TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.2K photos
1.5K videos
211 files
4.1K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ኦሮሚያ ክልል አምስት መቶ ሺህ (500,000) የአፍ መሸፈኛ (ማስክ) እና 48,000 ሊትር ሳኒታይዘር እንዳዘጋጀ ገልጿል። በቅርቡ ለነዋሪዎች እንደሚያሰራጭ አሳውቋል።

በኦሮሚያ የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል በአራት አካባቢዎች የለይቶ ማቆያዎች ተዘጋጅተዋል። ለህክምና የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችም ተሟልተዋል ተብሏል።

በክልል የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ምልክት የታየበትን ሰው ጥቆማ ለመስጠት የ24 ሰዓት አገልግሎት የሚሰጥ ነፃ የስልክ መስመር 6955 ይፋ ተደርጓል።

#etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

ኢትዮጵያ ውስጥ ከገቡ በኃላ ኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የተረጋገጠው ሁለት ጃፓናውያን ነገ ጠዋት ' በአውሮፕላን አምቡላንስ ' ከኢትዮጵያ ወደ ጃፓን ይወሰዳሉ።

[ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

በአዋሽ ሰባት የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ቀድሞ ለመከላከል የሚረዱ ስራዎች እየተሰሩ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ከእነዚህም ስራዎች ውስጥ ለቫይረሱ ሊያጋልጡ የሚችሉ ከ100 በላይ የሺሺ መጠቀሚያ እቃዎች እንዲቃጠሉ ተደርገዋል።

11 የጫት ንግድ ቤቶች ደግሞ ለቫይረሱ በሚያጋልጥ ሁኔታ ሰዎች ሰብስበው ሲያስቅሙ ተደርሶባቸው ታሽገዋል፤ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ ይቀጥላልም ተብሏል።

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ በመላው አውስትራሊያ ግድ የማያሰኙ ግልጋሎት ሰጪዎች ከዛሬ ጀምሮ ዝግ እንደሚሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አስታውቀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከዛሬ ጀምሮ ምግብ ቤቶች ፣ ቡና ቤቶች ፣ የአካል እንቅስቃሴ መስሪያ ሥፍራዎች ፣ ሲኒማ ቤቶች፣ ሆቴሎች ፣ ክለቦች ፣ የቤት ውስጥ ስፖርት ማዘውተሪያዎች፣ የመዝናኛ ቤቶችና የእምነት ቤቶች ዝግ እንደሚሆኑ ገልፀዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ የገበያ አዳራሾች ክፍት በመሆናቸው አውስትራሊያውያን 'ኃላፊነት በጎደለው' ሁኔታ በሸመታ ሊራኮቱ እንደማይገባ አሳስበዋል።

#ኤስቢኤስ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጣልያን በ24 ሰዓት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ 651 ሰዎች ሞተዋል። አጠቃላይ በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥርም 5,476 ደርሷል። በሌላ በኩል 5,560 አዲስ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ በ24 ሰዓት የተመዘገበ ሲሆን አጠቃላይ ተጠቂዎችም 59,138 ደርሰዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የብሪታንያ ዜጎች 'ኃላፊነት በጎደለው' ሁኔታ እንዳይሸምቱ ፣ በቂ ምግብ ስላለም ለሌሎች እያሰቡ ፣ ኃላፊነት በተሞላበት መልኩ እንዲገዙ ጥሪ ተላልፎላቸዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

የሰላም ሚኒስቴር አመራሮች እና ሰራተኞች በአዲስ አበባ ላምበረት መነኻሪያ ተገኝተዉ የኮሮና ቫይረስ የመከላከል ስራ አከናወኑ

ክብርት የሰላም ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚልን ጨምሮ የሚኒሰቴር መስሪያ ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች ዛሬ መጋቢት 13 ቀን 2012 ዓ.ም ጠዋት በላምበረት መነሃሪያ ተገኝተዉ ለመንገደኞች እጅ የማስታጠብ ፣ የሳይነተሪ ዕደላ እና ስለ ቫይረሱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎችን አከናወናዉነዋል ።

ክብርት የሰላም ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ኢትዮጵያዊያን ከተባበርንና ተጋግዘን ከሰራን የማንሻገረዉ ችግር፣ የማንፈታዉ ፈተና የለም ብለዋል ።

አሁን በአገር ደረጃ የተፈጠረዉን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ሁላችንም ትኩረት ሰጥተን ሳንረበሽና ሳንደነግጥ ተገቢዉን ጥንቃቄ በማድረግ ችግሩን ማለፍ እንደሚቻል ክብርት ሚኒስትሯ ተናግረዋል ።

ምንጭ፦ የሰላም ሚኒስቴር
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከቼክ ሪፐብሊክ የቲክቫህ አባል፦

በቼክ ሪፐብሊክ አስፈላጊው ጥንቃቄ እየተደረገ እንኳን ቫይረሱ እየትስፋፋ ነው ኢትዮጵያ ያላችሁ ወገኖቼም የተነገሩትን መመሪያዎች እና የጥንቃቄ መልዕክቶች በኃላፊነት፣ በእኔነት ስሜት መተግበር አለብን። ሁላችንም አንድ ላይ የምንቆምበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፤ ሳንፈራ ጥንቃቄዎችን እናድርግ ብሎናል በቼክ ሪፐብሊክ የሚገኘው የቤተሰባችን አባል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጀርመን ቻንሰለር አንጌላ ሜርክል በኮሮና ቫይረስ ከተጠቁ ዶክተር ጋር መገናኘታቻውን ተከትሎ ቻንስለሯ ኳራንታይን ላይ መሆናቸውን ስካይ ኒውስ ዘግቧል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ቻይና የጸረ ኮሮና ቫይረስ ክትባት የመጀመርያ ደረጃ ሙከራ መጀመሯን አስታውቃለች። ቻይና ይህን ያስታወቀችው አሜሪካ ተመሳሳይ የክትባት ሙከራ ውጤታማነቱን በሲአትል ግዛት በሰዎች ላይ ከጀመረች በኋላ ነው።

በዓለም አቀፍ ደረጃ በዘርፉ በምርምር ስራ ላይ የተሰማሩ ሳይንትስቶች ገዳዩን ቫይረሱን ለመከላከል ብርቱ ምርምር በማድረግ መሆናቸውንም የፈረንሳዩ የዜና ወኪል አጃንስ ፍራንስ ፕረስ ዘግቧል።

ቻይና ሙከራዋ እንደጎርጎርሳዊያኑ አቆጣጠር እስከ ዓመቱ መጨረሻ ሊዘልቅ እንደሚችል አስታውቃለች። በዚህም የኮቪድ 19 ክትባት የመጀመርያው ምዕራፍ ሙከራ ተሳታፊ በጎ ፈቃደኞች ክትባቱን መውሰድ ጀምረዋል።

በጎ ዕድሜአቸው ከ18-60 ባለው ውስጥ የተካተተቱ 108 በጎ ፈቃደኞች በፕሮጀክቱ ውስጥ ተሳታፊ እየሆኑ ናቸው። በጎ ፈቃደኞቹ ሁለም የኮሮና ተሕዋሲ መጀመርያ ከተቀሰቀሰባት ማዕከላዊ የሕዋን ከተማ መሆናቸውን ዘገባው አመልክቷል።

ምንጭ፦ DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሩዋንዳ የኮቪድ-19 ኬዝ 19 ደርሷል!

በሩዳንዳ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቂዎች ቁጥር 19 ደርሰ። በዛሬው ዕለት 2 አዲስ የኮቪድ-19 ኬዞች ሪፖርት ተደርገዋል። አንደኛው የ32 ዓመት የሩዋንዳ ዜጋ ሲሆን ከዱባይ,UAE March 19 ወደ ሩዋንዳ እንደገባ ተገልጿል፤ ሁለተኛውም የ34 ዓመት የሩዋንዳ ዜጋ ሲሆን MARCH 20 ከዱባይ,UAE ወደ ሩዋንዳ የገባ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ትላንት ምሽት በሩዋንዳ መንግስት የተላለፈው ጥብቅ ትዕዛዝ ተግባራዊ መሆን ጀምሯል። በቪዲዮው ላይ የምትመለከቱት ከዚህ ቀደም በርካታ ሰዎች የሚተረማመሱበት የMusanze ባስ ማቆሚያ ነው። ዛሬ ባዶ ሆናል!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Italy #Russia #COVID19

ሩስያ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] ወረርሽኝ በብርቱ እየተጠቃች ያለችውን ጣልያንን ለመደገፍ ሐኪሞችን እና የህክምና ቁሳቁስ እየላከች መሆኗን አስታውቃለች።

ሩስያ በወረርሽኙ ክፉኛ የተጠቃችዉን ጣልያንን ለመደገፍ በዘጠኝ የጭነት አውሮፕላኖች የሕክምና ባለሞያዎች እና ቁሳቁስ ወደስፍራው ለማጓጓዝ በችካሎቭስኪ ወታደራዊ ሰፈር ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ገልጻለች።

በተልዕኮው ስምንት (8) ተንቀሳቃሽ የሕክምና ቡድኖችን ጨምሮ የሕክምና ቁሳቁስ እና የጸረ ቫይረስ [COVID-19] ርጭት ተሽከርካሪዎች ያካተተ መሆኑን ተገልጿል።

#AFP #DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አሜሪካ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] እየታመሰች ነው። በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 32,356 ደርሷል። የሚገርመው 8,114 ኬዝ የተመዘገበው በ24 ሰዓት ነው። በቫይረሱ የሞቱት ሰዎች ቁጥርም 414 ደርሰዋል።

የአለም ሀገራት መሪ ነኝ ምትለዋ ፣ በሀብት ቁጥር አንዷ፣ በሁሉ ነገር ቀዳሚ ነኝ ፣ በቴክኖሎጂው ፣ በህክምናዬ ሁሉ ነገሬ የዘመነ ነው የምትለው አሜሪካ ለኮሮና ቫይረስ ተንበርክካለች። የተጠቂዎች ቁጥር ከዛሬ ነገ ይገታል ሲባል እየጨመረ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#KENYA

በጎረቤት ሀገር ኬንያ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቂዎች ቁጥር 15 ደርሷል። 8ቱ ዛሬ ሪፖርት የተደረጉ ናቸው። አፍሪካ ውስጥ ያሉ የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ተጠቂዎች ቁጥር እያደር እየጨመረ ነው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ጣልያን!

"በሌላው ሀገር እየሆነ ያለውን የምትመለከቱ ከሆነ በእናተ በሀገራቹ ማድረግ ያለባችሁ ምርጫ ሳይሆን ግዴታ ነው። መጀመሪያ ምን ማድረግ እንዳለብን ግራ ተጋብተን ነበር አሁን ላይ ግን ምን እየሆነ እንዳለ አውቀናል። እኛ ጋር የሆነው በእናተ ላይ ሊሆን ይችላልና ለመግታት ማድረግ ያለባችሁን ከወዲሁ ጀምሩ አትቁሙ! የአንዱ ተሞክሮ ለሌላው ትምህርት ነውና ጥንቃቄን መሰረት አድርጋችሁ ተንቀሳቀሱ" - ዶ/ር ኢማኑኤላ #EBC

የኮሮና ቫይረስን [ኮቪድ-19] መግታት ቀላል ነው፦

- የእጅዎን ንፅህና በአግባቡ ይጠብቁ
- ሰዎች በተሰበሰቡበት አይሂዱ
- ማህበራዊ ርቀትዎን ይጠብቁ
- በተጨናነቁ የትራንስፖርት አመራጮችን አይጠቀሙ
- የጤና ባለሞያዎችን ምክር ያዳምጡ
- የጤና ሚኒስቴር መምሪያዎችን ይተግብሩ
- ስለ ኮቪድ ትክክለኛ መረጃ ከWHO፣ ከጤና ሚኒስቴር እና ከህበረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ብቻ ያግኙ!

ተጨማሪ ፦ 8335 / 952 ነፃ የስልክ መስመሮች ናቸው!

ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኝላችኃለን!
ሰላም እደሩ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
እንደምን አደራችሁ?

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንዚት አገልግሎት ከዛሬ ጀምሮ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር የተሳፋሪውን ቁጥር 50 በመቶ ቀንሶ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ ተሰምቷል።

የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ፥ እርምጃው የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር ያለመ መሆኑን አስታውቀዋል።

አያይዘውም ህብረተሰቡ የትራንስፖርት ጥግግት መጠንን በመቀነስ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠር የድርሻውን እንዲወጣም ጠይቀዋል።

ምንጭ፡ ኤፍ ቢ ሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ በሚመጡ ሁሉም መንገደኞች ላይ ተፈፃሚ የሚሆነው የ14 ቀናት በልዩ ማቆያ ማዕከል የመቆየት ግዴታ ተጀምሯል።

የጤና ሚኒስቴር ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ መንገደኞች በስካይ ላይት እና ጊዮን ሆቴሎች ከዛሬ ጀምሮ ለ14 ቀናት ተለይተው ይቆያሉ ብሏል። ቆይታቸውም በራሳቸው ወጪ የሚሸፈን ይሆናል ተብሏል።

ዲፕሎማቶች በኤምባሲዎቻቸው ተለይተው እንደሚቆዩ የጤና ሚኒስቴር ገልጿል። የትራንዚት ተጓዦችም እስከ ቀጣዩ ጉዟቸው ድረስ በስካይ ላይት ሆቴል ተለይተው ይቆያሉም ነው የተባለው።

ምንጭ፦ ኤፍ ቢ ሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia