነበር የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጾ ነበር።

በዚህም ምክር ቤቱ በወቅቱ በሰጠን ቃል፣ ቃጠሎው መፈጸሙን ገልጾ፣ “ ምን ያህል ተቃጥሎ ምን ያህል እንደቀረ አላወቅንም። እሳቱ ከባድ ነበር። ኮሚቴ ተልኳል ” ነበር ያለው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ የመስጂዱ ቃጠሎ ምክንያት ታወቀ ? መስጂዱ ሙሉ በሙሉ ነው የተቃጠለው ? ሲል ዛሬ ወደ ስፍራው የተላከውን ኮሚቴ ጠይቋል።

ኮሚቴው ምን መለሰ ?

“ በቃጠሎው ተጠርጥረው በቀጥጥር ስር የዋሉ አሉ። እስካሁን ምርመራ ላይ ናቸው። ከቃጠሎው ጀርባ ያለው ምክንያት አልታወቀም። ምናልባት ግን ‘ሰዎቹ የአእምሮ ችግር ያለባቸው ናቸው’ እያሉ ነው።

‘እኔ ነኝ ጉዳዩን የፈጸምኩት’ ብሎ የተያዘ ሰው አለ። አንድ ሁለት ሰዎች ተይዘዋል። አሁን ተረጋግቷል። ተማሪዎቹም ወደ ትምህርታቸው ተመልሰዋል። ከክልልም ከዞንም ዛሬ መጥተው ልጆቹን አወያይተዋል።

መስጂዱ ሙሉ ለሙሉ ነው የተቃጠለው። ይህ መስጂድ ተትቶ ሌላ መስጂድ እንዲሰራ የመንግስት አካል ፈቅዷል። የተቃጠለው መስጂድ ተሰርቶ ያለቀ ነበር። አሁን ሌላ መስጂድ መስራት ሊጀመር ነው ” ብሏል።

የመስጂዱ የአዳሪ ትምህርት ቤት ከመስጂዱ ቅጥር ግቢ ውጪ ስለሆነ እንዳልተቃጠለ፣ በዚህም ወደ 300 የሚሆኑ ተማሪዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ እንደሆነ ኮሚቴው ገልጿል።

መስጂዱ ከመሰራቱ በፊት የአሁኑን ጥቃት ሊያደርስ የሚችል የተፈጠረ አለመግባባት ተፈጥሮ ነበር ? ስንል ለኮሚቴው ጥያቄ አቅርበናል።

ኮሚቴው፣ “ አሁን እኛም ጠይቀን ነበር። ችግር እንዳልነበር ነው የተነገረን። እንደዛ የሆነ ነገር አልነበረም። ግን አሁን ሙሉ ለሙሉ እንደዚህ ነው ብለን ለማብራራት ምርመራው ገና እየቀጠለ በመሆኑ ማረጋጠጥ የቻልነው ነገር የለም ” ሲል መልሷል።

በወቅቱ ሲሰራ ከዞን አስተዳደር ተፈቅዶ እንደሆነ መረዳቱንም ገልጿል።

መስጂዱ ሲሰራ ምን ያህል ወጪ እንደጨረሰ ላቀረብነው ጥያቄ ኮሜቴው በሰጠን ምላሽ፣ የወጪውን መጠን እንዳልጠየቀ፣ ሆኖም በተማሪዎች መዋጭ ከተጀመረ በኋላ ህብረተሰቡ ተጨምሮበት ተውጣጥቶ የተሰራ እንደነበር ኮሚቴው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ 
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
💔561517😭106😡54👏48🕊29🤔21🥰10😢9🙏8
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሜክሲኮ ወደ ሚገኘው የፌደራል ፖሊሲ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንደሚወስዱት የፈዴራል ፖሊሶች ነግረውን ወደዚያ እየሄድን ነው" - ባለቤታቸው ወ/ሮ ስንታየሁ አለማየሁ። የቀድሞ ሰላም ሚንስትር ደኤታ አቶ ታዬ ዳንዳዓ ዛሬ ጠዋት ከችሎት በኃላ ከመኖሪያ ቤታቸው በፖሊስ መወሰዳቸውን ባለቤታቸው ገለፁ። የአቶ ታዬ ባለቤት ወ/ሮ ስንታየሁ አለማየሁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት ከጠዋት የችሎት ቀጠሯቸውን ተከታትለው…
#Update

አቶ ታዬ ደንዳዓ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነፃ የተባሉባቸው ሁለት የክስ ጭብጦች ተሻረ።

የአቶ ታዬ ዳንዳዓ የህግ ጥበቃ አበራ ንጉሱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት " የፈዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት አቶ ታዬ ነፃ የተባሉባቸው ክሶችን በመሻር እንዲከላከሉ ትዛዝ ሰጥቷል " ብለዋል።

" የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀር ሽብር እና ህግ መንግስት ጉዳዮች ችሎት 30/12/2016 ዓ/ም አቶ ታዬ ከተከሰሱባቸው ሶስት ክሶች ውስጥ አንደኛው ፤ ' በመንግስት ሀላፊነት ላይ እያሉ የህዝብ እና የመንግስት የተሰጣቸውን ሀላፊነት ወደ ጎን በመተው የፀር ሰላም ሀይሎች ሀሳብ ተቀባይነት እንዲያገኝ በማሰብ በግል ማህበራዊ ትስስር ገፃቸው የታጠቁ ሃይሎችን የሚደግፍ መልዕክት አስተላልፈዋል ' የሚለውን መከላከል ሳያስፈልጋቸው ነፃ ተብለው ነበር " ብለዋል ጠበቃቸው።

አክለውም የዋስትና መብታቸው በሰበር ሰሚ ችሎት ከተጠበቀላቸው በኃላ ከህግ ፍቃድ ውጭ የጦር መሳሪያ ይዘው መገኘት የሚለው አንዱን የክስ ጭብጥ እንዲከላከሉ በተሰጠው ብይን መሰረት በከፍተኛ ፍርድ ቤት እየተከታተሉ ነበር።

ሆኖም ዛሬ አቶ ታዬ ነፃ በተባሉበት ክስ ጭብጦች ላይ ቅሬታ እንዳለው የገለፀው አቃቤ ህግ " ተከሳሹ በቂ ማስረጃ ቀርቦባቸው መከላከል ሲገባቸው ነፃ መባላቸው አግባብነት የለውም " በማለት ለፈዴራል ጠቅላይ  ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ይግባኝ ሰሚ ችሎት የኢትዮጵያ ወንጀል ህግ አንቀጽ 251/ሐ ጠቅሶ ይግባኝ ማለቱን ተከትሎ ጉዳዩን ሲከታተል የነበረው ፍርድ ቤት ዛሬ ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ነፃ የተባሉበትን ክሶች ብይን ሽሮ እንዲከላከሉ አዟል።

ጠቃቸው አቶ አበራ ንጉሱ ፤ ለውሳኔ ብቻ ዛሬ በአምስተኛ ተለዋጭ ቀጠሮ መገኘታቸውን ጠቅሰው ችሎቱ የስር ፍርድ ቤት ውሳኔን ሽሮ እንዲከላከሉ ብይን በመስጠቱ ቅሬታ እንዳላቸው ገልፀው በቀጣይ ለሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ እንደሚሉ ገልፀዋል።

ይሁንና ደንበኛቸው ችሎት ተከታትለው ከተለያዩ ከቀትር በኃላ 10:00 በፌደራል ፖሊስ መወሰዳቸውን ከአቶ ታየ ባለቤት በስልክ እንደተነገራቸው ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
792😡336😭66🤔40😢33🕊18👏15💔13😱9🙏8🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አቶ ታዬ ደንዳዓ ከዚህ ቀደም በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነፃ የተባሉባቸው ሁለት የክስ ጭብጦች ተሻረ። የአቶ ታዬ ዳንዳዓ የህግ ጥበቃ አበራ ንጉሱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደተናገሩት " የፈዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት አቶ ታዬ ነፃ የተባሉባቸው ክሶችን በመሻር እንዲከላከሉ ትዛዝ ሰጥቷል " ብለዋል። " የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ የፀር ሽብር እና ህግ መንግስት…
#Update

አቶ ታዬ ደንደአ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ ፍርድ ቤት አዘዘ።

የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ታዬ ደንደአ የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ጉዳያቸውን ማረሚያ ሆነው እንዲከታተሉ ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፖሊስ አቶ ታዬን ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርቧል።

አቃቤ ህግ ከዚህ ቀደም የተዘጉ ሁለት ክሶችን ጨምሮ መዝገቡ በፍርድ ቤቱ እንዲቀሳቀስ ጠይቋል።

አቶ ታየ ደንደአ ለፍርድ ቤቱ " ትናንት የተያዝኩበት መንገድ ልክ አይደለም የኤሌክትሮኒክስ መገልገያዎቼ ተይዘዋል፤ ከጠበቃዬ ጋር ተማክሬ መቅረብ ነበረብኝ " በማለት ተከራክረዋል።

የግራና ቀኙ ክርክር የመረመረው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ አንደኛ የሽብር እና ህገ መንግስታዊ ጉዳዮች ችሎት የተከሳሹ የዋስትና መብት እንዲነሳ ወስኗል።

ተከሳሹ ጉዳያቸውን በማረሚያ ቤት ሆነው እንዲከታተሉ ትዕዛዝ በመስጠት የመከላከያ ምስክርን ለመስማት ለሰኔ 30 ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን ኤፍ ኤም ሲ ዘግቧል።

የአቶ ታዬ ደንደአ ባለቤት ምን አሉ ?

" ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቦ እንደነበር ነግሮኛል " - ወይዘሮ ስንታየሁ አለማየሁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ

አቶ ታዬ ደንዳዓ ዛሬ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን ባለቤታቸው ወይዘሮ ስንታየሁ አለማየሁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ወ/ሮ ስንታየሁ እንደተናገሩት አቶ ታዬን ዛሬ ጠዋት ለመጠየቅ ወደ ፈዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ እንዳመሩና ለሰዓታት ጠብቀው እንዳገኙዋቸው ገልፀዋል።

አቶ ታዬም ፍርድ ቤት ቀርበው እንደነበሩና የዋስትና መብታቸውን ተከልክለው በማረምያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ መደረጉን ነግሮኛል ብለዋል።

ወ/ሮ ስንታየሁ አክለውም ባለቤታቸውን አቶ ታየን ለምን እንደታሰረ ሲጠይቁት ዛሬ ፍርድ ቤት በነበረው ችሎት ፖሊስ ለፍርድ ቤት ሲያስረዳ " አቶ ታየ እየሸሹ እያሉ በቁጥጥር ስር አውያቸዋለሁ " ማለቱን ነግሮኛል ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ታዬ ዛሬ ያለ ህግ ጠበቃቸው ፍርድ ቤት እንደ ቀረቡ እና እስካሁንም ከጠበቃቸው ጋር እንዳልተገናኙ ባለቤታቸው ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
559😢501😡137😭40🤔36👏19🕊15🙏8😱5🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#ፍትሕ " አያንቱ ላይ የግብረ-ስጋ ድፍረት ወንጀል የፈጸመው ግለሰብ በፖሊስ አዛዥ ተባባሪነት እንዲሸሽ ተደርጓል " - የአያንቱ ታላቅ ወንድም 🚨 " ፖሊስ አዛዡን ከኃላፊነት ከማዉረድ የዘለለ ደፋሪዉን ለሕግ አቅርቦ ዉሳኔ የማሰጠት ስራ አልተሰራም !! " በሲዳማ ክልል፤ በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሻፋሞ ወረዳ ሹሮ ተብሎ በሚጠራዉ አከባቢ በእንጀራ አባቷ ቤት እያደገች የነበረች የ13 ዓመቷ ታዳጊ አያንቱ…
#Update

የ13 ዓመቷ አያንቱ ቱና ላይ የግብረስጋ ድፍረት በፈጸም የተጠረጠረውና ከአካባቢው ተሰውሮ የቆየው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል።

ቤተሰቦቿ " ድምፅ ስለሆናችሁን እናመሰግናለን ! " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም በሲዳማ ክልል፤ ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን፤ ሻፋሞ ወረዳ አያንቱ ቱና የተባለችን የ13 ዓመት ታዳጊ ላይ የግብረ ስጋ ድፍረት ወንጀል በመፈጸም የተጠረጠረው ወጣት በወቅቱ የወረዳዉ ፖሊስ አዛዥ በነበረ ግለሰብ አማካኝነት ከአከባቢው እንዲሰወር መደረጉን መረጃ አጋርቶ ነበር።

አያንቱም አካላዊና ስነ ልቦናዊ ጉዳት ደርሶባት ከትምህርት ገበታዋ ተለይታ በጣሊታ የህፃናት ማቆያ ከ1 ዓመት በላይ እንድትቀመጥ መደረጉ ቅር እንዳሰኛቸው ቤተሰቦቿ ድምጻቸውን አሰምተው ነበር።

ከአንድ ዓመት በላይ ዱካው ጠፍቶ የሰነበተዉ ተጠርጣሪ በትናትናዉ ዕለት ፖሊስ ባደረገዉ ክትትል ከኦሮሚያ ክልል፤ ምዕራብ አርሲ ዞን፤ ኮኮሳ ወረዳ " ሀንገሳ " ተብሎ ከሚጠራዉ አከባቢ በቁጥጥር ስር መዋሉን የሻፋሞ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር ሙሴ አወል ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የሲዳማ እና ኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ተጠሪጣሪዉን በቁጥጥር ስር በማዋል ረገድ በትብብር መስራታቸዉን የገለፁት አዛዡ የተጠርጣሪውን ወላጅ አባት ጨምሮ ተባባሪና ልጁን በመሸሸግ ሂደት ተሳታፊ የነበሩ የቤተሰቡ አባላትም በቁጥጥር ስር መዋላቸዉን ገልፀዋል።

" ብቸኛዋ እህቴ በግድ ተደፍራ ፍትህ ሳታገኝ ከ1 ዓመት በላይ በየቆችበት ወቅት ተረጋግቼ ትምህርቴን እየተማርኩ አልነበረም " ያለን ወንድሟ ጴጥሮስ ቱና " በልጁ መያዝ እኔም ሆነ ቤተሰቦቼ ደስተኛ ሆነናል፤ ከዚህ በኋላ ሙሉ ትኩረቴን ወደ ትምህርቴ አደርጋልሁ " ሲል ተናግሯል።

በቤተሰቡ ስምም " ድምጽ ስለሆናችሁን አመሰግናለሁ " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1.99K👏471🙏97😭74💔57😡31😢22🥰21🕊21
TIKVAH-ETHIOPIA
" የደረሰው ጉዳት ከባድ በመሆኑ ገና እያጣራን ነው " - የቡለን ወረዳ ፖሊስ ፅ/ቤት አዛዥ ➡️ " የባንክ ቤቱን ስራ አስኪያጁን ከቤቱ ይዘውት መጥተው ቢሮውን አስከፍተው ባንኩን ዘረፉት ፤ ባለሀብቶችንም በስም እየጠሩ ውጣ እያሉ ሲጠሩ ሰምቻለሁ የዘረፉትን ንብረት በኤፍ ኤሳር መኪናና በሞተር እየጫኑ ዘና ብለው ነው ወጥተው የሄዱት "  - የአይን እማኝ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል መተከል ዞን፤ ቡለን…
#Update

" ታጣቂዎቹ አሁንም እያስፈራሩን ነው " - የቡለን ከተማ ነዋሪዎች

የቡለን ከተማ ነዋሪዎች አሁንም ከፍተኛ ስጋት ላይ መሆናቸውን ገለፁ።

አስተያየታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት ነዋሪዎቹ " ከከተማው በቅርብ ርቀት የሚገኙት የሸኔ  ታጣቂዎች አሁንም ማስፈራሪያ እየላኩ ነው "  ብለዋል።

ትላንት ግንቦት 29/2017 ዓ.ም ከማለዳው እስከ ረፋዱ ድረስ ወደ ከተማው ዘልቀው የገቡት ታጣቂዎች  በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ካደረሱ በኃላ የዘረፉትን ንብረት በመኪና ጭነው ወስደዋል ብለዋል።

" ታጣቂዎቹ ይህንን ያህል ጥቃት ሲፈፅሙ በቂ የመንግስት የፀጥታ ሀይል በከተማው አልነበረም " ያሉት ነዋሪዎቹ " ከጥቃቱ በኃላ ግን የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከተማውን ተቆጣጥሮታል " ብለዋል።

" ከዋና ከተማው ቡለን በእግር የ2 ሰዓት መንገድ በሚወስድ ርቀት ' ጎንጎ ' በተባለ ቦታ ላይ ታጣቂዎቹ ይገኛሉ " ሲሉ የገለፁት ነዋሪዎቹ  " አሁንም በማህበርዊ ሚዲያ ' በቅርቡ እንመለሳለን ' እያሉ መልዕክት እያስተላለፉ ነው መንግስት አስፈላጊውን ጥበቃ ያድርግልን " ሲሉ ተማፅነዋል።

" ባለፈው ሳምንትም ተመሳሳይ የማስፈራሪያ መልዕክት ሲልኩ ሰምተን ለመንግስት አመራሮች ተናግረን ነበር " የሚሉት ነዋሪዎቹ  " ' ተራ አሉባልታ ነው ' በማለት የተቀበለን አልነበረም አሁንም ጥቃቱ  እንዳይደገም " ሲሉ ጠይቀዋል።

በቡለን ከተማ ትላንት ስለተፈፀመው ጥቃት ዝርዝር መረጃ ለማግኘት ለቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ሀሩን ዑመር የእጅ ስልካቸው ላይ ደውለን ብንጠይቃቸውም ምርመራ ላይ መሆናቸውንና አሁን ላይ ምንም መናገር እንደማይፈልጉ ገልፀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ባሕር ዳር
#TikvahEthiopiaFamilyBahirdar

@tikvahethiopia
571😢177😭67😡37🕊24🙏11🥰7😱6👏4
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

“ የሊቀ መንበሩን ባለቤት ጨምሮ ሦስት የታገቱ ሰዎች የደረሱበት አይታወቅም። 11ዱን ለቀዋቸዋል። ከታጋቾች አንዱ አጎቴ ነው። ይኑር ይሙት የምናውቀው ነገር የለም” - ነዋሪና የታጋች ቤተሰብ

➡️ “ በዞኑ ሽርካ ወረዳ 2016 ዓ/ም ጀምሮ ካህናትን ጨምሮ 113 ንጹሐን ተጨፍጭፈዋል። ከ30 በላይ ታፍነው ተወስደው የደረሱበት አልታወቀም ” - እናት ፓርቲ


በአርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ/ም በተፈጸመው ጥቃት ከሟቾች ባሻገር ታግተው የተወሰዱ የቀበሌው ሊቀ መንበር ባለቤትና እህትን ጨምሮ ሦስት ሰዎች ያሉበት እንደማይታወቅ ነዋሪዎችና የታጋች ቤተሰብ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

አንድ የስፍራው ነዋሪ በሰጡን ቃል፣ “ የሊቀ መንበሩን ባለቤት ጨምሮ ሦስት ያታገቱ ሰዎች የት እንደደረሱ አይታወቅም። ከታገቱት መካከል 11 ሰዎች ተለቀዋል” ብለዋል።

በሰሞንኛው ጥቃት ታግተው ተወስደው የነበሩ 11 ሰዎች መለቀቃቸውን ገልጸው፣ “የአንጎዴቼ ቀበሌን ሊቀመንበር ስልጠና ብለው ወስደውት ስልጠና ላይ እያለ ነው ቤቱን አቃጥለው፣ ከብቱን ነድተው የወሰዷቸው” ሲሉም አስረድተዋል።

ሌላኛው ነዋሪና የታጋች ቤተሰብ፣ “አንደኛው ተጎጂ እኔ ነኝ። አካባቢያችንን ለቀን ወደ አጎራባች ቦታ ሂደናል። ያለው ችግር በጣም አስጊና ነው። መከላከያ ቢኖርም ህዝቡ በደረሰው ሰቆቃ ምክንያት በጣም ተደናግጧል” ብለዋል።

“ከታጋቾች አንዱ አጎቴ ነው። አቶ ሳህሌ ሙሉጌታ ይባላል። እስካሁን ድረስ ድምጹ የለም። ይኑር ይሙት የምናውቀው ነገር የለም” ያሉት ነዋሪው፣ የታገቱት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ/ም መሆኑን አስታውሰዋል።

በእለቱ 11 ሰዓት ከ20 ተኩሱ እንደተከፈተ አስታውሰው፣ “ቀን የዋለው ሚሊሻ ከአዳሪ ሚሊሻዎች ጋር እየተቀያየረ ባለበት ሰዓት ነው ጥቃት አድራሾቹ ቀበሌዋን ከዳር እስከ ዳር ነበር የያዟት” ብለዋል።

“አንድ ሚሊሻ ‘ተበላህ፣ ተበላህ ሰዎቹ እዚጋ ደርሰዋል’ አለኝ። ሮጠን ነው ያመለጥነው። ታጣቂው ቀድሞኝም ነበር፤ እላዬ ላይ አውቶማቲክ ነው የከፈተብኝ፤ ከማሰሮ ውስጥ እንደሚወጣ ባቄላ ነው የተረፍኩት” ሲሉም አስረድተዋል።

ሥጋት ያደረባቸው የሥፍራው ነዋሪዎች እቃቸውን እየጫኑ ወደ አቅራቢያ ከተሞች እየተፈናቀሉ መሆኑን፣ ሰሞኑን በአካባቢው መከላከያ ቢኖርም ቁጥራቸው አስተኛ እንደሆነ የገለጹት ነዋሪዎቹ፣ “መንግስት ይየን፤ አሁንስ ዋስትናችን ምንድን ነው?” ሲሉ ጠይቀዋል።

እናት ፓርቲ ስለጥቃቱ ባወጣውና ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መግለጫ ምን አለ?

በጀጁ ወረዳ አንጎዴቼ ቀበሌ ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ/'ም “ሸኔ” በደረሰው ጥቃት “ተገደሉ” ስለተባሉት ንጹሐን የተሰማውን ሀዘን ገልጾ፣ “ታፍነው የተወሰዱ ንጹሐን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እንጠይቃለን” ብሏል። 

በጥቃቱ ካህኑን ጨምሮ ሌሎች ሰዎች እንደተገደሉ ጠቅሶ፣ “ሁለት ሰዎች በጥይት ተመትተው በሕክምና ላይ ሲሆኑ፣ ሌሎች 5 ሰዎች ታፍነው እስካሁን የደረሱበት አልታወቀም” ሲል ገልጿል።

ስለሰሞኑ ግድያም፣ “የካህኑና ምዕመናኑ ግድያ የዘር ተኮር ጭፍጨፋ ፕሮጀክቱ አካልም ነው” ብሏል። 

በዞኑ ጥቃት በተደጋሚ መፈጸሙ እንደሚታወቅ ጠቅሶ፣ “በዞኑ ሽርካ ወረዳ 2016 ዓ/ም መስከረም ጀምሮ ካህናትን ጨምሮ 113 ንጹሐን በግፍ ተጨፍጭፈዋል። ከ30 በላይ ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን የደረሱበት አልታወቀም” ሲልም ፓርቲው በመግለጫው አትቷል። (የፓርቲው ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
 
ቲክቫህ ኢትዮጵያ 
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
484😭472😡36🕊11🙏10👏5😱5😢5🥰3🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

" ከ564 በላይ የወላይታ ድቻ ደጋፊዎች ከእስር ተፈተዋል " - የወላይታ ዞን ፖሊስ

➡️ " የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስና የአዲስ አበባ ፖሊስ በወቅቱ የወሰዱት እርምጃ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ አድርጓል ! "

በአዲስ አበባ ፖሊስ በእስር ላይ የነበሩ የወላይታ ድቻ ደጋፊዎች መለቀቃቸውን የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ አሳውቋል።
 
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰኔ 01/2017 ዓ/ም የድቻ ደጋፊዎች በከተማ ውስጥ ተዘዋዉረዉ በፈጠሩት አለመግባባት ምክንያት የአዲስ አበባ ፖሊስ ከፌዴራል ፖሊስና ሌሎች የጸጥታ አካላት ጋር በመሆን በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው የድቻ ደጋፊዎች መካከል፦
- በቂርቆስ ክፍሌ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ፑፑላሬ ፖሊስ ጣቢያ 245 ፣
- ቦሌ ቡልቡላ 68 ፣
- በየካ ክፍለ ከተማ 50፣
- ልደታ ክፍለ ከተማ 201 የተጠረጠሩ የወላይታ ድቻ ደጋፊዎች የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ ከኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስና ከአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ ጋር በመነጋገር ከእስር እንዲፈቱ መደረጋቸው ተገልጿል።

አጠቃላይ በተለያየ ክፍለ ከተማ የታሰሩ  ከ564 በላይ የወላይታ ድቻ ደጋፊዎች ናቸው ከእስር የተፈቱት።

የዞኑ ፖሊስ " የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስና የአዲስ አበባ ፖሊስ የድቻ ደጋፊዎች በከተማዉ ውስጥ በተለያየ ቦታ ተንቀሳቅሰዉ የፈጠሩትን ያለመግባባት ለመፍታት በወቅቱ የወሰዱት እርምጃ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ ያስቀረ በመሆኑ ያስመሰግናል " ብሏል።

አሁን ላይ ሌሎች የተወሰኑ በወንጀል ድርጊት ተጠርጥረው ጉዳዮች በፍርድ ሂደት የሚገኙ መኖራቸው ተጠቁሟል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
1.22K😡287👏66😭43💔38🕊36🤔27🙏25🥰21😢19😱14
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሕገ ወጥ እስር ማለት እንዲህ አይነት እስር ነው። እስሩ ኢ-ሥነ ስርዓታዊም ነው ፤ ኢ-ሕገ መንግስታዊም ነው " - የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ጠበቃ በፓሊስ ቁጥጥር ሥር የዋለው የጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ ጠበቃ፣ " ጋዜጠኛው አላግባብ በፖሊስ ኃይል ነው አሁን ታስሮ ያለው እንጂ በህግ ኃይል አይደለም " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ጠበቃው ቤተማርያም ኃይሉ በሰጡት ቃል፣ " ይህ ሰው 'ይፈታ'…
#Update

ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ የዋስትና መብት ተከብሮ ከእስር እንዲፈታ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰበር ሰሚ ችሎት ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 5/ 2017 ዓ.ም. ወስኗል።

ሰበር ሰሚ ችሎቱ በዛሬ ውሎው የስር ፍርድ ቤቶች የሰጡትን የጋዜጠኛው በዋስ ይለቀቅ ውሳኔ ማጽናቱን ጠበቃው አቶ ቤተማሪያም አለማየሁ ገልጸዋል።

ጋዜጠኛው ለሦስተኛ ጊዜ በዋስ ከእስር እንዲፈታ በፍርድ ቤቶች ቢወሰንም ከእስር አለመፈታቱን ጠበቃው ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ተናግረዋል።

@tikvahethiopia
368😭129😡56👏20💔17🤔15😢12🙏10🥰5😱3🕊2
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ዛሬ በህንድ አህመዳባድ በደረሰው የቦይንግ 787-8 ድሪምላይነር አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የሞቱ ሰዎች ወደ 294 እንደሚጠጉ ተነግሯል።

በአውሮፕላሉ ውስጥ ከነበሩ 242 ሰዎች አንድ ሰው በህይወት ሲተርፍ ሌሎች ህይወታቸው አልፏል።

አውሮፕላኑ በተነሳ በትንሽ ደቂቃ የተከሰከሰው በአንድ የህክምና ኮሌጅ ውስጥ ነው። በኮሌጁ በሚገኝ ህንጻ ውስጥ የነበሩ የጤና ተማሪዎች ህይወታቸው ማለፉን ተከትሎ አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 294 አካባቢ መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

@tikvahethiopia
😭1.5K406💔170😢92🙏40🕊38😱21🤔18👏16🥰10