TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.1K photos
1.5K videos
211 files
4.09K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
በደብሊን የተደረገ አቀባበል! በሴቶች ብቻ የተመራው የበረራ ቡድን ደብሊን ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። የበረራ ቡድኑ በአሁን ሰዓት ወደ USA ዋሺንግተን ዲሲ በረራውን ቀጥሏል። ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየርመንገድ @tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በሰላም ገብተዋል!

በሴቶች ብቻ የተመራው በረራ #USA ዋሺንግተን ዲሲ አርፏል። በስፍራውም በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋን ጨምሮ በርካቶች የደመቀ አቀባበል አድርገውላቸዋል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ArbaMinch

በአርባምንጭ ከተማ ለሚገነባው አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ዌልነስ ሪዞርት ግንባታ ጅማሮ የሚሆን የቦታ ቅየሳ ስራዎችን ባለሞያዎች ማከናወን ጀምረዋል።

በአርባ ምንጭ ከተማ በአፍሪካ ከሲሼልስ ከሚገኘው ግዙፉ ሆቴልና ሪዞርት በመቀጠል አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆቴልና ሪዞርት እንደሚገነባ ከዚህ ቀደም ይፋ መደረጉ ይታወቃል፡፡

ግንባታው በሚከናወነበት ስፍራ የኩባንያው ባለቤቶችና የውጪ ሀገር ባለሃብቶች ቦታው ድረስ በመምጣት ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት ያላቸው ለሆቴሉና ሪዞርት ግንባታ ስራዎች ዝግጅት የሚረዱ የመረጃ ግብዓቶችን የመሰብሰብ ስራ ሲከናወኑም ቆይተዋል፡፡

ከዚሁ ግንባታ ስራ ጋር በተያያዘ በዚህም ሳምንት ከቀን 25 ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የቦታ ልኬትና ማመቻቸት ስራዎች በአለም-አቀፍ የግንባታ ባለሙያዎች ግንባታው በሚያርፍበት ስፍራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡

#BrishZewde #TikvahFamily
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች፦

- ባንግላዴሽ በዛሬው ዕለት 3 በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ግለሰቦች በሀገሯ መገኘታቸውን አረጋግጣለች። ግለሰቦቹ 20-35 የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ናቸው። ሁለቱ ከጣልያን የተመለሱ ሲሆኑ አንደኛው ደግሞ የግለሰቦቹ ቤተሰብ ነው።

- በኳታር በኮሮና ቫይረስ የተጠቁ ተጨማሪ 3 ግለሰቦች መኖራቸው ተረጋግጧል። በዚህም በኳታር በኮሮና የተጠቁ ሰዎች 12 ደርሰዋል።

- በኢራን በኮሮና ቫይረስ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 194 ደርሰዋል። በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ደግሞ 6,566 ሆነዋል። በ24 ሠዓት ውስጥ 743 አዲስ ኬዞች ተመዝግበዋል።

- በሳዑዲ አረቢያ ተጨማሪ 4 ግለሰቦች በኮሮና ቫይረስ መጠቃታቸው ተሰምቷል። ይህም በሀገሪቱ በኮሮና የተጠቁ ሰዎችን ቁጥር 11 አድርሶታል።

- በአርጀንቲና በኮሮና ቫይረስ የሞተ ግለሰብ መኖሩ ዛሬ ሪፖርት ተደርጓል። በሀገሪቱ 9 ሰዎች በቫይረሱ ተይዘዋል።

ከደቂቃዎች በኃላ በአፍሪካ ያለው ሁኔታ እንመለከታለን!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች ከአፍሪካ፦

- በአፍሪካ ኮሮና ቫይረስ የተዛመተባቸው ሀገራት 9 ናቸው። ሀገራቱም፦ ግብፅ፣ አልጄሪያ፣ ሞሮኮ፣ ቶጎ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሴኔጋል፣ ካሜሮን፣ ቱኒዝያ ናቸው።

- እስካሁን ድረስ በቶጎ፣ ቱኒዝያ፣ ናይጄሪያ አንድ አንድ ሰው ብቻ ነው በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተያዘው።

- ካሜሮን እና ሞሮኮ በሀገራቸው ሁለት የኮሮና ቫይረስ ኬዞች አሉ፤ በደቡብ አፍሪካ 3 በሴኔጋል ደግሞ 4 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተዋል።

- በግብፅ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 49 ናቸው፤ በአልጄርያ ደግሞ 19 ሰዎች ተጠቅተዋል።

- ከላይ በተዘረዘሩት 9 የአፍሪካ ሀገራት ውስጥ በዛሬው ዕለት የተመዘገበ አዲስ የኮሮና ቫይረስ ኬዝ የለም።

- በኢትዮጵያ ምንም የኮሮና ቫይረስ ኬዝ የለም። ከቀናት በፊት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሰጠው መግለጫ የኮሮና ቫይረስ ተመሳሳይ ምልክት የታየባቸው ሁለት ሰዎች በለይቶ ማቆያ ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን እስካሁን የግለሰቦቹ ውጤት አልተገለፀም።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ዶክተር ሊያ ታደሰ፦ "የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች [UAE] ውስጥ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሁለት ኢትዮጵያውያን የኤምሬትስ ነዋሪ ሲሆኑ በዛ ሀገር ለአመታት የኖሩ እና በቅርቡም ጉዞ ያላደረጉ መሆኑን አረጋግጠናል" #EliasMeseret @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrLiaTadesse

በUAE በኮሮና ቫይረስ እንደተያዙ በሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር ከተነገረላቸው ሁለቱ ኢትዮጵያውያን መካከል አንደኛው ግለሰብ ድጋሚ ተመርምረው ቫይረሱ እንደሌለባቸው ተረጋግጧል ሲሉ ዶክተር ሊያ ታደሰ ዛሬ ጥዋት በትዊተር ገፃቸው አሳውቀዋል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
እናት ፓርቲ! ዛሬ የካተት 29 / 2012 ዓ/ም 'የእናት ፓርቲ' መስራች ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል። በጉባኤው ተሳታፊ የነበሩ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላትም ጉባኤውን ከላይ በፎቶው እንደምትመለከቱት አጋርተዋል። @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዛሬ በእናት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡ የእናት ፓርቲ አመራሮች፦

- ፕሬዝደንት ፡ ዶ/ር ኃ/ኢየሱስ ሙሉቀን
- ም/ፕሬዝደንት ፡ ዶ/ር ሠይፈሥላሴ አያሌው
- ጠቅላይ ፀሐፊ ፡ አቶ ጌትነት ወርቁ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETHIOPIA

UNICEF ለኢትዮጵያ ለኮሮና ቫይረስ [COVID-19] በሽታ ዝግጅት እና መከላከል የሚውል የኢንፌክሽን መከላከያ ኬሚካል (በረኪና) ለግሷል፡፡

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኮሮና ቫይረስ በሽታ (የኮቪድ-19) አስመልክቶ የተዘጋጀ መግለጫ፦

በሀገር ዓቀፍ ደረጃ በመካሄድ ላይ ያለ የዝግጅት ሁኔታ፦

• በሁሉም ወደ ሀገር መግቢያ ጣቢያዎች አራት መቶ ስልሳ ሰባት ሺህ ሁለት መቶ ሰማኒያ (467,280) በሙቀት መለያ (ኢቦላና ኮቪድ-19 በማጣመር) አልፈዋል፡፡

• በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በ7ቱ መግቢያዎች ሁለት መቶ ሰባ ሰባት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሰባት (277,977) በሙቀት መለያ ያለፉ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ሀምሳ ስምንት (6,858) በሽታውን ሪፖርት ካደረጉ ሃገራት የመጡ ናቸው፡፡

• በሽታውን ሪፖርት ከተደረገባቸው አገራት የመጡ ተጓዞች የጤና መረጃ ቅጽ ከመሙላታቸው በተጨማሪ ባሉበት ቦታ ለ14 ቀናት የሚደረግ የጤና ክትትል ተደርጎላቸው ያጠናቀቁ አንድ ሺህ ዘጠና ሶስት (1093) ክትትል ተደርጎላቸው ያጠናቀቁ ናቸው፡፡ በአሁኑ ሰዓት አንድ ሺህ ሃያ አንድ (1021) የሚሆኑት ደግሞ የጤና ክትትል ላይ ይገኛሉ፡፡

More https://telegra.ph/COVID19-03-08

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#EthiopianAirlines

አቶ ተወልደ ገብረማርያም፦

"በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሴቶች የተለየ ማበረታቻ፤ ልዩ ድጋፍ የለም። ሴት ሰራተኞቻችን የተለየ ድጋፍም አይፈልጉም ምክንያቱም ችሎታና ብቃት አላቸው። ባህላዊና ታሪካዊ በሴቶች ላይ ያለውን የተዛባ አስተሳሰብ ማሻሻል ችለናል። በኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ሰዓት በሁሉም ዘርፍ ከአብራሪነት ጀምሮ ሴቶች በስኬት ላይ ናቸው። ይህንንም ማሳካት የቻልነው በጥረታችን ነው። አስቸጋሪ ኃላፊነቶችን ሴቶች በስኬት በማጠናቀቅ በአየር መንገዱ ቀዳሚዎች ናቸው።"

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ሰሜን ኮሪያ ውስጥ ከኮሮናቫይረስ ስጋት ጋር በተያያዘ በለይቶ ማቆያ እንዲቀመጡ ተፈርዶባቸው የነበሩ 60 ያክል ዲፕሎማቶች ተለቀው ሩስያ ገቡ።

ወደ ሩስያዋ ቭላዲቮሶስቶክ ከተማ ያቀናው አውሮፕላን በውስጡ በርካታ የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን ይዞ ነበር።

ሰሜን ኮሪያ፤ ከዋና ከተማዋ ፒዮንግያን ተነስቶ ወደ ተቀረው ዓለም አውሮፕላን ሲበርባት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ይህ የመጀመሪያው ነው። የበረራ ቁጥር KOR271 በምሥራቃዊቷ የሩስያ ከተማ ሰኞ ማለዳ አርፏል።

ኤምባሲዎች ውስጥ የሚሠሩ በርካታ ሰዎች ወርሃ ጥርና የካቲት መባቻን ከሚኖሩበት ግቢ ንቅንቅ እንዳይሉ ተደርገው ነበር።

ሰሜን ኮሪያ ኮሮናቫይረስ እንዳይስፋፋ በሚል ስጋት የውጭ አገር ዲፕሎማቶችን ሰብስባ ለይቶ ማቆያ ውስጥ እንዲገቡ ያደረገችው ባለፈው ወር ነበር።

#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Forbes

የፎርብስ መጽሔት የአፍሪካ እትም የሆነው ፎርብስ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴን ከ50 ተጽዕኖ ፈጣሪ የአፍሪካ ሴቶች አንዷ አድርጎ መርጧቸዋል፡፡

መጽሔቱ ከፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ በተጨማሪ የሶልሬብልስ ኩባንያ መሥራችና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ወ/ሮ ቤተልሔም ጥላሁንንም ከ50ዎቹ ተጽዕኖ ፈጣሪ የአፍሪካ ሴቶች መካከል አድርጎ መርጧታል፡፡

#ኢቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

የጣልያን እግር ኳስ በኮሮና ቫይረስ መረበሹን ቀጥሏል !

የኮሮና ቫይረስ በዘንድሮው የውድድር ዓመት ካለፉት አመታት ሳቢነቱን ጨምሮ አዝናኝ የሆነውን የጣልያን ሴርያ እያደበዘዘው ይገኛል ፡፡

በትላንትናው እለት ተጠባቂ መርሀ ግብሮች በዝግ ስታዲየም ሲከሄዱ ከወደ ፔስካራ ክለብ የተሰማው ደግሞ መነጋገሪያ ሆኗል ፡፡

የፔስካራ ቡድን በሴሪ ቢ ጨዋታ በቤንቬኒቶ ሲሸነፉ ከጨዋታው አስቀድሞ የትንፋሽ መከላከያ ( Protective masks ) አድርገው ሲገቡ በእለቱ የመሀል ዳኛ ጨዋታውን በዚህ መልኩ ማድረግ እንደማይችሉ ተገልፆላቸዋል ፡፡

Join : https://t.iss.one/joinchat/AAAAAFb8M0pNEZTiGM68rg

@tikvahethiopia @tikvahethsport
የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዶሃ!

ኮሮና ቫይረስን በተመለከተ ወቅታዊ መረጃዎች፦

- ቀጠር ከህንድ ፣ ፊሊፒንስ ፣ ስሪላንካ ፣ ባንግላዴሽ ፣ ፓኪስታን፣ ቻይና፣ ግብጽ፣ ኢራን፣ ኢራቅ፣ ሌባኖስ፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ሶሪያ፣ ኔፓል፣ ታይላንድ በሚነሱ ግለሰቦች ላይ ክልከላ ጥላለች።

- በበሽታው የተጠቁ ግለሰቦች 15 የደረሱ ሲሆን፣ በተለይም በትላንትናው እለት ቫይረሱ ከተገኘባቸው ሶስት ግለሰቦች ጋር ንክኪ ያደረጉ ግለሰቦች እየተፈለጉ አስፈላጊው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑ ተገልጿል።

- የበሽታው ምልክቶች በሚስተዋሉበት ጊዜ 16000 ነጻ የስልክ መስመር ላይ ደውሎ ማሳወቅ፤

- በት/ቤቶች አካባቢ ያለው ስጋት ዝቅተኛ በመሆኑ የመማር ማስተማር ስራው ከከፍተኛ ጥንቃቄ ጋር እንዲቀጥል ተደርጓል። ሆኖም ግን በመንግስት ት/ቤቶች ጠዋት ጠዋት የሚደረጉ ስብሰባዎች እንዲቋረጡ ተወስኗል።

- መወሰድ ያለባቸው ጥንቃቄዎች የመኪና መስኮቶችን መክፈት፣ ከግለሰቦች ጋር በእጅ መጨባበጥን ጨምሮ የሚደረጉ ንክኪዎችን በተቻለ መጠን ማስወገድ፣ እጅን ቢያንስ ለ 20 ሰከንዶች ያክል ደጋግሞ መታጠብ፣ ሲያስሉ እና ሲያስነጥሱ አፍን እና አፍንጫን በክንድዎ መሸፈን፤

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE

የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን 858 የሚሆኑ ለአራት ወር ያሰለጠናቸው የክልል ልዩ ኃይል ሰራዊት አባላት በብር ሸለቆ መደበኛ ሠራዊት ማሰልጠኛ የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር አሊ ዲኒ በተገኙበት ማስመረቁን ከፌዴራል ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡

ዓላማውም በክልሉ የሚካሄደውን 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ ከማድረግ አንፃር ያለውን የሰው ኃይል እጥረት በመቅረፍ የክልሉንና የህዝቡን ፀጥታ እና ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ በመጠበቅ በክልሉ ያለውን የህግ የበላይነት የበለጠ ለማጠናከር ያለመ ነው ተብሏል።

#EBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#COVID19

ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ዛሬ ጠዋት የኮሮና ቫይረስን አጠቃላይ ሁኔታ ለመከታተል ከተቋቋመው ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡

ቡድኑ ከሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች የተውጣጣ ሲሆን፤ በፌደራል እና በክልል ደረጃ በጤና ሚኒስቴር አማካኝነት እየተመራ ቁልፍ የመከላከልና የቅድመ ዝግጁነት ሥራ በማከናወን ላይ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

መረጋጋት፣ የጤና ሚኒስቴር ያዘጋጀውን የመከላከል መመሪያ ተግባራዊ ማድረግና ማኅበረሰባችን በመከላከልና ቅድመ ዝግጅት ላይ ያለውን ግንዛቤ ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አንስተዋል፡፡

ኮሚቴው ተያያዥ የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ተጽዕኖዎችን በውጤታማነት ለመቋቋም የሚቻልባቸውን አማራጮችም እንደሚያፈላልግ እስካሁን በወሰድናቸው ርምጃዎች እተማመናለሁ ብለዋል ዶ/ር አብይ።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአፍሪካ በኮሮና ቫይረስ የተመዘገበው ሞት!

በግብፅ በኮሮና ቫይረስ ተይዞ ህክምና ሲደረግለት የነበረው ጀርመናዊ ቱሪስት መሞቱና በአፍሪካ አህጉር የመጀመርያው ሆኖ መመዝገቡ ተገልጿል፡፡ የ60 አመቱ ጀርመናዊ ግብፅ በደረሰ ከሳምንት በኋላ ምልክቱ እንደታየበት ተጠቅሷል፡፡

ግለሰቡ በወቅቱ ሬድ ሲ ሪዞርት ሆስፒታል ገብቶ የህክምና ክትትል በማድረግ ላይ እንደነበረ ዘገባው አመልክቷል፡፡ ኤኤፍፒ የዜና ወኪል ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው የአተነፋፈስ ስርዓቱ በአጣዳፊ የሳንባ ምች መጎዳቱን ያሳያል ተብሏል፡፡ በሽተኛው ወደ ገለልተኛ ማቆያ ክፍል መዘዋወር ፈቃደኛ እንዳልሆነ ከገለፀ በኋላ ሊሞት እንደቻለ ተነግሯል፡፡

#BBC #AFP
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#PMOEthiopia

ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት አመራር እና አባላት ጋር ውይይት አድርገዋል። ለሀገራቸው ያላቸው ፍቅር አስደናቂ መሆኑንም ተናግረዋል። አያይዘውም አባላቱ ያላቸውን ሁሉ ለሀገራቸው ለመስጠት ቆራጥ እንደሆኑ መናገራቸውን ነው የተገለፀው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia