መንግስት ንብረታችንን እየነጠቀን ነው...
መኪና የተነጠቀባቸው የቤተሰባችን አባላት፦
"መንግስት የህዝብ ንብረት መንጠቅ ተያይዞታል። ኮድ 2 ኦሮ VAN መኪኖች የሰጠን ኦሮሚያ መንገድ ትራንስፖርት ስህተት ካለበት የሰጠ አካል ነው መጠየቅ ያለበት ህዝብ ያለጥፋቱ እየተገላታ ነው። ኮድ 2 ኦሮ van መኪኖች እየቀሙ ቃሊቲ ግምሩክ መጋዘን እያስቀምጡ ነው እነሱ የሚሉት ኮድ 3 መሆን ነበረባቸው፤ ኮድ 2 የማይፈቀድ ከሆነ መጠየቅ ያለበት የሰጠ አካል የኦሮሚያ መንገድ ትራንስፖርት ነው የአንድ ሀገር ህግ እስከሆነ በመሀል ህዝብ እየተሰቃየ ነው። ኮድ 3 A.A ያላወጣነው የአ.አ ከተማ መንገድ ትራንስፖርት አላስተናግዳችሁም በማለቱ ነው እንጂ በወቅቱ ጠይቀን ነበር፤ እና ለዚህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መለሰ መሰጠት ያለበት የአ.አ ከተማ መንገድ ትራንስፖርት ባለስልጣን ነው"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
መኪና የተነጠቀባቸው የቤተሰባችን አባላት፦
"መንግስት የህዝብ ንብረት መንጠቅ ተያይዞታል። ኮድ 2 ኦሮ VAN መኪኖች የሰጠን ኦሮሚያ መንገድ ትራንስፖርት ስህተት ካለበት የሰጠ አካል ነው መጠየቅ ያለበት ህዝብ ያለጥፋቱ እየተገላታ ነው። ኮድ 2 ኦሮ van መኪኖች እየቀሙ ቃሊቲ ግምሩክ መጋዘን እያስቀምጡ ነው እነሱ የሚሉት ኮድ 3 መሆን ነበረባቸው፤ ኮድ 2 የማይፈቀድ ከሆነ መጠየቅ ያለበት የሰጠ አካል የኦሮሚያ መንገድ ትራንስፖርት ነው የአንድ ሀገር ህግ እስከሆነ በመሀል ህዝብ እየተሰቃየ ነው። ኮድ 3 A.A ያላወጣነው የአ.አ ከተማ መንገድ ትራንስፖርት አላስተናግዳችሁም በማለቱ ነው እንጂ በወቅቱ ጠይቀን ነበር፤ እና ለዚህ ጉዳይ ለኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን መለሰ መሰጠት ያለበት የአ.አ ከተማ መንገድ ትራንስፖርት ባለስልጣን ነው"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የራይድ አሽከርካሪ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት፦
የራይድ አሽከርካሪዎች የሆኑ የቤተሰባችን አባላት ህጋዊ ሆነን እየሰራን በየአካባቢው እየተደበደብን ነው ሲሉ ቅሬታ አሰምተዋል። በአሁን ሰዓት የራይድ አሽከርካሪ 'ተደብድቦ' የረር አለማየሁ ህንፃ ጋር በርካታ የራይድ አሽከርካሪ ተሰብስቦ ፖሊስና የሚዲያ ሰዎችን እየጠበቀ እንደሆነ ገልፀውልናል ። ህጋዊ ስራ እየሰራን መደብደብ የለብንም፣ ንብረታችን መኪናችንም መሰባበር የለበትም፣ በነፃነት መስራት አልቻልንም፣ ወከባ ይደርስብናል መንግስት ካለ ህግ ያስከብር ሲሉ አሳስበዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የራይድ አሽከርካሪዎች የሆኑ የቤተሰባችን አባላት ህጋዊ ሆነን እየሰራን በየአካባቢው እየተደበደብን ነው ሲሉ ቅሬታ አሰምተዋል። በአሁን ሰዓት የራይድ አሽከርካሪ 'ተደብድቦ' የረር አለማየሁ ህንፃ ጋር በርካታ የራይድ አሽከርካሪ ተሰብስቦ ፖሊስና የሚዲያ ሰዎችን እየጠበቀ እንደሆነ ገልፀውልናል ። ህጋዊ ስራ እየሰራን መደብደብ የለብንም፣ ንብረታችን መኪናችንም መሰባበር የለበትም፣ በነፃነት መስራት አልቻልንም፣ ወከባ ይደርስብናል መንግስት ካለ ህግ ያስከብር ሲሉ አሳስበዋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Ethiotelecom
"የሞባይል ድምፅ እና ኢንተርኔት የተቋረጠው በቴክኒክ ችግር ነው" - ኢትዮ ቴሌኮም
ኢትዮ ቴሌኮም ትላንት ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት የሞባይል ድምፅ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ከምሽቱ 12:15 ጀምሮ ተቋርጦ እንደነበር ገልጿል።
ትላንት ከምሽቱ 1:10 ጀምሮ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲሁም ከምሽት 4:30 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ችግሩ ተግቶ አገልግሎቱ መቀጠሉን አሳውቋል። ተቋሙ ደንበኞች ላሳዩት ትዕግስት ምስጋና ያቀረበ ሲሆን ለተፈጠረው እንግልት ይቅርታ ጠይቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"የሞባይል ድምፅ እና ኢንተርኔት የተቋረጠው በቴክኒክ ችግር ነው" - ኢትዮ ቴሌኮም
ኢትዮ ቴሌኮም ትላንት ባጋጠመው የቴክኒክ ችግር ምክንያት የሞባይል ድምፅ እና ኢንተርኔት አገልግሎት ከምሽቱ 12:15 ጀምሮ ተቋርጦ እንደነበር ገልጿል።
ትላንት ከምሽቱ 1:10 ጀምሮ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች እንዲሁም ከምሽት 4:30 ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ችግሩ ተግቶ አገልግሎቱ መቀጠሉን አሳውቋል። ተቋሙ ደንበኞች ላሳዩት ትዕግስት ምስጋና ያቀረበ ሲሆን ለተፈጠረው እንግልት ይቅርታ ጠይቋል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
ከሰኞ የካቲት 09 ቀን 2012 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን እያደረገ ሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትላንትናው ውሎ 'የኦሮሚያ ቤተክህነት አደራጅ ኮሚቴ' ላይ ውሳኔ ማስተላለፉን ሐራ ዘተዋሕዶ ዘግቧል ውሳኔውም፡-
- ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን፣ አባ ገብረ ማርያም ነጋሳ፣ ዲ/ን ኀይለ ሚካኤል ታደሰ፣ ቄስ በድሳ ፥ ከዛሬ የካቲት 11 ቀን ጀምሮ እስከ ሚቀጥለው የግንቦቱ ምላዓተ ጉባኤ ድረስ በጥፋታቸው ተጸጽተው ከተግባራቸው በይቅርታ እስኪመለሱ ድረስ ሥልጣነ ክህነታቸው እንዲያዝ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ልዩነት በሌለው ድምፅ ወስኗል፤
- “የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እናዳራጃለን” በማለት በመዋቅር ላይ መዋቅር በመፍጠራቸው እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ማኅተም አስቀርፀው በመንቀሳቀሳቸው፣ በአገሪቱ ሕግ ይጠየቃሉ፤
- ያስቀረፁት ማኅተም ገቢ እንዲደረግ፤ የከፈቷቸው ጽሕፈት ቤቶች፥ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም የተከፈቱ እና ሕገ ወጥ በመኾናቸው እንዲዘጉ እንዲደረግ ወስኗል፤
- ኢሬቻንና ዋቄፈናን ከኦርቶዶክስ ክርስትና ጋራ ኾነ ብለው እያመሳሰሉ ለሚያደናግሩ፤ ቤተ ክርስቲያንን ያለስሟ ስም እየሰጡ ለሚተቹ እና በቡድኑ ድጋፍ ለታተሙ መጻሕፍት፥ የሊቃውንት ጉባኤ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በአማርኛ ቋንቋዎች መልስ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶሱ አዟል፡፡
#ሐራዘተዋሕዶ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከሰኞ የካቲት 09 ቀን 2012 ዓ.ም አስቸኳይ ጉባኤውን እያደረገ ሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በትላንትናው ውሎ 'የኦሮሚያ ቤተክህነት አደራጅ ኮሚቴ' ላይ ውሳኔ ማስተላለፉን ሐራ ዘተዋሕዶ ዘግቧል ውሳኔውም፡-
- ሊቀ አእላፍ ቀሲስ በላይ መኰንን፣ አባ ገብረ ማርያም ነጋሳ፣ ዲ/ን ኀይለ ሚካኤል ታደሰ፣ ቄስ በድሳ ፥ ከዛሬ የካቲት 11 ቀን ጀምሮ እስከ ሚቀጥለው የግንቦቱ ምላዓተ ጉባኤ ድረስ በጥፋታቸው ተጸጽተው ከተግባራቸው በይቅርታ እስኪመለሱ ድረስ ሥልጣነ ክህነታቸው እንዲያዝ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ልዩነት በሌለው ድምፅ ወስኗል፤
- “የኦሮሚያ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እናዳራጃለን” በማለት በመዋቅር ላይ መዋቅር በመፍጠራቸው እና በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም ማኅተም አስቀርፀው በመንቀሳቀሳቸው፣ በአገሪቱ ሕግ ይጠየቃሉ፤
- ያስቀረፁት ማኅተም ገቢ እንዲደረግ፤ የከፈቷቸው ጽሕፈት ቤቶች፥ በቤተ ክርስቲያኒቱ ስም የተከፈቱ እና ሕገ ወጥ በመኾናቸው እንዲዘጉ እንዲደረግ ወስኗል፤
- ኢሬቻንና ዋቄፈናን ከኦርቶዶክስ ክርስትና ጋራ ኾነ ብለው እያመሳሰሉ ለሚያደናግሩ፤ ቤተ ክርስቲያንን ያለስሟ ስም እየሰጡ ለሚተቹ እና በቡድኑ ድጋፍ ለታተሙ መጻሕፍት፥ የሊቃውንት ጉባኤ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በአማርኛ ቋንቋዎች መልስ እንዲሰጥ ቅዱስ ሲኖዶሱ አዟል፡፡
#ሐራዘተዋሕዶ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
መኪናቸው የተያዘባቸው ባለንብረቶች ቅሬታ፦
መኪናቸውን የተቀሙ ግለሰቦች ዛሬ ምክንትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ በሚገኙበት የከተማው መስተዳደር ደጃፍ ቅሬታ ማሰማታቸውን ፌደል ፖስት ዘግቧል።
ቅሬታ አሰሚ ባለነብረቶች እንደተናገሩት ከሆነ 600 የሚጠጉ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአዲሰ አበባ እና በደቡብ ክልል በ2 ቁጥር ታርጋ የተሰጣቸው D4D እና ዳማስ መኪኖቻቸው ተይዞባቸዋል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቃሊቲ ጎሙሩክ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የበተነው ሰርኩርላር ደብዳቤ እንደሚያሳየው መኪኖቹ በህዝብ አገልግሎት ሰበብ ገብተው በግል አገልግሎት ሲሰሩ በመገኘታቸው ነው ለግል አገልግሎት በሚቀረጥ የቀረጥ ሂሳብ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ያሉት ብሏል።
ምንጭ፦ ፊደል ፖስት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
መኪናቸውን የተቀሙ ግለሰቦች ዛሬ ምክንትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ኡማ በሚገኙበት የከተማው መስተዳደር ደጃፍ ቅሬታ ማሰማታቸውን ፌደል ፖስት ዘግቧል።
ቅሬታ አሰሚ ባለነብረቶች እንደተናገሩት ከሆነ 600 የሚጠጉ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአዲሰ አበባ እና በደቡብ ክልል በ2 ቁጥር ታርጋ የተሰጣቸው D4D እና ዳማስ መኪኖቻቸው ተይዞባቸዋል።
በጉምሩክ ኮሚሽን የአዲስ አበባ ቃሊቲ ጎሙሩክ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት የበተነው ሰርኩርላር ደብዳቤ እንደሚያሳየው መኪኖቹ በህዝብ አገልግሎት ሰበብ ገብተው በግል አገልግሎት ሲሰሩ በመገኘታቸው ነው ለግል አገልግሎት በሚቀረጥ የቀረጥ ሂሳብ እንዲከፍሉ እየተገደዱ ያሉት ብሏል።
ምንጭ፦ ፊደል ፖስት
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#UPDATE - የሟቾች ቁጥር 1,874 ደርሷል - በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 73,336 በኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 1,874 የደረሰ ሲሆን 73,336 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 12,921 መድረሳቸውን ተመልክተናል። @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#UPDATE
- የሟቾች ቁጥር 2,012 ደርሷል
- በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 75,307
በኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 2,012 የደረሰ ሲሆን 75,307 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 14,942 መድረሳቸውን ተመልክተናል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
- የሟቾች ቁጥር 2,012 ደርሷል
- በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር 75,307
በኮሮና ቫይረስ [#COVID19] የሞቱ ሰዎች ቁጥር 2,012 የደረሰ ሲሆን 75,307 ሰዎች ደግሞ በቫይረሱ ተጠቅተዋል። ከበሽታው አገግመው ከሆስፒታል የወጡ ሰዎች ቁጥር ደግሞ 14,942 መድረሳቸውን ተመልክተናል።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የድጋፍ ሰልፍ...
ዛሬም የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድን የለውጥ አመራር የሚደግፉ ሰልፎች በኦሮማያ ክልል ሲካሄዱ እንደነበር ተመልክተናል።
በዛሬው ዕለት የድጋፍ ሰልፍ ከተደረገባቸው ከተሞች አንዱ ለገጣፎ ለገዳዲ ነው። በድጋፍ ሰልፉ በርካታ ቁጥር ያላቸው የለገጣፎ ለገዳዲ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በተመሳሳይ በመቱ ከተማ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የለውጥ አመራር የሚደግፍ የድጋፍ ሰልፍ ተደርጓል። በሰልፉ ላይ የተገኙ የመቱ ነዋሪዎች በስድብ እና በጥላቻ በፍፁም ለውጥ ሊመጣ አይችልም ብለዋል።
#LegetafoLegedadi #FBC #WondeMettu
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዛሬም የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድን የለውጥ አመራር የሚደግፉ ሰልፎች በኦሮማያ ክልል ሲካሄዱ እንደነበር ተመልክተናል።
በዛሬው ዕለት የድጋፍ ሰልፍ ከተደረገባቸው ከተሞች አንዱ ለገጣፎ ለገዳዲ ነው። በድጋፍ ሰልፉ በርካታ ቁጥር ያላቸው የለገጣፎ ለገዳዲ ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።
በተመሳሳይ በመቱ ከተማ የጠቅላይ ሚኒስትሩን የለውጥ አመራር የሚደግፍ የድጋፍ ሰልፍ ተደርጓል። በሰልፉ ላይ የተገኙ የመቱ ነዋሪዎች በስድብ እና በጥላቻ በፍፁም ለውጥ ሊመጣ አይችልም ብለዋል።
#LegetafoLegedadi #FBC #WondeMettu
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በሳውዲ አረቢያ 11 ኢትዮጵያውያን ተይዘዋል...
ሳውዲ አረቢያ ከሰሞኑን ሕጋዊ ሆነው በምድሯ እየኖሩ ያልተፈቀደላቸውን ሥራ የሚሠሩ የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ማሠር መጀመሯ ተሰማ። በሕጉ መሠረት አንድ የውጭ ዜጋ ወደሳውዲ ሲገባ እንዲሠራ በተፈረደለትን የሥራ መስክ የማይሠራ ከሆነ እንደ ሕገወጥ ይቆጠራል።
በዚሁም መሠረት #ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ አንድ ሺህ ገደማ የሚሆኑ የሌሎች ሃገራት ዜጎች ሕጋዊ ሆነው ሳለ ፈቃድ ከተሰጣቸው የሥራ መስክ ውጭ በመሠማራታቸው በሁለት ሳምንት ውስጥ መታሠራቸውን DW ዘግቧል። በጅዳ ቆንስል ጀነራል አቶ አብዱ ያሲን እንደገለጹት በዚህ የሳውዲ መንግሥት ርምጃ 11 ኢትዮጵያውያን ተይዘዋል።
#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ሳውዲ አረቢያ ከሰሞኑን ሕጋዊ ሆነው በምድሯ እየኖሩ ያልተፈቀደላቸውን ሥራ የሚሠሩ የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ማሠር መጀመሯ ተሰማ። በሕጉ መሠረት አንድ የውጭ ዜጋ ወደሳውዲ ሲገባ እንዲሠራ በተፈረደለትን የሥራ መስክ የማይሠራ ከሆነ እንደ ሕገወጥ ይቆጠራል።
በዚሁም መሠረት #ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ አንድ ሺህ ገደማ የሚሆኑ የሌሎች ሃገራት ዜጎች ሕጋዊ ሆነው ሳለ ፈቃድ ከተሰጣቸው የሥራ መስክ ውጭ በመሠማራታቸው በሁለት ሳምንት ውስጥ መታሠራቸውን DW ዘግቧል። በጅዳ ቆንስል ጀነራል አቶ አብዱ ያሲን እንደገለጹት በዚህ የሳውዲ መንግሥት ርምጃ 11 ኢትዮጵያውያን ተይዘዋል።
#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"ትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ ይስተካከል፤ ካልሆነ ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ አውጁ" - ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል
''በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ጣልቃ ገብነት እንዲሁም በትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ የማይስተካከል ከሆነ ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ ልታውጁ ይገባል" ሲሉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መልዕክት አስተላለፉ።
ዶክተር ደብረፅዮን ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት ህወሓት የተመሰረተበትን 45ኛውን ዓመት አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በመቐለ ስታዲየም ለታደሙ ሰዎች ባደረጉት ንግግር ነው።
የትግራይ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ደብረፅዮን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የስልጣን ጊዜያችሁ [የአባልነት ጊዜ] እያለቀ ስለሚገኝ ከመበታተናችሁ በፊት ታሪክ ስሩ።
በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጣልቃ ገብነት፣ በተለይም ትግራይን በተመለከተ በመሪዎች ደረጃ የተሰጡት የጥላቻና የፀረ ህዝብ ንግግሮችን በይፋ ኮንኑ" ብለዋል። አክለውም "ይህ የማይሆን ከሆነ ትግራይ ራሷን የቻለች አገር መሆኗን ወስኑ፤ አውጁ" ብለዋል።
"አገር በመበተን ሂደት ነበሩ ተብላችሁ በታሪክ እንዳትወቀሱ፤ ግዳጃችሁን ተወጡም" በማለት መልዕክታቸውን በትግራይ ስታዲየም ለተሰበሰበው ህዝብ አስተላልፈዋል።
#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
''በኢትዮጵያ እየተከሰተ ያለው ጣልቃ ገብነት እንዲሁም በትግራይ ላይ ያለው ጥላቻ የማይስተካከል ከሆነ ትግራይ ራስዋን የቻለች አገር ናት ብላችሁ ልታውጁ ይገባል" ሲሉ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል መልዕክት አስተላለፉ።
ዶክተር ደብረፅዮን ይህንን መልዕክት ያስተላለፉት ህወሓት የተመሰረተበትን 45ኛውን ዓመት አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በመቐለ ስታዲየም ለታደሙ ሰዎች ባደረጉት ንግግር ነው።
የትግራይ ምክትል ፕሬዝደንት ዶ/ር ደብረፅዮን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ባስተላለፉት መልዕክት፤ "የስልጣን ጊዜያችሁ [የአባልነት ጊዜ] እያለቀ ስለሚገኝ ከመበታተናችሁ በፊት ታሪክ ስሩ።
በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው ጣልቃ ገብነት፣ በተለይም ትግራይን በተመለከተ በመሪዎች ደረጃ የተሰጡት የጥላቻና የፀረ ህዝብ ንግግሮችን በይፋ ኮንኑ" ብለዋል። አክለውም "ይህ የማይሆን ከሆነ ትግራይ ራሷን የቻለች አገር መሆኗን ወስኑ፤ አውጁ" ብለዋል።
"አገር በመበተን ሂደት ነበሩ ተብላችሁ በታሪክ እንዳትወቀሱ፤ ግዳጃችሁን ተወጡም" በማለት መልዕክታቸውን በትግራይ ስታዲየም ለተሰበሰበው ህዝብ አስተላልፈዋል።
#BBC
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ፎቶዎች ከትግራይ ስታዲየም መቐለ...
#የካቲት11 - የትግራይ ህዝብ የደርግ ስርዓትን ለመገርሰሰ የትጥቅ ትግል የጀመረበት 45ኛው ዓመት የየካቲት 11 በዓል "በመስመራችን ጸንተን ለመመከት" በሚል መሪ ቃል በትግራይ ስታዲየም በድምቀት ተክብሯል።
#TPLF
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#የካቲት11 - የትግራይ ህዝብ የደርግ ስርዓትን ለመገርሰሰ የትጥቅ ትግል የጀመረበት 45ኛው ዓመት የየካቲት 11 በዓል "በመስመራችን ጸንተን ለመመከት" በሚል መሪ ቃል በትግራይ ስታዲየም በድምቀት ተክብሯል።
#TPLF
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia