This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ በስልጣን ላይ ስለመቆየት እና የሀገሪቱን ህዝብ ስለማገልገል ... #DrAbiyAhemed
ቪድዮ: ፋይል
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ቪድዮ: ፋይል
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ!
በገብረ ጉራቻ ከተማ በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ አራት የመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ አባላት ላይ ጉዳት ደረሰ። ትናንት (ሃሙስ) ምሽት 2፡30 ገደማ በሰሜን ሸዋ ዞን ኩዩ ወረዳ ገብረ ጉራቻ ከተማ የተፈጸመው ጥቃት ፖሊስ ጣቢያ ፊት ለፊት መሆኑን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ ደንደዓ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጥቃቱ የመንግሥት የጸጥታ አስከባሪ አካላትን ለመግደል ያለመ መሆኑን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
የግድያ ሙከራው ኢላማ ከነበሩት መካከል የኩዩ ወረዳ ፖሊስ ኃላፊ ዋና ሳጅን አዱኛ ደቀባ እና አብረዋቸው የነበሩ ሌላ የወረዳው ፖሊስ አባል እንደሚገኙበት አስተዳዳሪው ይናገራሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው የፖሊስ አባላቱ እራት በልተው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ግቢ እየገቡ ሳለ እንደነበር የሚናገሩት የኩዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ፤ በፖሊስ አባላቱ ላይ በሁለት አቅጣጫ ተኩስ እንደተከፈተባቸው ያስረዳሉ።
"ዋና ሳጅን አዱኛ እግራቸውን ነው የተመቱት። አብሯቸው የነበረው የፖሊስ አባል ደግሞ እጁን ነው የተመታው" የሚሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ የተኩስ ድምጽ ሰምተው ወደ በስፍራው የተገኙ ሌሎች ሁለት የቀበሌ ሚሊሻዎች ላይም ተኩስ ተከፍቶ ጉዳት ደርሶባቸዋል" በማለት ትናንት ምሽት በገብረ ጉራቻ ከተማ የተፈጠረውን ክስተት ያስረዳሉ።
አቶ ደረጄ በአራቱም የጸጥታ አስከባሪ አካላት ላይ የደረሰው ጉዳት ለህይወት የሚያስጋ አለመሆኑን የተናገሩ ሲሆን፤ ሶስቱ እግራቸው ላይ አንዱ ደግሞ እጁ ላይ ጉዳት ማጋጠሙን አስረድተዋል።
More👇
https://telegra.ph/BBC-12-06
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በገብረ ጉራቻ ከተማ በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ አራት የመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ አባላት ላይ ጉዳት ደረሰ። ትናንት (ሃሙስ) ምሽት 2፡30 ገደማ በሰሜን ሸዋ ዞን ኩዩ ወረዳ ገብረ ጉራቻ ከተማ የተፈጸመው ጥቃት ፖሊስ ጣቢያ ፊት ለፊት መሆኑን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ ደንደዓ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ጥቃቱ የመንግሥት የጸጥታ አስከባሪ አካላትን ለመግደል ያለመ መሆኑን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።
የግድያ ሙከራው ኢላማ ከነበሩት መካከል የኩዩ ወረዳ ፖሊስ ኃላፊ ዋና ሳጅን አዱኛ ደቀባ እና አብረዋቸው የነበሩ ሌላ የወረዳው ፖሊስ አባል እንደሚገኙበት አስተዳዳሪው ይናገራሉ።
ጥቃቱ የተፈጸመው የፖሊስ አባላቱ እራት በልተው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ግቢ እየገቡ ሳለ እንደነበር የሚናገሩት የኩዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ፤ በፖሊስ አባላቱ ላይ በሁለት አቅጣጫ ተኩስ እንደተከፈተባቸው ያስረዳሉ።
"ዋና ሳጅን አዱኛ እግራቸውን ነው የተመቱት። አብሯቸው የነበረው የፖሊስ አባል ደግሞ እጁን ነው የተመታው" የሚሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ የተኩስ ድምጽ ሰምተው ወደ በስፍራው የተገኙ ሌሎች ሁለት የቀበሌ ሚሊሻዎች ላይም ተኩስ ተከፍቶ ጉዳት ደርሶባቸዋል" በማለት ትናንት ምሽት በገብረ ጉራቻ ከተማ የተፈጠረውን ክስተት ያስረዳሉ።
አቶ ደረጄ በአራቱም የጸጥታ አስከባሪ አካላት ላይ የደረሰው ጉዳት ለህይወት የሚያስጋ አለመሆኑን የተናገሩ ሲሆን፤ ሶስቱ እግራቸው ላይ አንዱ ደግሞ እጁ ላይ ጉዳት ማጋጠሙን አስረድተዋል።
More👇
https://telegra.ph/BBC-12-06
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ኡቡንቱ #Ubuntu #አርባምንጭዩኒቨርሲቲ
(ዶክተር ዳምጠው ዳርዛ) የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ በዩኒቨርሲቲው ስላለው ሰላም እንዲሁም አጠቃላይ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፈዋል፦
"በከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች የአዕምሮ ሥራ የሚሰሩ ተማሪዎች ናቸው፡፡ በዩኒቨርሲቲው የሚቆዩበት ጊዜም አጭር በመሆኑ ባላቸው ጊዜ አዕምሯቸውን ሙሉ ለሙሉ በሳይንሱ ሥራ ላይ ቢያተኩሩ ወደፊት ለሀገራቸውም ሆነ ለራሳቸው ሙሉ የሆነ የዕውቀትና የክህሎት አስተሳሰብ ታጥቀው ይወጣሉ፡፡ ይህ ባልሆነበት ግን በሌሎች ሀሳብና አስተሳሰብ ጊዜን ማባከን በተሟላ መልኩ ሊያገኙት የሚችሉትን ነገሮችን ያጓድላል፡፡ እኛም እንደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አሁን ላይ ትኩረት አድርገን እየሰራን የምንገኘው ጊዜን መሻማት ላይ ነው፡፡ በዚህም የትምህርት ዘመኑ ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲቀጥል እየሰራን እንገኛለን፡፡ ሌሎች ግቢዎች ላይ የሚፈጠሩ ችግሮች እኛንም እኩል የሚያሙን ጉዳዮች ናቸው፡፡ ያሉ ችግሮች ተቀርፈው ጊዜን በአግባቡ መጠቀም እንዲቻል ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
(ዶክተር ዳምጠው ዳርዛ) የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጋር በነበራቸው ቆይታ በዩኒቨርሲቲው ስላለው ሰላም እንዲሁም አጠቃላይ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተከታዩን መልዕክት አስተላልፈዋል፦
"በከፍተኛ ትምህርት ተቋሙ ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች የአዕምሮ ሥራ የሚሰሩ ተማሪዎች ናቸው፡፡ በዩኒቨርሲቲው የሚቆዩበት ጊዜም አጭር በመሆኑ ባላቸው ጊዜ አዕምሯቸውን ሙሉ ለሙሉ በሳይንሱ ሥራ ላይ ቢያተኩሩ ወደፊት ለሀገራቸውም ሆነ ለራሳቸው ሙሉ የሆነ የዕውቀትና የክህሎት አስተሳሰብ ታጥቀው ይወጣሉ፡፡ ይህ ባልሆነበት ግን በሌሎች ሀሳብና አስተሳሰብ ጊዜን ማባከን በተሟላ መልኩ ሊያገኙት የሚችሉትን ነገሮችን ያጓድላል፡፡ እኛም እንደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ አሁን ላይ ትኩረት አድርገን እየሰራን የምንገኘው ጊዜን መሻማት ላይ ነው፡፡ በዚህም የትምህርት ዘመኑ ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲቀጥል እየሰራን እንገኛለን፡፡ ሌሎች ግቢዎች ላይ የሚፈጠሩ ችግሮች እኛንም እኩል የሚያሙን ጉዳዮች ናቸው፡፡ ያሉ ችግሮች ተቀርፈው ጊዜን በአግባቡ መጠቀም እንዲቻል ሁሉም የድርሻውን መወጣት ይጠበቅበታል፡፡"
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#Setaweet
#አለኝታ
#orangetheworld
#16DaysOfActivism
#GenerationEquality
ጾታዊ እኩልነት ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ ለማምጣት እና ጾታዊ ጥቃትን ለመቀነስ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረገው የ16 ቀን ንቅናቄ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ሴታዊት የተሰኘው ድርጅትም በማህበራዊ ድረ፟ ገጾች ላይ ፎቶግራፎችን፣ ምስሎችን፣ የተለያዩ የውይይት ርእሶችን በመፍጠር እየሰሩ ይገኛሉ፡፡
ቪድዮውን ሼር ያድርጉት!
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#አለኝታ
#orangetheworld
#16DaysOfActivism
#GenerationEquality
ጾታዊ እኩልነት ላይ የአስተሳሰብ ለውጥ ለማምጣት እና ጾታዊ ጥቃትን ለመቀነስ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚደረገው የ16 ቀን ንቅናቄ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ ሴታዊት የተሰኘው ድርጅትም በማህበራዊ ድረ፟ ገጾች ላይ ፎቶግራፎችን፣ ምስሎችን፣ የተለያዩ የውይይት ርእሶችን በመፍጠር እየሰሩ ይገኛሉ፡፡
ቪድዮውን ሼር ያድርጉት!
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#FakeNewsAlert
"የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ የስራ መልቀቂያ አላስገቡም!"-የመከላከያ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል
አቶ ለማ መገርሳ የስራ መልቀቂያ አስገብተዋል ተብሎ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሐሰት መሆኑን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። የመከላከያ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ እንዳስታወቀው ሚንስትሩ አቶ ለማ መገርሳ መልቀቂያ አላስገቡም ብሏል።
አቶ ለማ በአሜሪካ ስራቸውን በማከናወን ላይ ናቸው የስራ መልቀቂያ አስገቡ ተብሎ እየተናፈሰ ያለው መረጃ ከአውነት የራቀ መሆኑን አስታውቋል። የኮሚንኬሽን ክፍሉ ለሬድዮ ጣቢያው እንደገለፀው በተቋም ደረጃ እንደዚህ አይነት መረጃ የለም ውሸት ነው ሲል የተናገረ ሲሆን ከዛ ውጪ የሚናፈሰው ወሬ የፖለቲከኞች እንጂ በተቋም ደረጃ ስለዚህ ጉዳይ የተነሳ ነገር የለም ብሏል፡፡
(ETHIO FM 107.8)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ የስራ መልቀቂያ አላስገቡም!"-የመከላከያ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል
አቶ ለማ መገርሳ የስራ መልቀቂያ አስገብተዋል ተብሎ እየተናፈሰ ያለው ወሬ ሐሰት መሆኑን የመከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። የመከላከያ ሚንስቴር የህዝብ ግንኙነት ክፍል ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ ጣቢያ እንዳስታወቀው ሚንስትሩ አቶ ለማ መገርሳ መልቀቂያ አላስገቡም ብሏል።
አቶ ለማ በአሜሪካ ስራቸውን በማከናወን ላይ ናቸው የስራ መልቀቂያ አስገቡ ተብሎ እየተናፈሰ ያለው መረጃ ከአውነት የራቀ መሆኑን አስታውቋል። የኮሚንኬሽን ክፍሉ ለሬድዮ ጣቢያው እንደገለፀው በተቋም ደረጃ እንደዚህ አይነት መረጃ የለም ውሸት ነው ሲል የተናገረ ሲሆን ከዛ ውጪ የሚናፈሰው ወሬ የፖለቲከኞች እንጂ በተቋም ደረጃ ስለዚህ ጉዳይ የተነሳ ነገር የለም ብሏል፡፡
(ETHIO FM 107.8)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በድጋሚ ለሀገራችን መንግስት ጥሪ እናቀርባለን!
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያሉ እንቅስቃሴዎችን በንቃት ሲከታተል ቆይቷል። ተማሪዎች የሚያቀርቡትን ቅሬታዎች፣ ጥያቄዎች፣ የሚደርሱባቸው ችግሮችን በገፁ አማካኝነት ለሚመለከታቸው ሲያቀርብ ነበር። ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት የነበረው እንቅስቃሴ እና በዚህ ዓመት የተመለከትናቸው ፈፅሞ የሚገናኙ አይደሉም። መረጃዎች ሁሉ መልካቸውን የሚቀይሩበት፣ ነገሮች የሚቀጣጠሉበት ሁኔታም ከዚህ በፊት ገጥሞን አያውቅም።
ከዚህ ቀደም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በጋር ሆነው ችግሮቻቸው እንዲፈቱላቸው ሲተገሉ፣ ሢጠይቁ፣ ድምፃቸውን በጋራ ሲያሰሙ ነው የምናውቀው አሁን ግን እየተመለከትነው ያለነው ነገር እጅግ ተቃራኒው ነው። ይህ ጉዳይ ነገ ሳይሆን ዛሬ እልባት ካልተሰጠው ሀገሪቷን ከባድ ፈተና ውስጥ ይከታታል። በየዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከህግ በላይ የሆኑ አካላት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴዎች በዝምታ እየታለፈ፣ በሚዲያዎች እየቀርቡ የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች መስጠት ተማሪዎችን እና የተማሪ ወላጆችን እያስቆጣ ነው።
ውድ ቤተሰበቦቻችን ዛሬም የሚሰማን የመንግስት አካል ካለ እንጮሃለን፤ የት የት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተለይተው እንዳይማሩ እየተደረገ እንደሆነ፣ የት የት ዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደተቋረጠ፣ የትኞቹ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ተማሪዎች ማስፈራሪያ እንደሚደርሳቸው፣ በየትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የማስጠንቀቂያ ወረቀቶች እንደልብ እንደሚሰራጩ፣ ከየትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በስጋት ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ግቢ ለቀው እንደወጡ፣ በየትኛው ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚደርሳቸውን ማስፈራሪያ ምክንያት ሰግተው አዳራሽ ውስጥ እንዳሉ መንግስትና የዩኒቨርሲቲ አስተዳደሮች ጠንቅቀው እንደሚያውቁ እናምናለን።
ተጨማሪ አንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-12-06
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያሉ እንቅስቃሴዎችን በንቃት ሲከታተል ቆይቷል። ተማሪዎች የሚያቀርቡትን ቅሬታዎች፣ ጥያቄዎች፣ የሚደርሱባቸው ችግሮችን በገፁ አማካኝነት ለሚመለከታቸው ሲያቀርብ ነበር። ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት የነበረው እንቅስቃሴ እና በዚህ ዓመት የተመለከትናቸው ፈፅሞ የሚገናኙ አይደሉም። መረጃዎች ሁሉ መልካቸውን የሚቀይሩበት፣ ነገሮች የሚቀጣጠሉበት ሁኔታም ከዚህ በፊት ገጥሞን አያውቅም።
ከዚህ ቀደም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በጋር ሆነው ችግሮቻቸው እንዲፈቱላቸው ሲተገሉ፣ ሢጠይቁ፣ ድምፃቸውን በጋራ ሲያሰሙ ነው የምናውቀው አሁን ግን እየተመለከትነው ያለነው ነገር እጅግ ተቃራኒው ነው። ይህ ጉዳይ ነገ ሳይሆን ዛሬ እልባት ካልተሰጠው ሀገሪቷን ከባድ ፈተና ውስጥ ይከታታል። በየዩኒቨርሲቲ ውስጥ ከህግ በላይ የሆኑ አካላት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴዎች በዝምታ እየታለፈ፣ በሚዲያዎች እየቀርቡ የተዛቡ እና የተሳሳቱ መረጃዎች መስጠት ተማሪዎችን እና የተማሪ ወላጆችን እያስቆጣ ነው።
ውድ ቤተሰበቦቻችን ዛሬም የሚሰማን የመንግስት አካል ካለ እንጮሃለን፤ የት የት ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተለይተው እንዳይማሩ እየተደረገ እንደሆነ፣ የት የት ዩኒቨርሲቲ ትምህርት እንደተቋረጠ፣ የትኞቹ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ተማሪዎች ማስፈራሪያ እንደሚደርሳቸው፣ በየትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የማስጠንቀቂያ ወረቀቶች እንደልብ እንደሚሰራጩ፣ ከየትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ በስጋት ምክንያት በርካታ ተማሪዎች ግቢ ለቀው እንደወጡ፣ በየትኛው ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በሚደርሳቸውን ማስፈራሪያ ምክንያት ሰግተው አዳራሽ ውስጥ እንዳሉ መንግስትና የዩኒቨርሲቲ አስተዳደሮች ጠንቅቀው እንደሚያውቁ እናምናለን።
ተጨማሪ አንብቡ👇
https://telegra.ph/ETH-12-06
840 ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረቢያ ተመለሱ!
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሳኡዲ አረቢያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት በሳኡዲ እስር ቤቶች ከአምስት እስከ ስምንት አመት ተፈርዶባቸው የነበሩ 840 ኢትዮጵያዊያን በፈቃዳቻው ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።
ኢትዮጵያዊያኑ ቀይ ባህርን አቋርጠው የሳኡዲን ድንበር ሲሻገሩ የተያዙ እና በሳኡዲ አረቢያ በጂዳ እና ጂዛን ግዛት በሚገኙ እስር ቤቶች ይኖሩ የነበሩ ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ ወጣቶች መሆናቸው ተጠቅሷል። ተመላሾቹ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማሪፊያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ዮሃንስ ሾዴ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሳኡዲ አረቢያ መንግስት ጋር ባደረገው ስምምነት መሰረት በሳኡዲ እስር ቤቶች ከአምስት እስከ ስምንት አመት ተፈርዶባቸው የነበሩ 840 ኢትዮጵያዊያን በፈቃዳቻው ዛሬ ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።
ኢትዮጵያዊያኑ ቀይ ባህርን አቋርጠው የሳኡዲን ድንበር ሲሻገሩ የተያዙ እና በሳኡዲ አረቢያ በጂዳ እና ጂዛን ግዛት በሚገኙ እስር ቤቶች ይኖሩ የነበሩ ሲሆኑ፣ አብዛኞቹ ወጣቶች መሆናቸው ተጠቅሷል። ተመላሾቹ አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማሪፊያ ሲደርሱ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የቆንስላ ጉዳዮች ዳይሬክተር ጄኔራል አቶ ዮሃንስ ሾዴ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#FakePage
ይህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ስም የተከፈተ እና ከ4,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ ሃሰተኛ ነው። ገፁ ላይም እየተላለፉ የሚገኙት መልዕክቶች የጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳልሆኑ አረጋግጠናል። ትክክለኛው የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ የግል የፌስቡክ ገፅ በፌስቡክ Verify የተደረገና ከ300,000 በላይ ተከታይ ያለው ብቻ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ይህ በጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ስም የተከፈተ እና ከ4,000 በላይ ተከታዮች ያሉት የፌስቡክ ገፅ ሃሰተኛ ነው። ገፁ ላይም እየተላለፉ የሚገኙት መልዕክቶች የጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳልሆኑ አረጋግጠናል። ትክክለኛው የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አሊ የግል የፌስቡክ ገፅ በፌስቡክ Verify የተደረገና ከ300,000 በላይ ተከታይ ያለው ብቻ ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ስራ አመራር ቦርድ አባላት የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክትን እየጎበኙ ነው!
በአምባሳደር ግርማ ብሩ የተመራው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቦርድ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የመስክ ጉብኝት እያደረገ ነው፡፡ በጉብኝቱ ወቅት አምባሰደር ግርማ እንደተናገሩት ጉብኝቱ ፕሮጀክቱን ከሰነድ ሪፖርት ባለፈ በአካል የማየት እና የመገምገም ዓላማ አለው።
ጉብኝቱ ከፕሮጀክቱ የስራ ተቋራጮች ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር በመወያየት ያጋጠሙ ችግሮችና ደካማ አፈፃፀሞች ካሉ በግልፅ በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ለመስቀመጥ እንዲሁም ፕሮጀክቱ በቀጣይ በተሻለ አፈፃፀም ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በመስክ ምልከታውም የስራ አመራር ቦርድ አባላቱ የፕሮጀክቱን የተለያዩ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ በዶ/ር አብርሃም በላይ እና በፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ በኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሰፋ ያለ ገለጻና ማብራሪያ ተሠጥቷቸዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላም ከፕሮጀክቱ የስራ ተቋራቱጮች ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር በተለይ በቅድሚያ ኃይል ያመነጫሉ ተብሎ በሚጠበቁት ሁለቱ ዩኒቶች ማለትም ዩኒት 9 እና 10 የስራ አፈጻጸም ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ማካሄዳቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል፡፡
(ኢቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በአምባሳደር ግርማ ብሩ የተመራው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስራ አመራር ቦርድ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የመስክ ጉብኝት እያደረገ ነው፡፡ በጉብኝቱ ወቅት አምባሰደር ግርማ እንደተናገሩት ጉብኝቱ ፕሮጀክቱን ከሰነድ ሪፖርት ባለፈ በአካል የማየት እና የመገምገም ዓላማ አለው።
ጉብኝቱ ከፕሮጀክቱ የስራ ተቋራጮች ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር በመወያየት ያጋጠሙ ችግሮችና ደካማ አፈፃፀሞች ካሉ በግልፅ በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫ ለመስቀመጥ እንዲሁም ፕሮጀክቱ በቀጣይ በተሻለ አፈፃፀም ተጠናክሮ በሚቀጥልበት ሁኔታ ላይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በመስክ ምልከታውም የስራ አመራር ቦርድ አባላቱ የፕሮጀክቱን የተለያዩ የሲቪልና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ስራዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈጻሚ በዶ/ር አብርሃም በላይ እና በፕሮጀክቱ ዋና ስራ አስኪያጅ በኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ ሰፋ ያለ ገለጻና ማብራሪያ ተሠጥቷቸዋል፡፡
ከጉብኝቱ በኋላም ከፕሮጀክቱ የስራ ተቋራቱጮች ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ጋር በተለይ በቅድሚያ ኃይል ያመነጫሉ ተብሎ በሚጠበቁት ሁለቱ ዩኒቶች ማለትም ዩኒት 9 እና 10 የስራ አፈጻጸም ዙሪያ ጥልቅ ውይይት ማካሄዳቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል፡፡
(ኢቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ETHIOPIA
10 የፓለቲካ ፓርቲዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በጋራ ለመስራት በትላንትናው ዕለት ስምምነቱ ላይ ደርሰዋል። ፓርቲዎቹ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ኢሌሌ ሆቴል ተፈራርመዋል።
ፓርቲዎቹም፦
•የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
•የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)
•የአፋር ህዝቦች ነፃነት ፓርቲ ፣
•የሲዳማ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ፣
•የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ
•የጋምቤላ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ
•የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
•የአገው ሀገር አቀፍ ሸንጎ
•የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና
•የካፋ አረንጓዴ ፓርቲ ናቸው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
10 የፓለቲካ ፓርቲዎች በሀገር አቀፍ ደረጃ በጋራ ለመስራት በትላንትናው ዕለት ስምምነቱ ላይ ደርሰዋል። ፓርቲዎቹ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን ስምምነት በትላንትናው እለት በአዲስ አበባ ኢሌሌ ሆቴል ተፈራርመዋል።
ፓርቲዎቹም፦
•የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)
•የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ)
•የአፋር ህዝቦች ነፃነት ፓርቲ ፣
•የሲዳማ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ ፣
•የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ
•የጋምቤላ ህዝቦች ነፃነት ንቅናቄ
•የቅማንት ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ
•የአገው ሀገር አቀፍ ሸንጎ
•የሞቻ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እና
•የካፋ አረንጓዴ ፓርቲ ናቸው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#GAMBELA
በጋምቤላ ያለ ሰሌዳ ቁጥር ሲንቀሳቀሱና መንጃ ፈቃድ በሌላቸው ግለሰቦች ሲነዱ የነበሩ 101 ሞተር ሳይክሎች መያዙን የከተማዋ ፖሊስ ገለፀ።
በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ ቁጥጥር ስታቲስቲክስ ኦፊሰር ምክትል ኢንስፔክተር ታደለ አየለ ንደገለፁት ሞተር ሳይክሎቹ የተያዙት አንዳንዶቹ ያለ መንጃ ፈቃድ ሲያሽከረክሩ ቀሪዎቹ ደግሞ የሰሌዳ ቁጥር ስለሌላቸው ነው ብለዋል።
በተደረገው ድንገተኛ ቁጥጥር 101 ሞተር ሳይክሎች የተያዙ ሲሆን ቁጥጥሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። ከተያዙት ሞተር ሳይክሎች መካከል 27ቱ የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ የመንጃ ፈቃድ በሌላቸው ግለሰቦች ሲሽከረከሩ የነበሩ ናቸው።
በተለይም በከተማዋ የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው ሞተር ሳይክሎች አደጋ አድርሰው የሚጠፉበት ሁኔታ መኖሩን ምክትል ኢንስፔክተሩ ጠቁመው ችግሩን ለመፍታት የትራፊክ ፖሊስ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጋምቤላ ያለ ሰሌዳ ቁጥር ሲንቀሳቀሱና መንጃ ፈቃድ በሌላቸው ግለሰቦች ሲነዱ የነበሩ 101 ሞተር ሳይክሎች መያዙን የከተማዋ ፖሊስ ገለፀ።
በክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የትራፊክ አደጋ ቁጥጥር ስታቲስቲክስ ኦፊሰር ምክትል ኢንስፔክተር ታደለ አየለ ንደገለፁት ሞተር ሳይክሎቹ የተያዙት አንዳንዶቹ ያለ መንጃ ፈቃድ ሲያሽከረክሩ ቀሪዎቹ ደግሞ የሰሌዳ ቁጥር ስለሌላቸው ነው ብለዋል።
በተደረገው ድንገተኛ ቁጥጥር 101 ሞተር ሳይክሎች የተያዙ ሲሆን ቁጥጥሩ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስረድተዋል። ከተያዙት ሞተር ሳይክሎች መካከል 27ቱ የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ የመንጃ ፈቃድ በሌላቸው ግለሰቦች ሲሽከረከሩ የነበሩ ናቸው።
በተለይም በከተማዋ የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው ሞተር ሳይክሎች አደጋ አድርሰው የሚጠፉበት ሁኔታ መኖሩን ምክትል ኢንስፔክተሩ ጠቁመው ችግሩን ለመፍታት የትራፊክ ፖሊስ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
(ENA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ODP #ADAMA
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) የክልል አመራሮች በብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ህገ ደንብ ዙሪያ እየመከሩ ነው። በአዳማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ውይይት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የኦዲፒ የዞን አመራሮች ተሳትፈዋል።
በምክክር መድረኩ በውህድ ፓርቲው ፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ህገ ደንብና የድርጅቱ አወቃቀር ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። ከዚህ ባለፈም በፓርቲው ዙሪያ በሚነሱ የተለያዩ የግልጸኝነት ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት የሚደረግ መሆኑን ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) የክልል አመራሮች በብልጽግና ፓርቲ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ህገ ደንብ ዙሪያ እየመከሩ ነው። በአዳማ ከተማ እየተካሄደ በሚገኘው በዚህ ውይይት በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የኦዲፒ የዞን አመራሮች ተሳትፈዋል።
በምክክር መድረኩ በውህድ ፓርቲው ፕሮግራም፣ በመተዳደሪያ ህገ ደንብና የድርጅቱ አወቃቀር ዙሪያ ውይይት እየተደረገ ይገኛል። ከዚህ ባለፈም በፓርቲው ዙሪያ በሚነሱ የተለያዩ የግልጸኝነት ጥያቄዎች ዙሪያ ውይይት የሚደረግ መሆኑን ከኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመላክታል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TIGRAY
በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን መኾኒ ከተማ ትናንት ሌሊት በደረሰው የእሳት አደጋ 2 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የራያ አዘቦ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ገለፀ።
የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሓየሎም ረዳኢ እንደገለፁት የእሳት አደጋው ያጋጠመው ትናንት ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ነው የደረሰው። የአደጋው መንስኤ የኤሌክትሪክ ገመድ እርስ በራሱ ተጠላልፎ በፈጠረው እሳት ሲሆን በከተማው የገበያ ቦታ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት አድርሷል።
በአደጋው የ56 ነጋዴዎች ዘይትና ጫማ ሙሉ በሙሉ ወድሟል ። ህብረተሰቡ ባደረገው ርብርብ በሌሎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ ሱቆች ላይ ተጨማሪ አደጋ ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል።
(ኢዜአ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን መኾኒ ከተማ ትናንት ሌሊት በደረሰው የእሳት አደጋ 2 ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን የራያ አዘቦ ወረዳ ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ገለፀ።
የፅህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሓየሎም ረዳኢ እንደገለፁት የእሳት አደጋው ያጋጠመው ትናንት ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይ ነው የደረሰው። የአደጋው መንስኤ የኤሌክትሪክ ገመድ እርስ በራሱ ተጠላልፎ በፈጠረው እሳት ሲሆን በከተማው የገበያ ቦታ ሁለት ሚሊዮን ብር የሚገመት ጉዳት አድርሷል።
በአደጋው የ56 ነጋዴዎች ዘይትና ጫማ ሙሉ በሙሉ ወድሟል ። ህብረተሰቡ ባደረገው ርብርብ በሌሎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ ሱቆች ላይ ተጨማሪ አደጋ ሳያደርስ በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጓል።
(ኢዜአ)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ህዳር29
ለ14ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበረው የኢትዮጰያ ብሔር ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሰላም እንዲከበር የፀጥታ አካለት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
“ህገ-መንግስታዊ ቃል ኪዳናችን ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ቃል ህዳር 29 ቀን 2012 ዓ/ም በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት 14ኛው የኢትዮጰያ ብሔር ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአዲስ አበባ ስታዲየም በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡
በበዓሉ ላይ ለመታደም እንግዶች ወደ አዲስ አበባ እየገቡ መሆኑን ኮሚሽኑ ጠቁሞ በብሔራዊ ደረጃ በሚከበረውና በርካታ ህዝብ የሚታደምበት በዓል በሰላም እንዲከበር ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ፣ የኦሮሚያና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽኖች እንዲሁም ሌሎች ተቋማትን ያካተተ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት ተዋቅሮ ስራ መጀመሩን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡
More👇
https://telegra.ph/ETH-12-07
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለ14ኛ ጊዜ በአዲስ አበባ ከተማ የሚከበረው የኢትዮጰያ ብሔር ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በሰላም እንዲከበር የፀጥታ አካለት አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቀው ወደ ስራ መግባታቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡
“ህገ-መንግስታዊ ቃል ኪዳናችን ለዘላቂ ሰላም” በሚል መሪ ቃል ህዳር 29 ቀን 2012 ዓ/ም በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አዘጋጅነት 14ኛው የኢትዮጰያ ብሔር ፣ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በአዲስ አበባ ስታዲየም በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡
በበዓሉ ላይ ለመታደም እንግዶች ወደ አዲስ አበባ እየገቡ መሆኑን ኮሚሽኑ ጠቁሞ በብሔራዊ ደረጃ በሚከበረውና በርካታ ህዝብ የሚታደምበት በዓል በሰላም እንዲከበር ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ፣ የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ፣ የኦሮሚያና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽኖች እንዲሁም ሌሎች ተቋማትን ያካተተ የፀጥታ ኮማንድ ፖስት ተዋቅሮ ስራ መጀመሩን ኮሚሽኑ ገልጿል፡፡
More👇
https://telegra.ph/ETH-12-07
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የሚዘጉ መንገዶች!
ህዳር 29 "የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን" አስመልከቶ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚከናወኑ ልዩ ልዩ ስነ-ስርዓት ተጀምረው እስከሚጠናቁ ድረስ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር፡-
• ከሰንጋ ተራ ወደ ለገሃር
• ከሜክሲኮ አደባባይ በለገሃር ወደ አዲስ አበባ ስታዲየም
• ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሃር
• ከሀራምቤ ሆቴል ወደ ለገሃር
• ከሀራምቤ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ሲሆኑ፡-
ከፕሮግራሙ ዋዜማ ማታ ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሚካሄደው ስነ-ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በስታዲየም ዙሪያ እና አካባቢው በግራና ቀኝ ለረጅም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የገለፀ ሲሆን፤ ህብረተሰቡ ለጸጥታ አጠራጣሪ የሆኑ ነገሮች ሲያጋጥሙት ይሁን የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በስልክ ቁጥሮች-
11-5-52-63-03 ፣
011-5-52-40-77 ፣
0115-52-63-02 ፣
011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 እና 987 መጠቀም እንደሚችል ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ህዳር 29 "የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን" አስመልከቶ በአዲስ አበባ ስታዲየም የሚከናወኑ ልዩ ልዩ ስነ-ስርዓት ተጀምረው እስከሚጠናቁ ድረስ የትራፊክ መጨናነቅ እንዳይፈጠር፡-
• ከሰንጋ ተራ ወደ ለገሃር
• ከሜክሲኮ አደባባይ በለገሃር ወደ አዲስ አበባ ስታዲየም
• ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሃር
• ከሀራምቤ ሆቴል ወደ ለገሃር
• ከሀራምቤ ሆቴል ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ሲሆኑ፡-
ከፕሮግራሙ ዋዜማ ማታ ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታዲዮም የሚካሄደው ስነ-ስርዓት ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በስታዲየም ዙሪያ እና አካባቢው በግራና ቀኝ ለረጅም ሆነ ለአጭር ጊዜ ተሽከርካሪ አቁሞ መሄድ ፍፁም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የገለፀ ሲሆን፤ ህብረተሰቡ ለጸጥታ አጠራጣሪ የሆኑ ነገሮች ሲያጋጥሙት ይሁን የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በስልክ ቁጥሮች-
11-5-52-63-03 ፣
011-5-52-40-77 ፣
0115-52-63-02 ፣
011-1-11-01-11 ወይም በነፃ ስልክ መስመር 991 እና 987 መጠቀም እንደሚችል ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ባህርዳር ከነማ ከ መቐለ 70 እንደርታ!
የባሕር ዳር ከነማ እና የመቀሌ 70 እንደርታ ቡድኖች ደጋፊዎች ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ በጋራ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል፡፡
በከተማዋ የሚገኙ የመንገድ ዳርቻዎችንና መናፈሻዎችን ነው በጋራ ሲያጸዱ ያረፈዱት፡፡ የጽዳት ዘመቻው በባሕር ዳር ከተማ የጽዳት ዘመቻ ሥራ በቋሚነት በሚያከናውኑ
በጎፈቃደኞች የተዘጋጀ ነው።
(TIKVAH FAMILY)
Join👇
@tikvahethsport
የባሕር ዳር ከነማ እና የመቀሌ 70 እንደርታ ቡድኖች ደጋፊዎች ዛሬ በባሕር ዳር ከተማ በጋራ የጽዳት ዘመቻ አካሂደዋል፡፡
በከተማዋ የሚገኙ የመንገድ ዳርቻዎችንና መናፈሻዎችን ነው በጋራ ሲያጸዱ ያረፈዱት፡፡ የጽዳት ዘመቻው በባሕር ዳር ከተማ የጽዳት ዘመቻ ሥራ በቋሚነት በሚያከናውኑ
በጎፈቃደኞች የተዘጋጀ ነው።
(TIKVAH FAMILY)
Join👇
@tikvahethsport
እግር ኳስ ለሰላም፣ ለፍቅር፣ ለአንድነት፣ ለአብሮነት፣ ለሀገር ግንባታ!
#ባህርዳር_ከነማ
#መቐለ70_እንደርታ
PHOTO : ጋንታ መቐለ 70 እንደርታ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ባህርዳር_ከነማ
#መቐለ70_እንደርታ
PHOTO : ጋንታ መቐለ 70 እንደርታ
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ህዳር29
ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ በኦሮሚያ ክልል አዘጋጅነት ለሚከበረው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በድምቀትና በሰላም መጠናቀቅ የቡራዩ ከተማ ድርሻ ወስዶ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ። እንግዶችን ተቀብሎ ከማስተናገድ ጀምሮ እስከበዓሉ ፍጻሜ የሚያግዙ ከ100 በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በከተማ አስተዳደሩ መዘጋጀታቸውም ተጠቁሟል።
(EPA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ በኦሮሚያ ክልል አዘጋጅነት ለሚከበረው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በድምቀትና በሰላም መጠናቀቅ የቡራዩ ከተማ ድርሻ ወስዶ እየሠራ መሆኑ ተገለጸ። እንግዶችን ተቀብሎ ከማስተናገድ ጀምሮ እስከበዓሉ ፍጻሜ የሚያግዙ ከ100 በላይ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በከተማ አስተዳደሩ መዘጋጀታቸውም ተጠቁሟል።
(EPA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የተሰማሩ ሁለት ፖሊሶች ተገደሉ! በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ አዱላላ ቦኩ በሚባል ቀበሌ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጠርጣሪን ለመያዝ የተሰማሩ ሁለት የዞኑ የፖሊስ አባላት መገደላቸውን ፖሊስ አስታወቀ። የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ሽፈራው ጉቱ "ፖሊሶች ወደ ቀበሌው ሄደው ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ሲሉ 'ለምን ይያዛሉ?' በሚል ረብሻ ተነስቶ የአከባቢው…
የፖሊስ አባላት ላይ የግድያና የአካል ጉዳት አድርሰዋል የተባሉ 46 ተጠርጣሪዎች ተያዙ!
በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ ህግን ለማስከበር በተሰማሩ የፖሊስ አባላት ላይ የግድያና የአካል ጉዳት አድርሰዋል ተብለው የተጠረጠሩ 46 ግለሰቦች መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።
የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር አስቻለው አለሙ እንደገለጹት ትናንት የተያዙ እነዚህ ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ትእዛዝ ለማስፈጸም በተሰማሩ የፖሊስ አባላት ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ተብለው ነው።
እንደ ኮማንደሩ ማብራሪያ አራት የፖሊስ አባላት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለማስከበር በአዳማ ወረዳ አዱላላ ቦኩ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ህዳር 24/2012 ዓ.ም ከንጋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ከሩብ አካባቢ ያመራሉ።
ፖሊሶቹ በአካባቢው እንደደረሱ ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ ሲሞክሩ ለምን ይያዛሉ በሚል በአካባቢው ሁከት ይነሳል። በዚህ ወቅት የፖሊስ አባላቱ ሁከቱን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ ሁለት አባላት በስላት በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ኮማንደር አስቻለው አመልክተዋል።
“ፖሊሶቹ የታጠቁት መሳሪያ በርቆም አንድ ሲቪል ህይወቱ ሲያልፍ በሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ደግሞ በድብደባ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል “ብለዋል።
የማቾቹ አስክሬን ለቤተሰቦቻቸው በማስረከብ የቀብር ስነ ስርዓታቸው መፈጸሙን የገለጹት ኮማንደር አስቻለው ጉዳት የደረሰባቸው ሁለቱ የፖሊስ አባላት ደግሞ ፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል ተልከው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑንም አስታውቀዋል። በአካባቢው በተደረገው አሰሳ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 46 ግለሰቦች ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑንም ገልጸዋል።
(ENA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ ህግን ለማስከበር በተሰማሩ የፖሊስ አባላት ላይ የግድያና የአካል ጉዳት አድርሰዋል ተብለው የተጠረጠሩ 46 ግለሰቦች መያዙን ፖሊስ አስታወቀ።
የዞኑ ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር አስቻለው አለሙ እንደገለጹት ትናንት የተያዙ እነዚህ ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ትእዛዝ ለማስፈጸም በተሰማሩ የፖሊስ አባላት ላይ ጥቃት ፈጽመዋል ተብለው ነው።
እንደ ኮማንደሩ ማብራሪያ አራት የፖሊስ አባላት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ለማስከበር በአዳማ ወረዳ አዱላላ ቦኩ ቀበሌ ገበሬ ማህበር ህዳር 24/2012 ዓ.ም ከንጋቱ አስራ ሁለት ሰዓት ከሩብ አካባቢ ያመራሉ።
ፖሊሶቹ በአካባቢው እንደደረሱ ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ ሲሞክሩ ለምን ይያዛሉ በሚል በአካባቢው ሁከት ይነሳል። በዚህ ወቅት የፖሊስ አባላቱ ሁከቱን ለማረጋጋት ቢሞክሩም ከቁጥጥር ውጪ ሆኖ ሁለት አባላት በስላት በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ኮማንደር አስቻለው አመልክተዋል።
“ፖሊሶቹ የታጠቁት መሳሪያ በርቆም አንድ ሲቪል ህይወቱ ሲያልፍ በሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ደግሞ በድብደባ ከፍተኛ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል “ብለዋል።
የማቾቹ አስክሬን ለቤተሰቦቻቸው በማስረከብ የቀብር ስነ ስርዓታቸው መፈጸሙን የገለጹት ኮማንደር አስቻለው ጉዳት የደረሰባቸው ሁለቱ የፖሊስ አባላት ደግሞ ፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል ተልከው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑንም አስታውቀዋል። በአካባቢው በተደረገው አሰሳ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የተጠረጠሩ 46 ግለሰቦች ተይዘው ምርመራ እየተደረገባቸው መሆኑንም ገልጸዋል።
(ENA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ170 ሚሊየን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ!
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ170 ሚሊየን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኦርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅትም ህብረቱ ለኢትዮጵያ ጤና፣ ምርጫ ቦርድ ማጠናከሪያ፣ የስራ እድል ፈጠራ እና ኢንቨስትመንት የሚውል የ170 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ አድርጓል።
ከዚህ ውስጥ 50 ሚሊየን ዩሮ ለጤና የሚውል ሲሆን፥ 10 ሚሊየን ዩሮው ደግሞ ለስራ እድል ፈጠራና ኢንቨስትመንት እንዲሁም 10 ሚሊየን ዩሮ ለምርጫ ቦርድ ማጠናከሪያ ይውላል ተብሏል።
ከዚህ ባለፈም 100 ሚሊየን ዩሮው በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ማዕቀፍ ስምምነት መሰረት ሃገር በቀል ማሻሻያውን በቀጥታ ለማገዝ ይውላል ነው የተባለው። በተጨማሪም ድጋፉ የቀጠናውን መሰረተ ልማት ትስስር ለማሳደግ የሚውልም ይሆናል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia
የአውሮፓ ህብረት ለኢትዮጵያ የ170 ሚሊየን ዩሮ የገንዘብ ድጋፍ አደረገ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከአውሮፓ ኮሚሽን ፕሬዚዳንት ኦርሱላ ቮን ደር ሌይን ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱ ወቅትም ህብረቱ ለኢትዮጵያ ጤና፣ ምርጫ ቦርድ ማጠናከሪያ፣ የስራ እድል ፈጠራ እና ኢንቨስትመንት የሚውል የ170 ሚሊየን ዩሮ ድጋፍ አድርጓል።
ከዚህ ውስጥ 50 ሚሊየን ዩሮ ለጤና የሚውል ሲሆን፥ 10 ሚሊየን ዩሮው ደግሞ ለስራ እድል ፈጠራና ኢንቨስትመንት እንዲሁም 10 ሚሊየን ዩሮ ለምርጫ ቦርድ ማጠናከሪያ ይውላል ተብሏል።
ከዚህ ባለፈም 100 ሚሊየን ዩሮው በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት ማዕቀፍ ስምምነት መሰረት ሃገር በቀል ማሻሻያውን በቀጥታ ለማገዝ ይውላል ነው የተባለው። በተጨማሪም ድጋፉ የቀጠናውን መሰረተ ልማት ትስስር ለማሳደግ የሚውልም ይሆናል።
(ኤፍ ቢ ሲ)
@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia