#NewsAlert
እስካሁን ድረስ ምንም የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ኬዝ ሳይመዘገብባት የቆየችው ደቡብ ሱዳን ዛሬ የመጀመሪያውን የቫይረሱን ታማሚ ሪፖርት አድርጋለች።
የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የተገኘባት ግለሰብ የ29 ዓመት ወጣት ስትሆን FEBRUARY 28 ከኢትዮጵያ ወደ ደቡብ ሱዳን የገባችና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደርገላት የነበረች እንደሆነ ተገልጿል።
ምንጭ፦ ሮይተርስ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እስካሁን ድረስ ምንም የኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ኬዝ ሳይመዘገብባት የቆየችው ደቡብ ሱዳን ዛሬ የመጀመሪያውን የቫይረሱን ታማሚ ሪፖርት አድርጋለች።
የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የተገኘባት ግለሰብ የ29 ዓመት ወጣት ስትሆን FEBRUARY 28 ከኢትዮጵያ ወደ ደቡብ ሱዳን የገባችና በለይቶ ማቆያ ውስጥ ክትትል ሲደርገላት የነበረች እንደሆነ ተገልጿል።
ምንጭ፦ ሮይተርስ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#RepublicOfSouthSudan
የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ዛሬ መጋቢት 27/2012 ዓ/ም ያወጣው መግለጫ እንዳመለከተው የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የተገኘባት የ29 ዓመት ወጣት ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) በኩል ከኔዘርላንድ ወደ ደቡብ ሱዳን የገባች ናት።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የደቡብ ሱዳን ምክትል ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ዛሬ መጋቢት 27/2012 ዓ/ም ያወጣው መግለጫ እንዳመለከተው የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] የተገኘባት የ29 ዓመት ወጣት ከአንድ ወር በፊት በአዲስ አበባ (ኢትዮጵያ) በኩል ከኔዘርላንድ ወደ ደቡብ ሱዳን የገባች ናት።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#BREAKING
በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡
አንዲት የ60 ዓመት ታማሚ መጋቢት 19 ፣ 2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማከሚያ ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ሲሆን በመጋቢት 22፣ 2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው መረጋገጡ ይታወሳል፡፡
ይሁንና ከመጋቢት 22 አንስቶ ላለፉት ስድስት ቀናት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል፡፡
የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በህልፈተ ህይወታቸው የተሰማውን ሀዘን ገልጾ ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል፡፡
#MoH #EPHI #EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮሮና ቫይረስ ምክንያት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታውቋል፡፡
አንዲት የ60 ዓመት ታማሚ መጋቢት 19 ፣ 2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምልክት ታይቶባቸው በለይቶ ማከሚያ ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው የነበረ ሲሆን በመጋቢት 22፣ 2012 ዓ.ም በኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው መረጋገጡ ይታወሳል፡፡
ይሁንና ከመጋቢት 22 አንስቶ ላለፉት ስድስት ቀናት በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ ሲሆን በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል፡፡
የኢፌዴሪ ጤና ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በህልፈተ ህይወታቸው የተሰማውን ሀዘን ገልጾ ለቤተሰቦቻቸው መፅናናትን ተመኝቷል፡፡
#MoH #EPHI #EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጅቡቲ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 59 ደረሱ!
በጅቡቲ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 252 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 8 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በሀገሪቱ ያሉ አጠቃላይ የቫይረሱ ተጠቂዎች 59 ደርሰዋል።
በተጨማሪ አንድ (1) ሌላ በቫይረሱ የተያዘ ሰው ከበሽታው ማገገሙን የጅቡቲ የጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም አጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 9 ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጅቡቲ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 252 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 8 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በሀገሪቱ ያሉ አጠቃላይ የቫይረሱ ተጠቂዎች 59 ደርሰዋል።
በተጨማሪ አንድ (1) ሌላ በቫይረሱ የተያዘ ሰው ከበሽታው ማገገሙን የጅቡቲ የጤና ሚኒስቴር አሳውቋል። በዚህም አጠቃላይ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 9 ደርሷል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrAbiyAhemedAli
በኮቪድ-19 ሕይወቷ ላለፈው ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ እና ወዳጆች ከልቤ መጽናናትን እመኛለሁ። ነፍሷ ዘላለማዊ ረፍትን ታግኝ።
ዜናውን የሰማችሁ ሁሉ #እንድትረጋጉ እና የወጡትን መመሪያዎች በጥብቅ እንድትከተሉ አሳስባለሁ።
የሚገጥመንን ሁኔታ በጋራ ለማስተናገድ በምንዘጋጅበት በዚህ ጊዜ፣ በእምነት ጸንተን ቫይረሱ በማኅበረሰባችን መካከል እንዳይሠራጭ በትጋት ልንሠራ ያስፈልጋል።
አካላዊ ርቀታችሁን ጠብቁ። እጆቻችሁን በሚገባ ታጠቡ። በምትችሉት መንገድ ሁሉ ለሌሎች ድጋፍ አድርጉ።
(የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮቪድ-19 ሕይወቷ ላለፈው ኢትዮጵያዊት ቤተሰብ እና ወዳጆች ከልቤ መጽናናትን እመኛለሁ። ነፍሷ ዘላለማዊ ረፍትን ታግኝ።
ዜናውን የሰማችሁ ሁሉ #እንድትረጋጉ እና የወጡትን መመሪያዎች በጥብቅ እንድትከተሉ አሳስባለሁ።
የሚገጥመንን ሁኔታ በጋራ ለማስተናገድ በምንዘጋጅበት በዚህ ጊዜ፣ በእምነት ጸንተን ቫይረሱ በማኅበረሰባችን መካከል እንዳይሠራጭ በትጋት ልንሠራ ያስፈልጋል።
አካላዊ ርቀታችሁን ጠብቁ። እጆቻችሁን በሚገባ ታጠቡ። በምትችሉት መንገድ ሁሉ ለሌሎች ድጋፍ አድርጉ።
(የኢፌዴሪ ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse
ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ የሀዘን መግለጫ፦
በዛሬው እለት በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምክንያት በሀገራችን የአንድ ሰው ህይወት ሊያልፍ ችሏል። ታማሚዋ በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ለይቶ ማቆያ ህክምና ሲደረግላቸው ነበር።
ከቀናት በፊት ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል ተዛውረው ጥብቅ ክትትል ሲደረግላቸው የነበረ ቢሆንም በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል።
በዚህም የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በእራሴና በጤና ሚንስቴር ስም እየገለጽኩ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከጤና ሚኒስቴር የተሰጠ የሀዘን መግለጫ፦
በዛሬው እለት በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምክንያት በሀገራችን የአንድ ሰው ህይወት ሊያልፍ ችሏል። ታማሚዋ በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ለይቶ ማቆያ ህክምና ሲደረግላቸው ነበር።
ከቀናት በፊት ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል ተዛውረው ጥብቅ ክትትል ሲደረግላቸው የነበረ ቢሆንም በዛሬው እለት ህይወታቸው አልፏል።
በዚህም የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በእራሴና በጤና ሚንስቴር ስም እየገለጽኩ ለቤተሰቦቻቸው እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TikurAnbessaSpecializedHospital
ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክትትል የሚፈልጉ ተመላላሽ ታካሚዎቹ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ ባሉበት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል።
የሆስፒታሉ የሕክምና ባለሙያዎች በተመላላሽ ታካሚዎቹ ሞባይል ስልኮች ላይ በመደወል ማማከርን ጨምሮ አስፈላጊውን አገልግሎት እየሰጧቸው መሆኑን ሆስፒታሉ ገልጿል።
#EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ክትትል የሚፈልጉ ተመላላሽ ታካሚዎቹ ለኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተጋላጭ እንዳይሆኑ በማሰብ ባሉበት አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መጀመሩን አስታውቋል።
የሆስፒታሉ የሕክምና ባለሙያዎች በተመላላሽ ታካሚዎቹ ሞባይል ስልኮች ላይ በመደወል ማማከርን ጨምሮ አስፈላጊውን አገልግሎት እየሰጧቸው መሆኑን ሆስፒታሉ ገልጿል።
#EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር ሊያ ታደሰ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ዙሪያ የሰጡትን መግለጫ በዚህ አጭር ቪድዮ መከታተል ትችላላችሁ። ቪድዮ ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የተገኘ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኬንያ በኮቪድ-19 የተያዙ ሰዎች 142 ደረሱ!
የኬንያ ጤና ሚንስቴር መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ አስራ ስድስት (16) ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኬንያ ጤና ሚንስቴር መግለጫ እየሰጠ ይገኛል። ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ አስራ ስድስት (16) ተጨማሪ ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrMercyMwangangi
በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ አስራ ስድስት (16) ሰዎች ውስጥ አስራ አምስቱ (15) ኬንያውያን ሲሆኑ አንደኛው (1) ናይጄሪያዊ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በቫይረሱ መያዛቸው ከተረጋገጠ አስራ ስድስት (16) ሰዎች ውስጥ አስራ አምስቱ (15) ኬንያውያን ሲሆኑ አንደኛው (1) ናይጄሪያዊ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrMercyMwangangi
በኬንያ ባለፉት 24 ሰዓት 530 የላብራቶሪ ምርመራ የተደርገ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ነው 16 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው። እስካሁን ኬንያ ውስጥ በአጠቃላይ 3,836 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኬንያ ባለፉት 24 ሰዓት 530 የላብራቶሪ ምርመራ የተደርገ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ ነው 16 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው። እስካሁን ኬንያ ውስጥ በአጠቃላይ 3,836 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጓል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#MoH_KENYA
ትላንት ኬንያ ውስጥ ተጨማሪ አራት (4) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በመረጋገጡ የትላንትናውን ሪፖርት ጨምሮ አሁን ሪፖርት ከተደረገው ጋር አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 142 መድረሳቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። የኬንያ ጤና ሚኒስቴርም ቀደም ብሎ ያወጣውን የ138 ሰዎች ኬዝ ሪፖርት በማስተካከል 142 አድርጎታል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ትላንት ኬንያ ውስጥ ተጨማሪ አራት (4) ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው በመረጋገጡ የትላንትናውን ሪፖርት ጨምሮ አሁን ሪፖርት ከተደረገው ጋር አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች 142 መድረሳቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። የኬንያ ጤና ሚኒስቴርም ቀደም ብሎ ያወጣውን የ138 ሰዎች ኬዝ ሪፖርት በማስተካከል 142 አድርጎታል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኬንያ የኮሮና ቫይረስ ወቅታዊ ሁኔታ፦
• በቫይረሱ የተያዙ ታማሚዎች ብዛት - 142
• ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ያገገሙ - 4
• ህይወታቸው ያለፈ - 4
ምንጭ፦ የኬንያ ጤና ሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
• በቫይረሱ የተያዙ ታማሚዎች ብዛት - 142
• ከበሽታው ሙሉ በሙሉ ያገገሙ - 4
• ህይወታቸው ያለፈ - 4
ምንጭ፦ የኬንያ ጤና ሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ ፦
• በኬንያ 530 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 16 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
• በጅቡቲ 252 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 8 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
• በኢትዮጵያ 59 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
• በኬንያ 530 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 16 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
• በጅቡቲ 252 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 8 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
• በኢትዮጵያ 59 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 5 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ላይቤሪያ የ2 ሰዎችን ሞት ሪፖርት አደረገች!
በላይቤሪያ ባለፉት 24 ሰዓት የ2 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ከሟቾቹ አንዱ የጤና ባለሞያ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ ቀደም ሪፖርት ከተደረገው ሞት ጋር አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 3 ደርሷል።
በተጨማሪ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 3 በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችም አስራ ሶስት (13) ደርሰዋል።
#SamiraSawlani
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በላይቤሪያ ባለፉት 24 ሰዓት የ2 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ከሟቾቹ አንዱ የጤና ባለሞያ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ከዚህ ቀደም ሪፖርት ከተደረገው ሞት ጋር አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 3 ደርሷል።
በተጨማሪ ባለፉት 24 ሰዓት በተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ 3 በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችም አስራ ሶስት (13) ደርሰዋል።
#SamiraSawlani
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጣልያን የ24 ሰዓት የኮቪድ-19 ሪፖርት ፦
ባለፉት 24 ሰዓት በጣልያ የ525 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ቁጥሩ ባለፉት 5 ቀናት ሪፖርት ከተደረጉት #ዝቅተኛ ነው። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 15,887 ደርሷል።
በተጨማሪ በ24 ሰዓት 4,316 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ወደ 128,948 ከፍ ብሏል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባለፉት 24 ሰዓት በጣልያ የ525 ሰዎች ሞት ተመዝግቧል። ቁጥሩ ባለፉት 5 ቀናት ሪፖርት ከተደረጉት #ዝቅተኛ ነው። አጠቃላይ የሟቾች ቁጥር 15,887 ደርሷል።
በተጨማሪ በ24 ሰዓት 4,316 ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል። አጠቃላይ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎችን ቁጥር ወደ 128,948 ከፍ ብሏል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኮሮና ቫይረስ የሚስፋፋበትን ፍጥነት ተመልከቱ ፦
• ጥር 27/2012 ዓ/ም አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 28,000
• የካቲት 27/2012 ዓ/ም አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 98,500
• ዛሬስ ? ዛሬ አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 1,245,207
ቁጥራዊ መረጃው ዓለም አቀፍ ሁኔታን የሚመለከት ነው!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
• ጥር 27/2012 ዓ/ም አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 28,000
• የካቲት 27/2012 ዓ/ም አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 98,500
• ዛሬስ ? ዛሬ አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር - 1,245,207
ቁጥራዊ መረጃው ዓለም አቀፍ ሁኔታን የሚመለከት ነው!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#BREAKING
በኢትዮጵያ ሁለተኛው ሞት ተመዘገበ!
በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምክንያት በሀገራችን በዛሬው እለት ሁለተኛ ሰው ህይወት ማለፉን ስገልጽ በከፍተኛ ሀዘን ነው። ታማሚው በለይቶ ማቆያ ከመጋቢት 24 ጀምሮ ህክምና ሲደረግላቸው የነበርና ከገቡበት ቀን ጀምሮ በጽኑ ህሙማን ክፍል ክትትል ላይ የነበሩ ናቸው። በዚህም የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በእራሴና በጤና ሚንስቴር ስም እየገለጽኩ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።
(የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ሁለተኛው ሞት ተመዘገበ!
በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምክንያት በሀገራችን በዛሬው እለት ሁለተኛ ሰው ህይወት ማለፉን ስገልጽ በከፍተኛ ሀዘን ነው። ታማሚው በለይቶ ማቆያ ከመጋቢት 24 ጀምሮ ህክምና ሲደረግላቸው የነበርና ከገቡበት ቀን ጀምሮ በጽኑ ህሙማን ክፍል ክትትል ላይ የነበሩ ናቸው። በዚህም የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን በእራሴና በጤና ሚንስቴር ስም እየገለጽኩ ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን እመኛለሁ።
(የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia