#HAWASSA
የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፦
- ሐሰተኛ የብር ኖቶች ህትመት ሲያካሂድ የነበረ አንድ የውጭ ዜግነት ያለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሏል።
- ፖሊስ ሰሞኑን ባካሄደው ክትትል በተደራጀ መንገድ የተሰረቁ ስምንት ሁለት እግር ብስክሌቶች እና አራት መኪኖችም በቁጥጥር ስር በማዋል በ27 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
- ተሸከርካሪዎቹ ከተሰረቁ በኋላ ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ለማስመሰል ሰነድ ተዘጋጅቶላቸው ለአገልግሎት እንዲውሉ ይደረግ ነበር።
- ተለይቶ ያልተገለፀ የውጭ አገር ዜግነት ያለው ግለሰብም ሐሰተኛ የብር ኖቶች ህትመት ሲያካሂድ ከነሙሉ ቁሳቁሱ መያዙን መምሪያው ያስታወቀ ሲሆን ምርመራም እየተካሄደበት ነው።
- አብዛኞቹ የስርቆት ወንጀሎች በረቀቀ መንገድ የተፈፀሙ መሆናቸውን የጠቆመው ፖሊስ፤ ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው ጥረት የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ እንደነበርም ተገልጿል፡፡
[የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ ኢቢሲ]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሐዋሳ ከተማ ፖሊስ መምሪያ፦
- ሐሰተኛ የብር ኖቶች ህትመት ሲያካሂድ የነበረ አንድ የውጭ ዜግነት ያለው ግለሰብ በቁጥጥር ስር አውሏል።
- ፖሊስ ሰሞኑን ባካሄደው ክትትል በተደራጀ መንገድ የተሰረቁ ስምንት ሁለት እግር ብስክሌቶች እና አራት መኪኖችም በቁጥጥር ስር በማዋል በ27 ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ እያካሄደ ይገኛል።
- ተሸከርካሪዎቹ ከተሰረቁ በኋላ ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ለማስመሰል ሰነድ ተዘጋጅቶላቸው ለአገልግሎት እንዲውሉ ይደረግ ነበር።
- ተለይቶ ያልተገለፀ የውጭ አገር ዜግነት ያለው ግለሰብም ሐሰተኛ የብር ኖቶች ህትመት ሲያካሂድ ከነሙሉ ቁሳቁሱ መያዙን መምሪያው ያስታወቀ ሲሆን ምርመራም እየተካሄደበት ነው።
- አብዛኞቹ የስርቆት ወንጀሎች በረቀቀ መንገድ የተፈፀሙ መሆናቸውን የጠቆመው ፖሊስ፤ ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር ለማዋል በተደረገው ጥረት የህብረተሰቡ ሚና ከፍተኛ እንደነበርም ተገልጿል፡፡
[የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር፣ ኢቢሲ]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
"የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ፈተና በታብሌት በመጠቀም የምንፈትን እንደሆነ ላበስር እወዳለሁ" - ዶ/ር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ [የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር]
#ArtsTv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ArtsTv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና ኦላይን ይሰጣል ወይ?
አዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ በቅርቡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ አዳሪ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኦንላይን ይሰጣል ማለታቸውን ከአርትስ ቴሌቪዥን ሰምተናል።
ይህንን ተከተትሎ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፈተናዎች ኤጀንሲ አምርተን ነበር፡፡ በዛም አንድ የተቋሙን ሰራተኛ በጉዳዩ ዙሪያ ጠይቀን በሰጡን መረጃ መሰረት የሀገር አቀፍ የፈተናዎች ኤጀንሲ እስካሁን ፈተናው በወረቀት እንደሚሆን ታሳቢ አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸውልናል፡፡
ነገር ግን አሁን ላይ በተለይም ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ከመጡ በኀላ አገልግሎቱን መስጠት በሚቻልባቸው አከባቢዎች ፈተናውን በኦንላይን ለመስጠት የታሰበ ነገር እንዳለ እንጂ እስካሁን የተረጋገጠ ነገር እንደሌለና መስሪያቤታቸውም በዚህ ጉዳይ በሚዲያ አንዳንድ ነገሮችን ከመስማት ውጪ ምንም ተጨባጭ ነገር እንዳልደረሰው አክለው ነግረውናል፡፡
#TikvahFamily
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዶክተር ኢንጅነር ጌታሁን መኩሪያ በቅርቡ በቤንሻንጉል ጉሙዝ አዳሪ ትምህርት ቤትን በመረቁበት ወቅት የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና በኦንላይን ይሰጣል ማለታቸውን ከአርትስ ቴሌቪዥን ሰምተናል።
ይህንን ተከተትሎ ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ፈተናዎች ኤጀንሲ አምርተን ነበር፡፡ በዛም አንድ የተቋሙን ሰራተኛ በጉዳዩ ዙሪያ ጠይቀን በሰጡን መረጃ መሰረት የሀገር አቀፍ የፈተናዎች ኤጀንሲ እስካሁን ፈተናው በወረቀት እንደሚሆን ታሳቢ አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸውልናል፡፡
ነገር ግን አሁን ላይ በተለይም ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ከመጡ በኀላ አገልግሎቱን መስጠት በሚቻልባቸው አከባቢዎች ፈተናውን በኦንላይን ለመስጠት የታሰበ ነገር እንዳለ እንጂ እስካሁን የተረጋገጠ ነገር እንደሌለና መስሪያቤታቸውም በዚህ ጉዳይ በሚዲያ አንዳንድ ነገሮችን ከመስማት ውጪ ምንም ተጨባጭ ነገር እንዳልደረሰው አክለው ነግረውናል፡፡
#TikvahFamily
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
#GERD
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕና የግብፁ አቻቸው አብዱል ፋታህ አል ሲሲ በታላቁ ኅዳሴ ግድብ ድርድር ዙሪያ በስልክ መምከራቸው ተነግሯል።
በውይይቱም ትራምፕ ግብፅ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ተገኝታ በግድቡ ድርድር ሰነድ ላይ መፈረሟን አድንቀዋል። ይሁንና ካይሮ የፈረመችበትን ሰነድ አዲስ አበባ ካለማወቋም ባሻገር በጋራ የተዘጋጀ ባለመሆኑ እንደማትቀበለው ግልፅ አቋማን ማሳወቋ እና የዩናይትድ ስቴትስን ለግብፅ የመወገን አካሄድ መተቸቷ ይታወሳል።
ትራምፕ የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተቀበለውን የስምምነት ሰነድ ግብፅ መፈረሟ በግድቡ ድርድር ላይ ለመስማማት ያላትን ጥሩ ፍላጎት እና የፖለቲካ ታማኝነት ያሳየ ሲሉ ማወደሳቸውን ከካይሮ ቤተ መንግሥት የወጣ መግለጫ አትቷል።
[አሐዱ ቴሌቪዥን]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕና የግብፁ አቻቸው አብዱል ፋታህ አል ሲሲ በታላቁ ኅዳሴ ግድብ ድርድር ዙሪያ በስልክ መምከራቸው ተነግሯል።
በውይይቱም ትራምፕ ግብፅ ባለፈው ሳምንት በዋሽንግተን ተገኝታ በግድቡ ድርድር ሰነድ ላይ መፈረሟን አድንቀዋል። ይሁንና ካይሮ የፈረመችበትን ሰነድ አዲስ አበባ ካለማወቋም ባሻገር በጋራ የተዘጋጀ ባለመሆኑ እንደማትቀበለው ግልፅ አቋማን ማሳወቋ እና የዩናይትድ ስቴትስን ለግብፅ የመወገን አካሄድ መተቸቷ ይታወሳል።
ትራምፕ የኢትዮጵያ መንግሥት ያልተቀበለውን የስምምነት ሰነድ ግብፅ መፈረሟ በግድቡ ድርድር ላይ ለመስማማት ያላትን ጥሩ ፍላጎት እና የፖለቲካ ታማኝነት ያሳየ ሲሉ ማወደሳቸውን ከካይሮ ቤተ መንግሥት የወጣ መግለጫ አትቷል።
[አሐዱ ቴሌቪዥን]
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
#USA #EGYPT #GERD #SUDAN #ETHIOPIA
የግብፅ ፕሬዝዳንት ቃል-አቀባይ ባሳም ራዲ አሜሪካ የግድቡ ስምምነት በ3ቱም አገራት እስኪፈረም ከኢትዮጵያ ፣ ሱዳንና ግብፅ መተባበሯን እንደምትቀጥል ትራምፕ ለፕሬዝዳንት አል-ሲሲ በስልክ መናገራቸውን ገልፀዋል። የፕሬዘዳንቱ ቃል አቀባይ ግብጽ ስምምነቱን መፈረሟን አረጋግጠዋል።
#EsheteBekele
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የግብፅ ፕሬዝዳንት ቃል-አቀባይ ባሳም ራዲ አሜሪካ የግድቡ ስምምነት በ3ቱም አገራት እስኪፈረም ከኢትዮጵያ ፣ ሱዳንና ግብፅ መተባበሯን እንደምትቀጥል ትራምፕ ለፕሬዝዳንት አል-ሲሲ በስልክ መናገራቸውን ገልፀዋል። የፕሬዘዳንቱ ቃል አቀባይ ግብጽ ስምምነቱን መፈረሟን አረጋግጠዋል።
#EsheteBekele
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
#COVOD19
የጣሊያን መንግስት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ትምህርት ቤቶችን እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ሊዘጋ ነው።
ትምህርት ቤቶቹ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በሚል እንደሚዘጉ የሃገሪቱን ባለስልጣናት ዋቢ ያደረገው የሬውተርስ ዘገባ ያመላክታል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም ለሁለት ሳምንታት ይዘጋሉ ነው የተባለው፤ አሁን ላይ የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸው የሃገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል።
በጣሊያን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ይገኛል። እስካሁን ባለው መረጃም 79 ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ፥ ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል።
#ሬውተርስ #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጣሊያን መንግስት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ ትምህርት ቤቶችን እና ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ሊዘጋ ነው።
ትምህርት ቤቶቹ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ በሚል እንደሚዘጉ የሃገሪቱን ባለስልጣናት ዋቢ ያደረገው የሬውተርስ ዘገባ ያመላክታል።
ከዚህ ጋር ተያይዞም ለሁለት ሳምንታት ይዘጋሉ ነው የተባለው፤ አሁን ላይ የቫይረሱ ስርጭት ከፍተኛ በሆነባቸው የሃገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ተዘግተዋል።
በጣሊያን የኮሮና ቫይረስ ስርጭት በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ይገኛል። እስካሁን ባለው መረጃም 79 ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ፥ ከ2 ሺህ 500 በላይ ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል።
#ሬውተርስ #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
በነገራችን ላይ በአሜሪካ በኮሮና ቫይረስ [COVID-19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 11 ደርሷል፤ 10 ሰዎች የሞቱት ከዋሽንግቶን ስቴት ሲሆን አንድ ሰው ደግሞ ካሊፎርኒያ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE ዓለም አቀፍ መረጃ፦ - የሟቾች ቁጥር 3,164 ከፍ ብሏል - በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 92,823 ዛሬ ባገኘነው ሪፖርት በኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 3,164 የደረሰ ሲሆን 92,823 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 48,469 ደርሰዋል። @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
ዓለም አቀፍ መረጃ፦
ዛሬ ባገኘነው ሪፖርት በኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 3,252 የደረሰ ሲሆን 95,143 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 51,435 ደርሰዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዓለም አቀፍ መረጃ፦
ዛሬ ባገኘነው ሪፖርት በኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 3,252 የደረሰ ሲሆን 95,143 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 51,435 ደርሰዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 4, 2020
#COVID19
በአሜሪካዋ ካሊፎርኒያ ግዛት አንድ ሰው በኮሮና ቫይረስ መሞቱን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል። ትላንት በግዛቷ የ71 ዓመት አዛውንት በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፤ አዛውንቱ ባለፈው ወር መነሻዋን ሳንፍራንሲስኮ ባደረገችው መርከብ ሳይሳፈሩ እንዳልቀረ ተገልጿል።
የአሁኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠርና የሚያደርገውን ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው ተብሏል። ከዚህ ቀደም ዋሽንግተን እና ፍሎሪዳ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጃቸው ይታወሳል።
ከኋይት ሃውስ የወጡ መረጃዎች ደግሞ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ በመላው አሜሪካ ለማድረግ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ያመላክታል።
ለኮሮና ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የተቋቋመውን ቡድን የሚመሩት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ማይክ ፔንስ ማንኛውም አሜሪካዊ በህክምና ባለሙያ ከታዘዘ ግዴታ ምርመራ ማድረግ እንዳለበት ገልጸዋል።
#BBC #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአሜሪካዋ ካሊፎርኒያ ግዛት አንድ ሰው በኮሮና ቫይረስ መሞቱን ተከትሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጇል። ትላንት በግዛቷ የ71 ዓመት አዛውንት በቫይረሱ ሳቢያ ለህልፈት ተዳርገዋል፤ አዛውንቱ ባለፈው ወር መነሻዋን ሳንፍራንሲስኮ ባደረገችው መርከብ ሳይሳፈሩ እንዳልቀረ ተገልጿል።
የአሁኑ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የቫይረሱን ስርጭት ለመቆጣጠርና የሚያደርገውን ጉዳት ለመቀነስ ያለመ ነው ተብሏል። ከዚህ ቀደም ዋሽንግተን እና ፍሎሪዳ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ማወጃቸው ይታወሳል።
ከኋይት ሃውስ የወጡ መረጃዎች ደግሞ የኮሮና ቫይረስ ምርመራ በመላው አሜሪካ ለማድረግ የሚያስችል ዝግጅት መደረጉን ያመላክታል።
ለኮሮና ቫይረስ ምላሽ ለመስጠት የተቋቋመውን ቡድን የሚመሩት ምክትል ፕሬዚዳንቱ ማይክ ፔንስ ማንኛውም አሜሪካዊ በህክምና ባለሙያ ከታዘዘ ግዴታ ምርመራ ማድረግ እንዳለበት ገልጸዋል።
#BBC #ኤፍቢሲ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
#UPDATE
ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሹመዋል። ከዚህ ቀደም የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ሀላፊም ሆነው ሰርተዋል። ከመቐለ ዩንቨርስቲ በህክምና ትምህርት ዲግሪ ያገኙ ሲሆን ከጣልያኑ ፓርማ ዩንቨርስቲ በአለም አቀፍ ጤና ላይ ያተኮረ ትምህርት ተከታትለው ከስምንት አመት በፊት ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።
ምንጭ፦ fidelPost.com
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሹመዋል። ከዚህ ቀደም የኦሮሚያ ጤና ቢሮ ሀላፊም ሆነው ሰርተዋል። ከመቐለ ዩንቨርስቲ በህክምና ትምህርት ዲግሪ ያገኙ ሲሆን ከጣልያኑ ፓርማ ዩንቨርስቲ በአለም አቀፍ ጤና ላይ ያተኮረ ትምህርት ተከታትለው ከስምንት አመት በፊት ሁለተኛ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል።
ምንጭ፦ fidelPost.com
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
42ኛው የካራማራ የድል በዓል የመታሠቢያ ቀን!
የዛሬ 42 አመት ተስፋፊው የመሀመድ ዚያድባሬ ኃይል ካራማራ ላይ አከርካሪው ተሠበረ። በውጤቱም በምስራቅ 700 ኪ.ሜ እንዲሁም በደቡብ 300 ኪ.ሜ ዘልቆ በወረራ ይዞት ከነበረው የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ተጠራርጎ ወጣ ።
ወድቃ የነበረችው ሰንደቃችንም ዳግም ተነስታ በክብር ከፍ አለች።
ይህን በአባቶቻችን ደምና አጥንት እና በእናቶቻችን ደጀንነት ያገኘነውን የመላ ኢትዮጵያውያን የጋራ ደማቅ የድል ታሪክ ለማክበር ድሉ በተገኘበት ዛሬ የካቲት 26 ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በኢትዮ ኩባ ወዳጅነት ፓርክ (በትግላችን ሐውልት) ላይ ለማክበር ዝግጅት ተጠናቋል።
በዝግጅቱ ላይ፦
- በጦርነቱ ወቅት በአመራር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች (ጀኔራሎችን ጨምሮ ) ሌሎች መስመራዊ መኮንኖች
- ለድሉ መገኘት ቁልፍ ሚና የተወጡ የጀግናው አየር ኃይላችን አብራሪዎች
- በጦርነቱ የተሳተፉ ባለሌላ ማዕረግተኛ ወታደሮች (የጀብድ ሜዳይ የተሸለሙ ጭምር )
- በጦርነቱ ቤተሠቦቻቸውን ያጡ የኩባ ተማሪዎችና የህፃናት አንባ ልጆች
- ለኢትዮጵያ ድጋፍ በመስጠት በጦርነቱ የተሳተፉ ሀገራት አምባሳደሮች /ተወካዮቻቸው እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ።
በመሆኑም ታሪክና ሀገር ወዳድ የሆናችሁ ዜጎች በዕለቱ በቦታው ላይ ተገኝታችሁ የመታሠቢያ በዓሉን በድምቀት እንድታከብሩ ተጋብዛችሗል።
የበዓሉ ጊዜያዊ አስተባባሪዎች፣ ኮረማሽ የጉዞ ማህበር ከማይክ መላከ የኢትዮ- ኩባ ወዳጅነት ማህበር እና በኢትዮጵያ የኩባ ኤምባሲ ጋር በመተባበር።
#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የዛሬ 42 አመት ተስፋፊው የመሀመድ ዚያድባሬ ኃይል ካራማራ ላይ አከርካሪው ተሠበረ። በውጤቱም በምስራቅ 700 ኪ.ሜ እንዲሁም በደቡብ 300 ኪ.ሜ ዘልቆ በወረራ ይዞት ከነበረው የኢትዮጵያ ሉዓላዊ ግዛት ተጠራርጎ ወጣ ።
ወድቃ የነበረችው ሰንደቃችንም ዳግም ተነስታ በክብር ከፍ አለች።
ይህን በአባቶቻችን ደምና አጥንት እና በእናቶቻችን ደጀንነት ያገኘነውን የመላ ኢትዮጵያውያን የጋራ ደማቅ የድል ታሪክ ለማክበር ድሉ በተገኘበት ዛሬ የካቲት 26 ከጠዋቱ 4:00 ጀምሮ በኢትዮ ኩባ ወዳጅነት ፓርክ (በትግላችን ሐውልት) ላይ ለማክበር ዝግጅት ተጠናቋል።
በዝግጅቱ ላይ፦
- በጦርነቱ ወቅት በአመራር ላይ የነበሩ የቀድሞ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች (ጀኔራሎችን ጨምሮ ) ሌሎች መስመራዊ መኮንኖች
- ለድሉ መገኘት ቁልፍ ሚና የተወጡ የጀግናው አየር ኃይላችን አብራሪዎች
- በጦርነቱ የተሳተፉ ባለሌላ ማዕረግተኛ ወታደሮች (የጀብድ ሜዳይ የተሸለሙ ጭምር )
- በጦርነቱ ቤተሠቦቻቸውን ያጡ የኩባ ተማሪዎችና የህፃናት አንባ ልጆች
- ለኢትዮጵያ ድጋፍ በመስጠት በጦርነቱ የተሳተፉ ሀገራት አምባሳደሮች /ተወካዮቻቸው እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ።
በመሆኑም ታሪክና ሀገር ወዳድ የሆናችሁ ዜጎች በዕለቱ በቦታው ላይ ተገኝታችሁ የመታሠቢያ በዓሉን በድምቀት እንድታከብሩ ተጋብዛችሗል።
የበዓሉ ጊዜያዊ አስተባባሪዎች፣ ኮረማሽ የጉዞ ማህበር ከማይክ መላከ የኢትዮ- ኩባ ወዳጅነት ማህበር እና በኢትዮጵያ የኩባ ኤምባሲ ጋር በመተባበር።
#EliasMeseret
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ በሚል መሪ ቃል የተለያየ ሀሳብ ያላቸወን የፓለቲካ ፓርቲ አመራሮችን፣ አክቲቪስቶችን፣ ታዋቂ ግለሰቦችንና አርቲስቶችን ያሳትፋል የተባለውና የካቲት 15 2012 ዓ.ም በአዲስ አበባ ሊካሄድ የነበረው ሩጫ መራዘሙ ይታወሳል፡፡
አዘጋጆቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት ውድድሩ መጋቢት 20 እንዲካሄድ ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የፍቃድ ደብዳቤ ማግኘቱን ገልጸውልናል፡፡
ይህን አስመልክቶም የፊታችን ቅዳሜ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በዮድ አቢሲኒያ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥና ሁሉም ሚዲያዎች በቦታው ተገኝተው የዚህን የሰላም ሩጫ ሂደቶች እንዲዘግቡ አዘጋጆቹ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አዘጋጆቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላኩት መልዕክት ውድድሩ መጋቢት 20 እንዲካሄድ ከአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር የፍቃድ ደብዳቤ ማግኘቱን ገልጸውልናል፡፡
ይህን አስመልክቶም የፊታችን ቅዳሜ ከረፋዱ አራት ሰዓት ላይ በዮድ አቢሲኒያ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥና ሁሉም ሚዲያዎች በቦታው ተገኝተው የዚህን የሰላም ሩጫ ሂደቶች እንዲዘግቡ አዘጋጆቹ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
ተጨማሪ መረጃ ለቲክቫህ ቤተሰቦች፦
'ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ' የጎዳና ላይ ሩጫ አዘጋጆች በTIKVAH-ETH በኩል ለሚመዘገቡ የቤተሰቡ ተሳታፊዎች 250 ብር የነበረውን የቲቨርት ዋጋ 150 ማድረጋቸው ይታወሳል አሁንም ይኸው ምዝገባ ቀጥሎ ሩጫው ሲቃረብ ለተመዝጋቢዎች የቲሸርቶች የሚገኙባቸውን ቦታዎች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
ለመመዝገብ፡- https://forms.gle/H3R8nxTamrMPyieN7
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
'ለፍቅር እንሩጥ ጥላቻን እናምልጥ' የጎዳና ላይ ሩጫ አዘጋጆች በTIKVAH-ETH በኩል ለሚመዘገቡ የቤተሰቡ ተሳታፊዎች 250 ብር የነበረውን የቲቨርት ዋጋ 150 ማድረጋቸው ይታወሳል አሁንም ይኸው ምዝገባ ቀጥሎ ሩጫው ሲቃረብ ለተመዝጋቢዎች የቲሸርቶች የሚገኙባቸውን ቦታዎች የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
ለመመዝገብ፡- https://forms.gle/H3R8nxTamrMPyieN7
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
ጤና ሚኒስቴር፦
"የቀድሞ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ሃላፊ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ:: መልካም የስራ ጊዜ!"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"የቀድሞ የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጤና ቢሮ ሃላፊ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ የኢፌድሪ ጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ:: መልካም የስራ ጊዜ!"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
#UPDATE
የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ እንዲሁም የባንኮች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን ሲያገለግሉ ነበሩት አቶ አቢ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነ እንደተሾሙ ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።
ምንጭ፦ ዋዜማ ሬድዮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ እንዲሁም የባንኮች ማህበር ፕሬዝዳንት በመሆን ሲያገለግሉ ነበሩት አቶ አቢ ሳኖ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዝዳንት ሆነ እንደተሾሙ ዋዜማ ሬድዮ ዘግቧል።
ምንጭ፦ ዋዜማ ሬድዮ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
በባሌ ዞን ጎባ ከተማ በህግ ጥላ ስር ለሚገኝ ተጠርጣሪ የአልኮል መጠጥ ደብቆ ለማቀበል የሞከረ ግለሰብ በአንድ ዓመት ከሁለት ወር እስራት እንዲቀጣ መደረጉን የጎባ ወረዳ ፍርድ ቤት ገለፀ።
የጎባ ወረዳ ፍርድ ቤት በአቶ ሄኖክ ዳምጤ ላይ የፍርድ ውሳኔውን ያሳለፈው የካቲት 25 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት ነው፡፡
ግለሰቡ ለቅጣት የተዳረገው የካቲት 24 ቀን 2012 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በጎባ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ጥላ ስር ለሚገኙ ጓደኞቹ በድብቅ የአረቄ መጠጥ ለማስገባት ሲሞክር በጥበቃ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ በመያዙ ነው፡፡
#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጎባ ወረዳ ፍርድ ቤት በአቶ ሄኖክ ዳምጤ ላይ የፍርድ ውሳኔውን ያሳለፈው የካቲት 25 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት ነው፡፡
ግለሰቡ ለቅጣት የተዳረገው የካቲት 24 ቀን 2012 ዓ.ም ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት አካባቢ በጎባ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በነፍስ ማጥፋት ወንጀል ተጠርጥረው በህግ ጥላ ስር ለሚገኙ ጓደኞቹ በድብቅ የአረቄ መጠጥ ለማስገባት ሲሞክር በጥበቃ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት እጅ ከፍንጅ በመያዙ ነው፡፡
#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ATTENTION
በአሁን ሰዓት በባሌ ሮቤ የአንበጣ መንጋ በስፋት እየታየ እንደሚገኝ የሮቤ ቲክቫህ ቤተሰቦች ሪፖርት አድርገዋል። መንጋው ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል የሚደረግ ጥረት እየተመለከትን አይደለም ያሉት ቤተሰቦቻችን መንጋው ጉዳት ሳያደርስ ሁሉም አካል ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
#Melaku
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአሁን ሰዓት በባሌ ሮቤ የአንበጣ መንጋ በስፋት እየታየ እንደሚገኝ የሮቤ ቲክቫህ ቤተሰቦች ሪፖርት አድርገዋል። መንጋው ጉዳት እንዳያደርስ ለመከላከል የሚደረግ ጥረት እየተመለከትን አይደለም ያሉት ቤተሰቦቻችን መንጋው ጉዳት ሳያደርስ ሁሉም አካል ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል።
#Melaku
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
March 5, 2020
#GERD
የዓረብ ሊግ ሀገራት የህዳሴ ግድብ ስምምነትን እንዲደግፉ ግብፅ ያቀረበችውን ምክረ ሀሳብ ሱዳን ውድቅ ማድረጓ ተገልጿል።
ግብፅ በካይሮ በተካሄደው 153ኛ የዓረብ ሊግ ሀገራት የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ነው በህዳሴ ግድብ ድርድር ዙሪያ የሊጉ አባል ሀገራት ከሱዳን እና ከግብፅ ጎን እንዲሆኑ የሚጠይቅ ምክረ ሀሳብ ያቀረበችው።
ሱዳን በበኩሏ በግብፅ በኩል የቀረበውን የዓረብ ሊግ ድጋፍ ምክረ ሀሳብን ውድቅ አድርጋለች።
ስሟም ከዚህ ጋር ተያይዞ እንዲነሳ እንደማትፈልግ በይፋ ያስታወቀችው ሱዳን፥ ምክረ ሀሳቡ ብሄራዊ ጥቅሟን የሚጎዳ እንደሆነም ገልፃለች።
ሱዳን የዓረብ ሊግ ሀገራት በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር አለመግባባት ውስጥ ጣልቃ እንዳይገቡ ፍላጎቷ መሆኑንም አስገንዝባለች።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የዓረብ ሊግ ሀገራት የህዳሴ ግድብ ስምምነትን እንዲደግፉ ግብፅ ያቀረበችውን ምክረ ሀሳብ ሱዳን ውድቅ ማድረጓ ተገልጿል።
ግብፅ በካይሮ በተካሄደው 153ኛ የዓረብ ሊግ ሀገራት የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ነው በህዳሴ ግድብ ድርድር ዙሪያ የሊጉ አባል ሀገራት ከሱዳን እና ከግብፅ ጎን እንዲሆኑ የሚጠይቅ ምክረ ሀሳብ ያቀረበችው።
ሱዳን በበኩሏ በግብፅ በኩል የቀረበውን የዓረብ ሊግ ድጋፍ ምክረ ሀሳብን ውድቅ አድርጋለች።
ስሟም ከዚህ ጋር ተያይዞ እንዲነሳ እንደማትፈልግ በይፋ ያስታወቀችው ሱዳን፥ ምክረ ሀሳቡ ብሄራዊ ጥቅሟን የሚጎዳ እንደሆነም ገልፃለች።
ሱዳን የዓረብ ሊግ ሀገራት በኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ድርድር አለመግባባት ውስጥ ጣልቃ እንዳይገቡ ፍላጎቷ መሆኑንም አስገንዝባለች።
#ኤፍቢሲ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
March 5, 2020
የባልደራስ እና መኢአድ ቅንጅት...
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 30፣ 2012 ዓ/ም ፓርቲዎች ጥምረታቸዉን እንዲያስገቡ ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት፣ በነገው ዕለት አርብ የካቲት 27/2012 ዓ/ም ከቀኑ በ5:00 ሰዓት የሚደረግ የሁለት ፓርቲዎች የ"ባልደራስ መኢአድ" ቅንጅት ይፈጥራሉ።
#ስንታየሁቸኮል
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 30፣ 2012 ዓ/ም ፓርቲዎች ጥምረታቸዉን እንዲያስገቡ ባስቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት፣ በነገው ዕለት አርብ የካቲት 27/2012 ዓ/ም ከቀኑ በ5:00 ሰዓት የሚደረግ የሁለት ፓርቲዎች የ"ባልደራስ መኢአድ" ቅንጅት ይፈጥራሉ።
#ስንታየሁቸኮል
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
March 5, 2020
TIKVAH-ETHIOPIA
#GONDAR "ተጠርጣሪዎቹ ምንም ዓይነት የህክምና ፍቃድ የላቸውም" - ፖሊስ በጎንደር ከተማ ጌዜ ያለፈባቸው መድሃኒቶችን ሲያሰራጩ የተያዙት ተጠርጣሪዎች ምንም ዓይነት የህክምና ፈቃድ እንደሌላቸው ተገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ ማራኪ ክፍለ ከተማ ልኡል አለማየሁ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚገኙ ተማሪዎች የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን መድሃኒቶች ሲያሰራጩ ነው የተያዙት። ፖሊስ ከህዝብ በደረሰው ጥቆማ መሰረት…
#UPDATE
የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን መድኃኒቶች ሲያከፋፍሉ ነበሩ የተባሉ 13 ካናዳዊያን እና ሁለት ኢትዮጵያዊያን እያንዳንዳቸው በ20ሺህ ብር ዋስ መለቀቃቸውን በጎንደር የሦስተኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ደሳለኝ አበራ ለቢቢሲ ገለጹ።
15ቱ ግለሰቦች ትላንት የካቲት 25 ቀን 2012 ዓ. ም. በዋስ እንደተለቀቁ ገልጸዋል። 15ቱ ግለሰቦች ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ በሚገኝ ትምህርት ቤት የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን መድኃኒቶች በመስጠት ላይ እያሉ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አየልኝ ታከለው ለቢቢሲ ገልጸዋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን መድኃኒቶች ሲያከፋፍሉ ነበሩ የተባሉ 13 ካናዳዊያን እና ሁለት ኢትዮጵያዊያን እያንዳንዳቸው በ20ሺህ ብር ዋስ መለቀቃቸውን በጎንደር የሦስተኛ ዋና ፖሊስ ጣቢያ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር ደሳለኝ አበራ ለቢቢሲ ገለጹ።
15ቱ ግለሰቦች ትላንት የካቲት 25 ቀን 2012 ዓ. ም. በዋስ እንደተለቀቁ ገልጸዋል። 15ቱ ግለሰቦች ጎንደር ከተማ ቀበሌ 18 አካባቢ በሚገኝ ትምህርት ቤት የመጠቀሚያ ጊዜ ያለፈባቸውን መድኃኒቶች በመስጠት ላይ እያሉ በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የጎንደር ከተማ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አየልኝ ታከለው ለቢቢሲ ገልጸዋል።
ምንጭ፦ ቢቢሲ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
March 5, 2020
በምዕራብ ኦሮሚያ በመንግስት እና የኦሮሞ ነጻነት ሸማቂ ተዋጊ ባለው ቡድን መካከል ያለውን ግጭት ለመፍታት ራሱን "ፍርቱ" ብሎ የሰየመ የእርቅ እና ሰላም ኮሚቴ ተቋቁሞ ስራ መጀመሩን ዛሬ አስታወቀ።
ኮሚቴው በአራቱ የምዕራብ ኦሮሚያና ጉጂ ዞኖች ላይ እርቅ ወርዶ ከሚመሩበት ወታደራዊ እዝ እንዲወጡ፣ በሲቪል አስተዳደር ስር እንዲገቡም እሰራለሁ ብሏል። የክልሉ መንግስት ይህንን ጅምር በበጎ እንደሚመለከተው እና ኮሚቴው የወጠነውም እንዲሳካ ፍላጎቱ መሆኑን አሳውቋል።
ፍርቱ የእርቅ እና ሰላም ኮሚቴ በመንግስት እና በሸማቂ ተዋጊዎች አለመግባባት ምክንያት በህዝቡ ላይ የደረሰው እና እየደረሰ ነው ያለው እንግልት እንዲቆም የማቀርበውን የእርቅ ጥሪ በማይቀበለው ላይ የተለመዱ ዓለም አቀፍ የቅጣት ተሞክሮዎች እንዲተገበሩ ጫና አደርጋለሁ ብሏል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
ኮሚቴው በአራቱ የምዕራብ ኦሮሚያና ጉጂ ዞኖች ላይ እርቅ ወርዶ ከሚመሩበት ወታደራዊ እዝ እንዲወጡ፣ በሲቪል አስተዳደር ስር እንዲገቡም እሰራለሁ ብሏል። የክልሉ መንግስት ይህንን ጅምር በበጎ እንደሚመለከተው እና ኮሚቴው የወጠነውም እንዲሳካ ፍላጎቱ መሆኑን አሳውቋል።
ፍርቱ የእርቅ እና ሰላም ኮሚቴ በመንግስት እና በሸማቂ ተዋጊዎች አለመግባባት ምክንያት በህዝቡ ላይ የደረሰው እና እየደረሰ ነው ያለው እንግልት እንዲቆም የማቀርበውን የእርቅ ጥሪ በማይቀበለው ላይ የተለመዱ ዓለም አቀፍ የቅጣት ተሞክሮዎች እንዲተገበሩ ጫና አደርጋለሁ ብሏል።
ምንጭ፦ የጀርመን ድምፅ ሬድዮ
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
March 5, 2020