#ETHIOPIA የወልዋሎና የመቐለ 70 እንደርታ ደጋፊዎች የኣንበጣ መንጋን በማስወገድ ዘመቻ ላይ!
PHOTO: JHON
@tsegabwolde @tikvahethiopia
PHOTO: JHON
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#CBE
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥቅምት 03/2012 ከ30,000 ለሚልቁ ሰራተኞቹ በላከው የውስጥ ማስታወሻ የደንበኛ አገልግሎት የሚሰጡ የድርጅቱ ሠራተኞች በሥራ ሰዓት የስልክ ጥሪን ጨምሮ የማህበራዊ ሚድያ እና ሌሎች የሞባይል ስልክ አገልግሎቶችን እንዳይጠቀሙ ከልክሏል።
በሲስተም መጨናነቅ ምክንያትና የኤቲኤም ማሽኖች በአግባቡ ባለመሥራታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ የደንበኞቹ ቅሬታ እየጠነከረ የመጣበት ባንኩ፣ በስትራቴጂክ እና ኢኖቬሽን ክፍሉ አማካኝነት አጠናሁ ባለው የዳሰሳ ጥናት መሠረት፤ የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መጥቶ የከፋ ደረጃ ላይ ደርሷል።
ለዚህም አንኳር ተብለው ከተቀመጡ ምክንያቶች መካከል የደንበኞች አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች የሞባይል ስልክ አጠቃቀም ሆኖ በመገኘቱ በውስጥ እርምጃው እንዳስፈለገ የውስጥ ማስታወሻው ላይ መጠቀሱን አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ዘግቧል።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥቅምት 03/2012 ከ30,000 ለሚልቁ ሰራተኞቹ በላከው የውስጥ ማስታወሻ የደንበኛ አገልግሎት የሚሰጡ የድርጅቱ ሠራተኞች በሥራ ሰዓት የስልክ ጥሪን ጨምሮ የማህበራዊ ሚድያ እና ሌሎች የሞባይል ስልክ አገልግሎቶችን እንዳይጠቀሙ ከልክሏል።
በሲስተም መጨናነቅ ምክንያትና የኤቲኤም ማሽኖች በአግባቡ ባለመሥራታቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ የደንበኞቹ ቅሬታ እየጠነከረ የመጣበት ባንኩ፣ በስትራቴጂክ እና ኢኖቬሽን ክፍሉ አማካኝነት አጠናሁ ባለው የዳሰሳ ጥናት መሠረት፤ የደንበኞች አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሽቆለቆለ መጥቶ የከፋ ደረጃ ላይ ደርሷል።
ለዚህም አንኳር ተብለው ከተቀመጡ ምክንያቶች መካከል የደንበኞች አገልግሎት ሰጪ ሠራተኞች የሞባይል ስልክ አጠቃቀም ሆኖ በመገኘቱ በውስጥ እርምጃው እንዳስፈለገ የውስጥ ማስታወሻው ላይ መጠቀሱን አዲስ ማለዳ ጋዜጣ ዘግቧል።
ምንጭ፦ አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሰሜን ወሎ ዞን በአፋር ክልል እና አማራ ክልሎች አጎራባች ቀበሌዎች ላይ ያለው የፀጥታ ሁኔታ የአንበጣ መንጋውን በሙሉ አቅም ለመከላከል እንዳስቸገራቸው የአካባቢው አርሶ አደሮች ተናግረዋል፡፡ የበረሃ አንበጣው በተከሰተባቸው የሀብሩ እና ራያ ቆቦ ወረዳዎች ላይ በእንስሳት መኖ እና በሰብል ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ነው፡፡
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ባሳለፍነው በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች የፀጥታ መደፍረስ አጋጥሞ እንደነበር ይታወቃል፤ ከሰሞኑ ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያዎች በሚሰራጩ ወሬዎች ግጭት ተፈጥሮባቸው በነበሩ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ስጋት ውስጥ ወድቀው እንደነበር አይዘነጋም። በሁሉም አካባቢዎች በሚባል ደረጃ ሁኔታዎች ተረጋግተዋል። አንፃራዊ ሰላምም ሰፍኗል። አባ ገዳዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ታች ድረስ ወርደው ህዝቡን የማረጋጋት ስራ፣ የማወያየት ስራ እየሰሩ ይገኛሉ። በተለይ በማህበራዊ ሚዳያዎች ትላንት ሰኞ ግጭት ሊፈጠር ነው፣ መንገድ ሊዘጋ ነው፣ እልቂት ይፈፀማል ተብሎ ሲወራባቸው የነበሩት ከተሞች ከባለፈው ሳምንት በተሻለ ሰላም እና መረጋጋት ሰፍኖባቸው መደበኛ እንቅስቃሴዎች ተጀምረው ነው የዋሉት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባሳለፍነው በተለያዩ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች የፀጥታ መደፍረስ አጋጥሞ እንደነበር ይታወቃል፤ ከሰሞኑ ደግሞ በማህበራዊ ሚዲያዎች በሚሰራጩ ወሬዎች ግጭት ተፈጥሮባቸው በነበሩ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች ስጋት ውስጥ ወድቀው እንደነበር አይዘነጋም። በሁሉም አካባቢዎች በሚባል ደረጃ ሁኔታዎች ተረጋግተዋል። አንፃራዊ ሰላምም ሰፍኗል። አባ ገዳዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች ታች ድረስ ወርደው ህዝቡን የማረጋጋት ስራ፣ የማወያየት ስራ እየሰሩ ይገኛሉ። በተለይ በማህበራዊ ሚዳያዎች ትላንት ሰኞ ግጭት ሊፈጠር ነው፣ መንገድ ሊዘጋ ነው፣ እልቂት ይፈፀማል ተብሎ ሲወራባቸው የነበሩት ከተሞች ከባለፈው ሳምንት በተሻለ ሰላም እና መረጋጋት ሰፍኖባቸው መደበኛ እንቅስቃሴዎች ተጀምረው ነው የዋሉት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ባሌ_ሮቤ | ባለፉት ሁለት እና ሶስት ቀናት በማህበራዊ ሚዲያ ብዙ ሲባልባት የነበረችው የባሌ ሮቤ ከተማ ወደ ቀደመው ሰላማዊ እንቅስቃሴዋ እየተመለሰች እንደምትገኝ ተገልጿል። የንግድ እና የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ወደነበረበት ተመልሷል። በሁሉም ቀበሌዎች ውይይቶች እየተደረጉ ይገኛሉ። የሀገር ሽማግሌዎች እና አባ ገዳዎች ህዝቡ ወደቀደመው ሰላማዊ ኑሮው እንዲመለስ ከፍተኛ ስራ እየሰሩ ናቸው። ከሰሞኑ ግጭት ጋር በተያያዘ 27 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል።
Via NIGI
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via NIGI
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ADAMA
የአዳማ ከተማ የዛሬ ውሎ ፍፁም የተረጋጋና ሰላማዊ ነው። የንግድ ተቋማት ወደስራቸው ተመልሰዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደቀደመው ሁኔታ እየተመለሰ ይገኛል። አብዛኛው የትምህርት ተቋማት ግን ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ተማሪዎች አልተገኙም። የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደሚሉት በተማሪዎች መካከል ግጭት እንዳይፈጠር በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት አላኩም ብለዋል። በትላናንትናው ዕለት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከተማይቱ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷን ገልፆ በቀጣይ ቀናትም ትምህርት ቤቶች ወደ ስራ ይመለሳሉ ሲል ገልጿል።
PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዳማ ከተማ የዛሬ ውሎ ፍፁም የተረጋጋና ሰላማዊ ነው። የንግድ ተቋማት ወደስራቸው ተመልሰዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ወደቀደመው ሁኔታ እየተመለሰ ይገኛል። አብዛኛው የትምህርት ተቋማት ግን ዛሬም እንደተዘጉ ናቸው ተማሪዎች አልተገኙም። የቲክቫህ ቤተሰቦች እንደሚሉት በተማሪዎች መካከል ግጭት እንዳይፈጠር በመስጋት ወላጆች ልጆቻቸውን ትምህርት ቤት አላኩም ብለዋል። በትላናንትናው ዕለት የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከተማይቱ ወደ ሰላማዊ እንቅስቃሴ መመለሷን ገልፆ በቀጣይ ቀናትም ትምህርት ቤቶች ወደ ስራ ይመለሳሉ ሲል ገልጿል።
PHOTO: IBRO(አዳማ ቲክቫህ ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA
ሰሞኑን በተለያዩ ከተሞች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ባሉበት ቦታ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ብሔራዊ የአደጋ ስጋት ኮሚሽን ገለፀ።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፈው ሳምንት ተከስቶ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኞች ለአንድ ወር የሚሆን የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ ተልኳል።
ከምዕራብ አርሲ ዶዶላ ተፈናቅለው በሁለት ቤተክርስቲያናት ለሚገኙ ዜጎች የምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
በዚሁ መሰረት በዶዶላ ለተፈናቀሉ 3 ሺህ 366 ዜጎች እህል፣ አልሚ ምግብ፣ ዘይት፣ ጥራጥሬ፣ ብስኩትና ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ተልከውላቸዋል ነው ያሉት።
https://telegra.ph/ETH-10-29-5
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰሞኑን በተለያዩ ከተሞች በተከሰቱ ግጭቶች ምክንያት ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ ዜጎች ባሉበት ቦታ ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን ብሔራዊ የአደጋ ስጋት ኮሚሽን ገለፀ።
የኮሚሽኑ የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ ዛሬ ለኢዜአ እንደገለጹት ባለፈው ሳምንት ተከስቶ በነበረው ግጭት ለተፈናቀሉ ወገኞች ለአንድ ወር የሚሆን የምግብና የቁሳቁስ ድጋፍ ተልኳል።
ከምዕራብ አርሲ ዶዶላ ተፈናቅለው በሁለት ቤተክርስቲያናት ለሚገኙ ዜጎች የምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ድጋፎች እንዲደርሳቸው ተደርጓል።
በዚሁ መሰረት በዶዶላ ለተፈናቀሉ 3 ሺህ 366 ዜጎች እህል፣ አልሚ ምግብ፣ ዘይት፣ ጥራጥሬ፣ ብስኩትና ሌሎች ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ተልከውላቸዋል ነው ያሉት።
https://telegra.ph/ETH-10-29-5
Via ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መግለጫ! @tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት!
የሀገሪቱን ሰላም ማስጠበቅ የሁሉም ኢትዮያውያን የጋራ ኃላፊነት መሆኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታውቋል። ጠቅላይ ምክር ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳለው የሃይማኖት ተቋማትም ይህን የጋራ ኃላፊነት የመወጣትና በዚህ ረገድ ህዝቡን የመምከር ሀገራዊ ግዴታ አለባቸው ብሏል፡፡ ባለፉት ወራት በቤተ አምልኮዎች እና በመስጅዶች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት ቢፈፀምም ህብረተሰቡን በማረጋጋት ነገሩን በትእግስት ሲያልፍ መቆየቱን ምክር ቤቱ ገልጿል።
More👇
https://telegra.ph/ETH-10-29-9
Via ኢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሀገሪቱን ሰላም ማስጠበቅ የሁሉም ኢትዮያውያን የጋራ ኃላፊነት መሆኑን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታውቋል። ጠቅላይ ምክር ቤቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ እንዳለው የሃይማኖት ተቋማትም ይህን የጋራ ኃላፊነት የመወጣትና በዚህ ረገድ ህዝቡን የመምከር ሀገራዊ ግዴታ አለባቸው ብሏል፡፡ ባለፉት ወራት በቤተ አምልኮዎች እና በመስጅዶች ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት ቢፈፀምም ህብረተሰቡን በማረጋጋት ነገሩን በትእግስት ሲያልፍ መቆየቱን ምክር ቤቱ ገልጿል።
More👇
https://telegra.ph/ETH-10-29-9
Via ኢቢሲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
359 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል!
ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች አጋጥሞ ከነበረው ግጭትና ጥቃት ጋር በተያያዘ 359 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ያለው ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ከፍያለው ተፈራ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇(BBC)
https://telegra.ph/ETH-10-29-7
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ባለፈው ሳምንት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች አጋጥሞ ከነበረው ግጭትና ጥቃት ጋር በተያያዘ 359 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ። በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ያለው ሁኔታ እየተረጋጋ መምጣቱን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ከፍያለው ተፈራ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👇(BBC)
https://telegra.ph/ETH-10-29-7
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ASTU
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ዛሬ ጠዋት ለ4 ቀናት የሚቆይ የደም ልገሳ ፕሮግራም ተጀምሯል። የደም ልገሳ ፕሮግራሙን ያዘጋጁት ክለብ 20/25 ከአዳማ ከተማ ደም ባንክ ጋር በመተባበር ነው። ዛሬ በነበረው የደም ልገሳ ላይ በርካታ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
Via Hiwi(ቲክቫህ አዳማ-ASTU ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (ASTU) ዛሬ ጠዋት ለ4 ቀናት የሚቆይ የደም ልገሳ ፕሮግራም ተጀምሯል። የደም ልገሳ ፕሮግራሙን ያዘጋጁት ክለብ 20/25 ከአዳማ ከተማ ደም ባንክ ጋር በመተባበር ነው። ዛሬ በነበረው የደም ልገሳ ላይ በርካታ ተማሪዎች ተሳትፈዋል።
Via Hiwi(ቲክቫህ አዳማ-ASTU ቤተሰብ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#BreakingNews
የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳድ ሀሪሪ ስልጣናቸውን እንደሚለቁ ገለፁ። በዋትስ አፕ ላይ የተጣለ ታክስን በመቃወም ተጀምሮ በሀገሪቱ አለ የተባለውን የፖለቲካ ሙስና እና የኢኮኖሚ ቀውስን ወደ መቃወም በተቀየረ አመፅ ሀገሪቱ ስትናጥ ቆይታለች። አመፁ ከተቀሰቀሰ ጀምሮም ሊባኖስ ለ13 ቀናት ሙሉ በሙሉ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዋ ተዘግቶ፣ ባንኮች እና ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ተቋርጠውባት ሰንብታለች።
https://telegra.ph/LBN-10-29
ምንጭ፦ አልጀዚራ( ኤፍ ቢ ሲ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የሊባኖስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሳድ ሀሪሪ ስልጣናቸውን እንደሚለቁ ገለፁ። በዋትስ አፕ ላይ የተጣለ ታክስን በመቃወም ተጀምሮ በሀገሪቱ አለ የተባለውን የፖለቲካ ሙስና እና የኢኮኖሚ ቀውስን ወደ መቃወም በተቀየረ አመፅ ሀገሪቱ ስትናጥ ቆይታለች። አመፁ ከተቀሰቀሰ ጀምሮም ሊባኖስ ለ13 ቀናት ሙሉ በሙሉ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴዋ ተዘግቶ፣ ባንኮች እና ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ተቋርጠውባት ሰንብታለች።
https://telegra.ph/LBN-10-29
ምንጭ፦ አልጀዚራ( ኤፍ ቢ ሲ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ETHIOPIA | የገምሹ በየነ የግንባታ ኩባንያ ሰራተኞች በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መርሐቤቴ ወረዳ ከሚገኝ የሥራ ቦታቸው ለቀው መውጣት ጀመሩ።
ሰራተኞቹ ባለፈው እሁድ በኩባንያው ንብረቶች ላይ ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ ከአካባቢው ለቀው እንዳይወጡ በአካባቢው ነዋሪዎች ታግደው እንደነበር ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ተናግረዋል።
ከሰራተኞቹ መካከል አንዱ የሆኑት አቶ እንዳልካቸው በላይ ወደ 300 ገደማ ይሆናሉ የተባሉት ሰራተኞች በመከላከያ ሰራዊት ታጅበው ከመረሐቤቴ መውጣታቸውን ለጀርመን ሬድዮ ጣቢያ አረጋግጠዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰራተኞቹ ባለፈው እሁድ በኩባንያው ንብረቶች ላይ ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ ከአካባቢው ለቀው እንዳይወጡ በአካባቢው ነዋሪዎች ታግደው እንደነበር ለጀርመን ድምፅ ሬድዮ ተናግረዋል።
ከሰራተኞቹ መካከል አንዱ የሆኑት አቶ እንዳልካቸው በላይ ወደ 300 ገደማ ይሆናሉ የተባሉት ሰራተኞች በመከላከያ ሰራዊት ታጅበው ከመረሐቤቴ መውጣታቸውን ለጀርመን ሬድዮ ጣቢያ አረጋግጠዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE
በተለያዩ የምርመራ መዝገቦች በሽብር ትጠረጠራላችሁ በሚል ለወራት በእስር ላይ ሆነው ምርመራ ሲደረግባቸው የቆዩ ሰዎች ዛሬ ከእስር ተፈተዋል፡፡ እስረኞቹ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባላት፣ የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት አመራሮች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ከሰኔ 15 የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በተያያዘ ተጠርጥራችኋል በሚል ታስረው የነበሩ ይገኙበታል፡፡
ከተፈቱት መካከል፦
1ኛ) አንተነህ ስለሺ
2ኛ) ንጉሡ ይልቃል
3ኛ) ዮናስ አሰፋ
4ኛ) ሽገዛ ሙሉጌታ
5ኛ) በዕውቀቱ በላቸው
6ኛ) ኤልያስ ገብሩ
7ኛ) መርከቡ ኃይሌ
8ኛ) ስንታየሁ ቸኮል
9ኛ) ወ/ሮ ደስታ አሰፋ
10ኛ) ምስጋና ጌታቸው
11ኛ) ጌታቸው አምባቸው
12ኛ) ሲያምር ጌቴ
እና ሌሎችም እንደሚገኙበት የታወቀ ሲሆን፣ የአብን ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ በለጠ ካሳ #አልተፈቱም።
Via #ASRATTV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በተለያዩ የምርመራ መዝገቦች በሽብር ትጠረጠራላችሁ በሚል ለወራት በእስር ላይ ሆነው ምርመራ ሲደረግባቸው የቆዩ ሰዎች ዛሬ ከእስር ተፈተዋል፡፡ እስረኞቹ የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ አባላት፣ የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክር ቤት አመራሮች፣ ጋዜጠኞች እና ሌሎች ከሰኔ 15 የመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር በተያያዘ ተጠርጥራችኋል በሚል ታስረው የነበሩ ይገኙበታል፡፡
ከተፈቱት መካከል፦
1ኛ) አንተነህ ስለሺ
2ኛ) ንጉሡ ይልቃል
3ኛ) ዮናስ አሰፋ
4ኛ) ሽገዛ ሙሉጌታ
5ኛ) በዕውቀቱ በላቸው
6ኛ) ኤልያስ ገብሩ
7ኛ) መርከቡ ኃይሌ
8ኛ) ስንታየሁ ቸኮል
9ኛ) ወ/ሮ ደስታ አሰፋ
10ኛ) ምስጋና ጌታቸው
11ኛ) ጌታቸው አምባቸው
12ኛ) ሲያምር ጌቴ
እና ሌሎችም እንደሚገኙበት የታወቀ ሲሆን፣ የአብን ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ እና አቶ በለጠ ካሳ #አልተፈቱም።
Via #ASRATTV
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የብርጋዴር ጄኔራል አሳምነው ጽጌ ባለቤት ወይዘሮ ደስታ አሠፋ በዛሬው ዕለት ጥቅምት 17/2012 ዓ/ም ከእስር ተፈተዋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ክርስቲያን ታደለ ከእስር አልተፈቱም!
የአብን ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም ቀርበው የአስራ አምስት ቀን የክስ መመስረቻ የተጠየቀባቸው ሲሆን በመጪው አርብም ይጠናቀቃል። እስከ አርብ ባለው ጊዜም ውስጥ ክስ ካልተመሰረተ የዋስትና መብታቸውንም ማቅረብ እንደሚችሉ ተነግሯቸዋል። ስለ አፈታታቸው ሁኔታም እስካሁን ባለው እንደማይታወቅና ክስ የሚያስመሰርት ሁኔታ ይኑር አይኑር እንዲሁም ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎች በመጪው ቀናት እንደሚታወቁም ተናግሯል። አቶ ክርስቲያንን ጨምሮ ዘጠኝ አባላት እንዳልተፈቱም ጠበቃ አበረ ለቢቢሲ የገለፁት።
Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአብን ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ክርስቲያን ታደለ ፍርድ ቤት ከዚህ ቀደም ቀርበው የአስራ አምስት ቀን የክስ መመስረቻ የተጠየቀባቸው ሲሆን በመጪው አርብም ይጠናቀቃል። እስከ አርብ ባለው ጊዜም ውስጥ ክስ ካልተመሰረተ የዋስትና መብታቸውንም ማቅረብ እንደሚችሉ ተነግሯቸዋል። ስለ አፈታታቸው ሁኔታም እስካሁን ባለው እንደማይታወቅና ክስ የሚያስመሰርት ሁኔታ ይኑር አይኑር እንዲሁም ሌሎች ዝርዝር ሁኔታዎች በመጪው ቀናት እንደሚታወቁም ተናግሯል። አቶ ክርስቲያንን ጨምሮ ዘጠኝ አባላት እንዳልተፈቱም ጠበቃ አበረ ለቢቢሲ የገለፁት።
Via BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ምስራቅ_ዕዝ
የህብረተሰቡን #ሰላምና #ደህንነት የማስጠበቅ ስራን እንደሚያጠናክር የምስራቅ ዕዝ አስታወቀ። የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ስራን በተጠናከረ መልኩ እንደሚያስቀጥል በሀገር መከላከያ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዘውዱ በላይ አስታወቁ።
ዋና አዛዡ ዛሬ በጅግጅጋ ገርባሳ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም የመካከለኛ አመራሮች ስልጠና በተጀመረበት ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ሰላም የሚያውኩ አካላትን በመከላከሉ ረገድ ሰራዊቱ ከነዋሪው ጋር በመሆን የሚጠበቅበትን ግዳጅ ተወጥቷል።
“በአሁኑ ወቅትም በቀጠናው የተለያዩ የጸብ አጫሪነትና የጸረ ሰላም ተግባር ሲፈጠሩ ሰራዊቱ ከክልል የጸጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሰላምን የማስከበር ስራ እያከናወነ ይገኛል” ብለዋል። በዚህም የቀጠናው የሰላም ሁኔታ ከዓመት ዓመት መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
በቅርቡ በቀጠናው አንዳንድ ከተሞች በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ለማሰማት ዜጎች ወደ አደባባይ የወጡበትን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን አጀንዳ ለማራመድ የሞከሩ ጥቂት ግለሰቦች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ይህም ህብረተሰቡ በብሔርና በሃይማኖት ግጭት ውስጥ እንዲገባ ለማድረግ እንደነበረ ጠቅሰዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህብረተሰቡን #ሰላምና #ደህንነት የማስጠበቅ ስራን እንደሚያጠናክር የምስራቅ ዕዝ አስታወቀ። የህብረተሰቡን ሰላምና ደህንነት የማስጠበቅ ስራን በተጠናከረ መልኩ እንደሚያስቀጥል በሀገር መከላከያ የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ዘውዱ በላይ አስታወቁ።
ዋና አዛዡ ዛሬ በጅግጅጋ ገርባሳ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ተቋም የመካከለኛ አመራሮች ስልጠና በተጀመረበት ወቅት እንደገለጹት ባለፉት ዓመታት የህብረተሰቡን ሰላም የሚያውኩ አካላትን በመከላከሉ ረገድ ሰራዊቱ ከነዋሪው ጋር በመሆን የሚጠበቅበትን ግዳጅ ተወጥቷል።
“በአሁኑ ወቅትም በቀጠናው የተለያዩ የጸብ አጫሪነትና የጸረ ሰላም ተግባር ሲፈጠሩ ሰራዊቱ ከክልል የጸጥታ አካላትና ከህብረተሰቡ ጋር በመሆን ሰላምን የማስከበር ስራ እያከናወነ ይገኛል” ብለዋል። በዚህም የቀጠናው የሰላም ሁኔታ ከዓመት ዓመት መሻሻል እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
በቅርቡ በቀጠናው አንዳንድ ከተሞች በሰላማዊ መንገድ ድምጻቸውን ለማሰማት ዜጎች ወደ አደባባይ የወጡበትን አጋጣሚ በመጠቀም የራሳቸውን አጀንዳ ለማራመድ የሞከሩ ጥቂት ግለሰቦች እንደነበሩ አስታውሰዋል። ይህም ህብረተሰቡ በብሔርና በሃይማኖት ግጭት ውስጥ እንዲገባ ለማድረግ እንደነበረ ጠቅሰዋል።
ምንጭ፡- ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia