This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ወቅታዊው የሀገራች ሁኔታ ለፖሊስም ፈተና ሆኖበታል🤔
Ethiopian Federal Police Commission
መደበኛ ባልሆነ መንገድ፣ በተለያዩ አካባቢዎች በራሳቸው የፖሊስን ስራ በመከወን የሚንቀሳቀሱ ወጣቶችን ከዚህ በኋላ እንደማይታገስ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ምንጭ፦ ሸገር FM 102.1 /ትዕግስት ዘሪሁን/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Ethiopian Federal Police Commission
መደበኛ ባልሆነ መንገድ፣ በተለያዩ አካባቢዎች በራሳቸው የፖሊስን ስራ በመከወን የሚንቀሳቀሱ ወጣቶችን ከዚህ በኋላ እንደማይታገስ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
ምንጭ፦ ሸገር FM 102.1 /ትዕግስት ዘሪሁን/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UPDATE
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሶስትዮሽ ውይይት ውጪ ሌሎች ምክረ ሀሳቦችን እንደማትቀበል የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዛሬ ገልፀዋል።
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዛሬው ዕለት ለካቢኔ አባላት እና ለባለድርሻ አካላት የግድቡን አሁናዊ ገፅታ እና በግብፅ ወቅታዊ አቋም ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸውም የግድቡን አሁናዊሁኔታ እና የወደፊት እቅዶች ላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፥ በዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በትኩረትና በተገቢው ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል እየተደረገ ባለው ውይይት ዙሪያም ሚኒስትሩ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፥ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የቀጣናውን እና የተፋሰሱን ሀገራት ግንኙነት የሚያጠናከር መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሆኖም ግን ግብጽ ከሶስትዮሹ ውይይት ውጪ በሱዳን ካርቱም በተደረገው ውይይት ላይ ያቀረበችው ምክረ ሃሳብ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጥስ መሆኑ መሆኑን አስታውቀዋል። ግብጽ ባቀረበችው ምክረ ሀሳብ ላይም በየዓመቱ 40 ቢሊየን ሜትር ኪዮብ ውሃ ይለቀቅልኝ ማለቷ እና የአስዋን ግድብ ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ 165 ሜትር ሲደርስ ኢትዮጵያ ውሃ መልቀቅ አለባት፤ እንዲሁም ሶስተኛ ወገን በአደራዳሪነት ይግባ የሚል አቋም ማቅረቧን አንስተዋል።
ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት፥ #ግብፅ ያቀረበችው መክረ ሃሳብ ኢትዮጵያ በውሃው ላይ ያላትን መብት የሚጥስ እና ብሄራዊ ጥቅሟን የሚጎዳ በመሆኑ ኢትዮጵያ መቼም ቢሆን የምትቀበለው አይሆንም ብለዋል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ኢትዮጵያ ከሶስትዮሽ ውይይት ውጪ ሌሎች ምክረ ሀሳቦችን እንደማትቀበል የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ዛሬ ገልፀዋል።
የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ በዛሬው ዕለት ለካቢኔ አባላት እና ለባለድርሻ አካላት የግድቡን አሁናዊ ገፅታ እና በግብፅ ወቅታዊ አቋም ላይ ማብራርያ ሰጥተዋል። ሚኒስትሩ በማብራሪያቸውም የግድቡን አሁናዊሁኔታ እና የወደፊት እቅዶች ላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፥ በዚህም የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ በትኩረትና በተገቢው ፍጥነት እየተከናወነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ በኢትዮጵያ፣ ሱዳን እና ግብፅ መካከል እየተደረገ ባለው ውይይት ዙሪያም ሚኒስትሩ ገለጻ አድርገዋል። በዚህም ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፥ የታላቁ የህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የቀጣናውን እና የተፋሰሱን ሀገራት ግንኙነት የሚያጠናከር መሆኑን ጠቅሰዋል።
ሆኖም ግን ግብጽ ከሶስትዮሹ ውይይት ውጪ በሱዳን ካርቱም በተደረገው ውይይት ላይ ያቀረበችው ምክረ ሃሳብ የኢትዮጵያን ሉአላዊነት የሚጥስ መሆኑ መሆኑን አስታውቀዋል። ግብጽ ባቀረበችው ምክረ ሀሳብ ላይም በየዓመቱ 40 ቢሊየን ሜትር ኪዮብ ውሃ ይለቀቅልኝ ማለቷ እና የአስዋን ግድብ ከፍታ ከባህር ጠለል በላይ 165 ሜትር ሲደርስ ኢትዮጵያ ውሃ መልቀቅ አለባት፤ እንዲሁም ሶስተኛ ወገን በአደራዳሪነት ይግባ የሚል አቋም ማቅረቧን አንስተዋል።
ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ እንደተናገሩት፥ #ግብፅ ያቀረበችው መክረ ሃሳብ ኢትዮጵያ በውሃው ላይ ያላትን መብት የሚጥስ እና ብሄራዊ ጥቅሟን የሚጎዳ በመሆኑ ኢትዮጵያ መቼም ቢሆን የምትቀበለው አይሆንም ብለዋል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ethio telecom | ኢትዮ ቴሌኮም የ2012 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ሩብ ዓመት የዕቅዱን 98% በማሳካት 10.1 ቢሊዮን የኢትዮጵያ ብር ማግኘቱን ግለጿል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#GONDAR
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡለትን ተማሪዎች ዛሬ ጥቅምት 06/ 2012 ዓ.ም እየተቀበለ ይገኛል፡፡ አቀባበሉ ነገም የሚቀጥል ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ለልጆቼ ምቾትና ደህንነት ሲባል በተደራጀ መልኩ አቀባበሉን እያከናወንኩ እገኛለሁ ብሏል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ዳይሬክሬክተሮች፣ ዲኖች፣ ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የተማሪ ህብረት የከተማ አስተዳደሩና ነዋሪዎች እንዲሁም የፓሊስና ፀጥታ አካላት በተናበበ ሁኔታ በእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ተማሪዎችን በማስተናገድ ላይ እንደሆኑም በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው "እናንተን ማገልገል መታደል ነውና "ሃገራችን ለማገልገል ቆርጠን ተነስተናል!" ዓመቱ እውቀት ዘርተን ጥበብ የምናጭድበት፣ መልካም አመለካከት አብቅለን የምናሳድግበት ይሁን! ሲልም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
GONDAR UNIVERSITY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደቡለትን ተማሪዎች ዛሬ ጥቅምት 06/ 2012 ዓ.ም እየተቀበለ ይገኛል፡፡ አቀባበሉ ነገም የሚቀጥል ሲሆን ዩኒቨርሲቲው ለልጆቼ ምቾትና ደህንነት ሲባል በተደራጀ መልኩ አቀባበሉን እያከናወንኩ እገኛለሁ ብሏል። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት፣ ምክትል ፕሬዚዳንቶች፣ ዳይሬክሬክተሮች፣ ዲኖች፣ ትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ የተማሪ ህብረት የከተማ አስተዳደሩና ነዋሪዎች እንዲሁም የፓሊስና ፀጥታ አካላት በተናበበ ሁኔታ በእንኳን ደህና መጣችሁ መርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው ተማሪዎችን በማስተናገድ ላይ እንደሆኑም በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አሳውቋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው "እናንተን ማገልገል መታደል ነውና "ሃገራችን ለማገልገል ቆርጠን ተነስተናል!" ዓመቱ እውቀት ዘርተን ጥበብ የምናጭድበት፣ መልካም አመለካከት አብቅለን የምናሳድግበት ይሁን! ሲልም መልካም ምኞቱን ገልጿል።
GONDAR UNIVERSITY
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የዓለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የእውቅና መድረክ የፊታችን እሁድ በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል፡፡
በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች፣ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ የሚከናወነው ይህ የደስታ መግለጫ ዝግጅት እሁድ ጥቅምት 9፣2012 ዓ.ም ከቀኑ 11 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት እንደሚዘልቅ የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ አስታውቋል።
Via #WaltaTV
@tsehabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ የዓለም የኖቤል የሰላም ተሸላሚ መሆናቸውን በማስመልከት የሰላም ሚኒስቴር ሀገር አቀፍ የእውቅና መድረክ የፊታችን እሁድ በሚሊኒየም አዳራሽ ያካሂዳል፡፡
በመድረኩ ላይ ከፍተኛ የፌደራልና የክልል ባለስልጣናት፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ዲፕሎማቶች፣ የሃይማኖት አባቶችና መሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችን ጨምሮ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ይታደማሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
በሚሊኒየም አዳራሽ የሚከናወነው ይህ የደስታ መግለጫ ዝግጅት እሁድ ጥቅምት 9፣2012 ዓ.ም ከቀኑ 11 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 3 ሰዓት እንደሚዘልቅ የሰላም ሚኒስቴር መግለጫ አስታውቋል።
Via #WaltaTV
@tsehabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ባለፈው ዓመት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት ላይ ያጋጠመውን ችግር ለማጣራት የተቋቋመው ኮሚቴ መረጃ አሰባስቦ ማጠናቀቁን ለሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ተናግሯል። የተሰበሰበውን መረጃ አጠናቅሮ ሪፖርት ማዘጋጀት የቀረው መሆኑንም ገልጿል። ኮሚቴው ጉዳዩን በገለልተኛነት እንዲያጣራ በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተዋቀረ ሲሆን ሪፖርቱንም ለእርሳቸው የቀርባል። ትምህርት ሚኒስቴር፣ ሀገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ እንዲሁም ፈተናውን የሚያዘጋጀው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በማጣራት ሂደቱ ላይ መረጃ የተሰበሰበባቸው ተቋማት መሆናቸውን የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊና የአጣሪ ኮሚቴው ሰብሳቢ ዶ/ር ጌታሁን ጋረደው ተናግረዋል።
ዶ/ር ጌታሁን ጋረደው...
"አጠቃላይ ከአሰራር ከአደረጃጀት ጀምሮ ያለው ሁኔታ ምን ይመስላል ቀድሞ የተቋማቱን ግንኙነት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ የፈተናዎች ኤጀንሲና ፈተናውን የሚያወጣው አካል ግንኙነቶችን check ማድረግ፤ ከዚህ በፊት የነበረው አሰራር ማጣራት ነበር እሱ ተጠናቋል። ከዛ በኃላ በዚህ ዓመት ፈተና ደግሞ የተከሰቱ ችግሮች ነበሩ ችግሮቹ ምንድናቸው የሚለውን የየተቋማቱን check ማድረግ ነበር። የትምህርት ሚኒስቴርን፣ የፈተናዎች ኤጀንሲን ሌሎችም በዚህ ስራ የተሳተፉ አካላትን ማናገር ተችሏል። መረጃም ተሰብስቧል። አሁን ላይ ሪፖርት አዘጋጅቶ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ማቅረብ ነው ሚቀረው።"
ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም/ጋዜጠኛ በየነ ወልዴ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር ጌታሁን ጋረደው...
"አጠቃላይ ከአሰራር ከአደረጃጀት ጀምሮ ያለው ሁኔታ ምን ይመስላል ቀድሞ የተቋማቱን ግንኙነት የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ የፈተናዎች ኤጀንሲና ፈተናውን የሚያወጣው አካል ግንኙነቶችን check ማድረግ፤ ከዚህ በፊት የነበረው አሰራር ማጣራት ነበር እሱ ተጠናቋል። ከዛ በኃላ በዚህ ዓመት ፈተና ደግሞ የተከሰቱ ችግሮች ነበሩ ችግሮቹ ምንድናቸው የሚለውን የየተቋማቱን check ማድረግ ነበር። የትምህርት ሚኒስቴርን፣ የፈተናዎች ኤጀንሲን ሌሎችም በዚህ ስራ የተሳተፉ አካላትን ማናገር ተችሏል። መረጃም ተሰብስቧል። አሁን ላይ ሪፖርት አዘጋጅቶ ለሚመለከተው አካል ሪፖርት ማቅረብ ነው ሚቀረው።"
ምንጭ፦ ሸገር ኤፍ ኤም/ጋዜጠኛ በየነ ወልዴ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮ-ቴሌኮም አንዳንድ የመንግሥት አካላት በስሜ የሚሰጡትን መግለጫ ያቁሙ ሲል አሳስቧል፡፡ ሃላፊነታቸው የማይፈቅድላቸው ተቋማት ኩባንያውን ወደግል ባለሃብቶች ስለማዛወር መግለጫ ይሰጣሉ፡፡ ይህን ማሳሰቢያ ዛሬ በሰጡት ጋዜጠዊ መግለጫ የተነጋሩት ሥራ አስፈጻሚዋ ፍሬሕይወት ታምሩ ናቸው- ብሏል የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ዘገባ፡፡
Via Ethio FM/wazema/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
Via Ethio FM/wazema/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በኢትዮጵያ ንግድና ዘርፍ ማህበራትና በቻይናው CCPIT አዘጋጅነት በኢትዮጵያ ለሁለተኛ ጊዜ ለሚዘጋጀው ቻይና-አፍሪካ ኤክስፓ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ተሰጥቷል፡፡
የአፍሪካ-ቻይና አንድ አካል የሆነው ቻይና-ኢትዮ ኤክስፖ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 14 ድረስ በአዲስ አበባ በኤግዚቢሽን ማዕከል እንደሚዘጋጅ ዛሬ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተጠቁሟል፡፡
በዚህ ኤክስፓ 40 የሚሆኑ በግብርና፣ በኢነርጂ፣ በICT፣ በቴክኖሎጂ፣ በኮንስትራክሽንና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ የቻይና ትላልቅ ኩባንያዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገር ውስጥ ከሚገኙ የንግዱ ማህበረሰቦች ጋር የገቢያና የሽያጭ ትስስርን ለማጎልበት አይነተኛ ሚና ይጫወታል ተብሎለታል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው እንደተጠቆመው አራት ቀን ከሚቆየው ከዚህ ኤክስፓ ጎን ለጎን በመክፈቻው ቀን "China Africa Cooperation Forum" በሂልተን ሆቴል ይካሄዳል ተብሏል፡፡ ኤክስፖው ጥቅምት 11 ከአራት ሰዓት ጀምሮ በድምቀት የሚከፈት ይሆናል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአፍሪካ-ቻይና አንድ አካል የሆነው ቻይና-ኢትዮ ኤክስፖ ዘንድሮ ለሁለተኛ ጊዜ ከጥቅምት 11 እስከ ጥቅምት 14 ድረስ በአዲስ አበባ በኤግዚቢሽን ማዕከል እንደሚዘጋጅ ዛሬ በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተጠቁሟል፡፡
በዚህ ኤክስፓ 40 የሚሆኑ በግብርና፣ በኢነርጂ፣ በICT፣ በቴክኖሎጂ፣ በኮንስትራክሽንና በሌሎች ዘርፎች የተሰማሩ የቻይና ትላልቅ ኩባንያዎች የሚሳተፉ ሲሆን ሀገር ውስጥ ከሚገኙ የንግዱ ማህበረሰቦች ጋር የገቢያና የሽያጭ ትስስርን ለማጎልበት አይነተኛ ሚና ይጫወታል ተብሎለታል፡፡
በጋዜጣዊ መግለጫው እንደተጠቆመው አራት ቀን ከሚቆየው ከዚህ ኤክስፓ ጎን ለጎን በመክፈቻው ቀን "China Africa Cooperation Forum" በሂልተን ሆቴል ይካሄዳል ተብሏል፡፡ ኤክስፖው ጥቅምት 11 ከአራት ሰዓት ጀምሮ በድምቀት የሚከፈት ይሆናል፡፡
#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢ/ር ታከለ ከስልጣናቸው አይነሱም...
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ታከለ ዑማ ከሥልጣናቸው እንደማይነሱ አንድ ለኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) ቅርበት ያላቸው ግለሰብ ተናገሩ። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማን በመምራት ላይ የሚገኙት አቶ ታከለ ከሥልጣናቸው ይነሳሉ የሚሉ ዘገባዎች ባለፉት ጥቂት ቀናት በሰፊው ተሰራጭተው ነበር። የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ከትናንትናው ዕለት ጀምሮ በአዲስ አበባ ውይይት በማድረግ ላይ ነው። ፓርቲው ዛሬ ምሽት ስብሰባውን ሲያጠናቅቅ የአቶ ታከለ ዑማን ጨምሮ በተወያየባቸው ጉዳዮች ላይ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ፓርቲው በሚሰጠው መግለጫ ጠንከር ያሉ ጉዳዮችን እንደሚነሳ ስማቸው እንዳይገለፅ የፈለጉ ሰው ለጀርመን ሬድዮ ተናግረዋል። ኢ/ር ታከለ ዑማ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ሆነው የተሾሙት ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም. ነበር። ዋና ከተማዋን መምራት ከመጀመራቸው በፊት የኦሮሚያ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሠርተዋል።
Via DW/የጀርመን ድምፅ ሬድዮ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አቶ ታከለ ዑማ ከሥልጣናቸው እንደማይነሱ አንድ ለኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) ቅርበት ያላቸው ግለሰብ ተናገሩ። በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማን በመምራት ላይ የሚገኙት አቶ ታከለ ከሥልጣናቸው ይነሳሉ የሚሉ ዘገባዎች ባለፉት ጥቂት ቀናት በሰፊው ተሰራጭተው ነበር። የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ (ኦዲፒ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ከትናንትናው ዕለት ጀምሮ በአዲስ አበባ ውይይት በማድረግ ላይ ነው። ፓርቲው ዛሬ ምሽት ስብሰባውን ሲያጠናቅቅ የአቶ ታከለ ዑማን ጨምሮ በተወያየባቸው ጉዳዮች ላይ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ፓርቲው በሚሰጠው መግለጫ ጠንከር ያሉ ጉዳዮችን እንደሚነሳ ስማቸው እንዳይገለፅ የፈለጉ ሰው ለጀርመን ሬድዮ ተናግረዋል። ኢ/ር ታከለ ዑማ የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ሆነው የተሾሙት ሐምሌ 10 ቀን 2010 ዓ.ም. ነበር። ዋና ከተማዋን መምራት ከመጀመራቸው በፊት የኦሮሚያ ትራንስፖርት ቢሮ ኃላፊ ሆነው ሠርተዋል።
Via DW/የጀርመን ድምፅ ሬድዮ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የODP ስብሰባ ተጠናቋል!
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ በዛሬው እለት ስብሰባውን አጠናቀቀ። ማእከላዊ ኮሚቴው ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማጠናቀቁ ተገልጿል።
ማእከላዊ ኮሚቴው በስብሰባው የፓርቲውን እና የክልሉን መንግስት የስራ አፈፃፀም የገመገመ ሲሆን፥ በወቅታዊ ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይም ተወያይቷል። የፓርቲው የውስጥ አንድነት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ሪፎርምንም እንዲሁም እንደ ሀገር እና እንደ ክልል የተጀመሩ ለውጦች ዙሪያም ምክክር አድርጓል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኦሮሞ ዴሞክራቲክ ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ በዛሬው እለት ስብሰባውን አጠናቀቀ። ማእከላዊ ኮሚቴው ለሁለት ቀናት በአዲስ አበባ ከተማ ሲያካሂድ የነበረውን ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ማጠናቀቁ ተገልጿል።
ማእከላዊ ኮሚቴው በስብሰባው የፓርቲውን እና የክልሉን መንግስት የስራ አፈፃፀም የገመገመ ሲሆን፥ በወቅታዊ ሀገራዊ እና ክልላዊ ጉዳዮች ላይም ተወያይቷል። የፓርቲው የውስጥ አንድነት እና የፖለቲካ ፓርቲዎች ሪፎርምንም እንዲሁም እንደ ሀገር እና እንደ ክልል የተጀመሩ ለውጦች ዙሪያም ምክክር አድርጓል።
Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በትግራይ ክልል የሰልፍ ክልከላ...
👉በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ የሚደርስን ጥቃት ለመቃወም የተጠራ ሰልፍ ፈቃድ መከልከሉን አዘጋጆቹ ገለፁ።
👉ክልሉ ሕጋዊ ማኅተም ያለው ድርጅት ኃላፊነት እንዲወስድ ከመጠየቁ ውጪ "የተደረገ ክልከላ የለም" ብሏል።
በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ለመቃወም በመጭው እሁድ በመቐለ ከተማ ለማካሄድ አቅደውት የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ የከተማው አስተዳድር ክልከላ እንዳደረገባቸው አዘጋጆቹ ተናገሩ። "ይህም መንግሥት የሴቶች ጥቃትን ለመከላከል ዝግጁ እንዳልሆነ ማሳያ ነው" ብለዋል። የከተማው አስተዳደር በበኩሉ "ለሰላማዊ ሰልፉ ኃላፊነት የሚወስድ ተቋም ሊኖር ይገባል ነው ያልነው እንጂ አልከለከልንም"ብሏል።
Via VOA Amharic
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👉በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ የሚደርስን ጥቃት ለመቃወም የተጠራ ሰልፍ ፈቃድ መከልከሉን አዘጋጆቹ ገለፁ።
👉ክልሉ ሕጋዊ ማኅተም ያለው ድርጅት ኃላፊነት እንዲወስድ ከመጠየቁ ውጪ "የተደረገ ክልከላ የለም" ብሏል።
በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ የሚደርሰው ጥቃት ለመቃወም በመጭው እሁድ በመቐለ ከተማ ለማካሄድ አቅደውት የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ የከተማው አስተዳድር ክልከላ እንዳደረገባቸው አዘጋጆቹ ተናገሩ። "ይህም መንግሥት የሴቶች ጥቃትን ለመከላከል ዝግጁ እንዳልሆነ ማሳያ ነው" ብለዋል። የከተማው አስተዳደር በበኩሉ "ለሰላማዊ ሰልፉ ኃላፊነት የሚወስድ ተቋም ሊኖር ይገባል ነው ያልነው እንጂ አልከለከልንም"ብሏል።
Via VOA Amharic
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ በዓለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት ዋና ፀሃፊ ፔቴሪ ታላስ የተመራ የልኡካን ቡድን በብሄራዊ ቤተ መንግስት ተቀብለው አነጋግረዋል፡፡ ዋና ፀሃፊው የዓለም አቀፍ የሚቲዎሮሎጂ ድርጅት የአፍሪካ ፅህፈት ቤት በአዲስ አበባ መከፈቱን በማስመልከት ለፕሬዝዳንት ሣህለ ወርቅ ገለጻ አድርገዋል፡፡
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትግራይ ክልል አዲስ ገቢ የዩኒቨርሲቲ ተማሪችን አማራ ክልል ወደሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች አልክም አለ!
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ገ/መስቀል ካሕሳይ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፡ "ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ወደ ሚሰነዘሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች እና ኃላፊነት ወደማይወስድ ክልል አዲስ ተማሪዎችን ላለመላክ የክልሉ አቋም ነው" ብለዋል።
"አማራ ክልል የተመደቡት 600 ተማሪዎች እንደማይሄዱ ለሚመለከተው የፌደራል መንግሥት አሳውቀናል። ይህ የክልሉ አቋም ነው" ሲሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተናግረዋል።
ዘንድሮ በትግራይ ክልል የዩኒቨሲቲ መግብያ ፈተና ወስደው ማለፍ የቻሉ የተማሪዎች ቁጥር ከ9000 በላይ መሆኑን የጠቀሱ ኃላፊው፤ ወደ አማራ ክልል ተመድበው የነበሩ ተማሪዎች ከ2000 በላይ እንደነበረ እና ከሚመለከታቸው የፌደራል መንግስት አካላት ጋር በተደረገው ውይይት ወደ 600 ዝቅ እንዲል መደረጉን ተናግረዋል። "ከአንድ ወር ተኩል በላይ የክልሉ መንግሥት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሲወያይ ቆይቷል።
የተቀሩ 600 ተማሪዎችን ሌላ ቦታ እንዲመደቡ ይሰራል። ይህ የማይሆን ከሆነ ግን የትግራይ ክልል ሌላ አማራጭ ይፈልጋል እንጂ ተማሪዎቹን ወደዛ አይልክም" ብለዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👉https://telegra.ph/eth-10-17-3
ምንጭ፦ ቢቢሲ አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ገ/መስቀል ካሕሳይ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፡ "ማንነትን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ወደ ሚሰነዘሩባቸው ዩኒቨርሲቲዎች እና ኃላፊነት ወደማይወስድ ክልል አዲስ ተማሪዎችን ላለመላክ የክልሉ አቋም ነው" ብለዋል።
"አማራ ክልል የተመደቡት 600 ተማሪዎች እንደማይሄዱ ለሚመለከተው የፌደራል መንግሥት አሳውቀናል። ይህ የክልሉ አቋም ነው" ሲሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ተናግረዋል።
ዘንድሮ በትግራይ ክልል የዩኒቨሲቲ መግብያ ፈተና ወስደው ማለፍ የቻሉ የተማሪዎች ቁጥር ከ9000 በላይ መሆኑን የጠቀሱ ኃላፊው፤ ወደ አማራ ክልል ተመድበው የነበሩ ተማሪዎች ከ2000 በላይ እንደነበረ እና ከሚመለከታቸው የፌደራል መንግስት አካላት ጋር በተደረገው ውይይት ወደ 600 ዝቅ እንዲል መደረጉን ተናግረዋል። "ከአንድ ወር ተኩል በላይ የክልሉ መንግሥት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ሲወያይ ቆይቷል።
የተቀሩ 600 ተማሪዎችን ሌላ ቦታ እንዲመደቡ ይሰራል። ይህ የማይሆን ከሆነ ግን የትግራይ ክልል ሌላ አማራጭ ይፈልጋል እንጂ ተማሪዎቹን ወደዛ አይልክም" ብለዋል።
ተጨማሪ ያንብቡ👉https://telegra.ph/eth-10-17-3
ምንጭ፦ ቢቢሲ አማርኛ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ኢንጂነር ታከለ ኡማ አሁንም በስራ ላይ ይገኛሉ። ኢንጂነር ር ታከለ ከኃላፊነታቸው ተነስተዋል ተብሎ የወጣው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ለመግለጽ እንፈልጋለን።" Mayor Office Of AA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከሰሞኑ ስለክቡር ከንቲባው የሚሰራጨው መረጃ ሁለት አይነት ነበር፦ አንደኛው ክቡር ምክትል ከንቲባ ኢ/ር ታከለ ከስልጣን ተነስተዋል የሚል ነው፤ ይህ ፍፁም ስህተት የሆነ መረጃ ነው። ኢ/ር ታከለ አሁም ስራ ላይ ናቸው። ይህንንም ከTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት እና ከቅርብ ሰዎቻቸው አረጋግጠናል።
ሁለተኛው እና እስካሁን ግልፅ ምላሽ ያላገኘው፦“ምክትል ከንቲባው ከኃላፊነታቸው ይነሳሉ” የሚለው መረጃ ነው። ከደቂቃዎች በፊት ከንቲባ ጽ/ቤት ያወጣው መግለጫ ምክትል ከንቲባው አሁን በሥራ ላይ መሆናቸውን እንጂ በቦታው ላይ ስለመቀጠላቸው በግልጽ ያለው ነገር የለም።
ሁሉንም በቀጣይ ቀናት የምናውቀው ይሆናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሁለተኛው እና እስካሁን ግልፅ ምላሽ ያላገኘው፦“ምክትል ከንቲባው ከኃላፊነታቸው ይነሳሉ” የሚለው መረጃ ነው። ከደቂቃዎች በፊት ከንቲባ ጽ/ቤት ያወጣው መግለጫ ምክትል ከንቲባው አሁን በሥራ ላይ መሆናቸውን እንጂ በቦታው ላይ ስለመቀጠላቸው በግልጽ ያለው ነገር የለም።
ሁሉንም በቀጣይ ቀናት የምናውቀው ይሆናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
Hong Kong
በሆንግ ኮንግ ከተማ የምክር ቤት አዳራሽ ውስጥ ዛሬም ለሁለተኛው ቀን ትርምስ ሰፍኗል። የዲሞክራሲ ደጋፊ ተቃዋሚዋቾ ዛሬም የከተማይቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሬ ላምን በጩኸት መረበሻቸው ተዘግቧል። ትናንት የተቃዋሚዎቹ ጩኸት ላም ንግግር እስከጀመሩበት ጊዜ ድረስ በመቀጠሉ ለአጭር ጊዜ ከምክር ቤቱ ለመውጣት ተገደው ነበር። ወደ ምክር ቤቱ ተመልሰው ማንበቡን ለመቀጠል ቢሞክሩም ተቃውሞው በመቀጠሉ የምክር ቤቱ ካውንስል ፕረዚዳንት አንድሪው ልዩንግ ስብሰባውን በተኑት። ኬሪ ላም በመጨረሻ ንግግራቸውን በቴሌቪዥን አሰሙ።
Via VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሆንግ ኮንግ ከተማ የምክር ቤት አዳራሽ ውስጥ ዛሬም ለሁለተኛው ቀን ትርምስ ሰፍኗል። የዲሞክራሲ ደጋፊ ተቃዋሚዋቾ ዛሬም የከተማይቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ከሬ ላምን በጩኸት መረበሻቸው ተዘግቧል። ትናንት የተቃዋሚዎቹ ጩኸት ላም ንግግር እስከጀመሩበት ጊዜ ድረስ በመቀጠሉ ለአጭር ጊዜ ከምክር ቤቱ ለመውጣት ተገደው ነበር። ወደ ምክር ቤቱ ተመልሰው ማንበቡን ለመቀጠል ቢሞክሩም ተቃውሞው በመቀጠሉ የምክር ቤቱ ካውንስል ፕረዚዳንት አንድሪው ልዩንግ ስብሰባውን በተኑት። ኬሪ ላም በመጨረሻ ንግግራቸውን በቴሌቪዥን አሰሙ።
Via VOA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
🔖እናስተዋዉቅዎ!
ያሻዎትን ፈልገው የማያጡበት #ÇÁĻŽÂĎÒ ÇOLLÊCTÌOŅ አዳዲስ ፣ ጥራት እና አስተማማኝ ዋስትና ያላቸውን 📱ስልኮች እንደየ ምርጫቹ ሁሉም አይነት ፣ 💻laptops ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንዲሁም የዘመኑን fashion የጠበቁ ልዩ ልዩ ጫማዎችን ከ በቂ ቁጥር እና style ጋር ከ 1400 - 1800 ብር ድረስ ይዘንልዎ መተናል ከ 1 በላይ ሲገዙ አስተያየት እናረጋለን። እንዲሁም ያገለገሉ ላፕቶፖችን እንገዛለን እንሸጣለን።አቅርቦታችንን ለማየት join our channel ለበለጠ መረጃ ይደዉሉ።
🏢 አድራሻ : ቦሌ በድጋሚ እንኳን አደረሳቹ!!!
☎️0919870785☎️
☎️0930628541☎️
https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEMAkUfIXbwkbFPC3w
☀️መልካም ቀን ይሁንላችሁ! #ETHIOPIA☀️
ያሻዎትን ፈልገው የማያጡበት #ÇÁĻŽÂĎÒ ÇOLLÊCTÌOŅ አዳዲስ ፣ ጥራት እና አስተማማኝ ዋስትና ያላቸውን 📱ስልኮች እንደየ ምርጫቹ ሁሉም አይነት ፣ 💻laptops ኪስ በማይጎዳ ዋጋ እንዲሁም የዘመኑን fashion የጠበቁ ልዩ ልዩ ጫማዎችን ከ በቂ ቁጥር እና style ጋር ከ 1400 - 1800 ብር ድረስ ይዘንልዎ መተናል ከ 1 በላይ ሲገዙ አስተያየት እናረጋለን። እንዲሁም ያገለገሉ ላፕቶፖችን እንገዛለን እንሸጣለን።አቅርቦታችንን ለማየት join our channel ለበለጠ መረጃ ይደዉሉ።
🏢 አድራሻ : ቦሌ በድጋሚ እንኳን አደረሳቹ!!!
☎️0919870785☎️
☎️0930628541☎️
https://t.iss.one/joinchat/AAAAAEMAkUfIXbwkbFPC3w
☀️መልካም ቀን ይሁንላችሁ! #ETHIOPIA☀️
9ኛው ለዛ ሽልማት አሸናፊዎች...
የአመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ ይህ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በአድማጭ ተመልካች በተሰበሰበ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት ጃንቦ ጆቴ "በልባ" በተሰኝ ነጠላ ዜማ ማሸነፍ ችሏል።
የአመቱ ምራጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራም ተዋናይ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በተመልካች በተሰበሰብ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህ መሰረት አበበ ባልቻ(አስናቀ) ከዘመን ድራማ አሸናፊ መሆን ችሏል።
የአመቱ ምርጥ አዲስ ድምፃዊ ዘርፍ 40% በዳኞች 60% ከአድማጭ ተመልካች በተሰበሰብ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህ ዘርፍ ድምፃዊት ቸሊና ማሸነፍ ችላለች።
የአመቱ ምርጥ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ተዋናይት ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ከተመልካች ድምፅ የተሰበሰብ ሲሆን በዚህ መሰረት አርቲስት ሀና ዮሃንስ ከዘመን ድራማ ማሸነፍ ችላለች።
የአመቱ ምርጥ የሙዚቃ ቪዲዮ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ከተመልካች በተሰበሰበ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህ መሰረት ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ "ከእሁድ እስከ እሁድ" በተሰኝው ቪዲዮ ክሊፕ ማሸነፍ ችሏል።
የአመቱ ምርጥ ዘፈን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በዳኞች ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት በሀይሉ ታፈሰ (ዚጊ ዛጋ) "ሰርካለሜ" በተሰኝው ዘፈን ማሸነፍ ችሏል።
የአመቱ ምርጥ ተዋናይት ዘርፍ 60% የዳኞች ድምፅ 40% በተመልካች ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት የምስራች ግርማ በቁራኛዬ ፊልም ማሸነፍ ችላለች።
የአመቱ ምርጥ ተዋናይ ዘርፍ 60% የዳኞች ድምፅ 40% በተመልካች ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት ዘሪሁን ሙላት በቁራኛዬ ፊልም ማሸነፍ ችሏል።
ተጨማሪ👇
https://telegra.ph/ETH-10-18
Via ዳሰሳ አዲስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአመቱ ምርጥ ነጠላ ዜማ ይህ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በአድማጭ ተመልካች በተሰበሰበ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት ጃንቦ ጆቴ "በልባ" በተሰኝ ነጠላ ዜማ ማሸነፍ ችሏል።
የአመቱ ምራጥ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራም ተዋናይ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በተመልካች በተሰበሰብ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህ መሰረት አበበ ባልቻ(አስናቀ) ከዘመን ድራማ አሸናፊ መሆን ችሏል።
የአመቱ ምርጥ አዲስ ድምፃዊ ዘርፍ 40% በዳኞች 60% ከአድማጭ ተመልካች በተሰበሰብ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህ ዘርፍ ድምፃዊት ቸሊና ማሸነፍ ችላለች።
የአመቱ ምርጥ ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ተዋናይት ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ከተመልካች ድምፅ የተሰበሰብ ሲሆን በዚህ መሰረት አርቲስት ሀና ዮሃንስ ከዘመን ድራማ ማሸነፍ ችላለች።
የአመቱ ምርጥ የሙዚቃ ቪዲዮ ዘርፍ ሙሉ በሙሉ ከተመልካች በተሰበሰበ ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህ መሰረት ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ "ከእሁድ እስከ እሁድ" በተሰኝው ቪዲዮ ክሊፕ ማሸነፍ ችሏል።
የአመቱ ምርጥ ዘፈን ዘርፍ ሙሉ በሙሉ በዳኞች ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት በሀይሉ ታፈሰ (ዚጊ ዛጋ) "ሰርካለሜ" በተሰኝው ዘፈን ማሸነፍ ችሏል።
የአመቱ ምርጥ ተዋናይት ዘርፍ 60% የዳኞች ድምፅ 40% በተመልካች ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት የምስራች ግርማ በቁራኛዬ ፊልም ማሸነፍ ችላለች።
የአመቱ ምርጥ ተዋናይ ዘርፍ 60% የዳኞች ድምፅ 40% በተመልካች ድምፅ የተወሰነ ሲሆን በዚህም መሰረት ዘሪሁን ሙላት በቁራኛዬ ፊልም ማሸነፍ ችሏል።
ተጨማሪ👇
https://telegra.ph/ETH-10-18
Via ዳሰሳ አዲስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1633ኛ መደበኛ ሎተሪ...
1633ኛው መደበኛ ሎተሪ ሐሙስ ጥቅምት 06/ 2012 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል፡፡
1ኛ. 600,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 008066
2ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 030161
3ኛ. 150,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 017189
4ኛ. 60,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 269526
5ኛ. 30,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 128542
6ኛ. 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,200 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 025112፣166902 እና 336902
7ኛ. 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 600 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 029015፣ 249934 እና 012007
8ኛ. 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 150 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4540
9ኛ. 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 6386
10ኛ. 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 90 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 0671
11ኛ. 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 913
12ኛ. 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 45 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 907
13ኛ. 3400 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 30 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 42
14ኛ. 34,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 15 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 2 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡
ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
1633ኛው መደበኛ ሎተሪ ሐሙስ ጥቅምት 06/ 2012 ዓ.ም በብሔራዊ ሎተሪ ዕድል አዳራሽ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ በህዝብ ፊት ወጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት የወጡት የአሸናፊ ዕጣ ቁጥሮች እንደሚከተሉት ሆነዋል፡፡
1ኛ. 600,000 ብር የሚያስገኘው የ1ኛ ዕጣ ቁጥር 008066
2ኛ. 300,000 ብር የሚያስገኘው የ2ኛ ዕጣ ቁጥር 030161
3ኛ. 150,000 ብር የሚያስገኘው የ3ኛ ዕጣ ቁጥር 017189
4ኛ. 60,000 ብር የሚያስገኘው የ4ኛ ዕጣ ቁጥር 269526
5ኛ. 30,000 ብር የሚያስገኘው የ5ኛ ዕጣ ቁጥር 128542
6ኛ. 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 1,200 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 025112፣166902 እና 336902
7ኛ. 3 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 600 የሚያስገኙት ዕጣ ቁጥሮች 029015፣ 249934 እና 012007
8ኛ. 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 150 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 4540
9ኛ. 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 120 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 6386
10ኛ. 34 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 90 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 0671
11ኛ. 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 60 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 913
12ኛ. 340 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 45 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 907
13ኛ. 3400 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 30 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር 42
14ኛ. 34,000 ዕጣዎች እያንዳንዳቸው ብር 15 የሚያስገኘው ዕጣ ቁጥር (የማስተዛዘኛ ዕጣ) ደግሞ 2 ቁጥር በመሆን ወጥቷል፡፡
ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር
@tsegabwolde @tikvahethiopia